Rafidim Youth Academy Public Relation Channel
Kanalga Telegram’da o‘tish
1 081
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
+27 kunlar
-1730 kunlar
Postlar arxiv
በተመሳሳይ ዘገባ በዚሁ በፈረንሳይ ቅርንጫፍ በአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤታችን በተካሄደ የክፍል ለክፍል የጥያቄና መልስ ውድድር የዓመቱ መርሃግብር የመዝጊያ ውድድር ተከናውኗል ። በዚህም የ2018 ዓ.ም የዓመቱ አሸናፊ ተለይታለች ። እሷም የ4ኛ ክፍል ተማሪያችን የሆነችው ቢታንያ ሳሙኤል ናት 👏
ፎቶዎች እናጋራችኋለን ።
በራፊዲም ትምህርት ቤታችን የፈረንሳይ ቅርንጫፍ የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በዚህ ሳምንት የተለያዩ ተግባራት ተከናውነዋል ።
ከእነዚህ ከተከናወኑት ተግባራት መካከል ዋና ዋናዎቹን ስናጋራችሁ ፦ በየካ ክፍለ ከተማ በወረዳ 02 በተካሄደ የ6ኛ ክፍል እና የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች የጥያቄና መልስ ውድድር ተሳትፈናል ። በዚህም ታዲያ የትምህርት ቤታችን የ6ኛ ክፍል ተማሪ የሆነችው ማህሌት ቀለመወርቅ 2ኛ ሆና ውድድሩን ስታጠናቅቅ ከ8ኛ ክፍል ደግሞ ተማሪ ብሌን ሃ/ገብርኤል እንደኛ በመሆን ውድድሩን ማጠናቀቅ ችላለች ።
እኛ በዚህ ውጤት አና በተማሪዎቻችን ደስተኛ ነን ። መምህራን እና ተማሪዎችንም እንኳን ደስ አላችሁ ለማለት እንወዳለን 👏
ፎቶዎችን እናጋራለን ።
የፈተና ጊዜ ሲቃረብ ሁላችንም በመጠኑ መጨነቅ እና ከወትሮው ከፍ ባለ መጠን ውጥረት ውስጥ መግባታችን የተለመደ ነገር ነው(በድጋሜ የተለጠፈ)
።
ይህም ጤናማ ፍርሀት ለፈተና እንድንተጋ ስለሚረዳን በተሻለ ለመዘጋጀት እንዲሁም ጥሩ ትኩረት ለማድረግ ያስችለናል።
ሆኖም ግን ይህ ጭንቀት ወይም ቴንሽን መጠነኛ ካልሆነ ወደ መደናገር እና ከፍተኛ ለሆነ ውጥረት ይዳርገናል ። በዚህም የተነሳ ፈተናችንን በጥሩ እንዳናስኬድ እና ተገቢውን ትኩረት እንዳንሰጥ ያደረፈርገናል ።
ከዚህም ሀሳብ ጋር በተያያዘ ለዚህ አይነቱ #ጭንቀት እና ውጥረት ውስጥ #እንድንገባ አስተዋጽኦ ከሚያደርጉ #ምክንያቶች ውስጥ #ጥቂቶቹ:
አሉታዊ ሀሳቦች ወደ አዕምሮ በመምጣት ሀሳባችን በሙሉ ስለ ፈተናው አስከፊነት እና ስለውጤት መበላሸት አብዝተን ስናስብ ።
በቂ እና ምክንያታዊ ያልሆነ ግመታ እና ድምዳሜ አጠቃሎ ስለፈተናው ማሰብ ።
የውጫዊ ተፅእኖ እንደ ቤተሰብ ፣ መምህራን እና ጓደኛ የሚመጡ ጫናዎች አስተሳሰባችን ላይ ይህ መሆን አለበት ወይም መሆን የለበትም የሚል አቋም መያዝ ስህተትን እንዳንቀበል እና መሳሳትን እንድንፈራ ስለሚያረግ በፈተና መዳረሻ ከፍተኛ ለሆነ ውጥረት ይዳርገናል ።
ሙሉ ሀሳብን ወደ ፈተናው ይዘት እና ሁኔታ ከማተኮር ይልቅ ወደ ውጤት እና ነጥብ ብቻ ላይ ማተኮር እና ማስላት። እነዚህ ዋና ዋናዎቹ በፈተና ወቅት ውጥረትን እና ጭንቀትን የሚያስከትሉ ምክንያቶች ናቸው።
ስለዚህ ተፈታኞች የተወሰነ ዘዴን በመጠቀም ይህን አይነቱን ከፍተኛ ውጥረት መቆጣጠር የምትችሉበትን መንገድ አንድ በአንድ እንመልከት፤
ከፈተና በፊት ማድረግ የሚገባን ዜዴዎች፤ -
ፈተና ሲመጣ መጠነኛ ውጥረት እና ጭንቀት ተፈጥሮአዊ እና ሁሉም ተፈታኝ ተማሪ እንደሚያጋጥመው መረዳት።
ለፈተና ስንዘጋጅ አዎንታዊ እና በጎ ሀሳቦችን ማሰብ፡፡ ይህ ማለት ስለፈተናው ክብደት እና አስከፊነት ከማሰብ በተቃራኒው በአይነ ህሊና (visualization) ዘና ብለን ስንፈተን እና ፈተናውን በተገቢ መንገድ ስንፈተን በአእምሮችን መሳል ።
ከዚህ ጋር በተያያዘ ከዚህ ቀደም በክፍል ውስጥ በብቃት የሰራናቸውን ፈተናዎች እና የገኘነውን ጥሩ ውጤቶች ማሰብ። እናም ምን አይነት ፈተና ሊመጣ ይችላል ብለን አብዝተን አለመጨነቅ ይልቅ የሚመጣው ፈተና ከዚህ በፊት ከተማርነው የተለየ አለመሆኑን መረዳት እና መጪውም ፈተና በተመሳሳይ እንደምንሰራው ማሰብ።
ፈተና ማለት ከዚህ ቀደም ከተማርነው ነገር የተረዳነውን እና የቀሰምነውን እውቀት የምንለካበት መመዘኛ እንጂ የኛ የህይወት ምዕራፍ ማብቂያ ወይም አጠቃላይ ችሎታችንን የሚያመላክት አይደለም ።
ምክንያቱም ከላይ እንደ ምክንያት ለተቀመጡት ነጥቦች ከዚህ ሀሳብ በተያያዘ አንድ ተማሪ በፈተና ጥሩ ውጤት ባያገኝ እና ቢሳሳት ቀድሞውኑ ወደ ጭንቅላቱ የሚመጣው አለማወቁ ዋጋ እንደሚያስከፍለው እና ቤተሰቦቹም ሆነ መምህራን እንደ ሰነፍ እና ዋጋ እንደሌለው ስለሚገመት ስህተትን አስተካክሎ ለቀጣይ ለማሻሻል እና ለመማር መሰናክል ይፈጥራል።
ስለዚህ ማወቅ ያለብን አንድ ነገር ቢኖር መሳሳትን አለመፍራት እና ሁሌም ለማወቅ እና ራስን ለማሻሻል ዝግጅ መሆንን ነው ። እንዲሁም አሁን የምንፈተነው ፈተና እንዳሰብነው እንኳን ውጤቱ ባያስደስት ለቀጣይ ማስተካከል እና ማሻሻል እንደሚቻል ማመን።
ከጓደኞቻችን ጋር ያጠናነውን ነገር በጋራ ሆነን መጠያየቅ እና እርስ በርስ ያወቅነውን ነገር መለዋወጥ፡፡ ይህ ዘዴ ይበልጥ የማስታወስ ብቃታችንን እንደሚጨምር እና የተጠያየቅነው ነገር እንዳይረሳን ያረጋል ።
ከዚህም በተጨማሪ የተሳሳትነውን ነገር ድጋሚ እንድንከልስ እና እርማት እንድናረግ ያግዘናል።
የፈተና ቀን ሲቃረብ እንደ ወትሮው ዘና ማለት እና በቂ እረፍትና በቂ እንቅልፍ መተኛት ። ይህም ጭንቀትን ይቀንስልናል፣ እንዲሁም ተረጋግተን ያጠናነውን ነገር አስበን እንድንሰራ ይረዳናል።
ፈተና ከጀመርን በኋላ መድረግ የሚገቡን ነገሮች (ፈተና ላይ እያለን)፤
ወደ ፈተና ከመሄዳችን ቀደም ብለን ለፈተና የሚረዱንን መሳሪያዎች እና የመፈተኛ ቁሶችን ማዘጋጀት።
አብዝተን ፈተናን እና የምናመጣውን ነጥብ ስሌት አለመገመት ።
ፈተና ስንጨርስ የተሳሳትነውን ጥያቄ አብዝቶ ማሰብ እና ሌላ ተማሪ መጠየቅ ጭንቀት ውስጥ ስለሚከተን ከዚህ ይልቅ ቤት ሄደን እረፍት ማድረግ እና ለቀጣይ ፈተና መዘጋጀት ።
በፈተና ጊዜ ድንገተኛ ጭንቀት እና ድንጋጤ ከገጠመን ወዲያው የምንሰራውን ገታ አድርገን በጥልቀት አየር በአፍንጫችን ስበን ወደ ሳንባ እያስገባን መልሰን ማስወጣት ይህንንም እስክንረጋጋ መደጋገም ።
ፈተና በምንሰራ ጊዜ ግራ ያጋባንን እና እርግጠኛ ያልሆንበትን ጥያቄ በይለፍ ማቆየት እና ወደ ቀጣዩ ጥያቄ መሄድ ይህም ጊዜያችንን በአግባቡ እንድንጠቀም ይረዳናል። ነገር ግን ምልክት አድርገን ማለፍ፤ •
በተመሳሳይ እርግጠኛ ያልሆልንበትን መልስ ላይ ተደናግጠን መሰረዝ እና መደለዝን መቀነስ
ይህም ስንደነግጥ እና ስንጨነቅ የምናውቀውን መልስ ትተን ወደ ሌላ መልስ እንድሰጥ ስለሚያረግ መሰረዝና መደለዝን መቀነስ ።
ፈተናውን ወደ ማገባደድ ስንደርስ በይለፍ ያስቀመጥናቸውን ግራ ያጋቡንን ጥያቄዎች ጥቂት አስበንበት መልስ መስጠት ፤ ካልሆነም ደግሞ ብልሀት ተጠቅመን የግመታ መልስ ሰጥተን ወደ ቀጣዩ ጥያቄ መሄድ ።
በተደጋጋሚ ሰአትን አለመመልከት ወይም ሰአት በቃን አልበቃን እያልን አለመጨነቅ።
ይልቅ በጣም ሳንንቀራፈፍ ተረጋግተን ፈተናውን መስራት እና ፈተናውን ከጨረስን በኋላ ተመልሰን የሰራነውን ጥያቄ አጠቃላይ ማየት ያስፈልጋል።
ለሁሉም ተፈታኞች
መልካም የጥናትና የፈተና ጊዜ!
ማሳሰቢያ
👉 ለሬፊዲም ትምህርት ቤት ለሁለቱም ቅርንጫፍ 👇
👉 ሰኞ ግንቦት 24/2018 ብሔራዊ ምርጫ ስለሆነ ትምህርት የለም !!
👉 ከማክሰኞ እስከ ረዕቡ ( ግንቦት 25 እና 26) የፈተና የቅድመ ዝግጅት ስራ ስለሚሰራ ትምህርት አይኖርም !
👉 ሐሙስ ግንቦት 27/2018 መደበኛ ትምህርት ይኖራል !
መልካም ምሽት !
ዛሬ በቂርቆስ ቅርንጫፍ የቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤታችን የ7ተኛ ዙር የጥያቄና መልስ ውድድር ተከናውኗል ።
ፎቶዎች እነግራችኋለን 👇
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች የራፊዲም ትምህርት ቤት ቤተሰቦች እንኳን ለ1447ኛው የዒድ አል አድሐ (ዐረፋ) በዓል በሰላም እና በጤና አደረሳችሁ ። ትምህርት ቤታችን ራፊዲም መልካም በዓል ይሁንላችሁ ሲል ምኞቱን ይገልፃል ።
መልካም በዓል !
Endi mavjud! Telegram Tadqiqoti 2025 — yilning asosiy insaytlari 
