FastMereja.com
الذهاب إلى القناة على Telegram
إظهار المزيد
📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام FastMereja.com
تُعد قناة FastMereja.com (@fastmereja) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 48 827 مشتركاً، محتلاً المرتبة 3 622 في فئة التعليم والمرتبة 660 في منطقة Ethiopia.
📊 مؤشرات الجمهور والحراك
منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 48 827 مشتركاً.
بحسب آخر البيانات بتاريخ 22 يوليو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار -453، وفي آخر 24 ساعة بمقدار -5، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.
- حالة التحقق: غير موثّقة
- معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 11.22%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 7.21% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
- وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 5 477 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 3 522 مشاهدة.
- التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 20.
📝 الوصف وسياسة المحتوى
وصف القناة غير متوفر.
بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 23 يوليو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة التعليم.
48 827
المشتركون
-524 ساعات
-1237 أيام
-45330 أيام
أرشيف المشاركات
48 828
የኢትዮጵያን የሪል እስቴት ገበያ ለአለም አቀፍ ኢንቨስተሮች የሚያስተዋውቅ አዲስ ስምምነት ተፈረመ!
#Fastmereja I የኢትዮጵያ ሪል እስቴት አልሚዎች ማህበር (EREDA) እና ዶክሳ ቢዝነስ ትሬዲንግ ኃ.የተ.የግ.ማ. በኢትዮጵያ የሪል እስቴት ዘርፍን በሀገር ውስጥ እና በአለም አቀፍ ደረጃ ለማጠናከር የሚያስችሉ ሁለት ስትራቴጂካዊ የመግባቢያ ሰነዶችን በዛሬዉ እለት ተፈራረሙ፡፡
ስምምነቱ የሪል እስቴት ዘርፉን ትብብር ለማሳደግ፣ የሀገር ውስጥ እና የውጭ ኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስፋፋት እንዲሁም የዲያስፖራውን ተሳትፎ ለማሳደግ ያለመ መሆኑ ተገልጻል፡፡
በስምምነቱ መሠረት በሀገር ውስጥ የኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበርን ተቋማዊ አቅም ማጠናከር፣ የአባልነት መስፋፋትን መደገፍ፣ በመንግስት እና በግል ዘርፍ መካከል ያለውን ትብብር ማሳደግ እና የዕውቀት ልውውጥ መድረኮችን በጋራ ማዘጋጀት ዋና ዋና ትኩረቶች ሲሆኑ በዚህም ዶክሳ ቢዝነስ ትሬዲንግ ለተመረጡ መርሃግብሮች የኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር (EREDA) ተመራጭ የኢቨንት አስተባባሪ አጋር ሆኖ እንደሚሰራም ነዉ የተገለፀዉ።
በሌላ በኩል ስምምነቱ የዲያስፖራ ኢንቨስትመንትን ለማበረታታት እና የውጭ ምንዛሬ ገቢን ለማሳደግ ያለመ ሲሆን፣ የመጀመሪያዎቹ አለም አቀፍ የሪል እስቴትና ኢንቨስትመንት ትስስር ፕሮግራሞች በሪያድ (ሳውዲ አረቢያ)፣ በጆሃንስበርግ (ደቡብ አፍሪካ) እና በእስራኤል እንደሚካሄዱ ተጠቅሷል፡፡
ሁለቱ ተቋማት ቀደም ሲል እንደ “Addis Africa Real Estate Expo 2026” ያሉ ትልልቅ መድረኮችን በጋራ ማዘጋጀታቸው የሚታወስ ሲሆን፣ በቀጣይም የሚተገበሩ ፕሮጀክቶች በግልጽነት እና በተጠያቂነት መመሪያዎች የሚመሩ መሆናቸውን አረጋግጠዋል፡፡
ዶክሳ ቢዝነስ ትሬዲንግ ኃ.የተ.የግ.ማ. በቢዝነስ ልማት፣ በስትራቴጂካዊ ግንኙነት፣ በኢቨንት ማስተባበር፣ በማርኬቲንግ ኮሙኒኬሽን እና በባለድርሻ አካላት ትስስር ላይ የተሰማራ ድርጅት ሲሆን፣ ቢዝነሶችን፣ ባለሀብቶችን፣ መንግስታዊ ተቋማትን እና ማህበረሰቡን የሚያገናኙ ዘላቂና ፈጠራ ያላቸው መድረኮችን በመፍጠር ለኢኮኖሚያዊና ለኢንዱስትሪ ልማት አስተዋፅኦ ያደርጋል::
48 828
በላስታ ላሊበላ ለቀናት የተካሄደውን ምህላ ተከተሎ ዝናብ መጣሉ ተገለጸ
#FastMereja I በሰሜን ወሎ ዞን ላስታ ላሊበላና አካባቢው የክረምቱ ዝናብ ዘግይቶ በነበረበት ወቅት ለሰባት ቀናት የተካሄደውን ሃይማኖታዊ የምህላ ጸሎት ተከተሎ ወቅቱን የጠበቀ ዝናብ መጣል መጀመሩን የአካባቢው ነዋሪዎች አስታወቁ።
በሰሜን ወሎ ዞን በላስታ ላሊበላና በዙሪያው በሚገኙ አካባቢዎች የዘንድሮው የክረምት ዝናብ በመዘግየቱ ምክንያት ገበሬው ዘሩን በደረቁ ዘርቶ ከፍተኛ የስጋትና የጭንቀት ሁኔታ ውስጥ ወድቆ እንደነበር ተገልጿል። የአካባቢው ማህበረሰብና የገዳሙ አባቶች ከጥንት ጀምሮ ሲወርድ ሲወራረድ የመጣውን ባህላዊና ሃይማኖታዊ ስርዓት በመከተል ቤተ ሚካኤል (ጎልጎታ) ተሰብስበው ላለፉት ሰባት ቀናት አበይት የምህላ ጸሎት ሲያደርሱ ቆይተዋል።
በቅዱስ ላሊበላ ገዳም አባቶች ዘንድ በየዓመቱ በታኅሣሥ፣ በሰኔ እና በመስከረም ወራት የሚደረጉ የተለመዱ የምህላ ጸሎቶች እንዳሉ የሚታወቅ ሲሆን፣ የዘንድሮውን የዝናብ መዘግየት ተከተሎ የተደረገው የጸሎት ሥነ-ሥርዓት በስድስተኛው ቀን የዝናብ ምልክት ማሳየቱንና በሰባተኛው ቀን ደግሞ ምድሪቱን የሚያርስርቅ ዝናብ መጣሉ ተመልክቷል። ይህም በስጋት ውስጥ የነበረውን የአካባቢውን አርሶ አደርና አጠቃላይ የማህበረሰብ ክፍል ከፍተኛ ተስፋ ያሰነቀ አጋጣሚ ሆኗል።
48 828
የመገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን በጄኤፍኤም 106.7 ሬድዮ ጣቢያ ላይ የስድስት ወራት የስርጭት እግድጣለ
#FastMereja I የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን የጄኤፍኤም (JFM 106.7) ሬድዮ ጣቢያ የብሮድካስት ስርጭት ከሐምሌ 1/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሚቀጥሉት ስድስት ወራት ሙሉ ለሙሉ እንዲታገድ መወሰኑን አስታወቀ። ባለሥልጣኑ ውሳኔውን ያስ አስተላለፈው ጣቢያው በተደጋጋሚ የተሰጡትን የቃልና የጽሁፍ ማስጠንቀቂያዎች ሳይቀበል በመቅረቱ እና በአዋጅ ቁጥር 1238/2013 የተጣሉበትን የፈቃድ ውል ግዴታዎች ባለመወጣቱ እንደሆነ ገልጿል።
ባለሥልጣኑ ባደረገው የይዘት ክትትልና የአካል ኢንስፔክሽን ምልከታ ጣቢያው በህግ የተጣለበትን የሀገራዊ ይዘት ሽፋን አለማካተቱን፣ ህዝብን የሚያስተምሩና የሚያዝናኑ ፕሮግራሞችን ከማቅረብ መቆጠቡን እንዲሁም ለሀገራዊ እሴቶችና ለፖለቲካዊ-ኢኮኖሚያዊ እድገት አስተዋጽኦ የማድረግ ግዴታውን አለመወጣቱን አረጋግጧል። በውሳኔው መሰረት የኢትዮጵያ ኮሚዩኒኬሽን ባለሥልጣንም ጣቢያው የተመደበለትን 106.7 የሬድዮ ሞገድ በእግዱ ወቅት እንዳይጠቀም ማሳሰቢያ የሰጠ ሲሆን፣ ጣቢያው ለሕግ ተገዢ በመሆን ስርጭቱን በአስቸኳይ እንዲያቆም ታዟል።
48 828
ድምጻዊ አንዱዓለም ጎሳ «Waa’ee Jireenya Koo!» የተሰኘ አዲስ የሙዚቃ ሊለቅ መሆኑ ታወቀ
#FastMereja I ታዋቂው ድምጻዊ አንዱዓለም ጎሳ «Waa’ee Jireenya Koo!» በሚል ርዕስ ያዘጋጀውን አዲስ የሙዚቃ በቅርብ ቀን ለአድናቂዎቹ እንደሚያቀርብ ታወቀ።
ድምጻዊው የህይወቱን ጉዞ እና ገጠመኝ የሚያንጸባርቅበት እንደሆነ የሚጠበቀውን ይህንን አዲስ የሙዚቃ ሥራውን አስመልክቶ ይፋዊ የማስተዋወቂያ ፖስተር ባሰራጨበት ወቅት፣ ሥራው በቅርቡ እንደሚለቀቅ አረጋግጧል።
48 828
ድምጻዊ ጎሳዬ ተስፋዬ ምን አጋጠመው?
#FastMereja I ከለንደን ወደ አዲስ አበባ የተመለሰው ታዋቂው ድምጻዊ ጎሳዬ ተስፋዬ «ታምሜ ገባሁ» ሲል በማህበራዊ ትስስር ገጹ ባሰራጨው መረጃ አድናቂዎቹን ስጋት ውስጥ ጥሎ የነበረ ቢሆንም አደጋው አሳሳቢ እንዳልሆነ ታውቋል።
ድምጻዊው ከለንደን ወደ ኢትዮጵያ በመመለስ ላይ ሳለ በአየር መንገድ ውስጥ እርጥበት የነካው ሴራሚክ አዳልጦት የወደቀ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት በጥሩ ጤንነት ላይ እንደሚገኝ ተገልጿል።
ጉዳዩን በተመለከተ ወደ ድምጻዊው ያቀናው ጋዜጠኛ ሰይፉ ፋንታሁን ከጎሳዬ ጋር በመሆን በሰጠው ማብራሪያ፣ ያጋጠመው ክስተት ከፍተኛ የሚባል የጤና አደጋ እንዳልሆነና አድናቂዎቹ ስጋት እንዳይገባቸው መልዕክት አስተላልፏል።
48 828
በሳዑዲ አረቢያ 34 ኪሎ ግራም ሀሺሽ ወደ ሀገሪቷ ሊያስገቡ ሲሉ 4 ኢትዮጵያውያን በቁጥጥር ስር ዋሉ
#FastMereja | የሳዑዲ አረቢያ የድንበር ጠባቂ ኃይል በአሲር ክልል 34 ኪሎ ግራም የሐሺሽ አደንዛዥ ዕፅ ወደ ሀገር ውስጥ ለማስገባት ሲሞክሩ የነበሩ አራት ኢትዮጵያውያንን በቁጥጥር ስር ማዋሉን አስታወቀ።
የሀገሪቱ የድንበር ጠባቂ የመሬት ላይ ጥበቃ አባላት በአሲር ክልል ስር በሚገኘው የራቡአ ቀጠና ተጠርጣሪዎቹ የድንበር ደህንነት ህግን ጥሰው አደንዛዥ ዕፁን ለማስገባት ሲሞክሩ እጅ ከፍንጅ መያዛቸው ተገልጿል።
የሳዑዲ አረቢያ የሚመለከታቸው አካላት እንደገለጹት፣ በተጠርጣሪዎቹ ከተያዘው ዕፅ ጋር ወደሚመለከተው የፍትህ አካል እንዲተላለፉ ተደርጓል።
48 828
አትክልት ሻጯ ወ/ሮ ገነት ክንዱ የ3 ሚሊዮን ብር ሚሊዮን ሎተሪ ባለዕድል ሆኑ
#FastMereja I የወለጋ ነዋሪ የሆኑት ወ/ሮ ገነት ክንዱ ለአጭር የሥራ ጉዳይ ወደ አዲስ አበባ በመጡበት አጋጣሚ በቆረጡት የ100ኛ ዙር ሚሊዮን ሎተሪ ቲኬት በ5ኛ ዕጣ የ3 ሚሊዮን ብር ባለዕድል ሆኗል።
የሎተሪው ዕጣ ደራሽ የሆኑት ወ/ሮ ገነት ክንዱ በቋሚነት በወለጋ አካባቢ አትክልት በመንገድ ዳር በመሸጥ የሚተዳደሩ የዕለት ደራሽ የንግድ እንቅስቃሴ ውስጥ የሚገኙ እናት ናቸው። ለሥራ ጉዳይ ወደ መዲናዋ አዲስ አበባ ባቀኑበት ወቅት የቆረጡት ይህ ቲኬት ያልተጠበቀ ትልቅ የገንዘብ ዕድል ይዞላቸዋል።
ወ/ሮ ገነት ያገኙትን የ3 ሚሊዮን ብር የገንዘብ ስጦታ ሙሉ በሙሉ እስካሁን ሲያካሂዱት የቆዩትን የአትክልት ንግድ ሥራ ለማስፋፋት፣ ለማጠናከር እና ደረጃውን ለማሻሻል የሚያውሉት መሆኑን ተናግሯል።
48 828
የሙዝ ጫካ
#FastMereja I በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በቤንች ሸኮ ዞን ደቡብ ቤንች ወረዳ በ482 አርሶ አደሮች በ435 ሄክታር መሬት ላይ በኩታ-ገጠም አሰራር የለማው የሙዝ ምርት፣ አካባቢውን ወደ ደንነት በመቀየር የተፈጥሮ ሥነ-ምህዳርን ከመጠበቁ ባሻገር የአርሶ አደሩን ገቢ በከፍተኛ ሁኔታ እያሳደገ መሆኑ ተገለጸ።
ይህ በደቡብ ቤንች ወረዳ የተመዘገበው ውጤት የክልሉን የሙዝ ምርት አቅም በእጅጉ ያጎላው ሲሆን፣ በክልል ደረጃ ከ73 ሺህ 785 ሄክታር በላይ መሬት በሙዝ በመሸፈኑ 13 ነጥብ 8 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለሀገር ውስጥ ገበያ ማቅረብ ተችሏል።
48 828
ያለ ንብረት ማስያዣ ብድር የሚሰጠው «ኪሴ» ፕላትፎርም በይፋ ሥራ ጀመረ!
#Fastmereja I አሪፍፔይ ፋይናንሻል ቴክኖሎጂስ አ.ማ፣ ኤምዚ ቴክ እና መፍትሔ ማይክሮፋይናንስ አ.ማ በመተባበር «ኪሴ» የተሰኘ አዲስ በወኪሎች (Agents) የሚመራ የዲጂታል ጥቃቅን ብድር ፕላትፎርም በዛሬዉ እለት በይፋ አስተዋወቁ።
ይህ የሦስትዮሽ አጋርነት በሀገራችን በአነስተኛና ጥቃቅን ንግዶች ዘርፍ የሚታየውን የፋይናንስ አቅርቦት እጥረት ለመቅረፍ የታለመ ሲሆን፤ ያለ ምንም መደበኛ ንብረት ማስያዣ(Collateral-free) በህብረተሰቡ ዘንድ ባለው ማህበራዊ እምነት እና የዕለት ተዕለት ግንኙነት ላይ በመመስረት አገልግሎቱን ተዳራሽ እንደሚደረግ ነዉ የተገለፀዉ።
መፍትሔ ማይክሮፋይናንስ አ.ማ፦ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የተመዘገበ ሕጋዊ አበዳሪ ተቋም በመሆን የብድር ካፒታሉንና የፋይናንስ አቅርቦቱን ያመቻቻል።ኤምዚ ቴክ (MZ Tech)፦ የ«ኪሴ» ፕላትፎርም ልማትና የቴክኖሎጂ መሰረተ ልማቱን ያበለጸገ ሲሆን፣ ሀገር አቀፍ የወኪሎችን መረብ ይመራል።አሪፍፔይ ፋይናንሻል ቴክኖሎጂስ አ.ማ፦ በሀገር አቀፍ የክፍያ መደቡ (Payment Gateway) አማካኝነት የብድር መውጫ፣ የመልስ ክፍያ ዝውውር እና የዲጂታል ክፍያ ሂደቶችን ያመቻቻል።
ተበዳሪዎች በአካባቢያቸው በሚገኙ የሰለጠኑ ወኪሎች አማካኝነት ለአጭር ጊዜ የንግድ ብድር ማመልከት እንደሚችሉ የተጀለፀ ሲሆን ማመልከቻው በመፍትሔ ማይክሮፋይናንስ እንደተጸደቀም፣ በአሪፍፔይ የክፍያ መስመር በኩል በጥቂት ሰዓታት ውስጥ በቀጥታ ወደ ደንበኛው የሞባይል ዋሌት ወይም የባንክ ሂሳብ ገቢ እንደሚደረግ ተገልጿል።
መድረኩ የብድር ብቃትን ለመመዘን አማራጭ መረጃዎችን (Alternative Data) በመጠቀሙ፣ መደበኛ የፋይናንስ ሰነድ ወይም መያዣ የሌላቸውን ስራ ፈጣሪዎችና አነስተኛ ነጋዴዎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ ሲሆን፤ የሀገሪቱን የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን እቅድ ለማፋጠን ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ተብሏል።
48 828
ተደራሽ የቁጠባና ብድር ህብረት ስራ ማህበር የ9ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን አከበረ!
#Fastmereja:-ተደራሽ ማህበረሰብ አቀፍ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኃላፊነቱ የተወሰነ የህብረት ሥራ ማህበር በአገር አቀፍ ደረጃ የቅርንጫፎቹን ቁጥር 33 በማድረስ እና ከ1.5 ቢሊዮን ብር በላይ አጠቃላይ ካፒታል በማፍራት የ9ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን በዛሬው ዕለት በድምቀት አክብሯል።
ማህበሩ በ4 ኪሎ የኢትዮጵያ ፖስታ ህንፃ ላይ በሚገኘው ዋና ቢሮው ባካሄደው የዚህ በዓል ስነ-ስርዓት ላይ የኢትዮጵያ ህብረት ሥራ ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ጌትነት ታደሰ፣ ምክትል ኮሚሽነር አቶ አብዲ ሙመድ፣ የተቋሙ የሥራ አመራር ኮሚቴ ሰብሳቢ ወ/ሮ አልማዝ ኦልጅራ ጨምሮ የክልልና የከተማ አስተዳደር የሥራ ኃላፊዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
የተደራሽ የቁጠባና ብድር ኃላፊነቱ የተወሰነ የህብረት ስራ ማህበር መስራችና ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ አለማየሁ ታመነ እንደገለፁት ማህበሩ በሐምሌ ወር 2009 ዓ.ም በ24 መስራች አባላት እና በ24 ሺህ ብር መነሻ ካፒታል በአዲስ አበባ አራዳ ክፍለ ከተማ እንደተመሰረተ ያስታወሰው የተቋሙ መግለጫ፤ ባለፉት ስድስት ዓመታት ባደረገው ስትራቴጂካዊ የሪፎርም ንቅናቄ አሁን ላይ የአባላቱን ቁጥር ከ27 ሺህ 900 በላይ ማድረስ መቻሉን ይፋ አድርጓል።
ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ ለተከታታይ ሦስት ዓመታት በቤተሰብ ደረጃ ተወስኖ የነበረው ተደራሽ፣ ከመስከረም 2013 ዓ.ም ጀምሮ ባደረገው አዲስ የአሠራር ለውጥ በአገር አቀፍ ደረጃ ፈጣን ዕድገት ማስመዝገብ መቻሉ ተመላክቷል።
ተቋሙ እስካሁን ከ2,500 በላይ አባላትን የብድር ተጠቃሚ ያደረገ ሲሆን፤ 443 አባላትን የቤት ባለቤት፣ 452 አባላትን ደግሞ የሥራና የቤት መኪና እንዲሁም የባጃጅ ባለቤት ማድረግ ያስቻለ ሲሆን ተቋሙ በአጠቃላይ ከ13 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች ቀጥተኛና ቀጥተኛ ያልሆነ የሥራ ዕድል መፍጠሩም ተገልጧል።
የማህበሩን የቀጣይ አቅጣጫ በተመለከተ በተሰጠው ማብራሪያ፣ ተቋሙ በቀጣይ 17 አዳዲስ ቅርንጫፎችን በመክፈት አጠቃላይ የቅርንጫፎቹን ቁጥር 50 ለማድረስ ማቀዱን ገልጿል።
የዲጂታል ኮር ባንኪንግ ሥርዓቱን ይበልጥ በማጠናከር የአገሪቱን ማዕከላዊ የፋይናንስ ክምችት ለማሳደግ የድርሻውን እንደሚወጣ የጠቀሰው ማህበሩ፣ እ.ኤ.አ በ2029 ከአፍሪካ ምርጥ 10 የቁጠባና ብድር ተቋማት ተርታ ለመሰለፍ ትልቅ ራዕይ ሰንቆ እየሰራ እንደሚገኝ አስታውቋል።
48 828
በምስራቅ ሸዋ በዛሬው ዕለት 20ሺህ የአቮካዶ ችግኝ ተተከለ
#FastMereja I ግሪን ዌቭ አሊያንስ ከአዋሽ ባንክ እና ከአዋሽ ኢንሹራንስ ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ዛሬ በምስራቅ ሸዋ ዞን አደዓ ወረዳ ጎዲኖ ጂቱ ወረዳ በታላቅ ሁኔታ ተካሂዷል። በመርሃ ግብሩ ላይ የዞኑ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣ የአዋሽ ባንክና የአዋሽ ኢንሹራንስ ዋና ስራ አስፈጻሚዎች፣ ታዋቂ አርቲስቶችና የአካባቢው ማህበረሰብ በተገኙበት 20 ሺህ የሚደርሱ የአቮካዶ ችግኞች ተተክሏል።
ይህ በዛሬው ዕለት የተከናወነው የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር በአካባቢው የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥና በስነ-ምህዳር ጥበቃ ላይ የጎላ አስተዋጽኦ ለማበርከት ታስቦ የተዘጋጀ ነው። በቦታው ላይ ተገኝተው የአረንጓዴ አሻራቸውን ያኖሩት የነዋሪዎችና የልዑካን ቡድኑ አባላት እንደገለጹት፣ የተተከሉት ችግኞች የምግብ ይዘት ያላቸው የአቮካዶ ዝርያዎች መሆናቸው ማህበረሰቡን በቀጥታ ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ታምኖበት የተመረጠ ነው።
በመርሃ ግብሩ ላይ የኦሮሚያ ክልል የምስራቅ ሸዋ ዞን አስተዳዳሪ አቶ አባቡ ዋቆ፣ የአዋሽ ባንክ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ፀሐይ ሽፈራው፣ የአዋሽ ኢንሹራንስ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ጅባት አለምነህ፣ እንዲሁም የግሪን ዌቭ አሊያንስ መስራች እና ዋና ስራ አስፈጻሚ አርቲስት ሚካኤል ነጋሳ በጋራ በመሆን ችግኝ ተክለዋል። ከተቋማቱ የስራ ባልደረቦች በተጨማሪ በርካታ ታዋቂ አርቲስቶች እና የማህበራዊ ሚዲያ ተፅኖ ፈጣሪዎች የችግኝ ተከላውን ሂደት በማስተባበርና ህዝቡን በማነቃቃት ረገድ ከፍተኛ ተሳትፎ አድርገዋል።
ይህን ታላቅ መርሃ ግብር ያስተባበረው ግሪን ዌቭ አሊያንስ ከአረንጓዴ ልማት፣ ከብዝሃ ህይወት እና ስነ ምህዳር ጥበቃ ጋር በተያያዘ የተለያዩ ፕሮጀክቶችን ቀርፆ በስፋት እየሰራ የሚገኝ ተቋም ነው። ድርጅቱ ላለፉት 5 ተከታታይ ዓመታት የሀገሪቱን የአረንጓዴ አሻራ ኢኒሼቲቭ በንቃት ሲደግፍ የቆየ ሲሆን፣ በተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች በርካታ የማህበረሰብ ክፍሎችን ያነቀነቁ የችግኝ ተከላ መረሃ ግብሮችን በማዘጋጀት እስካሁን ድረስ ከ2.6 ሚሊዮን በላይ ችግኞችን በተሳካ ሁኔታ መትክልና ማጽደቅ የቻለ መሆኑ ይታወቃል።
48 828
በዱባይ በዜጎች ላይ አሰቃቂ ግፍ ሲፈጽሙ የነበሩ አደገኛ የሰ ዎች አዘዋዋሪዎች በቁጥጥር ሥር ዋሉ
#FastMereja I የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ዱባይ ፖሊስ ጋር በመቀናጀት፣ በውጭ ሀገር ተደብቀው በበርካታ ኢትዮጵያውያን ላይ ኢሰብአዊ ድርጊቶችን ሲፈጽሙ የነበሩ ዳውድ ተፈሪ ለገሰ እና ደስታ ተገኝ አበጋዝ የተባሉ አደገኛ ሕገ-ወጥ የሰ ዎች አዘ ዋዋሪዎችን በቁጥጥር ሥር አውሎ ወደ ሀገር አስገብቷቸዋል።
የፌደራል ፖሊስ ባደረገው የጋራ ዘመቻ፣ ሁለቱ ዋና ተጠርጣሪዎች 105 ዜጎችን “በተለያዩ ካምፓኒዎች ስራ እናስቀጥራችኋለን’’ በማለት በማታለልና ከ188 ሚሊዮን ብር በላይ ከተጎጂዎች በመሰብሰብ ከፍተኛ የሰብአዊ መብት ጥሰት ሲፈጽሙ ቆይተዋል። ተጠርጣሪዎቹ በዱባይ የኢትዮጵያ ኤምባሲ በደረሰ ጥቆማ መነሻነት ክትትል ሲደረግባቸው የቆየ ሲሆን፣ በቁጥጥር ሥር ውለው ለኢትዮጵያ ተላልፈው ተሰጥተዋል።
እነዚህ ግለሰቦች ምንም ዓይነት ሕጋዊ ፍቃድ ሳይኖራቸው፣ ከአንድ ሰው ከ320,000 እስከ 600,000 ብር በመቀበል በቱሪስት ቪዛ ዱባይ ካስገቡ በኋላ፣ ተጎጂዎችን በተዘጋጀ ክፍል ውስጥ በማገት ለከፍተኛ ረሃብ፣ እንግልትና ጥቃት ሲዳርጉ የነበረ መሆኑ በምርመራ ተረጋግጧል። በተጨማሪም “የመኖሪያ ፍቃድ እናሰጣችኋለን” በሚል ተጨማሪ የገንዘብ ዘረፋ ሲፈጽሙ ቆይተዋል።
በሀገር ውስጥ ሆነው ሰዎችን በመመልመልና የባንክ አካውንት ከፍተው ገንዘብ በማሰባሰብ ሲተባበሩ የነበሩት ብዙአየሁ አውግቸው እና ራህመት አበበ የተባሉ ተባባሪዎቻቸውም በቁጥጥር ሥር ውለው ምርመራ እየተካሄደባቸው ይገኛል። ፖሊስ የቴክኖሎጂ ውጤቶችን በመጠቀም ከዱባይ የቀጥታ ቨርቹዋል የምስክርነት ቃላቸውን እየተቀበለ ሲሆን፣ ሕጋዊ ሽፋንን በመጠቀም ከሕገ-ወጥ አዘዋዋሪዎች ጋር የሚሰሩ ኤጀንሲዎች ላይም ምርመራውን አጠናክሮ ቀጥሏል።
48 828
ናይጄሪያ በሕዝብ ትራንስፖርት ውስጥ ንግድና ስብከትን የሚከለክል አዲስ ሕግ አሳለፈች
#FastMereja I የናይጄሪያ የሕግ መወሰኛ ምክር ቤት (ሴኔት) በትራፊክ ጥሰቶች ላይ ጠንከር ያሉ ቅጣቶችን የሚጥል አዲስ የሕግ ረቂቅ አጽድቋል። በአዲሱ ሕግ መሠረት በአውቶቡሶች፣ በሚኒባሶች እና በሌሎች የሕዝብ ትራንስፖርት ተሽከርካሪዎች ውስጥ ዕቃ ሲሸጡ፣ ሲነግዱ ወይም ሲሰብኩ የተገኙ ግለሰቦች የ33 ዶላር ቅጣት ይጠብቃቸዋል። ይህ ረቂቅ ሕግ ጸድቆ ሥራ ላይ ከመዋሉ በፊት አሁን የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ቦላ ቲኑቡ ፊርማን በመጠባበቅ ላይ ይገኛል።
የአገሪቱ ሕግ አውጪዎች እንደሚሉት ከሆነ እነዚህ አዳዲስ ጠንካራ ቅጣቶች የተዘጋጁት በትራፊክ አደጋ የሚጠፋውን ሕይወት ለመቀነስና የናይጄሪያን መንገዶች ደህንነታቸው የተጠበቀ ለማድረግ በማሰብ ነው። በርካታ የአካባቢው የሚዲያ ምንጮችን ጠቅሶ ዲደብሊው አፍሪካ እንደዘገበው ከሆነ ሕጉ በትራንስፖርት ውስጥ የሚደረጉ እንቅስቃሴዎችን ብቻ ሳይሆን አሽከርካሪዎችንም በጥብቅ የሚቀጣ ነው።
በዚህም መሠረት ጠጥቶ የሚያሽከረክር፣ ከፍጥነት ወሰን በላይ የሚነዳ ወይም የትራፊክ ምልክቶችን የማይከብር ማንኛውም አሽከርካሪ የ66 ዶላር ቅጣት ይጣልበታል። በተጨማሪም በመንገድ ላይ የሚደረግን የአልኮል ምርመራ ለመመርመር ፈቃደኛ ያልሆኑ አሽከርካሪዎች የ33 ዶላር ቅጣት፣ እስከ ስድስት ወር የሚደርስ እስራት ወይም ሁለቱንም ቅጣቶች በአንድ ላይ ሊጋፈጡ እንደሚችሉ በሕጉ ላይ ተደንግጓል።
48 828
የኢትዮጵያን የግብርና ምርታማነት ለማሳደግ ያለመ አዲስ የቴክኖሎጂ አማራጭ ይፋ ተደረገ
#FastMereja I በኢትዮጵያ የግብርና ምርታማነትን ለማሳደግ፣ የወጪ ንግድ ጥራትን ለመጠበቅ እና የአርሶ አደሩን ድካም ለመቀነስ የሰው ሰራሽ አስተዋጽኦ (AI) ቴክኖሎጂዎችን፣ ዘመናዊ የካሜራ ቁጥጥሮችን እና የከርሰ ምድር ሴንሰሮችን ያካተቱ አዳዲስ የግብርና መፍትሄዎች ወደ አገር ውስጥ እየገቡ መሆኑ ታውቋል።
ጎልደን ላንድ ቶኩማ የተሰኘው የግብርና ቴክኖሎጂ ድርጅት በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ፣ የሰብል ጤንነትን መከታተል የሚያስችሉ ክሮፕለር የቴክኖሎጂ ውጤት ወደ ኢትዮጵያ የግብርና ስርዓት ለማስገባት ሰፊ ዝግጅት እየተደረገ እንደሚገኘ ተነግሯል። ይህ ቴክኖሎጂ በአገሪቱ እየተተገበረ ያለውን የዲጂታል ግብርና ፍኖተ ካርታ እውን ለማድረግ ትልቅ ሚና እንደሚጫወት ታምኖበታል።
በተለይ በአገሪቱ የወጪ ንግድ ላይ ትልቅ ድርሻ ላላቸው እንደ ቡና እና የአትክልትና ፍራፍሬ ምርቶች ላይ ትኩረት አድርጎ የሚሰራው ይህ አዲስ አሰራር፣ ሰብሎች ከመሬት ሳይነቀሉ በካሜራ እና በሳተላይት ድጋፍ በሽታዎችን ቀድሞ ለመለየት ያስችላል። ሰብሎችን በአካል የመጎብኘትና የመቆጣጠር ወጪን እስከ 40 በመቶ እንደሚቀንስ የተረጋገጠ ሲሆን፣ አርሶ አደሮችና ባለሀብቶች የተሻለ የውሳኔ አሰጣጥ ብቃት እንዲኖራቸው ይረዳል ተብሏል።
ይህ የቴክኖሎጂ መፍትሄ በአሁኑ ወቅት በዓለም አቀፍ ደረጃ ከ22 በላይ አገራት ውስጥ ጥቅም ላይ የዋለ ሲሆን፣ በኢትዮጵያ ደግሞ በዋናነት ለትላልቅና መካከለኛ የንግድ እርሻዎች፣ ለቡና ላኪዎች፣ ለአግሮ-ኢንደስትሪዎች እና በተደራጁ የህብረት ስራ ማህበራት ስር ለሚገኙ አርሶ አደሮች ሰፊ ጠቀሜታ እንደሚሰጥ ይጠበቃል።
48 828
ከሊዮኔል ሜሲ ጋር በፎቶ የተነሳው ህጻን ላሚን ያማል መሆኑ ዩኒሴፍ የእውነተኝነቱን ምስክርነት ሰጠ
#FastMereja I በማህበራዊ ሚዲያ ላይ በስፋት ሲዘዋወር የነበረውና ታዋቂው የእግር ኳስ ኮከብ ሊዮኔል ሜሲ አንድን ህጻን ሲያጥብ የሚያሳየው ፎቶግራፍ እውነተኛ መሆኑን የተባበሩት መንግስታት የህጻናት መርጃ ድርጅት (UNICEF) ይፋዊ መግለጫ ሰጥቷል። በፎቶው ላይ የሚታየው ህጻን የስፔኑ ወጣት ኮከብ ላሚን ያማል መሆኑ ተረጋግጧል።
ይህ ታሪካዊ ፎቶግራፍ የተነሳው ከ18 ዓመታት በፊት በዩኒሴፍ (UNICEF) የገቢ ማሰባሰቢያ የበጎ አድራጎት ፕሮግራም ላይ እንደነበር ተገልጿል። በወቅቱ ገና ህጻን የነበረው ላሚን ያማል ከእናቱ ሺላ ጋር በመሆን ከሊዮኔል ሜሲ ጋር እንዲገናኝ የተደረገ ሲሆን፣ ፎቶግራፉን ያነሳው ታዋቂው ጆአን ሞንፎርት (Joan Monfort) መሆኑ ታውቋል።
ዩኒሴፍ ባወጣው ይፋዊ መግለጫ፣ ሁለቱ የእግር ኳስ ኮከቦች በአሁኑ ወቅት በሜዳ ላይ ከሚያሳዩት ድንቅ ብቃት ባሻገር፣ ከሜዳ ውጪም የዩኒሴፍ የበጎ ፈቃድ አምባሳደሮች በመሆን በመላው ዓለም ለሚገኙ ህጻናት መብትና ደህንነት በጋራ እየሰሩ እንደሚገኝ በኩራት ገልጿል።
በአሁኑ ወቅት ሁለቱ ተጫዋቾች በዓለም ዋንጫ ፍጻሜ እሁድ ይፋለማሉ።
48 828
ብረሽድ ባይ ቤቲ የውበት ማሰልጠኛ ተቋም ከ400 በላይ ሰልጣኞችን አስመረቀ!
#Fastmereja:- በውበትና ስልጠና ዘርፍ ለ11 ዓመታት ሲያገለግል የቆየው ብረሽድ ባይ ቤቲ (BBMI) የውበት ማሰልጠኛ ተቋም፣ ለሰባተኛ ዙር ያሰለጠናቸውን ከ400 በላይ ተማሪዎች በዛሬዉ እለት በኤልያና ሆቴል አስመርቋል።
ተመራቂዎቹ በሜካፕ፣ በሰው ሰራሽ አይላሽ አሰራር፣ በጥፍር ውበት፣ በኦምብሬ (የፀጉርና ጥፍር ቀለም ቅልቅል) እና በፌሻል ስልጠና ዘርፎች የሰለጠኑ ሲሆን፣ ስልጠናው በዘርፉ ያለውን የሰለጠነ የሰው ኃይል ፍላጎት ከመሙላት ባለፈ ለበርካታ ዜጎች የሥራ ዕድል የሚፈጥርመሆኑ ተገልጿል።
የተቋሙ መስራችና ባለቤት ወ/ሮ ቤተልሄም እስክንድር እንደገለጹት፣ ተመራቂዎቹ በቀጥታ ወደ ሥራ እንዲገቡ ከተለያዩ አጋር ድርጅቶች ጋር በትብብር እየተሠራ እንደሚገኝ ገልፀዉ ተቋሙም በመጀመሪያ ደረጃ የራሱን ድርጅት ሠራተኞች የሚቀጥረው ከራሱ ተማሪዎች መካከል መሆኑን ጠቁመዋል።
በተጨማሪም የራሳቸውን ሥራ መፍጠር ለሚፈልጉ ሰልጣኞች ከተመረጡ ባንኮች ኦና የብድር ተቋማት ጋር በመተባበር የብድር ሁኔታዎች መመቻቸታቸውም ነዉ የተገለፀዉ።
እንዲሁም ተማሪዎቹ ራሳቸውን እና ምርታቸውን ማስተዋወቅ እንዲችሉ ለማገዝም የዲጂታል ማርኬቲንግ፣ ቪዲዮግራፊ፣ ፎቶግራፊ እና የሕይወት ክህሎት ስልጠናዎች በነጻ ተጨማሪ ኮርስ ተደርገው ተሰጥተዋቸዋል።
ተቋሙ ማኅበራዊ ኃላፊነቱን ከመወጣት አንጻር ከመንግሥት አካላት ጋር በመተባበር አቅም ለሌላቸው ሴቶች እና መስማት ለተሳናቸው እህቶች ሙሉ በሙሉ በነጻ ስልጠና መስጠቱን እና ወደፊትም መስጠቱን እንደሚቀጥል ተገልጿል።
በቀጣይም በተለያዩ ምክንያት ከቤት መውጣት ለማይችሉ እናቶችና እህቶች ምቹ የሆነ የቤት ለቤት የኦንላይን (Online) ስልጠና ለመጀመር ዝግጅት መጠናቀቁን ጨምረው አስታውቀዋል።
48 828
የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት 100ኛ ዓመቱን እያከበረ ነው!
#FastMereja I የኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት (EPHI) የ100ኛ ዓመት የምሥረታ በዓሉን ባከበረበት መድረክ፣ ተቋሙ የሕዝብ ጤናን ለመጠበቅ የመንግስትን ቁርጠኝነት የሚያሳይ መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት አምባሳደር ታዬ አጽቀስላሴ ገለጹ። በበዓሉ አከባበር ላይ የተቋሙ አዲስ ብራንድ ይፋ የተደረገ ሲሆን ለቀድሞ አመራሮችና ተመራማሪዎችም እውቅና ተሰጥቷል።
የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት አምባሳደር ታዬ አጽቀስላሴ ለኢንስቲትዩቱ ሰራተኞች ላለፉት መቶ ዓመታት ላሳዩት ትጋትና ላበረከቱት አስተዋጽኦ ምስጋና አቅርበዋል። መንግስት የሀገር ኢኮኖሚን ለመገንባት የህዝብ ጤና ዋነኛው መሰረት መሆኑን እንደሚረዳ የገለጹት ፕሬዝዳንቱ፣ ለዚህም ሲባል የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩትን የመሰሉ ተቋማትን የመደገፍና የማጠናከር ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስገንዝበዋል።
የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ በበኩላቸው፣ ዛሬ የሚከበረው የአንድ ተቋም 100ኛ ዓመት ብቻ ሳይሆን አጠቃላይ የኢትዮጵያ የህብረተሰብ ጤና ዘርፍ የተጓዘበትን የዕድገት ጉዞ መሆኑን ገልጸዋል። ተቋሙ ከጤና ሚኒስቴር ጋር በመቀናጀት በወረርሽኝ ልየታ፣ ክትትልና ምላሽ አሰጣጥ ላይ ያስመዘገባቸውን ስኬቶች ያነሱት ሚኒስትሯ፣ መንግስት የጤና ተቋማትን በማስፋፋትና የጤና መድህን አገልግሎትን ተደራሽ በማድረግ ኃላፊነቱን እየተወጣ እንደሚገኝና ሚኒስቴሩ ለኢንስቲትዩቱ የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
ይህ መድረክ ለቀድሞ አመራሮች፣ ተመራማሪዎች እና ሰራተኞች እውቅና ለመስጠትና ለህብረተሰቡ የተገባውን ቃል ለመደገፍ የተዘጋጀ መሆኑን የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር መሳይ ሃይሉ ገልጸዋል። በአሁኑ ወቅት ተቋሙ 40 የሪፈራል ላቦራቶሪዎችን ማቋቋሙንና በክልሎች ድንገተኛ የሕብረተሰብ ጤና አደጋዎች መከላከያ ማዕከላትን በመገንባት ወረርሽኝን የመቆጣጠር ሥራውን በግንባር ቀደምትነት እየመራ እንደሚገኝ ጠቅሰው፣ ተቋሙ የአፍሪካ የህብረተሰብ ጤና የልህቀት ማዕከል ለመሆን በቁርጠኝነት እየሠራ መሆኑን አስታውቀዋል።
#ጤና
48 828
በሊንክድኢን ተፅዕኖ ፈጣሪ የሆኑ የኢትዮጵያ ባለሙያዎችና የይዘት ፈጣሪዎች ሊሸለሙ ነው
#Fastmereja:-በኢትዮጵያ በሊንክድኢን (LinkedIn) መድረክ ላይ ንቁ ተሳትፎ ላላቸው የዲጂታል ይዘት ፈጣሪዎች እና ባለሙያዎች እውቅና ለመስጠት የተቋቋመው “የሊንክድኢን ቼንጅሜከርስ አዋርድስ ኢትዮጵያ (LCAE)” የመጀመሪያውን የሽልማት ስነ-ስርዓት ሊያካሂድ መሆኑን በዛሬዉ እለት በተሰጠ መግለጫ ተገልጿል።
ይህ መርሃ ግብር የፊታችን ሐምሌ 25 ቀን 2018 ዓ.ም (August 1, 2026) በአዲስ አበባ ማዘጋጃ ቤት ቲያትር አዳራሽ በደመቀ ሁኔታ ይካሄዳል።
በጉሩጂ ኤአር ኢትዮጵያ ከዥማ ሚዲያና ፕሮዳክሽን ጋር በመተባበር በተዘጋጀው በዚህ የክብር ምሸት ላይ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ የኢንዱስትሪ መሪዎችና የልማት አጋሮች የሚታደሙ ሲሆን፤ በህዝብ ጥቆማ፣ በድምፅ አሰጣጥ እና በባለሙያዎች ጥብቅ ግምገማ ያለፉ ድንቅ እጩዎች ሽልማት ይበረከትላቸዋል።
የጉሩጂ ኤአር ኢትዮጵያ መስራችና ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ያብስራ መካሻ እንደገለጹት፤ ሽልማቱ በሀገሪቱ የሙያ ስነ-ምህዳር ውስጥ የነበረውን ክፍተት ለመሙላትና ይዘታቸው ሌሎችን የሚያነቃቃና ትርጉም ያለው ሙያዊ ውይይት የሚፈጥሩ ሰዎችን ለማበረታታት ያለመ ነው፡፡
ይህ አገር አቀፍ ሽልማት በሳይንስና ቴክኖሎጂ (STEM)፣ በጤና፣ በስራ ፈጠራ፣ በአየር ንብረት እና በማርኬቲንግ ጨምሮ በ6 ዋና ዋና ምድቦች የተከፋፈለ ሲሆን፤ ከዲጂታል መድረክ ባሻገር በተጨባጭ ማህበረሰባዊ ተፅዕኖ የፈጠሩ ባለሙያዎችን ይሸልማል።
የሊንክድኢን ተፅእኖ ፈጣሪዎች ሽልማት ኢትዮጵያ (LCAE) በሀገሪቱ ሙያዊ እና ማህበራዊ መልክዓ-ምድር ላይ በተጨባጭ የሚለካ ተፅዕኖ እያሳደሩ ያሉ ግለሰቦችን እና ድርጅቶችን እውቅና የሚሰጥ የኢትዮጵያ የመጀመሪያው ብሔራዊ፣ ሁለገብ ዘርፍ መድረክ ነው።
#ኹነት
48 828
የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ያዘጋጀው ታላቅ የሥራ ትስስር (Job Fair) ተካሄደ
#FastMereja I የተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በ2018 ዓ.ም ስልጠናቸውን ያጠናቀቁ ምሩቃንን እና ሌሎች የቴክኒክና ሙያ ሰልጣኞችን በቀጥታ ከቀጣሪ ድርጅቶች ጋር ለማገናኘት ያለመ የመጀመሪያው የሥራ ትስስር (Job Fair) ዛሬ ሐምሌ 09 ቀን 2018 ዓ.ም. በታላቅ ድምቀት አካሂዷል።
የተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ዋና ዲን አቶ ተሾመ ፌይሳ ዋክቶሌ ለፋስት መረጃ በሰጡት ቃል እንደገለጹት፤ ይህ የሥራ አውደሪ የተዘጋጀው ቀጣሪ ኢንዱስትሪዎችንና ሥራ ፈላጊ ሰልጣኞችን በአንድ መድረክ በማገናኘት፣ ሁለቱም ወገኖች ተፈላጊ ሰራተኛና የሥራ ዕድል ፍለጋ የሚያባክኑትን ጊዜና እንግልት ለመቀነስ ታስቦ የተዘጋጀ ነው። ኮሌጁ ይህንን መድረክ በተቋም ደረጃ ሲያዘጋጅ ለመጀመሪያ ጊዜ ሲሆን፣ ከዚህ ቀደም በሌሎች መንግስታዊ ባልሆኑ ድርጅቶችና አማካሪዎች አማካኝነት ይዘጋጅ የነበረውን መርሃ ግብር ተቋሙ በባለቤትነት ተረክቦ ከተማ አቀፍ በሆነ መልኩ ማዘጋጀቱን አስረድተዋል።
በአውደሪው ላይ የኮሌጁ 967 መደበኛና የአጭር ጊዜ ሰልጣኞች ብቻ ሳይሆኑ፣ በአዲስ አበባ የሚገኙ 14ቱም ኮሌጆች ሰልጣኞቻቸውን ይዘው እንዲገኙ ጥሪ ተላልፎላቸዋል። ሰልጣኞቹ ከቀጣሪዎች ጋር ከመገናኘታቸው አስቀድሞ የሲቪ (CV) አጻጻፍ፣ የቃለ መጠይቅ ዝግጅት፣ አለባበስ እና የስራ ፈጠራ አስተሳሰብን በሚመለከት ሰፊ የአቅም ግንባታ ስልጠና ተሰጥቷቸዋል። ይህ ዝግጅት ምሩቃኑ በራስ የመተማመን ስሜት ኖሯቸው ወደ ሥራው ዓለም እንዲቀላቀሉ ትልቅ እገዛ እንደሚያደርግላቸው ታምኖበታል።
በዕለቱ በተካሄደው የሥራ አውደሪ ላይ ከሆቴል፣ ከኮንስትራክሽን፣ ከማኑፋክቸሪንግ፣ ከዘመናዊው የፈጠራ ግሪን ቴክኖሎጂ እና ከኢንፎርሜሽን ኮሙዩኒኬሽን ቴክኖሎጂ (ICT) ዘርፎች የተውጣጡ ከ35 በላይ ኢንዱስትሪዎች ተገኝተው የቅጥር ሂደቶችን ሲያከናውኑ ውለዋል። ከተለመደው የቅጥር ሁኔታ በተጨማሪ በኮሌጁ በቴክኖሎጂ (ICT) ዘርፍ የተደራጁና የሰው ሰራሽ አስተዋጽኦ (AI) መተግበሪያዎችን በመጠቀም ድረ-ገጾችንና የተለያዩ የፈጠራ ስራዎችን የሚሰሩ ወጣት ስራ ፈጣሪዎች የራሳቸውን ማሳያ ጥግ ይዘው ስራዎቻቸውን ለእይታ አቅርበዋል።
ለአንድ ቀን ብቻ የሚቆየው ይህ የሥራ አውደሪ መርሃ ግብር፣ በቀጣይም በየዓመቱ ከምረቃ ሥነ-ሥርዓት አስቀድሞ በቋሚነትና በስፋት የሚዘጋጅ ዓመታዊ መርሃ ግብር ሆኖ እንደሚቀጥል ዋና ዲኑ አቶ ተሾመ ፌይሳ ጨምረው ገልጸዋል።
#ኹነት
48 828
ባማኮን ሪል እስቴት በቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ አካባቢ የገነባውን ዘመናዊ አፓርታማ አስመረቀ!
#Fastmereja I ባማኮን ሪል እስቴት በቦሌ አዉሮፕላን ማረፊያ አካባቢ የገነባውንና ግንባታው ሙሉ በሙሉ የተጠናቀቀውን ዘመናዊ የመኖሪያ አፓርታማ ህንፃ በዛሬዉ እለት በይፋ መርቆ ለደንበኞቹ አስረከበ።
ፕሮጀክቱ በሀገሪቱ የታየውን ከፍተኛ የኢኮኖሚ ጫና እና የህንጻ መገንቢያ ቁሳቁሶች ዋጋ ንረት ተቋቁሞ፣ በደንበኞች ላይ ምንም ዓይነት ተጨማሪ ክፍያ ሳይጠይቅ መረከቡ ተገልጿል።
የባማኮን ሪል እስቴት የሽያጭና ማርኬቲንግ ዋና ኦፊሰር አቶ ፍሬው በየነ በምረቃው ሥነ-ሥርዓት ላይ እንደገለጹት፤ ህንፃው በአጠቃላይ 22 ሰፋፊ መኖሪያ ቤቶችን እና ተጨማሪ አንድ የፔንት ሃውስ (Penthouse) መኖሪያን ያካተተ መሆኑ ተገልጿል።
ህንፃው በየወለሉ (per floor) ሁለት አፓርታማዎችን ብቻ የያዘ ሲሆን፣ ይህም ቤቶቹ ሰፋፊ፣ ዘመናዊና ምቹ እንዲሆኑ ታስቦ የተገነባ መሆኑን ጠቁመዋል።
እንዲሁም በየወለሉ ላይ የሚገኙት “A” እና “B” የተሰኙት ቤቶች 206 እና 208 ካሬ ሜትር ስፋት ያላቸው ሲሆን፣ ለነዋሪዎች አስተማማኝ ፀጥታና ግላዊነትን (Privacy) የሚያጎናጽፉ የቅንጦት (Super Luxury) መኖሪያዎች መሆናቸው ተብራርቷል።
በተጨማሪም ቤቶቹ ዘመናዊ (Modern) እና የሀገር ውስጥ ባህላዊ ምግቦችን ለማዘጋጀት የሚረዳ (Traditional) ባለሁለት ኩሽናን ያካተቱ ሲሆን፣ ይህም የምግብ ሽታና ጭስ ወደ ሳሎን እንዳይሰራጭ ታስቦ የተሰራ ነው።
በሀገሪቱ የነበረው የገንዘብ ምንዛሬ ለውጥ (Devaluation)፣ የጦርነት ተፅዕኖ እና የነዳጅ ዋጋ መጨመር በህንፃ መገንቢያ ግብአቶች ላይ ከፍተኛ የዋጋ ጭማሪ ቢያስከትልም፤ ኩባንያው ደንበኞቹን ከተጨማሪ ክፍያ በጠበቀ መልኩ ቤቶቹን ማስረከብ መቻሉን የሥራ ኃላፊው ገልጸዋል።
በተጨማሪም ባማኮን በአጠቃላይ ስምንት እህት ኩባንያዎች ያሉት ሲሆን፣ እነዚህ ኩባንያዎች እርስ በርስ የሚደጋገፉበት ጠንካራ አቅም መኖሩ ሥራው ሳይስተጓጎል እንዲጠናቀቅ ከፍተኛ እገዛ ማድረጉን ገልጸዋል።
“ህንፃው ወደ ሽያጭ ከመውጣቱ በፊት ከ80% እስከ 85% የሚሆነው ግንባታው ተጠናቆ እንደነበር የተጠቀሰ ሲሆን ይህም በደንበኞች ላይ ምንም አይነት የዋጋ ጭማሪ ሳይደረግ ሙሉ በሙሉ አጠናቀዉ (Fully Finished) ለማስረከብ መቻላቸዉንም ገልፀዋል።
ባማኮን ሪል እስቴት ከተቋቋመ ሰባት ዓመታት የሆነው ሲሆን፣ አሁን ያስረከበው ህንፃ አራተኛ ፕሮጀክቱ ነው። ዋናው እናት ኩባንያ የሆነው ባማኮን ኢንጂነሪንግ በአዲስ አበባ የባንክ ዲስትሪክት አካባቢ በርካታ ግዙፍ ህንፃዎችን በመገንባት የሚታወቅና በዘርፉ ከ23 ዓመታት በላይ ልምድ ያለው ታላቅ ኩባንያ መሆኑ ይታወቃል።
#ቢዝነስ
