ru
Feedback
Rafidim Youth Academy Public Relation Channel

Rafidim Youth Academy Public Relation Channel

Открыть в Telegram

"ተማሪዎች ላይ መስራት አገር ላይ መስራት ነው!"

Больше
1 086
Подписчики
-124 часа
+57 дней
+530 день
Архив постов
በፈረንሳይ ቅርንጫፍ ትምህርት ቤታችን የክልል አቀፍ ፈተና ካስፈተንናቸው ተማሪዎች 97 % ማሳፋችንን እንገልፃለን ። ከዚሁ ጋር ተያይዞ የስድስተኛ ክፍል ተማሪዎችን ውጤት ደግሞ እንደተለቀቀ የምናሳውቃችሁ ይሆናል ።

👉 እንደሚታወቀው የስድስተኛ እና የስምንተኛ ክፍል የክልል አቀፍ የሚኒስትሪ ፈተና ውጤት በዛሬው ዕለት ተለቋል ። ታዲያ እኛም በቂርቆስ ቅርንጫፍ ትምህርት ቤታችን 100 % ተማሪዎቻችንን አሳልፈናል ። ከስድስተኛ ክፍል 51 ተማሪዎችን ከስምንተኛ ክፍል ደግሞ 42 ተማሪዎችን አሳልፈን እጅግ ደስ ብሎናል ። እንደ ትምህርት ቤትም ታላቅ ኩራት ይሰማናል ። 👉 ታዲያ በዚሁ አያይዘን የምናስታውሳችሁ የፊታችን ቅዳሜ በ27 / 10 / 2018 ዓ.ም የትምህርት ቤታችን የዓመቱ ትምህርት የመዝጊያ መርሃግብር በደማቅ ሁኔታ በአምባሳደር ቲያትር ቤት ይደረጋል ። የደረጃ ተማሪዎች እና የጥያቄ እና መልስ ውድድርን ከ 1ኛ እስከ 3ኛ ሁናችሁ ያጠናቀቃችሁ ተማሪዎች በዕለቱ ከጠዋቱ አንድ ሰዓት ላይ እንድትገኙ እያሳስባለን ። መልካም ምሸት 👏

በዓመቱ በተደረገው የጥያቄ እና መልስ ውድድር ከ1 እስከ 9 የወጡ ተማሪዎቻችን ናቸው ።

የተማሪዎች ሙዝ የመብላት ውድድር እጅግ አዝናኝ ነበር ።

👉 እንደሚታወቀው በሁለቱም ቅርንጫፍ ትምህርት ቤቶቻችን የሁለተኛውን መንፈቅ ዓመት የአጋማሽ ፈተና ሰጥተን ጨርሰናል ። በመሆኑም በዛሬው ዕለት በሁለቱም ቅርንጫፍ ለተማሪዎቻችን መልሰናል ። 👉 ዛሬ ደግሞ በፈረንሳይ ቅርንጫፍ የቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤታችን ወደ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የሚሸጋገሩትን የኬጂ 3 ተመራቂ ተማሪዎችን ምክንያት በማድረግ የመዝጊያ እና የሽኝት ፕሮግራም አድርገናል ። እጅግ ደስ የሚል ቀን አብረናቸው አሳልፈናል ። ተመልከቷቸው 👇

👉 ዛሬ በቂርቆስ ቅርንጫፍ የቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤታችን  የ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን መጠናቀቅን ምክንያት በማድረግ እና የደረጃ 2 ተመራቂ ተማሪዎች የቅድመ አንደኛ ትምህርታቸውን ማጠናቀቃቸውን በማስመልከት እጅግ ደማቅ ዝግጅት አድርገን ከልጆቻችን ጋር ቆንጆ ቀን አሳልፈናል ። በተለይም ተመራቂ ተማሪዎች መምህራኖቻቸውን አመስግነዋል ። ይህን ማዬት ደግሞ ለእኛ እጅግ የሚያኮራን ነገር ነው ። 👉 በመጨረሻም የሁለተኛው መንፈቅ ዓመት የማጠቃለያ ፈተና የፊታችን ሰኞ በ15 / 10 / 18 ዓ.ም  የሚጀምር መሆኑን እያሳወቅን ወላጆች በተሰጣችሁ ፕሮግራም መሰረት ልጆቻችሁን በማገዝ ለፈተና ብቁ ሆነው እንዲቀርቡ እንድታደርጉ መልክታችንን እናስተላልፋለን ። ፎቶዎች አሉን መልካም ምሽት

በነገው ዕለት በሁለቱም ቅርንጫፍ የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤታችን የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች የክልል አቀፍ የሚኒስትሪ እንደሚወስዱ ይታወቃል ። በመሆኑም ተማሪዎች ነገ ጠዋት አንድ ሰዓት ላይ ዩኒፎርማችሁን ለብሳችሁ እንዲሁም ምሳ እቃችሁን ይዛችሁ እንድትመጡ እናሳስባለን ። ከዚሁ ጋር ተያዬዞ ለፈተና የሚያስፈልጓችሁን እርሳስ ላፒስ ፣ መቅረጫ እንዲሁም የትምህርት ቤት መታወቂያ እና የመፈተኛ አይዲያችሁን እንዳትረሱ እናሳስባለን ። መልካም ምሽት

ዛሬ በቂርቆስ ቅርንጫፍ የቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤታችን የዓመቱ የመጨረሻ የጥያቄና መልስ  የአሸናፊዎች አሸናፊ ውድድር ተከናውኗል ። ታዲያ ይህን / ይችን አሸናፊያችንን ለይተን ያወቅን ሲሆን ማን እንደሆነ ግን በዓመቱ የመማር ማስተማር ሥራችንን መዝጊያ በምናደርግበት ደማቅ መርሃግብር ላይ የምንገልፅላችሁ ይሆናል ። የተወዳዳሪዎችን ፎቶ ግን ከታች እንደሚከተለው እናጋራችኋለን 👇 መልካም ምሽት

በራፊዲም ትምህርት ቤት በሁለቱም ቅርንጫፍ በዚህ ሳምንት ከአንድ እስከ አምስተኛ ክፍል እንዲሁም ለሰባተኛ ክፍል ተማሪዎች የክለሳ ሳምንት ነው ። በቀጣይ ሳምንት በ15 / 10 / 18 ዓ.ም ዕለተ ሰኞ ጀምሮ የሁለተኛው አጋማሽ የማጠቃለያ ፈተና የሚፈተኑ ይሆናል  ። የፈተና ፕሮግራሙን ነገ የምናጋራችሁ ይሆናል ። ከዚሁ ጋር በተያያዘም የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ተማሪዎችም የክልል አቀፍ የሚኒሰትሪ ፈተና ይወስዳሉ ። የሁለቱም ቅርንጫፍ የ6ኛ ክፍል ተማሪዎቻችን ዛሬ ጀምረዋል  ። በተመሳሳይ የ8ኛ ክፍል ተማሪዎቻችን ደግሞ በሁለቱም ቅርንጫፍ ሃሙስ የሚጀምሩ ይሆናል ። እንደ ማሳሰቢያ 👇 በሁለቱም ቅርንጫፍ ላላችሁ ተማሪዎች በትምህርት ቤቱ ላይ ያለባችሁን ማንኛውንም አይነት ክፍያ ከፍላችሁ አጠናቁ ። መልካም ምሽት

ዛሬ 6ኛ እና 8ኛ ክፍል ተማሪዎች የክልላዊ ፈተና በሚፈተኑበት ትምህርት ቤት ኦረንቴሽን የሚሰጥበት ቀን ነው  ። ኦረንቴሽን ከተቀበሉ በኋላም በቀጥታ ወደቤታቸው ስለሚመለሱ ወላጆች  ቁጥጥር እንድታደርጉ እና ዩኒፎርም መልበሳቸውን እንድታረጋግጡ እናሳስባለን ። መልካም ቀን

በተመሳሳይ ዘገባ በዚሁ በፈረንሳይ ቅርንጫፍ በአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤታችን በተካሄደ የክፍል ለክፍል የጥያቄና መልስ ውድድር የዓመቱ መርሃግብር የመዝጊያ ውድድር ተከናውኗል ። በዚህም የ2018 ዓ.ም የዓመቱ አሸናፊ ተለይታለች ። እሷም የ4ኛ ክፍል ተማሪያችን የሆነችው  ቢታንያ ሳሙኤል ናት 👏 ፎቶዎች እናጋራችኋለን ።

በራፊዲም ትምህርት ቤታችን የፈረንሳይ ቅርንጫፍ የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በዚህ ሳምንት የተለያዩ ተግባራት ተከናውነዋል ። ከእነዚህ ከተከናወኑት ተግባራት መካከል ዋና ዋናዎቹን ስናጋራችሁ  ፦ በየካ ክፍለ ከተማ በወረዳ 02 በተካሄደ የ6ኛ ክፍል እና የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች የጥያቄና መልስ ውድድር ተሳትፈናል ። በዚህም ታዲያ  የትምህርት ቤታችን የ6ኛ ክፍል ተማሪ የሆነችው ማህሌት ቀለመወርቅ 2ኛ ሆና ውድድሩን ስታጠናቅቅ  ከ8ኛ ክፍል ደግሞ  ተማሪ ብሌን ሃ/ገብርኤል እንደኛ በመሆን ውድድሩን ማጠናቀቅ ችላለች ። እኛ በዚህ ውጤት አና በተማሪዎቻችን ደስተኛ ነን ። መምህራን እና ተማሪዎችንም እንኳን ደስ አላችሁ ለማለት እንወዳለን 👏 ፎቶዎችን እናጋራለን  ።