fa
Feedback
ዜና ማዕዘን - Breaking

ዜና ማዕዘን - Breaking

رفتن به کانال در Telegram

እንኳን ወደ ዜና ማዕዘን - Breaking በደህና መጡ በቻናላችን 📌 ፈጣን ሀገራዊ #መረጃዎች 📺 📌 #ዓለም ዓቀፍ መረጃዎች 📢 📌 አዝናኝ እና አስተማሪ መረጃዎች 🔔 📌 ወቅታዊ ጉዳዮች ሁሉንም በአንድ ታገኛላችሁ 📣 #zena_maezen ለሀሳብ አስተያየት (ads) @zena_maezen_bot

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام ዜና ማዕዘን - Breaking

کانال ዜና ማዕዘን - Breaking (@zena_maezen) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 68 538 مشترک است و جایگاه 936 را در دسته موسیقی و رتبه 447 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 68 538 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 15 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر -1 952 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -45 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 3.43% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 2.87% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 2 356 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 1 968 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 14 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
እንኳን ወደ ዜና ማዕዘን - Breaking በደህና መጡ በቻናላችን 📌 ፈጣን ሀገራዊ #መረጃዎች 📺 📌 #ዓለም ዓቀፍ መረጃዎች 📢 📌 አዝናኝ እና አስተማሪ መረጃዎች 🔔 📌 ወቅታዊ ጉዳዮች ሁሉንም በአንድ ታገኛላችሁ 📣 #zena_maezen ለሀሳብ አስተያየት (ads) @zena_maezen_bot

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 16 ژوئن, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته موسیقی تبدیل کرده‌اند.

68 538
مشترکین
-4524 ساعت
-4267 روز
-1 95230 روز
آرشیو پست ها
"የአሜሪካ ሰባራ ሳንቲም ወደ ኢራን አይሄድም። 300 ቢሊዮን ዶላር ወይም 24 ቢሊዮን ዶላር ምንም ዓይነት ገንዘብ የለም ”- የአሜሪካ ምክትል ፕሬዝዳንት የአሜሪካ ምክትል ፕሬዚዳንት ጄዲ ቫንስ ኢራ
"የአሜሪካ ሰባራ ሳንቲም ወደ ኢራን አይሄድም። 300 ቢሊዮን ዶላር ወይም 24 ቢሊዮን ዶላር ምንም ዓይነት ገንዘብ የለም ”- የአሜሪካ ምክትል ፕሬዝዳንት የአሜሪካ ምክትል ፕሬዚዳንት ጄዲ ቫንስ ኢራን ከዩናይትድ ስቴትስ ጋር ባደረገቸው ስምምነት የተነሳ "ሰባራ ሳንቲም" ወደ ቴህራን አይሄድም በማለት ተናገሩ። ቫንስ ለፎክስ ኒውስ በሰጡት ቃለ ምልልስ፣ የቀድሞው ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ ለኢራን "ከ1 ቢሊዮን ዶላር በላይ በጥሬ ገንዘብ ሰጥተዋል" ሲሉ ከትራምፕ አስተዳደር ጋር አነጻጽረዋቸዋል። "ኳታር 300 ቢሊዮን ዶላር ለኢራን ትሰጣታለች እንዲሁም 24 ቢሊየን እንዳይንቀሳቀስ የተደረገ የቴህራን ሃብት ይለቀቃል" ስለተባለው ጉዳይ፣ ሲጠየቁ ቫንስ "በመሰረቱ ይህ የኢራናውያን ፕሮፓጋንዳ ነው" ብለዋል። "እየሆነ ያለው የተወሰኑ ግለሰቦች ለአገር ውስጥ ማኅበረሰብ ስምምነቱ በጎ እንደሆነ በተቻለ መጠን ለማሳየት እየሞከሩ ነው" ሲሉም ተናግረዋል። "የአሜሪካ ሰባራ ሳንቲም ወደ ኢራን አይሄድም። 300 ቢሊዮን ዶላር ወይም 24 ቢሊዮን ዶላር ምንም ዓይነት ገንዘብ" ብለው፣ ይሁን አንጂ "ግዴታቸውን የሚወጡ ከሆነ ለኢራን ጥቅም አለው" በማለት ኳታርና ሳዑዲ አረቢያ በኢራን መዋዕለ ነዋያቸውን ሊያፈሱ እንደሚችሉ ጠቁመዋል። @zena_maezen @zena_maezen

የሕወሃት ክስ እና የአረና ጠንካራ መግለጫ ሕወሃት የፌደራል መንግሥቱ በትግራይ ላይ አዲስ ጥቃት ለመክፈት የድሮን ጥቃቶችን፣ የጦር ሠራዊት እንቅስቃሴዎችንና እቀባዎችን በማድረግ እየተዘጋጀ ነው ሲል
የሕወሃት ክስ እና የአረና ጠንካራ መግለጫ ሕወሃት የፌደራል መንግሥቱ በትግራይ ላይ አዲስ ጥቃት ለመክፈት የድሮን ጥቃቶችን፣ የጦር ሠራዊት እንቅስቃሴዎችንና እቀባዎችን በማድረግ እየተዘጋጀ ነው ሲል ከሰሰ። የፌደራል ባለስልጣናት የትግራይ ኃይሎችን በጦርነት ሰባኪነት የሚከሱት የራሳቸውን ዝግጅት ለመሸፈንና የኢትዮጵያን ሕዝብም ሆነ ዓለማቀፉን ማኅበረሰብ ለማሳሳት ነው ያለው ሕወሃት፣ ባለፉት ሦስት ወራት ለተፈናቃዮች ይቀርብ የነበረው ሰብዓዊ እርዳታ መቋረጡንም ጭምር ወቅሷል። በሌላ በኩል ተቃዋሚው አረና ትግራይ፣ ሕወሃት ያወጣውን የግዳጅ ወታደራዊ ምልመላ አዋጅ አጥብቆ አውግዟል። ፓርቲው ባወጣው መግለጫ፣ የትግራይ ጸጥታ ኃይሎችና ተዋጊዎች ለትግራይ ሕዝብ ምንም ዓይነት ጥቅም በማያስገኝ ሌላ ዙር ጦርነት ላይ አንሳተፍም በማለት ድምፃቸውንና ተቃውሟቸውን እንዲያሰሙ ጥሪ አቅርቧል።

"ሩሲያ ከዩክሬን ጋር የሰላም ስምምነት መፈጸም አለባት" - አሜሪካ የአሜሪካ ፕሬዚዳንት የሆኑት ዶናልድ ትራምፕ ለአመታት በጦርነት ውስጥ ለሚገኙት ለሩሲያ እና ዩክሬን የሰላም ጥሪ አቀረቡ። በቡድን
"ሩሲያ ከዩክሬን ጋር የሰላም ስምምነት መፈጸም አለባት"  - አሜሪካ የአሜሪካ ፕሬዚዳንት የሆኑት ዶናልድ ትራምፕ ለአመታት በጦርነት ውስጥ ለሚገኙት ለሩሲያ እና ዩክሬን የሰላም ጥሪ አቀረቡ። በቡድን 7 (G7) ጉባዔ ላይ ባደረጉት ንግግር "ስምምነት ላይ እንዲደርሱ ማድረግ እችላለሁ" ብለዋል። ትራምፕ፣ "ሩሲያ ከዩክሬን ጋር የሰላም ስምምነት መፈፀም አለባት" ሲሉ ተደምጠዋል። "እኔ የምችለውን አደርጋለሁ" ሲሉ ጥረት ማድረጋቸውንና ጥረታቸውን እንደሚቀጥሉ ጠቁመዋል። አሜሪካ ሩሲያ እና ዩክሬንን ለማስታረቅ የጀመረችው የማሸማገል ሂደት ከኢራን ጋር በገባችው ጦርነት መስተጓጎል ገጥሞታል። @zena_maezen @zena_maezen

ሕንድ የተማሪዎች ፈተና ማጭበርበርን ለመከላከል ቴሌግራምን በጊዜያዊነት አገደች ማክሰኞ ሰኔ 9 ቀን 2018 ዓ.ም የሕንድ መንግሥት ብሔራዊ የሕክምና ትምህርት ቤት መግቢያ ፈተና (NEET 2026) ጥ
ሕንድ የተማሪዎች ፈተና ማጭበርበርን ለመከላከል ቴሌግራምን በጊዜያዊነት አገደች ማክሰኞ ሰኔ 9 ቀን 2018 ዓ.ም የሕንድ መንግሥት ብሔራዊ የሕክምና ትምህርት ቤት መግቢያ ፈተና (NEET 2026) ጥያቄዎችን አውጥቶ ለማጭበርበር ጥቅም ላይ ውሏል በሚል የቴሌግራም መተግበሪያን እስከ መጪው ሰኞ ድረስ በጊዜያዊነት አግዷል። ባለፈው ወር የፈተና ጥያቄዎች አስቀድመው በመውጣታቸው ፈተናው ተሰርዞ የነበረ ሲሆን፣ ይህም በመላ ሀገሪቱ የተማሪዎች ተቃውሞ ቀስቅሶ ነበር። የቴሌግራም መሥራች ፓቬል ዱሮቭ ውሳኔው ማጭበርበርን እንደማያስቆም እና የፈተና ሌቦች ወደ ሌላ መተግበሪያዎች እንደሚዛወሩ ገልጾ፣ ድርጊቱ ከ150 ሚሊዮን በላይ ንጹኃን ተጠቃሚዎችን የሚቀጣ ነው ሲል ተችቷል። የሕንድ መንግሥት ግን እገዳው እንደ መጨረሻ አማራጭ የተወሰደ መሆኑን አስታውቋል። @zena_maezen @zena_maezen

የኢራን ብሔራዊ ቡድን አሠልጣኝ “ከፍተኛ ጭቆና ደርሶብናል“ አሉ የኢራን ብሔራዊ ቡድን አሠልጣኝ አሚር ጋሌኖይ፣ ቡድናቸው በዓለም ዋንጫው ላይ “ከማንም በላይ ከፍተኛ ጭቆና” እየደረሰበት መሆኑን በም
የኢራን ብሔራዊ ቡድን አሠልጣኝ “ከፍተኛ ጭቆና ደርሶብናል“ አሉ የኢራን ብሔራዊ ቡድን አሠልጣኝ አሚር ጋሌኖይ፣ ቡድናቸው በዓለም ዋንጫው ላይ “ከማንም በላይ ከፍተኛ ጭቆና” እየደረሰበት መሆኑን በምሬት ገለጹ። ቡድናቸው ከኒው ዚላንድ ጋር ሁለት እኩል አቻ ከተለያየ በኋላ በሰጡት መግለጫ፣ በተጫዋቾቻቸው ላይ የመጨረሻ ሰዓት የጉዞ ክልከላ እንደተጣለባቸው ይፋ አድርገዋል። እንደ አሠልጣኙ ማብራሪያ፣ ጨዋታው እንደተጠናቀቀ በሎስ አንጀለስ ቆይተው ማረፍ ቢፈልጉም፣ በአስቸኳይ “ውጡ” ተብለው ሜክሲኮ ወደሚገኘው የሥልጠና ማዕከል እንዲመለሱ ተገደዋል። ይህ ያልተጠበቀ ውሳኔ ቀደም ሲል የኢራን ቡድን እስከ ዓለም ዋንጫው ፍጻሜ ድረስ በአሪዞና እንዲቆይ ከተያዘው ዕቅድ ውጪ መሆኑ ታውቋል። ቡድኑ ባልታሰበ ሁኔታ ወደ ሜክሲኮዋ ቲጁአና ከተማ እንዲዛወር መደረጉ ስሜታቸውን ክፉኛ እንደጎዳው የገለጹት አሠልጣኙ፣ “በአውሮፕላን ተሳፍረን እንድንሄድ በተሰጠን ትዕዛዝ በጣም ተረብሸናል፤ ነገሮችን ሆን ብለው አክብደውብናል” ብለዋል። ሆኖም ግን፣ ይህ ሁሉ ጫና እና ማስገደድ ቡድናቸውን ምርጥ ከመሆን ወደኋላ እንደማያስቀረው በጽኑ ተናግረዋል።

ጋዜጠኛ ሳልሳዊት ባይነሳኝ ለአንድ ሳምንት ታስራ መቆየቷ ተገለጠ ጋዜጠኛ ሳልሳዊት ባይነሳኝ ሰኔ 1 ቀን 2018 ዓ.ም አመሻሽ ላይ ከመኖሪያ ቤቷ በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋሏንና እስካሁን ፍርድ ቤት እ
ጋዜጠኛ ሳልሳዊት ባይነሳኝ ለአንድ ሳምንት ታስራ መቆየቷ ተገለጠ ጋዜጠኛ ሳልሳዊት ባይነሳኝ ሰኔ 1 ቀን 2018 ዓ.ም አመሻሽ ላይ ከመኖሪያ ቤቷ በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋሏንና እስካሁን ፍርድ ቤት እንዳልቀረበች ታናሽ እህቷ ሃይማኖት ባይነሳኝ ለዶይቸ ቬለ ገልጻለች። መጀመሪያ ላይ ከቤት ሰራተኛዋ ጋር በቁጥጥር ስር የዋለችው ጋዜጠኛዋ፣ በአሁኑ ወቅት ፒያሳ ጊዮርጊስ አካባቢ በሚገኘው 3ኛ ፖሊስ ጣቢያ የምትገኝ ሲሆን፣ የአራት ዓመት ህፃን ልጇን ትታ ለእስር መዳረጓ ታውቋል። ጋዜጠኛዋ የተያዘችበት ይፋዊ ምክንያት እስካሁን ባይገለጽም፣ የክስ መዝገቡ በነዲያቆን ዘላለም መዝገብ ስር በመሆኑ እስሯ ከሰሞኑ የአርሲ ግድያ ጋር በተያያዘ በሰራችው ፕሮግራም ሊሆን እንደሚችል ቤተሰቦቿ ይጠረጥራሉ። @zena_maezen @zena_maezen

ቴህራን በሊባኖስ ያለው ጦርነት ማብቃት ከኢራን ጋር ያለውን ጦርነት ለማቆም ‹‹ቅድመ ሁኔታ›› ነው አለች የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራግቺ ፤በሊባኖስ ላይ የሚሰነዘሩ የእስራኤል ጥቃቶች መ
ቴህራን በሊባኖስ ያለው ጦርነት ማብቃት ከኢራን ጋር ያለውን ጦርነት ለማቆም ‹‹ቅድመ ሁኔታ›› ነው አለች የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራግቺ ፤በሊባኖስ ላይ የሚሰነዘሩ የእስራኤል ጥቃቶች መቆምን ጨምሮ በሁሉም ግንባሮች ጦርነት ማብቃቱ በኢራን እና በአሜሪካ-እስራኤል መካከል ያለውን ጦርነት ለማቆም ‹‹ቅድመ ሁኔታ›› ነው ብለዋል። አራግቺ በዋና ከተማዋ ቴህራን ለተሰበሰቡ የዓለም አቀፍ የዲፕሎማቲክ ልዑካን እንደገለጹት፤ የሊባኖስ እና የኢራን ግንባሮች በሆነ መልኩ የተሳሰሩ እና እርስ በርስ ጥገኛ ሆነዋል። ከመጀመሪያው ቀን ጀምሮ የኢራን እስላማዊ ሪፐብሊክ በሊባኖስ ያለውን ጦርነት ማቆም ከኢራን ጋር ያለውን ጦርነት ለመጨረስ እንደ ቅድመ ሁኔታ ቆጥራዋለች። አሁን የጦርነቱ ማብቂያ ላይ ስለደረስን፣ በሊባኖስም ጦርነቱ ያበቃል ያሉት ሚኒስትሩ፤ በሊባኖስ የሚደረገውን የተኩስ አቁም በቅርቡ ከአሜሪካ ጋር ከተደረሰው ስምምነት ‹‹የማይነጠል›› አካል እንደሆነ ገልጸዋል። በስዊዘርላንድ ዓርብ ዕለት የሚጀመረው የአሜሪካ እና የኢራን ውይይት በሁለት ምዕራፎች እንደሚከፈል አራግቺ መናገራቸውን ታስኒም የተባለው የኢራን የዜና ወኪል ዘግቧል። እንደ አራግቺ ገለጻ፤የመጀመሪያው ምዕራፍ የሆርሙዝ ወሽመጥን፣ የባሕር ላይ ገደቦችን እና ከጦርነት በኋላ ያለውን የኢራን የመሠረተ ልማት መልሶ ግንባታ ጉዳዮችን የሚመለከት ሲሆን፤ ሁለተኛው ምዕራፍ ደግሞ በመጨረሻ ስምምነት ላይ በሚወሰኑ የኒውክሌር ጉዳዮች እና የማዕቀብ ማቃለያዎች ላይ ያተኩራል። @zena_maezen @zena_maezen

#Ethiopia #SouthSudan ኢትዮጵያ በደቡብ ሱዳን የመኖሪያ ቤት ግንባታ ልትጀምር ነው ተባለ የኢትዮጵያ ፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በደቡብ ሱዳን ዋና ከተማ ጁባ ዘመናዊ የመኖሪያ እና የንግድ
#Ethiopia #SouthSudan ኢትዮጵያ በደቡብ ሱዳን የመኖሪያ ቤት ግንባታ ልትጀምር ነው ተባለ የኢትዮጵያ ፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በደቡብ ሱዳን ዋና ከተማ ጁባ ዘመናዊ የመኖሪያ እና የንግድ ተቋማት ግንባታን ለመጀመር የሚያስችሉትን ሁሉንም አስፈላጊ ቅድመ ዝግጅቶች ማጠናቀቁን ገልጿል። ፕሮጀክቱ ወደ ትግበራ ምዕራፍ የተሸጋገረው ባለፈው ቅዳሜ በጁባ ከተማ በተፈረመው የመጨረሻ የኦፕሬሽን ውል መሰረት ነው። ስምምነቱ ቀደም ሲል በሁለቱ ወገኖች መካከል በአዲስ አበባ ተፈርሞ የነበረውን የመግባቢያ ሰነድ በቀጥታ ወደ ሥራ የሚያስገባ መሆኑ ተመልክቷል። ስምምነቱን የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈፃሚ ረሻድ ከማል (ዶ/ር) እና የደቡብ ሱዳን የመካከለኛው ኢኳቶሪያ ግዛት ገዥ ኢማኑኤል አዲል በጋራ ፈርመውታል። በዚህ ስትራቴጂካዊ አጋርነት መሠረት ኮርፖሬሽኑ በጁባ ከተማ በፍጥነት እያደገ የመጣውን የቤት ፍላጎት ለማሟላት የሚያስችሉ ዘመናዊ የንግድ ማዕከላትን እና የመኖሪያ ሕንፃዎችን ግንባታ በበላይነት ይመራል ተብሏል።

ሩሲያ በብሪታንያ ጠቅላይ ሚኒስትር ላይ ያደረገቸው ኢላማ "ከሽፏል" ተባለ ሩሲያ በጠቅላይ ሚኒስትር ኬር ስታርመር ሁለት ቤቶችና የግል ተሽከርካሪ (RAVA 4) ላይ ተኩስ እንዲፈጸም ተልዕኮ መስጠቷን
ሩሲያ በብሪታንያ ጠቅላይ ሚኒስትር ላይ ያደረገቸው ኢላማ "ከሽፏል" ተባለ ሩሲያ በጠቅላይ ሚኒስትር ኬር ስታርመር ሁለት ቤቶችና የግል ተሽከርካሪ (RAVA 4) ላይ ተኩስ እንዲፈጸም ተልዕኮ መስጠቷን አንድ የምርመራ ሪፖርት ይፋ አድርጓል። ሞስኮ ጥቃቱን ያቀነባበረችው የዩክሬን እና ሩማንያ ዜግነት ባለውና ዲፕሎማቲክ ፓስፖርት በተሰጠው ግለሰብ አማካኝነት ነው። በአውሮፓ ህብረት ባለሙያዎች ይፋ የሆነው የምርመራ ሪፓርት ሩሲያ በብሪታንያ ውስጥ ክፍፍል የሚፈጥሩ እና ሀሰተኛ መረጃ የሚያሰራጩ "ፅንፈኛ ቡድኖችን አደራጅታለች" ሲል ወንጅሏል። ዳይሬክት አክሽን ዩኬ "Direct Action UK" እና ተክቢር ፋውንዴሽን "Takbir Foundation" ከሩሲያ በሚያገኙት የገንዘብ ድጋፍ በበይነ መረብ ምልመላ በመፈፀም በአውሮፓ እና ኔቶ ላይ ተደጋጋሚ ተልዕኮ እየፈፀሙ ነው ሲል ሪፖርቱ አመላክቷል። የሩሲያ ባለስልጣናት የዩናይትድ ኪንግደም ጠቅላይ ሚኒስትር ኬር ስታርመር ላይ ስለተደረገው የጥቃት ሙከራ የሰጡት ማብራሪያ የለም። በለንደን የሚገኘው የሩሲያ ኤምባሲ ግን "ሩሲያን እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴሯን በወንጀል ነክ ጉዳዮች ጋር ለማያያዝ የሚደረግ ሙከራ ተቀባይነት የለውም" ሲል አጭር ምላሽ ሰጥቷል።  @zena_maezen @zena_maezen

"ፑቲን እና ዘለንስኪ የሆነ ነገር ለማድረግ ዝግጁ ናቸው" ትራምፕ የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጦርነቱን ለማቆም ፍላጎት እንዳላቸው ገለጹ። ትራምፕ በቡድን 7 ጉባዔ ላይ ባደረጉት ንግግር ትና
+2
"ፑቲን እና ዘለንስኪ የሆነ ነገር ለማድረግ ዝግጁ ናቸው" ትራምፕ የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጦርነቱን ለማቆም ፍላጎት እንዳላቸው ገለጹ። ትራምፕ በቡድን 7 ጉባዔ ላይ ባደረጉት ንግግር ትናንት በተከበረው 80ኛ አመት የልደት በዓላቸው ወቅት ከፕሬዚዳንት ፑቲን እና ዘለንስኪ ጋር "ደውለውልኝ ጥሩ ውይይት አድርገናል" ብለዋል። ትራምፕ "ባነሱት ሀሳብ ተነስተን ለሰላም በተመሳሳይ አቅጣጫ እንጓዛለን" ሲሉ ተናግረዋል። በዚሁ መድረክ ላይ "ፑቲን እና ዘለንስኪ የሆነ ነገር ለማድረግ ዝግጁ ናቸው" ሲሉ ተደምጠዋል። "በየወሩ 25 ሺህ ሰው እየሞተ ነው፣ ያን ማስቆም አለብን" በማለት ገልጸዋል። ኢራንና አሜሪካ ስምምነት ላይ መድረሳቸውን ተከትሎ አሜሪካ የጀመረችውን የሩሲያ እና የዩክሬን ድርድር ታስጀምራለች ተብሎ ይታሰባል። @zena_maezen @zena_maezen

ሕወሓትን የተቃወሙት የ76 አመት አዛውንት ታሰሩ በትግራይ ክልል የእንደርታ ተወላጅ የሆኑት የ76 ዓመቷ ነባር ታጋይ አኸዛ ሕሉፍ፣ በክልሉ ስላለው የፍትህ እጦት፣ የመልካም አስተዳደር እክል እና የፖ
ሕወሓትን የተቃወሙት የ76 አመት አዛውንት ታሰሩ በትግራይ ክልል የእንደርታ ተወላጅ የሆኑት የ76 ዓመቷ ነባር ታጋይ አኸዛ ሕሉፍ፣ በክልሉ ስላለው የፍትህ እጦት፣ የመልካም አስተዳደር እክል እና የፖለቲካ ብልሽት አስመልክተው ከሶስት ቀናት በፊት የሰጡት ቃለመጠይቅ መነጋገሪያ መሆኑን ተከትሎ በህወሓት ታጣቂዎች ታግተው መታሰራቸው ተሰማ። የወረዳ 70 እንደርታ የፈለግማያት ጣቢያ ነዋሪ የሆኑትን ይህችን ጀግና እናት ለምን ተነፈስሽ? ለምንስ ተናገርሽ?” በሚል ዛሬ መታሰራቸውን ተረጋግጧል። እንደ መረጃዎች ገለጻ ለእስራታቸው ዋነኛ ምክንያት የሆነው “ለምን ልጆች ወደ ጦርነት ይገባሉ?” በማለት ሰላማዊ ጥሪ ማቅረባቸውና እንደሌሎቹ የጦርነት ነጋሪት ለመጎሰም ፈቃደኛ አለመሆናቸው ሲሆን፣ የቀድሞው ህወሓት እስከ እድሜ ልክ የሚያስቀጣ አፋኝ ህግ ማውጣቱ በሚታወስበት በዚህ ወቅት የ76 ዓመት አዛውንት እና ነባር ተጋዳሊትን ለአመለካከታቸው ሲል ማሰሩ ከፍተኛ ቁጣንና ትዝብትን እየቀሰቀሰ ይገኛል። እስካሁንም እናት አኸዛ ሕሉፍ በታጣቂዎች ተወስደው የት ቦታ እንደታሰሩና አሁን ያሉበት ሁኔታ በትክክል አለመታወቁ ተገልጿል። via:- andafta @zena_maezen @zena_maezen

የሃንጋሪ ፓርላማ ቪክቶር ኦርባን ዳግም ወደ ሥልጣን እንዳይመለሱ የሚያግድ የዘመን ገደብ ሕግ አፀደቀ የሃንጋሪ ፓርላማ የጠቅላይ ሚኒስትርነት የሥልጣን ዘመንን ቢበዛ ወደ 8 ዓመት የሚገድብ የሕገ-መን
የሃንጋሪ ፓርላማ ቪክቶር ኦርባን ዳግም ወደ ሥልጣን እንዳይመለሱ የሚያግድ የዘመን ገደብ ሕግ አፀደቀ የሃንጋሪ ፓርላማ የጠቅላይ ሚኒስትርነት የሥልጣን ዘመንን ቢበዛ ወደ 8 ዓመት የሚገድብ የሕገ-መንግሥት ማሻሻያ አፅድቋል። ይህ ውሳኔ ለ16 ዓመታት አገሪቱን የመሩት የቀድሞው መሪ ቪክቶር ኦርባን ዳግም ወደ ሥልጣን እንዳይመለሱ የሚያግድ ነው። ማሻሻያው ባለፈው ሚያዝያ ወር ምርጫውን ያሸነፉት አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ፔተር ማጂያር ሃንጋሪን ወደ አውሮፓ ኅብረት መደበኛ መዋቅር ለመመለስና ግንኙነታቸውን ለማስተካከል ከጀመሯቸው የፖለቲካ ሥርዓት ለውጦች መካከል አንዱ ነው። ፓርላማው በተጨማሪም በኦርባን ዘመን ተቺዎችን ለመመርመር ይውል የነበረውን «የሉዓላዊነት ጥበቃ ቢሮ» ለማፍረስ ወስኗል። @zena_maezen @zena_maezen

አሜሪካ የባህር ላይ እገዳውን ማንሳቷን ተከትሎ ቢያንስ አምስት የኢራን መርከቦች በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ማለፋቸውን ኢራን አስታወቀች። @zena_maezen @zena_maezen
አሜሪካ የባህር ላይ እገዳውን ማንሳቷን ተከትሎ ቢያንስ አምስት የኢራን መርከቦች በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ማለፋቸውን ኢራን አስታወቀች። @zena_maezen @zena_maezen

አውሮፓ ኅብረት ዩክሬንና ሞልዶቫን በአባልነት ለመቀበል የሚያስችለውን ታሪካዊ ውይይት በይፋ ጀመረ የአውሮፓ ኅብረት (EU) የዩክሬን እና የሞልዶቫን ይፋዊ የአባልነት ድርድር ሂደት በሉክሰምበርግ በተ
አውሮፓ ኅብረት ዩክሬንና ሞልዶቫን በአባልነት ለመቀበል የሚያስችለውን ታሪካዊ ውይይት በይፋ ጀመረ የአውሮፓ ኅብረት (EU) የዩክሬን እና የሞልዶቫን ይፋዊ የአባልነት ድርድር ሂደት በሉክሰምበርግ በተደረገ በይነ-መንግሥታት ጉባኤ በይፋ አስጀምሯል። ዩክሬን የሩሲያን ወረራ እየተከላከለች ባለችበት በዚህ ወቅት የአውሮፓ ኅብረት አባልነትን እንደ ዋነኛ የደህንነት ዋስትና የምትመለከተው ሲሆን፣ የኅብረቱን የሕግና የዲሞክራሲ መስፈርቶች ለማሟላት የዓመታት የፖለቲካ ማሻሻያዎችን ማድረግ ይጠበቅባታል። ቀደም ሲል የዩክሬንን ጉዞ በቪቶ (Veto) ስትዘጋ የነበረችው ሐንጋሪ፥ የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር ቪክቶር ኦርባን ባለፈው ሚያዝያ ወር በምርጫ መሸነፋቸውን ተከትሎ፣ አዲሱ መሪ ፔተር ማጂያር የቪቶ መብታቸውን በማንሳታቸው ለዚህ ታሪካዊ ድርድር በር ከፍቷል። የኅብረቱ የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ኃላፊ ካያ ካላስ ውሳኔውን "ትልቅ ማይልስቶን" ሲሉ የገለጹት ሲሆን፣ ሁለቱም ሀገራት በአስቸጋሪ ሁኔታዎች ውስጥ ሆነው ያሳዩትን ቁርጠኝነት አድንቀዋል። @zena_maezen @zena_maezen

የአሜሪካ ቢ-52 (B-52) ወታደራዊ ቦምብ ጣይ አውሮፕላን በካሊፎርኒያ ተከሰከሰ ሰኞ ሰኔ 8 ቀን 2018 ዓ.ም የአሜሪካ አየር ኃይል ንብረት የሆነ ግዙፍ የቢ-52 (B-52) የረጅም ርቀት ቦምብ
የአሜሪካ ቢ-52 (B-52) ወታደራዊ ቦምብ ጣይ አውሮፕላን በካሊፎርኒያ ተከሰከሰ ሰኞ ሰኔ 8 ቀን 2018 ዓ.ም የአሜሪካ አየር ኃይል ንብረት የሆነ ግዙፍ የቢ-52 (B-52) የረጅም ርቀት ቦምብ ጣይ አውሮፕላን በካሊፎርኒያ ከሚገኘው ኤድዋርድስ አየር ኃይል ጦር ሰፈር ለመነሳት በሞከረበት ወቅት ተከስክሷል። በአደጋው የደረሰው የሰው ሕይወት ጉዳትም ሆነ የአደጋው መንስኤ እስካሁን በይፋ ያልታወቀ ሲሆን፣ የአደጋ ጊዜ ሠራተኞች በስፍራው ተሰማርተው ክትትል እያደረጉ ይገኛሉ። እያንዳንዳቸው 110 ሚሊዮን ዶላር የሚያወጡትና የኑክሌር መሣሪያዎችን ጭምር የመሸከም አቅም ያላቸው እነዚህ አውሮፕላኖች ለአሜሪካ አየር ኃይል ስትራቴጂካዊ የጦር መሣሪያዎች መሆናቸው ይታወቃል። @zena_maezen @zena_maezen

ደቡብ አፍሪካውያን አርቲስቶች ኮንሰርቶቻቸው በመላው አፍሪካ እየተሰረዙባቸው ነው በደቡብ አፍሪካ እየተካሄደ ያለው ህገ-ወጥ ስደተኞችን የማስወጣት ዘመቻ በአህጉሪቱ ደረጃ ከፍተኛ ተቃውሞ እያስከተለባት
ደቡብ አፍሪካውያን አርቲስቶች ኮንሰርቶቻቸው በመላው አፍሪካ እየተሰረዙባቸው ነው በደቡብ አፍሪካ እየተካሄደ ያለው ህገ-ወጥ ስደተኞችን የማስወጣት ዘመቻ በአህጉሪቱ ደረጃ ከፍተኛ ተቃውሞ እያስከተለባት ሲሆን፣ የሀገሪቱ የኪነጥበብ ባለሙያዎችም የዚህ ሰለባ እየሆኑ መምጣታቸውን የፍትህና ህገ-መንግስታዊ ልማት ሚኒስትሯ ማሞሎኮ ኩባዪ ገልጸዋል። ሚኒስትሯ ከኤስኤቢሲ ጋር ባደረጉት ቃለ-ምልልስ፣ በርካታ ደቡብ አፍሪካውያን ድምጻውያንና ተዋንያን በመላው አፍሪካ ሊያቀርቧቸው የነበሩት ዝግጅቶች በየሀገራቱ እየተሰረዙባቸው በመሆኑ ከፍተኛ የገቢ ኪሳራ እየደረሰባቸው ይገኛል። መንግስታቸው የወሰደው የጅምላ ማፈናቀል እርምጃ በህገ-ወጥ ስደተኞች ላይ እንጂ ከዘረኝነት የመነጨ እንዳልሆነ ለማስረዳት ቢሞክርም፣ በመላው አፍሪካ የሚገኙ የደቡብ አፍሪካ የንግድ ተቋማትና የኪነጥበብ ባለሙያዎች ግን የከፋ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጫና ውስጥ ወድቀዋል። ይህ በአህጉሪቱ የተነሳው የህዝብ ተቃውሞ በስፖርቱ ዘርፍም ጭምር መንጸባረቅ የጀመረ ሲሆን፣ በ2026 የፊፋ የዓለም ዋንጫ ላይ የደቡብ አፍሪካ ብሔራዊ ቡድን (ባፋና ባፋና) በሜክሲኮ 2 ለ 0 ሲሸነፍ አብዛኞቹ የአፍሪካ የእግር ኳስ አፍቃሪዎች ከደቡብ አፍሪካ ይልቅ ለሜክሲኮ ድጋፋቸውን ሰጥተዋል። የቡድኑ አምበል ሮንዌን ዊሊያምስ በዚህ ድርጊት ማዘኑን ገልጾ፣ "አፍሪካውያን ሁልጊዜም በዓለም ዋንጫ አንዳቸው ሌላውን ይደግፉ ነበር፣ የእኛ ጉዳይ ለምን የተለየ እንደሆነ ሊገባኝ አልቻለም" ሲል በለቅሶ የታጀበ ቅሬታውን አሰምቷል። ይህ ክስተት በደቡብ አፍሪካና በሌሎች የአፍሪካ ሀገራት መካከል ያለው ዲፕሎማሲያዊና ማኅበራዊ ውጥረት ምን ያህል አሳሳቢ ደረጃ ላይ እንደደረሰ ማሳያ ሆኗል። @zena_maezen @zena_maezen

በፊሊፒንስ ደቡባዊ ክፍል 6.2 ማግኒቲውድ የሆነ ጠንካራ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከሰተ ሰኞ ሰኔ 8 ቀን 2018 ዓ.ም በደቡባዊ ፊሊፒንስ ዳቫኦ ኦሪየንታል ግዛት ውስጥ በሬክተር ስኬል 6.2 ማግኒቲውድ
በፊሊፒንስ ደቡባዊ ክፍል 6.2 ማግኒቲውድ የሆነ ጠንካራ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከሰተ ሰኞ ሰኔ 8 ቀን 2018 ዓ.ም በደቡባዊ ፊሊፒንስ ዳቫኦ ኦሪየንታል ግዛት ውስጥ በሬክተር ስኬል 6.2 ማግኒቲውድ የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቷል። እንደ አሜሪካ የጂኦሎጂካል ሰርቬይ (USGS) ዘገባ፥ የመሬት መንቀጥቀጡ ማዕከሉን ከፖንዳጉይታን ከተማ 67 ኪሎ ሜትር ርቆ በባሕር ውስጥ ያደረገ ሲሆን፣ እስካሁን የደረሰ የሰው ሕይወት መጥፋትም ሆነ የንብረት ውድመት ሪፖርት አልተደረገም። ባለፈው ሳምንት በሀገሪቱ ሚንዳናኦ የባሕር ዳርቻ ላይ ተከስቶ በነበረው ሌላ የ7.8 ማግኒቲውድ የመሬት መንቀጥቀጥ ቢያንስ 61 ሰዎች መሞታቸውና ከ1,040 በላይ መቁሰላቸው ይታወሳል። @zena_maezen @zena_maezen

በኮንጎ የኢቦላ ቫይረስ ስርጭት በከፍተኛ ሁኔታ ማገርሸቱ ተገለፀ ሰኞ ሰኔ 8 ቀን 2018 ዓ.ም በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ባለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ 72 አዳዲስ የኢቦላ ተጠቂዎች በመመዝገባቸው፣
በኮንጎ የኢቦላ ቫይረስ ስርጭት በከፍተኛ ሁኔታ ማገርሸቱ ተገለፀ ሰኞ ሰኔ 8 ቀን 2018 ዓ.ም በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ባለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ 72 አዳዲስ የኢቦላ ተጠቂዎች በመመዝገባቸው፣ ወረርሽኙ ከተቀሰቀሰበት ካለፈው ግንቦት 7 ቀን ጀምሮ አጠቃላይ የተጠቂዎች ቁጥር 782 ደርሷል። የበሽታው ማዕከል በሆነችው ኢቱሪ ግዛት እና በሰሜን ኪቩ ተጨማሪ የጤና ቀጠናዎች ቫይረሱ የተስፋፋ ሲሆን፣ በበሽታው የሞቱት ሰዎች ቁጥር ወደ 181 አድጎ ገዳይነት ምጣኔው 23.1 በመቶ ደርሷል። የአፍሪካ በሽታ መከላከያ እና መቆጣጠሪያ ማዕከል (Africa CDC) ወረርሽኙን ለመግታት የቴክኒክ ድጋፍ እያደረገ ቢሆንም፣ ምላሹን በፍጥነት ለማድረስ የ21.5 ሚሊዮን ዶላር የገንዘብ እጥረት እና የሕክምና ቁሳቁሶች እጥረት ዋነኛ ፈተና መሆናቸው ተገልጿል። @zena_maezen @zena_maezen

የኖርዌይ አልጋ ወራሽ የእንጀራ ልጅ በአስገድዶ በደፈራ ወንጀል የ4 ዓመት እስራት ተፈረደበት ሰኞ ሰኔ 8 ቀን 2018 ዓ.ም በኖርዌይ ኦስሎ የሚገኝ ፍርድ ቤት የአልጋ ወራሽ ልዑል ሐኮን የእንጀራ ል
የኖርዌይ አልጋ ወራሽ የእንጀራ ልጅ በአስገድዶ በደፈራ ወንጀል የ4 ዓመት እስራት ተፈረደበት ሰኞ ሰኔ 8 ቀን 2018 ዓ.ም በኖርዌይ ኦስሎ የሚገኝ ፍርድ ቤት የአልጋ ወራሽ ልዑል ሐኮን የእንጀራ ልጅ የሆነውን የ29 ዓመቱን ማርየስ ቦርግ ሆይቢን (Marius Borg Hoiby) በደፈራ፣ በቤት ውስጥ ጥቃት እና በዕፅ ወንጀሎች ጥፋተኛ በማድረግ የ4 ዓመት እስራት ፈርዶበታል። ተከሳሹ ከደፈራ ወንጀሎቹ አንደኛውን የፈጸመው በአልጋ ወራሹ ይፋዊ መኖሪያ ቤት ምድር ቤት ውስጥ እንደነበር የተገለጸ ሲሆን፣ በጠበቃው በኩል በውሳኔው ላይ ይግባኝ እንደሚጠይቅ አስታውቋል። ይህ በሀገሪቱ ንጉሣዊ ቤተሰብ ስም ላይ ጥላ ያሳረፈው የፍርድ ሂደት ጥብቅ ክትትል የተደረገበት ሲሆን፣ አልጋ ወራሹ ልዑል ሐኮን ማርየስ እንደማንኛውም ዜጋ በሕግ ፊት እኩል ተጠያቂ መሆኑን በመግለጽ ከጉዳዩ ራሳቸውን አርቀዋል። @zena_maezen @zena_maezen

ብሪታንያ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ለሆኑ ታዳጊዎች የሶሻል ሚዲያ አጠቃቀምን ልታግድ ነው ሰኞ ሰኔ 8 ቀን 2018 ዓ.ም የብሪታንያ ጠቅላይ ሚኒስትር ኬር ስታርመር ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች
ብሪታንያ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ለሆኑ ታዳጊዎች የሶሻል ሚዲያ አጠቃቀምን ልታግድ ነው ሰኞ ሰኔ 8 ቀን 2018 ዓ.ም የብሪታንያ ጠቅላይ ሚኒስትር ኬር ስታርመር ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ታዳጊዎች እንደ ቲክቶክ፣ ስናፕቻት እና ኢንስታግራም ያሉ ማኅበራዊ ሚዲያዎችን እንዳይጠቀሙ ሙሉ በሙሉ የሚያግድ ሕግ ይፋ አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ መተግበሪያዎቹ ታዳጊዎችን ለሱሰኝነት እና ለአደገኛ ይዘቶች እያጋለጡ መሆኑን ጠቅሰው፣ እገዳው ታዳጊዎች ከማያውቋቸው እንግዳ ሰዎች ጋር እንዲገናኙ የሚያስችሉ የቪዲዮ ጌምና የላይቭ ስትሪሚንግ አገልግሎቶችንም እንደሚያካትት አስታውቀዋል። ይህ ሕግ በሚቀጥለው ዓመት ተግባራዊ ይደረጋል ተብሎ የሚጠቅስ ሲሆን፣ የዩቲዩብ (YouTube) ቃል አቀባይ በበኩሉ እንዲህ ዓይነቱ አጠቃላይ እገዳ ታዳጊዎችን ደህንነታቸው ወደማይጠበቁ አማራጮች ሊገፋፋቸው ይችላል ሲል አስጠንቅቋል። @zena_maezen @zena_maezen