Rafidim Youth Academy Public Relation Channel
前往频道在 Telegram
1 086
订阅者
-124 小时
+57 天
+530 天
帖子存档
በፈረንሳይ ቅርንጫፍ ትምህርት ቤታችን የክልል አቀፍ ፈተና ካስፈተንናቸው ተማሪዎች 97 % ማሳፋችንን እንገልፃለን ። ከዚሁ ጋር ተያይዞ የስድስተኛ ክፍል ተማሪዎችን ውጤት ደግሞ እንደተለቀቀ የምናሳውቃችሁ ይሆናል ።
👉 እንደሚታወቀው የስድስተኛ እና የስምንተኛ ክፍል የክልል አቀፍ የሚኒስትሪ ፈተና ውጤት በዛሬው ዕለት ተለቋል ። ታዲያ እኛም በቂርቆስ ቅርንጫፍ ትምህርት ቤታችን 100 % ተማሪዎቻችንን አሳልፈናል ። ከስድስተኛ ክፍል 51 ተማሪዎችን ከስምንተኛ ክፍል ደግሞ 42 ተማሪዎችን አሳልፈን እጅግ ደስ ብሎናል ። እንደ ትምህርት ቤትም ታላቅ ኩራት ይሰማናል ።
👉 ታዲያ በዚሁ አያይዘን የምናስታውሳችሁ የፊታችን ቅዳሜ በ27 / 10 / 2018 ዓ.ም የትምህርት ቤታችን የዓመቱ ትምህርት የመዝጊያ መርሃግብር በደማቅ ሁኔታ በአምባሳደር ቲያትር ቤት ይደረጋል ። የደረጃ ተማሪዎች እና የጥያቄ እና መልስ ውድድርን ከ 1ኛ እስከ 3ኛ ሁናችሁ ያጠናቀቃችሁ ተማሪዎች በዕለቱ ከጠዋቱ አንድ ሰዓት ላይ እንድትገኙ እያሳስባለን ።
መልካም ምሸት 👏
በዓመቱ በተደረገው የጥያቄ እና መልስ ውድድር ከ1 እስከ 9 የወጡ ተማሪዎቻችን ናቸው ።
👉 እንደሚታወቀው በሁለቱም ቅርንጫፍ ትምህርት ቤቶቻችን የሁለተኛውን መንፈቅ ዓመት የአጋማሽ ፈተና ሰጥተን ጨርሰናል ። በመሆኑም በዛሬው ዕለት በሁለቱም ቅርንጫፍ ለተማሪዎቻችን መልሰናል ።
👉 ዛሬ ደግሞ በፈረንሳይ ቅርንጫፍ የቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤታችን ወደ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የሚሸጋገሩትን የኬጂ 3 ተመራቂ ተማሪዎችን ምክንያት በማድረግ የመዝጊያ እና የሽኝት ፕሮግራም አድርገናል ። እጅግ ደስ የሚል ቀን አብረናቸው አሳልፈናል ።
ተመልከቷቸው 👇
👉 ዛሬ በቂርቆስ ቅርንጫፍ የቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤታችን የ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን መጠናቀቅን ምክንያት በማድረግ እና የደረጃ 2 ተመራቂ ተማሪዎች የቅድመ አንደኛ ትምህርታቸውን ማጠናቀቃቸውን በማስመልከት እጅግ ደማቅ ዝግጅት አድርገን ከልጆቻችን ጋር ቆንጆ ቀን አሳልፈናል ። በተለይም ተመራቂ ተማሪዎች መምህራኖቻቸውን አመስግነዋል ። ይህን ማዬት ደግሞ ለእኛ እጅግ የሚያኮራን ነገር ነው ።
👉 በመጨረሻም የሁለተኛው መንፈቅ ዓመት የማጠቃለያ ፈተና የፊታችን ሰኞ በ15 / 10 / 18 ዓ.ም የሚጀምር መሆኑን እያሳወቅን ወላጆች በተሰጣችሁ ፕሮግራም መሰረት ልጆቻችሁን በማገዝ ለፈተና ብቁ ሆነው እንዲቀርቡ እንድታደርጉ መልክታችንን እናስተላልፋለን ።
ፎቶዎች አሉን
መልካም ምሽት
በነገው ዕለት በሁለቱም ቅርንጫፍ የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤታችን የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች የክልል አቀፍ የሚኒስትሪ እንደሚወስዱ ይታወቃል ።
በመሆኑም ተማሪዎች ነገ ጠዋት አንድ ሰዓት ላይ ዩኒፎርማችሁን ለብሳችሁ እንዲሁም ምሳ እቃችሁን ይዛችሁ እንድትመጡ እናሳስባለን ። ከዚሁ ጋር ተያዬዞ ለፈተና የሚያስፈልጓችሁን እርሳስ ላፒስ ፣ መቅረጫ እንዲሁም የትምህርት ቤት መታወቂያ እና የመፈተኛ አይዲያችሁን እንዳትረሱ እናሳስባለን ።
መልካም ምሽት
ዛሬ በቂርቆስ ቅርንጫፍ የቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤታችን የዓመቱ የመጨረሻ የጥያቄና መልስ የአሸናፊዎች አሸናፊ ውድድር ተከናውኗል ።
ታዲያ ይህን / ይችን አሸናፊያችንን ለይተን ያወቅን ሲሆን ማን እንደሆነ ግን በዓመቱ የመማር ማስተማር ሥራችንን መዝጊያ በምናደርግበት ደማቅ መርሃግብር ላይ የምንገልፅላችሁ ይሆናል ።
የተወዳዳሪዎችን ፎቶ ግን ከታች እንደሚከተለው እናጋራችኋለን 👇
መልካም ምሽት
በራፊዲም ትምህርት ቤት በሁለቱም ቅርንጫፍ በዚህ ሳምንት ከአንድ እስከ አምስተኛ ክፍል እንዲሁም ለሰባተኛ ክፍል ተማሪዎች የክለሳ ሳምንት ነው ። በቀጣይ ሳምንት በ15 / 10 / 18 ዓ.ም ዕለተ ሰኞ ጀምሮ የሁለተኛው አጋማሽ የማጠቃለያ ፈተና የሚፈተኑ ይሆናል ። የፈተና ፕሮግራሙን ነገ የምናጋራችሁ ይሆናል ።
ከዚሁ ጋር በተያያዘም የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ተማሪዎችም የክልል አቀፍ የሚኒሰትሪ ፈተና ይወስዳሉ ። የሁለቱም ቅርንጫፍ የ6ኛ ክፍል ተማሪዎቻችን ዛሬ ጀምረዋል ። በተመሳሳይ የ8ኛ ክፍል ተማሪዎቻችን ደግሞ በሁለቱም ቅርንጫፍ ሃሙስ የሚጀምሩ ይሆናል ።
እንደ ማሳሰቢያ 👇
በሁለቱም ቅርንጫፍ ላላችሁ ተማሪዎች በትምህርት ቤቱ ላይ ያለባችሁን ማንኛውንም አይነት ክፍያ ከፍላችሁ አጠናቁ ።
መልካም ምሽት
ዛሬ 6ኛ እና 8ኛ ክፍል ተማሪዎች የክልላዊ ፈተና በሚፈተኑበት ትምህርት ቤት ኦረንቴሽን የሚሰጥበት ቀን ነው ። ኦረንቴሽን ከተቀበሉ በኋላም በቀጥታ ወደቤታቸው ስለሚመለሱ ወላጆች ቁጥጥር እንድታደርጉ እና ዩኒፎርም መልበሳቸውን እንድታረጋግጡ እናሳስባለን ።
መልካም ቀን
በተመሳሳይ ዘገባ በዚሁ በፈረንሳይ ቅርንጫፍ በአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤታችን በተካሄደ የክፍል ለክፍል የጥያቄና መልስ ውድድር የዓመቱ መርሃግብር የመዝጊያ ውድድር ተከናውኗል ። በዚህም የ2018 ዓ.ም የዓመቱ አሸናፊ ተለይታለች ። እሷም የ4ኛ ክፍል ተማሪያችን የሆነችው ቢታንያ ሳሙኤል ናት 👏
ፎቶዎች እናጋራችኋለን ።
በራፊዲም ትምህርት ቤታችን የፈረንሳይ ቅርንጫፍ የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በዚህ ሳምንት የተለያዩ ተግባራት ተከናውነዋል ።
ከእነዚህ ከተከናወኑት ተግባራት መካከል ዋና ዋናዎቹን ስናጋራችሁ ፦ በየካ ክፍለ ከተማ በወረዳ 02 በተካሄደ የ6ኛ ክፍል እና የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች የጥያቄና መልስ ውድድር ተሳትፈናል ። በዚህም ታዲያ የትምህርት ቤታችን የ6ኛ ክፍል ተማሪ የሆነችው ማህሌት ቀለመወርቅ 2ኛ ሆና ውድድሩን ስታጠናቅቅ ከ8ኛ ክፍል ደግሞ ተማሪ ብሌን ሃ/ገብርኤል እንደኛ በመሆን ውድድሩን ማጠናቀቅ ችላለች ።
እኛ በዚህ ውጤት አና በተማሪዎቻችን ደስተኛ ነን ። መምህራን እና ተማሪዎችንም እንኳን ደስ አላችሁ ለማለት እንወዳለን 👏
ፎቶዎችን እናጋራለን ።
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
