cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

Gedeo Tube🇪🇹

መረጃው ለሌሎች እንዲደርስ ሼር ያድርጉ! @Gedeotube

نمایش بیشتر
پست‌های تبلیغاتی
1 401
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
+47 روز
+1630 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

gereqixxa hashsha gadabekke roga'n calicalekke lola'n butinixxi lele'ma hexxeman ...olaa okone'n afendinaxxi unna woma tarja erge?
نمایش همه...
👍 4
#NewsAlert በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን በሬክተር ስኬል 4.8 ሆኖ የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ መከሰቱን የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የጂኦፊዚክስ፣ ህዋ ሳይንስ እና አስትሮኖሚ ኢንስቲትዩት አስታወቀ። በበና ፀማይ ወረዳ የተከሰተው ይህ የመሬት መንቀጥቀጥ አጎራባች በሆነው አሪ ዞን እንዲሁም ባለፈው ሳምንት ተመሳሳይ ክስተት ያስተናገደው የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልሉ ዳውሮ ዞን ጭምር የደረሰ እንደሆነ ነዋሪዎች እና ባለስልጣናት ለቢቢሲ ተናግረዋል። የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ትናንት እሁድ ግንቦት 4/2016 ዓ.ም. የተከሰተውን የመሬት መንቀጥቀጥ የመዘገበው ከሌሊቱ 6 ሰዓት ከ36 ደቂቃ ላይ እንደሆነ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የሶሲሞሎጂ ትምህርት ክፍል ኃላፊ ፕሮፌሰር አታላይ አየለ ለቢቢሲ ተናግረዋል። የመሬት መንቀጥቀጡ በሬክተር ስኬል 4.8 ሆኖ መመዝገቡን የሚያስረዱት ፕሮፌሰር አታላይ፤ ይህ መጠን “መካከለኛ” የሚል ደረጃ የሚሰጠው መሆኑን ገልጸዋል። የትናንቱ የመሬት መንቀጥቀጥ ልኬት ባለፈው ሳምንት በዳውሮ ዞን ከተመዘገበው 3 ሬክተር ስኬል ከፍ ያለ መሆኑን የሶሲሞሎጂ ትምህርት ክፍል ኃላፊው አስታውሰዋል። “ይን [የመሬት መንቀጥቀጥ] ዝቅተኛም፣ ከፍተኛ አይባልም። መካከለኛ ነው። [የሚያስከትለው] ውድመት እና ጥፋት ግን እንደ አካባቢው ቅርበት [የሚወሰን] ነው። ይህ ከተማ ውስጥ ቢፈጠር ብዙ ጉዳት ያደርሳል” ሲሉ የክስተቱ ሊያደርስ የሚችለውን የጉዳት ጠቅሰዋል። BBC
نمایش همه...
👍 1
gatowal lanqanen.... systemetixxe rakoban kadexxe yanene
نمایش همه...
👍 1
Photo unavailableShow in Telegram
i
نمایش همه...
Photo unavailableShow in Telegram
r
نمایش همه...
Photo unavailableShow in Telegram
የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና መርሐ ግብር ይፋ ሆነ አዲስ አበባ፣ ግንቦት 3፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የ2016 ትምህርት ዘመን የ2ኛ ደረጃ ማጠናቀቂያ ፈተና መርሐ ግብር ይፋ መሆኑን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አስታውቋል፡፡ የፈተና መርሐ ግብሩ በወረቀትና በበይነ መረብ የሚሰጠውን የፈተና የሚወስዱ ከትግራይ ክልል ውጭ በሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች ላሉ ተፈታኞች ነው ይፋ የተደረገው፡፡ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ተፈታኞች እና የሚመለከታቸው አካላት ዝግጅት እንዲያደርጉ አሳስቧል፡፡ የፈተና መርሐ ግብሩ ከታች ባለው ሰንጠረዥ ቀርቧል ፡-
نمایش همه...
ፋጭኧ! ባህላዊ የመንፃት ፕሮግራም ማጠቃለያ በካራ ሰንጎ።
نمایش همه...
ዛሬ ታርካዊ ቀን 29/08/2016 ዓ.ም በካራ ሶንጎ በጌዴኦ ዞን ቡሌ ወረዳ የእኔ አኮ ማኖዪ እና ጎሣሎ ያያ የአንድነት እና ዕርቀ ሰላም የፋጭኤ ፕሮግራም ማጠቃለያ ተደረገ።
نمایش همه...
#DV2025 የአሜሪካ ዲቪ ሎተሪ (Diversity Visa) 2025 አሸናፊዎች ነገ ይፋ ይደረጋሉ። ለዲቪ (Diversity Visa) 2025 ማመልከቻ የሞሉ በ dvprogram.state.gov/ESC/ ብቻ የማረጋገጫ ቁጥራቸውን በማስገባት ውጤቱን ወይም ማሸነፍ አለማሸነፋቸውን መመልከት ይችላሉ። NB. የማረጋገጫ ቁጥር ማመልከቻው ሲሞላ የተሰጠ ነው። ይህ ቁጥር የጠፋበት Forgot Confirmation Number በማለት አስፈለጊ መረጃ በመሙላት በኢሜል አዲስ ቁጥር ማግኘት ይቻላል። ውጤቱ በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ከምሽት 1 ሰዓት ጀምሮ ይፋ ይሆናል። የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር " የዲቪ (DV) ሎተሪ አሸንፋችኋል ፣ ከአሜሪካ ኤምባሲ ነው ምንደውለው / ይህን ኢሜል / ቴክስት የምንልከው " በማለት #የሚያጭበረብሩ_አካላት ስለሚኖሩ አመልካቾች እንዲጠነቀቁ አሳስቧል። አንድ አመልካች ዲቪ 2025 ደርሶት እንደሆነ እና እንዳልሆነ ማወቅ የሚችልበት ብቸኛው መንገድ ከላይ የተጠቀሰው ድረገጽ መሆኑን አስገንዝቧል። አሜሪካ በየዓመቱ ከአፍሪካ (ኢትዮጵያ ጨምሮ) ፣ እስያ ፣ አውሮፓ፣ ሰሜን አሜሪካ፣ ደቡብ አሜሪካ እና አውስትራሊያ 55 ሺህ ሰዎችን በዲቪ (DV) ሎተሪ ወደ ሀገሯ ታስገባለች።
نمایش همه...
👍 3
ኢትዮጵያ ለሶማሊያ ሰላምና መረጋጋት እያበረከተች ያለው አስተዋጽኦ ከፍተኛ ነው - የዩኤንሶም ኃላፊ ካትሪዮና ላይንግ *********** ኢትዮጵያ ለሶማሊያ ሰላምና መረጋጋት እያበረከተች ያለው አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑን የተመድ ዋና ፀሐፊ ልዩ ተወካይ እና በተባበሩት መንግስታት የሶማሊያ የድጋፍ ተልዕኮ (ዩኤንሶም) ኃላፊ ካትሪዮና ላይንግ ገለፁ፡፡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አጽቀ ሥላሴ ከተመድ ዋና ፀሐፊ ልዩ ተወካይ እና በተባበሩት መንግስታት የሶማሊያ የድጋፍ ተልዕኮ (ዩኤንሶም) ኃላፊ ካትሪዮና ላይንግ ጋር ፍሬያማ ውይይት አድርገዋል። በውይይታቸውም፤ በቀጣናው ሰላምና መረጋጋትን ለማስፈን በኢትዮጵያ እና በተባበሩት መንግስታት ድርጅት መካከል ያለውን አጋርነት የበለጠ ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ መክረዋል። አምባሳደር ታዬ አጽቀ ሥላሴ በውይይቱ ወቅት፤ ኢትዮጵያ በቀጠናው ሰላምና መረጋጋትን ለማስቀጠል ያላትን ቁርጠኝነት አረጋግጠዋል። የዩኤንሶም ኃላፊ ካትሪዮና ላይንግ በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ ለሶማሊያ ሰላምና መረጋጋት እያበረከተች ያለው ከፍተኛ አስተዋጽኦ የሚደነቅ መሆኑን መግለጻቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
نمایش همه...
👏 1