Rafidim Youth Academy Public Relation Channel
رفتن به کانال در Telegram
1 091
مشترکین
-124 ساعت
-77 روز
+430 روز
آرشیو پست ها
ለፈረንሣይ ቅርንጫፍ የአንደኛ ደረጃ እና ለቂርቆስ እንዲሁም የፈረንሳይ ቅርንጫፍ የቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤታችን ቤተሰቦች በሙሉ 👇
በሁለቱም ቅርንጫፍ የቅድመ መደበኛ እና የፈረንሳይ ቅርንጫፍ ደግሞ የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤታችን የ2019 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ምዝገባ ጀምረናል ።
በመሆኑም እንደሁልጊዜው ቀድመን የምንመዘግበው ነባር ተማሪዎቻችንን በመሆኑ ነባር ተማሪዎች ቀድማችሁ መመዝገብ አለባችሁ ። የመመዝገቢያ ቀነ ገደቡም ከነገ 10 / 7 11 / 2018 ዓ.ም እስከ 15 / 11 / 2018 ድረስ ሲሆን በእነዚህ ቀናት ብቻ መጥታችሁ መመዝገብ ትችላላችሁ ። ይህ ካልሆነ ግን በኋላ ላይ ለሚፈጠረው መጨናነቅም ሆነ ክፍተት ትምህርት ቤቱ ሃላፊነት የማይወስድ መሆኑን ለመግለጽ እንወዳለን ።
መልካም ምሽት
ለፈረንሣይ ቅርንጫፍ ትምህርት ቤታችን ቤተሰቦች በሙሉ 👇
የቅድመ መደበኛን ጨምሮ የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤታችንን የ2019 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ምዝገባ ጀምረናል ። በመሆኑም እንደሁልጊዜው ቀድመን የምንመዘግበው ነባር ተማሪዎቻችንን በመሆኑ ነባር ተማሪዎች ቀድማችሁ መመዝገብ አለባችሁ ። ይህ ካልሆነ ግን በኋላ ላይ ለሚፈጠረው መጨናነቅም ሆነ ክፍተት ትምህርት ቤቱ ሃላፊነት የማይወስድ መሆኑን ለመግለጽ እንወዳለን ።
መልካም ምሽት
መልዕክት 👇👇👇
በነገው ዕለት ሃምሌ 1 2018 ዓ.ም በሁለቱም ቅርንጫፍ ትምህርት ቤታችን የ2019 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ምዝገባን በይፋ እንጀምራለን ። እንደተለመደው ነባር ተማሪዎች በኋላ የሚኖረውን መጨናነቅ ለመቀነስ ሲባል አስቀድማችሁ በመመዝገብ ቦታችሁን እንድትይዙ እናሳስባለን ።
በሌላ ዜና በፈረንሳይ ቅርንጫፍ ትምህርት ቤታችን የክልል አቀፍ ፈተና ያስፈተንናቸውን የ6ኛ ክፍል ተማሪዎች 100 % ወይም ሙሉ በሙሉ ማሳለፋችንን በደስታ እናበስራለን ።
መልካም ምሽት
ዛሬ የትምህርት ቤታችን የራፊዲም ታላቅ ድግስ ተደርጓል ። 👏👏👏👏👏👏👏
ቤተሰቦቻችን ይህንን ደስ የሚል እና የሚያኮራ ጉዞ ከእናንተ ጋር እያደረግን ስለሆነ እጅግ ደስተኞች ነን ። ሃገርን የሚሰራ ትውልድ የመቅረፅ ትልቅ ሃላፊነትን እየተወጣን እንዳለን እናምናለን ። ለዚህም ደግሞ ዛሬ ያስመረቅናቸው ህፃናቶቻችን እና በዬደረጃው ጀግና ተማሪዎች ሆነው አንደኛ የሚወጡት አዳጊ ልጆቻችን ፤ ከውጤትም በላይ የሆነው ደግሞ የተማሪዎቻችን ግብረ ገብነት ስኬቶቻችንን የምንለካባቸው ግልፅ ማሳያዎች ናቸው ።
ዛሬ በአምባሳደር ቲያትር ቤት ከ500 በላይ ቤተሰቦቻችን የታደማችሁበት ፤ ኢትዮጵያን በትንሽ መድረክ ተወክላ ያዬንበት ቀን ነው ። በውዝዋዜ ፣ በድራማ በመዝሙሮች ቀናችን አምሮ ውሏል ። የታሪካዊ አርበኞች ታሪክ በልጆቻችን ጣፋጭ አንደበት ሲወሳ ነበር ። ዛሬ በሁለቱም ቅርንጫፍ 137 የኬጂ ተማሪዎችን መርቀን ወደ አንደኛ ክፍል ያሸጋገርንበት ዕለትም ነው ። ወደፊታችን ብሩህ መሆኑንም የትምህርት ቤታችን ሥራ አስኪያጅ አቶ ቢንያም ግርማ የደረስንበትን ከፍታ ገልፀውልናል ።
በዚህ መርሃግብር በዓመቱ በነበረው የክፍል ለክፍል ወድድር ከዬክፍላቸው አሸናፊ በመሆን ያጠናቀቁትን የምስክር ወረቀት የሰጠን ሲሆን ከሁለቱም ቅርንጫፍ ደግሞ የአሸናፊዎች አሸናፊ በመሆን ከአንደኛ እስከ ሶስተኛ የወጡትን ተማሪዎች ሽልማት ሸልመናል ።
በቀጣዩ ዓመት የአንደኛ ደረጃ ተማሪዎች ለመሆን ዛሬ ያስመረቅናቸው የኬጂ ተማሪዎቻችንም በቀጣይ ዓመት እንግዳ ነገር እንዳይሆንባቸው እና በደንብ እንዲላመዱት ብለን በማሰብ በዚህ ዓመት የክፍል ለክፍል ውድድር ማድረጋችን ይታወሳል ። በዚህም በዬቅርንጫፉ አንደኛ የወጡት ተማሪዎች ተሸልመዋል ።
በዓመቱ ትምህርት ከአንደኛ እስከ ሶስተኛ በመሆን በዬክፍሉ ያጠናቀቁ ተማሪዎችን የወርቅ የብር እና የነሃስ ሜዳሊያ ሸልመናል ። ከአጠቃላይ ክፍሎችም አንደኛ በመሆን በሁለቱም ቅርንጫፍ ከፍተኛ ውጤት ያመጡ ተማሪዎቻችንን ደግሞ የዋንጫ ሽልማት ሸልመናል ። በዚህ አጋጣሚ እነዚህ በሁለቱም ቅርንጫፍ አንደኛ የሆኑት ተማሪዎቻችን ሴቶች ናቸው ። ወደፊት ለሃገራቸው ብዙ እንደሚያበረክቱ እናምንባቸዋለን ።
እንኳን ለዚች ቀን አደረሰን !
ራፊዲም ትምህርት ቤት የእውቀት ቤት !
ነገ በዕለተ ቅዳሜ ሰኔ 27 ቀን የዓመቱ ስኬታማ የመማር እና የማስተማር ሥራችንን እና የድካማችንን ፍሬ የምናይበት ዕለት ነው ። በእርግጥ የራፊዲም ጥረት ፤ ትጋት እና ሂደት የዓመት ሳይሆን የዓመታት መሆኑ እርግጥ ነው ።
ነገእንደ አምና እንደ ታች አምናው የቅድመ መደበኛ ተማሪዎቻችንን ልናስመርቅ ፣ የደረጃ ተማሪዎቻችንን ልንሸልም ፣ መምህራኖቻችንን ልናመሰግን ብሎም ዳግም ለሌላ አዲስ ዓመት እና አዲስ ቀን ልንዘጋጅ የዓመቱን ሥራችንን ልንዘጋ ነው ።
ነገ ታላቁ ድግሳችን እንደ አምናው ሁሉ በተመሳሳይ በአምባሳደር ቲያትር ቤት ይደረጋል ። ታዲያ ወላጆች እንዲሁም ተማሪዎች ጠዋት 1 : 30 በስፍራው በመገኘት ያለንን ሰዓት በአግባቡ እንድንጠቀም እናሳስባለን ።
እንኳን ለዚች ቀን አደረሰን 👏
በፈረንሳይ ቅርንጫፍ ትምህርት ቤታችን የክልል አቀፍ ፈተና ካስፈተንናቸው ተማሪዎች 97 % ማሳፋችንን እንገልፃለን ። ከዚሁ ጋር ተያይዞ የስድስተኛ ክፍል ተማሪዎችን ውጤት ደግሞ እንደተለቀቀ የምናሳውቃችሁ ይሆናል ።
👉 እንደሚታወቀው የስድስተኛ እና የስምንተኛ ክፍል የክልል አቀፍ የሚኒስትሪ ፈተና ውጤት በዛሬው ዕለት ተለቋል ። ታዲያ እኛም በቂርቆስ ቅርንጫፍ ትምህርት ቤታችን 100 % ተማሪዎቻችንን አሳልፈናል ። ከስድስተኛ ክፍል 51 ተማሪዎችን ከስምንተኛ ክፍል ደግሞ 42 ተማሪዎችን አሳልፈን እጅግ ደስ ብሎናል ። እንደ ትምህርት ቤትም ታላቅ ኩራት ይሰማናል ።
👉 ታዲያ በዚሁ አያይዘን የምናስታውሳችሁ የፊታችን ቅዳሜ በ27 / 10 / 2018 ዓ.ም የትምህርት ቤታችን የዓመቱ ትምህርት የመዝጊያ መርሃግብር በደማቅ ሁኔታ በአምባሳደር ቲያትር ቤት ይደረጋል ። የደረጃ ተማሪዎች እና የጥያቄ እና መልስ ውድድርን ከ 1ኛ እስከ 3ኛ ሁናችሁ ያጠናቀቃችሁ ተማሪዎች በዕለቱ ከጠዋቱ አንድ ሰዓት ላይ እንድትገኙ እያሳስባለን ።
መልካም ምሸት 👏
በዓመቱ በተደረገው የጥያቄ እና መልስ ውድድር ከ1 እስከ 9 የወጡ ተማሪዎቻችን ናቸው ።
👉 እንደሚታወቀው በሁለቱም ቅርንጫፍ ትምህርት ቤቶቻችን የሁለተኛውን መንፈቅ ዓመት የአጋማሽ ፈተና ሰጥተን ጨርሰናል ። በመሆኑም በዛሬው ዕለት በሁለቱም ቅርንጫፍ ለተማሪዎቻችን መልሰናል ።
👉 ዛሬ ደግሞ በፈረንሳይ ቅርንጫፍ የቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤታችን ወደ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የሚሸጋገሩትን የኬጂ 3 ተመራቂ ተማሪዎችን ምክንያት በማድረግ የመዝጊያ እና የሽኝት ፕሮግራም አድርገናል ። እጅግ ደስ የሚል ቀን አብረናቸው አሳልፈናል ።
ተመልከቷቸው 👇
👉 ዛሬ በቂርቆስ ቅርንጫፍ የቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤታችን የ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን መጠናቀቅን ምክንያት በማድረግ እና የደረጃ 2 ተመራቂ ተማሪዎች የቅድመ አንደኛ ትምህርታቸውን ማጠናቀቃቸውን በማስመልከት እጅግ ደማቅ ዝግጅት አድርገን ከልጆቻችን ጋር ቆንጆ ቀን አሳልፈናል ። በተለይም ተመራቂ ተማሪዎች መምህራኖቻቸውን አመስግነዋል ። ይህን ማዬት ደግሞ ለእኛ እጅግ የሚያኮራን ነገር ነው ።
👉 በመጨረሻም የሁለተኛው መንፈቅ ዓመት የማጠቃለያ ፈተና የፊታችን ሰኞ በ15 / 10 / 18 ዓ.ም የሚጀምር መሆኑን እያሳወቅን ወላጆች በተሰጣችሁ ፕሮግራም መሰረት ልጆቻችሁን በማገዝ ለፈተና ብቁ ሆነው እንዲቀርቡ እንድታደርጉ መልክታችንን እናስተላልፋለን ።
ፎቶዎች አሉን
መልካም ምሽት
በነገው ዕለት በሁለቱም ቅርንጫፍ የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤታችን የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች የክልል አቀፍ የሚኒስትሪ እንደሚወስዱ ይታወቃል ።
በመሆኑም ተማሪዎች ነገ ጠዋት አንድ ሰዓት ላይ ዩኒፎርማችሁን ለብሳችሁ እንዲሁም ምሳ እቃችሁን ይዛችሁ እንድትመጡ እናሳስባለን ። ከዚሁ ጋር ተያዬዞ ለፈተና የሚያስፈልጓችሁን እርሳስ ላፒስ ፣ መቅረጫ እንዲሁም የትምህርት ቤት መታወቂያ እና የመፈተኛ አይዲያችሁን እንዳትረሱ እናሳስባለን ።
መልካም ምሽት
ዛሬ በቂርቆስ ቅርንጫፍ የቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤታችን የዓመቱ የመጨረሻ የጥያቄና መልስ የአሸናፊዎች አሸናፊ ውድድር ተከናውኗል ።
ታዲያ ይህን / ይችን አሸናፊያችንን ለይተን ያወቅን ሲሆን ማን እንደሆነ ግን በዓመቱ የመማር ማስተማር ሥራችንን መዝጊያ በምናደርግበት ደማቅ መርሃግብር ላይ የምንገልፅላችሁ ይሆናል ።
የተወዳዳሪዎችን ፎቶ ግን ከታች እንደሚከተለው እናጋራችኋለን 👇
መልካም ምሽት
በራፊዲም ትምህርት ቤት በሁለቱም ቅርንጫፍ በዚህ ሳምንት ከአንድ እስከ አምስተኛ ክፍል እንዲሁም ለሰባተኛ ክፍል ተማሪዎች የክለሳ ሳምንት ነው ። በቀጣይ ሳምንት በ15 / 10 / 18 ዓ.ም ዕለተ ሰኞ ጀምሮ የሁለተኛው አጋማሽ የማጠቃለያ ፈተና የሚፈተኑ ይሆናል ። የፈተና ፕሮግራሙን ነገ የምናጋራችሁ ይሆናል ።
ከዚሁ ጋር በተያያዘም የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ተማሪዎችም የክልል አቀፍ የሚኒሰትሪ ፈተና ይወስዳሉ ። የሁለቱም ቅርንጫፍ የ6ኛ ክፍል ተማሪዎቻችን ዛሬ ጀምረዋል ። በተመሳሳይ የ8ኛ ክፍል ተማሪዎቻችን ደግሞ በሁለቱም ቅርንጫፍ ሃሙስ የሚጀምሩ ይሆናል ።
እንደ ማሳሰቢያ 👇
በሁለቱም ቅርንጫፍ ላላችሁ ተማሪዎች በትምህርት ቤቱ ላይ ያለባችሁን ማንኛውንም አይነት ክፍያ ከፍላችሁ አጠናቁ ።
መልካም ምሽት
ዛሬ 6ኛ እና 8ኛ ክፍል ተማሪዎች የክልላዊ ፈተና በሚፈተኑበት ትምህርት ቤት ኦረንቴሽን የሚሰጥበት ቀን ነው ። ኦረንቴሽን ከተቀበሉ በኋላም በቀጥታ ወደቤታቸው ስለሚመለሱ ወላጆች ቁጥጥር እንድታደርጉ እና ዩኒፎርም መልበሳቸውን እንድታረጋግጡ እናሳስባለን ።
መልካም ቀን
