FMC Sport ፋና ስፖርት
This is Fana Media Corporation’s (FMC) Sport official Telegram channel. @Fanatelevision @afanoromofana @tigrignafana For more updates please visit https://fanamc.com/amharic/
نمایش بیشتر📈 تحلیل کانال تلگرام FMC Sport ፋና ስፖርት
کانال FMC Sport ፋና ስፖርት (@fmcsport) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 36 659 مشترک است و جایگاه 1 858 را در دسته ورزش و رتبه 944 را در منطقه أثيوبيا دارد.
📊 شاخصهای مخاطب و پویایی
از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 36 659 مشترک جذب کرده است.
بر اساس آخرین دادهها در تاریخ 02 سپتامبر, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 102 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -6 بوده و همچنان دسترسی گستردهای حفظ شده است.
- وضعیت تأیید: تأیید نشده
- نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 8.47% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 4.58% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب میکند.
- دسترسی پستها: هر پست به طور میانگین 3 106 بازدید دریافت میکند. در اولین روز معمولاً 1 679 بازدید جمعآوری میشود.
- واکنشها و تعامل: مخاطبان بهطور فعال حمایت میکنند؛ میانگین واکنش به هر پست 6 است.
📝 توضیح و سیاست محتوایی
نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاههای شخصی توصیف میکند:
“This is Fana Media Corporation’s (FMC) Sport official Telegram channel.
@Fanatelevision
@afanoromofana
@tigrignafana
For more updates please visit
https://fanamc.com/amharic/”
به لطف بهروزرسانیهای پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 03 سپتامبر, 2026)، کانال همواره بهروز و دارای دسترسی بالاست. تحلیلها نشان میدهد مخاطبان بهطور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته ورزش تبدیل کردهاند.
در حال بارگیری داده...
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 03 سپتامبر | +1 | |||
| 02 سپتامبر | +7 | |||
| 01 سپتامبر | 0 |
| 2 | ጋብሬል ማርቲኔሊ አል ሂላልን ተቀላቀለ
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 28፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የሳዑዲ አረቢያው ክለብ አል ሂላል ብራዚላዊውን የፊት መስመር ተጫዋች ጋብሬል ማርቲኔሊን ከአርሰናል ማስፈረሙን ይፋ አድርጓል።
አል ሂላል ለጋብሬል ማርቲኔሊ ዝውውር 60 ሚሊየን ፓውንድ ለአርሰናል መክፈሉን ቢቢሲ ዘግቧል።
ጋብሬል ማርቲኔሊ በ2025/26 የውድድር ዓመት ከአርሰናል ጋር የሊጉን ዋንጫ ማንሳቱ ይታወሳል።
የማርቲኔሊ የዝውውር ሂሳብ የአርሰናል የተጫዋች ሽያጭ ክብረ ወሰን በመሆን ተመዝግቧል።
አሌክስ ኦክስሌድ ቻምበርሊን በፈረንጆቹ 2017 ሊቨርፑልን በ35 ሚሊየን ፓውንድ በመቀላቀል የክለቡ የተጫዋች ሽያጭ ክብረ ወሰን ይዞ መቆየቱ ይታወሳል። | 423 |
| 3 | በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የሴቶች ብቻ የካራቴ ውድድር ተካሄደ
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 28፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ጄ.ኪ.ኤስ ኢትዮጵያ ፌዴሬሽን ከኢትዮጵያ ካራቴ ፌዴሬሽን ጋር በመተባበር ያዘጋጁት የመጀመሪያው የሴቶች ብቻ የካራቴ ውድድር በዛሬው ዕለት ተካሂዷል።
በዚሁ ወቅት የጄ.ኪ. ኤስ ኢትዮጵያ ፕሬዚዳንት ሰለሞን ዘውዱ እንዳሉት፤ ውድድሩ ፌዴሬሽኑ ከያዘው ሴት ስፖርተኞችን የማብቃት እቅድ አካል አንዱ ነው።
በውድድሩ ካዛና ክለብ በካታ ምድብ አንድ ወርቅ፣ አንድ ብር እና አንድ የነሀስ ሜዳልያዎችን በማግኘት የውድድሩ አጠቃላይ አሸናፊ ሆኗል፡፡
በውድድሩ ካንኩ ዳይ ክለብ በአንድ ወርቅ እና አንድ ብር 2ኛ እንዲሁም ዊነር ክለብ በአንድ ወርቅ እና ሁለት ነሀስ ሜዳልያዎች 3ኛ ደረጃን ይዘው አጠናቅቀዋል።
ከፍተኛ ፉክክር በታየበት የፋይት ውድድር 3 የወርቅ ሜዳልያዎችን የወሰደው ዊነር ክለብ አጠቃላይ አሸናፊ ሆኗል።
በውድድሩ ከ8 ቡድኖች የተውጣጡ 56 ተወዳዳሪዎች ተሳትፈዋል።
በዳዊት መሐሪ | 824 |
| 4 | የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የነሐሴ ወር ምርጥ አሰልጣኝ እጩዎች ይፋ ሆኑ
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 28፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ2026/27 የውድድር ዓመት የነሐሴ ወር ምርጥ አሰልጣኝ እጩዎች ይፋ ሆነዋል።
በዚህም መሰረት፡- አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ፣ ዣቢ አሎንሶ፣ ኢንዞ ማሬስካ እና ሰርጌጅ ጃኪሮቪች በእጩነት ቀርበዋል፡፡ | 1 407 |
| 5 | የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የነሐሴ ወር ምርጥ ተጫዋች እጩዎች ይፋ ሆኑ
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 28፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ2026/27 የውድድር ዓመት የነሐሴ ወር ምርጥ ተጫዋች እጩዎች ይፋ ሆነዋል።
በዚህም መሰረት፡- ሪያን ሼርኪ፣ ብሩኖ ፈርናንዴዝ፣ ሪካርዶ ካላፊዮሪ፣ ኮል ፓልመር፣ ጇ ፔድሮ፣ ማማዱ ሳንጋሬ፣ ዞላኪስ እና ዊሳ በእጩነት የቀረቡ ተጫዋቾች ናቸው፡፡ | 1 338 |
| 6 | ቶተንሃም ሆትስፐር ሙድሪክን ከቼልሲ አስፈረመ
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 26፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ቶተንሃም ሆትስፐር ዩክሬናዊውን ተጫዋች ሙድሪክን ከቼልሲ አስፈርሟል።
የሰሜን ለንደኑ ክለብ ቶተንሃም ሆትስፐር ተጫዋቹን ወደ ስብስቡ የቀላቀለው በውሰት ውል ነው።
የ25 ዓመቱ ተጫዋች በውሰት ውሉ መሰረት ለአንድ የውድድር ዓመት ያህል በሰሜን ለንደኑ ክለብ የሚቆይ ይሆናል።
ሙድሪክ በፈረንጆቹ 2023 ቼልሲን በ70 ሚሊየን ዩሮ መቀላቀሉ ይታወሳል።
ቶተንሃም ሆትሰፐር በክረምቱ የተጫዋቾች የዝውውር መስኮት ሳንድሮ ቶናሊ፣ ማቲያስ ፈርናንዴዝ፣ ሳቪኒሆ፣ ሮበርትሰን እና ኦማር ማርሙሽን የመሳሰሉ ተጫዋቾችን ማስፈረሙ ይታወሳል።
በአሰልጣኝ ሮቤርቶ ዲዘርቢ የሚመራው ቶተንሃም ሆትስፐር በሊጉ ያደረጋቸውን ተከታታይ ሁለት ጨዋታዎች መሸነፉ አይዘነጋም። | 2 297 |
| 7 | ማንቼስተር ሲቲ ንዳዬን ከኤቨርተን አስፈረመ
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 26፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ማንቼስተር ሲቲ ሴኔጋላዊውን ተጫዋች ኢሊማን ንዳዬ ከኤቨርተን ማስፈረሙን ይፋ አድርጓል።
ንዳዬ በማንቼስተር ሲቲ ቤት ለአምስት ዓመታት የሚያቆየውን ውል ተፈራርሟል።
ማንቼስተር ሲቲ ለ26 ዓመቱ ተጫዋች ዝውውር 65 ሚሊየን ፓውንድ ወጪ አድርጓል።
ንዳዬ ለኤቨርተን ባደረጋቸው 67 ጨዋታዎች 15 ግቦችን አስቆጥሮ 4 ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን አመቻችቶ አቀብሏል። | 2 078 |
| 8 | ማንቼስተር ሲቲ ኤንዞ ፈርናንዴዝን ከቼልሲ ለማሰፈረምተስማማ
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 26፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ማንቼስተር ሲቲ አርጀንቲናዊውን የመሐል ሜዳ ተጫዋች ኤንዞ ፈርናንዴዝ ከቼልሲ ለማስፈረም ከስምምነት ደርሷል።
ማንቼስተር ሲቲ ለ25 ዓመቱ ተጫዋች ዝውውር 125 ሚሊየን ፓውንድ እንደሚከፍል ዘ አትሌቲክ ዘግቧል።
ኤንዞ በፈረንጆቹ 2023 በ105 ሚሊየን ፓውንድ የዝውውር ሒሳብ ከፖርቹጋሉ ክለብ ቤኔፊካ የምዕራብ ለንደኑ ክለብ ቼልሲን መቀላቀሉ ይታወሳል፡፡
በአቤል ነዋይ | 2 250 |
| 9 | ባርሴሎና ጋብሬል ጄሱስን ከአርሰናል አስፈረመ
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 26፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የስፔኑ ክለብ ባርሴሎና ብራዚላዊውን የፊት መስመር ተጫዋች ጋብሬል ጄሱስን ከአርሰናል ማስፈረሙን ይፋ አድርጓል፡፡
ባርሴሎና ለተጨዋቹ ዝውውር 8 ነጥብ 6 ሚሊየን ፓውንድ ወጪ አድርጓል፡፡
ጋብሬል ጄሱስ በስፔኑ ክለብ እስከ ፈረንጆቹ 2029 ድረስ የሚያቆየውን ውል ተፈራርሟል፡፡
የ29 ዓመቱ ተጫዋች ለአርሰናል 123 ጨዋታዎችን አድርጎ 32 ግቦችን አስቆጥሯል፡፡
ጋብሬል ጄሱስ አርሰናል ከ22 ዓመታት በኋላ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዋንጫን ሲያሳካ የስብስቡ አካል ነበር፡፡
ተጫዋቹ ከአርሰናል በተጨማሪ ለማንቼስተር ሲቲ ተጫውቶ ማሳለፉ ይታወሳል፡፡
ከማንቼስተር ሲቲ ጋር የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ፣ የኤፍ ኤ ካፕ፣ የካራባኦ እና የኮሚኒቲ ሺልድ ዋንጫዎችን ማሳካቱ አይዘነጋም፡፡ | 2 272 |
| 10 | ሊዮኔል ሜሲ ከአርጀንቲና ብሔራዊ ቡድን ራሱን አገለለ
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 25፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ሊዮኔል ሜሲ ከአርጀንቲና ብሔራዊ ቡድን ራሱን ማግለሉን ይፋ አድርጓል።
ሜሲ ከአርጀንቲና ብሔራዊ ቡድን ጋር የዓለም ዋንጫ እና የኮፓ አሜሪካ ዋንጫን ማሳካቱ ይታወሳል።
ሜሲ ለአርጀንቲና ብሔራዊ ቡድን 207 ጨዋታዎችን አድርጎ 125 ግቦችን ያስቆጠረ ሲሆን ÷ 68 ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን ደግሞ አመቻችቶ አቀብሏል። | 2 672 |
| 11 | ሊቨርፑል ባርኮላን ከፒኤስጂ አስፈረመ
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 25፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ሊቨርፑል ፈረንሳዊውን የፊት መስመር ተጫዋች ብራድሊ ባርኮላን ከፒኤስጂ ማስፈረሙን ይፋ አድርጓል፡፡
ፈረንሳዊው ተጫዋች በመርሲሳይዱ ክለብ ለአምስት ዓመታት የሚያቆየውን ውል ተፈራርሟል፡፡
ሊቨርፑል ለዝውውሩ 125 ሚሊየን ዩሮ ክፍያ የፈጸመ ሲሆን፤ የተጫዋቹ ብቃት እየታየ ደግሞ ተጨማሪ 20 ሚሊየን ዩሮ ክፍያ የሚከፍል ይሆናል።
የ23 ዓመቱ ተጫዋች በፒኤስጂ በነበረው ቆይታ 153 ጨዋታዎችን አድርጎ 39 ግቦችን አስቆጥሯል፡፡
በሌላ በኩል ማንቼስተር ሲቲ ብራዚላዊውን የመስመር ተጫዋች አላን ኤሊያስን ከፓልሜራስ አስፈርሟል፡፡
አላን በማንቼስተር ሲቲ ቤት ለአምስት ዓመታት የሚያቆውን ውል መፈራረሙ ነው የተገለጸው፡፡
ማንቼስተር ሲቲ ለ22 ዓመቱ ተጫዋች 40 ሚሊየን ዩሮ የዝውውር ሂሳብ ወጪ አድርጓል፡፡
አላን ለፓልሜራስ ባደረጋቸው 96 ጨዋታዎች 9 ግቦችን አስቆጥሯል፡፡
ማንቼስተር ሲቲ በክረምቱ የተጫዋቾች የዝውውር መስኮት ኤሊዮት አንደርሰን፣ እና አዩብ ቡአዲን ማስፈረሙ ይታወሳል፡፡ | 2 557 |
| 12 | አስቶን ቪላ ከአርሰናል - የምሽቱ ተጠባቂ ጨዋታ
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 25 ፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የሁለተኛ ሳምንት መርሐ ግብር የአምናው ሻምፒዮን አርሰናል ከሜዳው ውጭ አስቶን ቪላን ይገጥማል፡፡
መድፈኞቹ ኮቨንትሪ ሲቲን በማሸነፍ የውድድር ዓመቱን የጀመሩ ሲሆን፤ ባለሜዳው ቪላ በበኩሉ በብራይተን በሰፊ የግብ ልዩነት ሽንፈት ማስተናገዱ ይታወሳል፡፡
ሁለቱ ቡድኖች በሊጉ እርስ በርስ ካደረጓቸው ያለፉት አምስት ጨዋታዎች በተመሳሳይ ሁለት ጊዜ ድል የቀናቸው ሲሆን፤ በቀሪው አንድ ጨዋታ ነጥብ ተጋርተዋል፡፡
ሁለቱን ቡድኖች የሚያገናኘው የሊጉ የሁለተኛ ሳምንት የመጨረሻ ጨዋታ ዛሬ ምሽት 4 ሰዓት ላይ በቪላ ፓርክ ይደረጋል፡፡ | 2 663 |
| 13 | ባርሴሎና ጋብሬል ጄሱስን ለማስፈረም ተስማማ
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የስፔኑ ክለብ ባርሴሎና ብራዚላዊውን የፊት መስመር ተጫዋች ጋብሬል ጄሱስን ከአርሰናል ለማስፈረም ተስማምቷል።
ባርሴሎና ለተጨዋቹ ዝውውር 8 ነጥብ 6 ሚሊየን ፓውንድ የዝውውር ሂሳብ ያቀረበ ሲሆን፣ በአርሰናል በኩል ጥያቄው ተቀባይነት ማግኘቱን ስካይ ስፖርት ዘግቧል።
ብራዚላዊው ተጫዋች የሕክምና ምርመራውን ለማድረግ እና በይፋ ውሉን ለመፈረም በነገው ዕለት ወደ ስፔን የሚያመራ ይሆናል። | 2 734 |
| 14 | ቼልሲ አርጀንቲናዊውን ግብ ጠባቂ ኢሚሊያኖ ማርቲኔዝን አስፈረመ
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ቼልሲ አርጀንቲናዊውን ግብ ጠባቂ ኢሚሊያኖ ማርቲኔዝን ከአስቶንቪላ ማስፈረሙን ይፋ አድርጓል፡፡
ኢሚሊያኖ ማርቲኔዝ በምዕራብ ለንደኑ ክለብ ለቼልሲ ለሁለት ዓመት የሚያቆየውን ውል ተፈራርሟል፡፡
ቼልሲ ለ33 ዓመቱ ግብ ጠባቂ ዝውውር 7 ነጥብ 5 ሚሊየን ፓውንድ ወጪ አድርጓል፡፡
ኢሚሊያኖ ማርቲኔዝ በአስቶንቪላ በነበረው ቆይታ ለቡድኑ 256 ጨዋታዎችን ማድረጉ ይታወሳል፡፡
ቼልሲ በክረምቱ የተጫቾች የዝውውር መስኮት ዳኒ ዌልቤክ እና ጆርዳን ሄንደርሰንን የመሳሳሉ ልምድ ያላቸውን ተጫዋቾች ማስፈረሙ ይታወሳል፡፡
በሁለተኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ቼልሲ ዛሬ ቀን 10 ሰዓት ላይ በሜዳው ስታምፎርድ ብሪጅ ብራይተንን ያስተናግዳል፡፡ | 2 663 |
| 15 | ዩናይትድ የመጀመሪያ ድሉን ለማሳካት
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በሁለተኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር በዛሬው ዕለት አራት ጨዋታዎች ይደረጋሉ።
በዚህም ምሽት 12 ሰዓት 30 ላይ ማንቼስተር ዩናይትድ በሜዳው ኦልድትራፎርድ ኢፕስዊች ታውንን ያስተናግዳል።
በመጀመሪያ ሳምንት የሊጉ ጨዋታ በሃል ሲቲ ሽንፈት የገጠመው ማንቼስተር ዩናይትድ የውድድር ዓመቱን የመጀመሪያ ድል ለማሳካት ወደ ሜዳ ይገባል።
ማንቼስተር ዩናይትድ ከዓመታት በኋላ ወደ ፕሪሚየር ሊጉ በተመለሰው ሃል ሲቲ መሸነፉን ተከትሎ የቡድኑ ብቃት ላይ ጥያቄዎች እንዲነሱ አድርጓል።
በአሰልጣኝ ማይክል ካሪክ የሚመሩት ቀያይ ሰይጣኖቹ በቀጣይ ጨዋታዎች የሚያደርጉት እንቅስቃሴ ይጠበቃል።
በ2025/26 የውድድር ዘመን በአሰልጣኝ ማይክል ካሪክ ስር መሻሻሎችን ማሳየቱ ይታወሳል።
ማንቼስተር ዩናይትድ በ2025/26 የውድድር ዓመት በካሪክ ስር ያሳየውን መሻሻል በዚህኛው የውድድር ዓመት ይበልጥ እንዲያሳድገውም በደጋፊዎች ዘንድ ይጠበቃል።
https://www.facebook.com/share/p/1BUSa1gHy1/?mibextid=wwXIfr | 2 458 |
| 16 | በሲድኒ ማራቶን አትሌት አዲሱ ጎበና ክብረወሰን በማሻሻል ጭምር አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በሲድኒ ማራቶን ኢትዮዽያዊው አትሌት አዲሱ ጎበና ክብረወሰን በማሻሻል ጭምር አሸንፏል።
ትናንት ምሽት ለ24ኛ ጊዜ በተካሄደው የማራቶን ውድድር አትሌት አዲሱ ጎበና 2 ሰዓት ከ4 ደቂቃ ከ42 ሰከንድ በመግባት ውድድሩን በቀዳሚነት አጠናቅቋል።
አትሌቱ የገባበት ሰዓትም የቦታው ክብረ ወሰን ሆኖ ተመዝግቧል።
በውድድሩ ጭምዴሳ ደበሌ 2ኛ፣ ጀማል መኮንን 5ኛ እንዲሁም የባለፈው ዓመት የርቀቱ አሸናፊ ኃይለማርያም ኪሮስ 6ኛ ደረጃን ይዘው ውድድራቸውን ጨርሰዋል።
በሴቶች ደግሞ ኬንያዊቷ አትሌት ፒርስ ጅፕችርችር በቀዳሚነት ውድድሩን አጠናቅቃለች።
በርቀቱ የተሳተፉት ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ሹሬ ደምሴ፣ ሄቨን ሀይሉ እና መሰረት አበባየሁ ከ3ኛ እስከ 5ኛ ያለውን ደረጃ በመያዝ ውድድራቸውን ማጠናቀቃቸውን ከፌዴሬሽኑ የተገኘው መረጃ ያመላክታል። | 2 437 |
| 17 | የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ድልድል ይፋ ሆነ
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 21፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የ2026/27 የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ድልድል የእጣ አወጣጥ ሥነ ሥርዓት በዛሬው ዕለት በሞናኮ ተካሂዷል፡፡
ለሦስተኛ ዓመት በሊግ የውድድር ቅርጽ በሚካሄደው የ2026/27 የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ውድድር የምድብ ጨዋታዎች አርሰናል ከሪያል ማድሪድ በኢምሬትስ ይገናኛሉ፡፡
በዚህም መሰረት የአርሰናል ተጋጣሚዎች፡- ሪያል ማድሪድ፣ ባየርን ሙኒክ፣ ቦሩሺያ ዶርትመንድ፣ ሪያል ቤቲስ፣ ሊል፣ ናፖሊ፣ ሳባህ እና ስላቪያ ፕራሃ ሆነዋል፡፡
ማንቼስተር ሲቲ በምድብ ጨዋታዎች ከባርሴሎና እና ፒኤስጂ ጋር ይገናኛል፡፡
ስፖርቲንግ ክለብ፣ ፖርቶ፣ ናፖሊ፣ አር ቢ ሌፕዚግ፣ ኤኢኬ አቴንስ እና ሎንስ ሌሎች የውሃ ሰማያዊዎቹ ተጋጣሚዎች ናቸው፡፡
ማንቼስተር ዩናይትድ ከባየርን ሙኒክ እና አትሌቲኮ ማድሪድ ጋር ይገናኛል፡፡
የማንቼስተር ዩናይትድ ተጋጣሚዎች፡- ባየርን ሙኒክ፣ አትሌቲኮ ማድሪድ፣ ሮማ፣ ስፖርቲንግ ክለብ፣ አር ቢ ሌፕዚግ፣ ቪያሪያል፣ ኮሞ፣ ሳባህ፣
የአምናው ሻምፒየን ፒ ኤስ ጂ ተጋጣሚዎች፡- ባርሴሎና፣ ጋላታሳራይ፣ ስሎቫን ብራቲስላቫ፣ ማንቼስተር ሲቲ፣ አስቶን ቪላ፣ ቪያሪያል፣ ኮሞ ናቸው፡፡
ሪያል ማድሪድ በበኩሉ ከአርሰናል በተጨማሪ ኢንተር ሚላን፣ ፒኤስቪ፣ ሮማ፣ አር ቢ ሌፕዚግ፣ ሻካታር ዶኔስክ፣ ላስክ እና ኤኢኬ አቴንስን የሚገጥም ይሆናል፡፡
የሊቨርፑል ተጋጣሚዎች፡- አትሌቲኮ ማድሪድ፣ ኢንተር ሚላን፣ ፖርቶ፣ ሎንስ፣ ቪያሪያል፣ ክለብ ብሩጅ፣ ፈነርባቼ እና ላስክ ሆነዋል፡፡
የባርሴሎና ተጋጣሚዎች፡- ፒ ኤስ ጂ፣ ማንቼስተር ሲቲ፣ አስቶን ቪላ፣ ኮሞ፣ ፌይኖርድ፣ ስፖርቲንግ ክለብ፣ ጋላታሳራይ እንዲሁም ሳባህ ናቸው፡፡
የባየርን ሙኒክ ተጋጣሚዎች፡- አርሰናል፣ ሪያል ቤቲስ፣ ቦዶ ግሊምት፣ ስላቪያ ፕራሃ፣ አ | 3 522 |
| 18 | የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የዕጣ ድልድል ዛሬ ይፋ ይሆናል
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 21፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የ2026/27 የውድድር ዓመት የዕጣ ድልድል በዛሬው ዕለት ይፋ ይሆናል፡፡
የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ከ2024/25 የውድድር ዓመት ወዲህ የቀደመ የጨዋታ ቅርጹን በመቀየር በሊግ ቅርጽ የተሳታፊ ቡድኖችን ቁጥር ወደ 36 በማሳደግ እየተካሄደ ይገኛል፡፡
ያለፉትን ሁለት ዓመታት የፈረንሳዩ ክለብ ፒኤስጂ በተከታታይ ሻምፒዮን በመሆን በመድረኩ አስደናቂ ጊዜ አሳልፏል፡፡
በአዲሱ የውድድር ዓመት ፒኤስጂ ሻምፒዮን የሚሆን ከሆነ በተከታታይ ሦስት ጊዜ የማሸነፍ ክብረ ወሰንን ከሪያል ማድሪድ ጋር የሚጋራ ይሆናል፡፡
https://www.facebook.com/share/p/1EahfDDLmb/?mibextid=wwXIfr | 3 393 |
| 19 | በግማሽ ማራቶን ውድድር አዲስ የዓለም ክብረወሰን ያስመዘገበው አትሌት ዮሚፍ ቀጄልቻ አቀባበል ተደረገለት
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 20፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአርጀንቲና ቦነስ አይረስ በተካሄደው የግማሽ ማራቶን ውድድር በወንዶች አዲስ የዓለም ክብረወሰን ያስመዘገበው አትሌት ዮሚፍ ቀጄልቻ እና በሴቶች የውድድሩን አዲስ የቦታ ክብረወሰን በማስመዝገብ ያሸነፈችው አትሌት ፎቴን ተስፋይ አቀባበል ተደረገላቸው።
አትሌት ዮሚፍ ቀጄልቻ 56:51 በሆነ ጊዜ በመግባት በዩጋንዳዊው አትሌት ጃኮብ ኪፕሊሞ ተይዞ የነበረውን 57:20 የዓለም ክብረወሰን በግማሽ ማራቶን በማሻሻል አዲሱን የዓለም ምርጥ ሰዓት ማስመዝገቡ ይታወሳል።
በሴቶች ውድድር ደግሞ አትሌት ፎቴን ተስፋይ 1:03:57 በሆነ ጊዜ በመግባት የውድድሩን የቦታ ክብረወሰን በማሻሻል በአንደኝነት ማሸነፏ አይዘነጋም።
ሁለቱ አትሌቶች አዲስ አበባ ሲገቡ የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ዴኤታ መኪዩ መሐመድ እና የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ኮማንደር አትሌት ስለሺ ስህንን ጨምሮ ሌሎች የፌዴሬሽኑ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት በፌዴራል ፖሊስ ማርሽ ባንድ አጃቢነት ደማቅ አቀባበል እንደተደረገላቸው ከፌዴሬሽኑ የተገኘው መረጃ ያመላክታል። | 4 102 |
| 20 | ኒውካስል ዩናይትድ ኒኮ ጎንዛሌዝን ከማንቼስተር ሲቲ አስፈረመ
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 20፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ)ኒውካስል ዩናይትድ ኒኮ ጎንዛሌዝን ከማንቼስተር ሲቲ ማስፈረሙን ይፋ አድርጓል።
ስፔናዊው የመሐል ሜዳ ተጫዋች ኒኮ ጎንዛሌዝ የረጅም ጊዜ ውል መፈረሙን ኒውካስል ዩናይትድ አሳውቋል።
ኒውካስል ዩናይትድ ለተጫዋቹ ዝውውር 48 ሚሊየን ፓውንድ ቅድመ ክፍያ የፈጸመ ሲሆን ቀሪው 4 ሚሊየን ፓውንድ ደግሞ የተጫዋቹ ብቃት እየታየ የሚከፈል መሆኑን ቢቢሲ ዘግቧል።
የ24 ዓመቱ ተጫዋች በማንቼስተር ሲቲ ቆይታው ለቡድኑ በሁሉም ውድድሮች 59 ጨዋታዎችን አድርጎ 4 ግቦችን አስቆጥሯል።
ኒኮ ጎንዛሌዝ በኒውካስል ዩናይትድ ቤት 6 ቁጥር ማልያን የሚለብስ ይሆናል።
በሌላ በኩል አስቶንቪላ ሴኔጋላዊውን የፊት መስመር ተጫዋች ኒኮላስ ጃክሰንን ከቼልሲ ለማስፈረም ተስማምቷል።
አስቶንቪላ ለጃክሰን ዝውውር በአጠቃላይ 65 ሚሊየን ፓውንድ ወጪ የሚያደርግ ሲሆን፤ 47 ነጥብ 5 ሚሊየን ፓውንድ ቅድመ ክፍያ ፈጽሟል።
ቀሪው ክፍያ ደግሞ የተጫዋቹ ብቃት እየታየ የሚከፈል ይሆናል።
ጃክሰን ቼልሲን በፈረንጆቹ 2023 ከተቀላቀለ በኋላ 81 ጨዋታዎችን አድርጎ 30 ግቦችን አስቆጥሯል።
በ2025/26 የውድድር ዓመት በውሰት ውል በባየርን ሙኒክ ማሳለፉ ይታወሳል።
ጃክሰን በቀጣይ የሕክምና ምርመራውን በማድረግ ቪላን የሚቀላቀል ይሆናል። | 3 191 |
