uk
Feedback
ዜና ማዕዘን - Breaking

ዜና ማዕዘን - Breaking

Відкрити в Telegram

እንኳን ወደ ዜና ማዕዘን - Breaking በደህና መጡ በቻናላችን 📌 ፈጣን ሀገራዊ #መረጃዎች 📺 📌 #ዓለም ዓቀፍ መረጃዎች 📢 📌 አዝናኝ እና አስተማሪ መረጃዎች 🔔 📌 ወቅታዊ ጉዳዮች ሁሉንም በአንድ ታገኛላችሁ 📣 #zena_maezen ለሀሳብ አስተያየት (ads) @zena_maezen_bot

Показати більше

📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу ዜና ማዕዘን - Breaking

Канал ዜና ማዕዘን - Breaking (@zena_maezen) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 68 454 підписників, посідаючи 934 місце в категорії Музика та 449 місце у регіоні Ефіопія.

📊 Показники аудиторії та динаміка

З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 68 454 підписників.

За останніми даними від 16 червня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на -1 983, а за останні 24 години на -60, загальне охоплення залишається високим.

  • Статус верифікації: Не верифікований
  • Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 3.43%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає 2.87% реакцій від загальної кількості підписників.
  • Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 2 353 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 1 969 переглядів.
  • Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 14.

📝 Опис та контентна політика

Автор описує ресурс як майданчик для висловлення суб'єктивної думки:
እንኳን ወደ ዜና ማዕዘን - Breaking በደህና መጡ በቻናላችን 📌 ፈጣን ሀገራዊ #መረጃዎች 📺 📌 #ዓለም ዓቀፍ መረጃዎች 📢 📌 አዝናኝ እና አስተማሪ መረጃዎች 🔔 📌 ወቅታዊ ጉዳዮች ሁሉንም በአንድ ታገኛላችሁ 📣 #zena_maezen ለሀሳብ አስተያየት (ads) @zena_maezen_bot

Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 17 червня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Музика.

68 454
Підписники
-6024 години
-4527 днів
-1 98330 день
Архів дописів
በትግራይ ሌላ ጦርነት እንዳይቀሰቀስ የፌደራል መንግስት ጣልቃ እንዲገባ ተጠየቀ የአረና ትግራይ ለሉዓላዊነትና ለዴሞክራሲ ፓርቲ መሥራችና ከፍተኛ አመራር አቶ ገብሩ አሥራት፣ ሕወሓት "ፅምዶ" የተባለ
በትግራይ ሌላ ጦርነት እንዳይቀሰቀስ የፌደራል መንግስት ጣልቃ እንዲገባ ተጠየቀ የአረና ትግራይ ለሉዓላዊነትና ለዴሞክራሲ ፓርቲ መሥራችና ከፍተኛ አመራር አቶ ገብሩ አሥራት፣ ሕወሓት "ፅምዶ" የተባለ ጣምራ ቡድን ፈጥሮ ለዳግም ጦርነት እየተዘጋጀና በሕዝቡ ላይ አፋኝ ሕጎችን እየጫነ ነው ሲሉ ከሰሱ። ጦርነት ናፋቂ ባሉት በዚህ ቡድን ምክንያት በክልሉ እያንዣበበ ያለውን የጦርነት ሥጋት ለመቀልበስ፣ የፌደራል መንግሥት በክልሉ ከሚገኙ ተቃዋሚ ፓርቲዎች፣ ከጊዜያዊ አስተዳደሩና ታጣቂ ኃይሎች ጋር ሁሉን አካታች የሆነ ሰላማዊ ድርድር በአስቸኳይ ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። ሕወሓት በኃይል ሥልጣን መቆጣጠሩ ቅቡልነት የሌለው ቢሆንም፣ ለሕዝቡ ሰላም ሲባል ውይይት አማራጭ የሌለው መፍትሔ መሆኑን አቶ ገብሩ ከሐራምቤ ሬዲዮ ጋር ባደረጉት ቆይታ ገልጸዋል። በተጨማሪም የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት በፌደራል መንግሥቱ በኩል ሙሉ በሙሉ አለመተግበሩ አሁን ላለው ውጥረት የራሱን አስተዋጽኦ ማድረጉን ፖለቲከኛው ጠቁመዋል። ቀደም ሲል በክልሉ ሰላም እንዲሰፍን ሲሠሩ የነበሩት የአፍሪካ ኅብረት፣ አሜሪካና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ያቋረጡትን የዲፕሎማሲ ሥራ በመቀጠል በሕወሓት ላይ ጠንካራ ጫና እንዲያሳድሩ ጥሪ አቅርበዋል። ሕወኃት ለግጭት የሚጋብዝ እንቅስቃሴ እያደረገ ስለመሆኑ መረጃዎች እየወጡ ቢሆንም፣ የፌደራል መንግሥት እስካሁን ድረስ በዚህ ጉዳይ ላይ የሰጠው ይፋዊ ማብራሪያ የለም። @zena_maezen @zena_maezen

ጠቅላይ ሚኒስትሩ እና ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተወዳደሩበት ምርጫ ክልሎች አሸነፉ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ለፓርላማ በተወዳደሩበት ምርጫ ክልል ማሸነፋቸውን ምርጫ ቦርድ ይፋ አድርጓል። ጠቅላ
ጠቅላይ ሚኒስትሩ እና ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተወዳደሩበት ምርጫ ክልሎች አሸነፉ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ለፓርላማ በተወዳደሩበት ምርጫ ክልል ማሸነፋቸውን ምርጫ ቦርድ ይፋ አድርጓል። ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በኦሮሚያ ክልል ለፓርላማ በተወዳደሩበት ጎማ ሁለት ምርጫ ክልል ማሸነፋቸውን ዛሬ ምሽት ምርጫ ቦርድ ይፋ አድርጓል። በምርጫ ክልሉ ብልጽግና ፓርቲ፣የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ፓርቲ ኢዜማ እና ነጻነት እና እኩልነት ፓርቲ ተወዳድረው ነበር። በክልሉ ከፍተኛ ድምጽ ያገኘው በልጽግና ነው ። በተጨማሪም በአማራ ክልል ባህርዳር ከተማ ምርጫ ክልል ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተመስገን ጥሩነህ አሸንፈዋል ብሏል ምርጫ ቦርድ።

የአውሮጳ የሕግና ፍትህ ማዕከል ስለ አርሲው የንጹሃን ጭፍጨፋ ለተመድ ያቀረበው ጥሪ የአውሮጳ የሕግና የፍትህ ማዕከል በኢትዮጵያ በተለይም በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን እየተባባሰ የመጣውንና በትንሹ የ3
የአውሮጳ የሕግና ፍትህ ማዕከል ስለ አርሲው የንጹሃን ጭፍጨፋ ለተመድ ያቀረበው ጥሪ የአውሮጳ የሕግና የፍትህ ማዕከል በኢትዮጵያ በተለይም በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን እየተባባሰ የመጣውንና በትንሹ የ37 ኦርቶዶክስ ክርስቲያኖችን ሕይወት የቀጠፈውን ዘግናኝ ግድያ አስመልክቶ ለተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የዘር ፍጅት መከላከል ቢሮ አስቸኳይ ጥሪ አቀረበ። ማዕከሉ ባወጣው መግለጫ መሠረት፣ በምርጫ ወቅት ጭምር ንጹሃን ዜጎች ሲገደሉና በሺዎች የሚቆጠሩ ሲፈናቀሉ የነበረ ሲሆን፣ ታጣቂዎች የቅዱስ ገብርኤልና የመድኃኔዓለም አብያተ ክርስቲያናትን መዝረፋቸውንና ማቃጠላቸውን በማስረጃ አስደግፎ አጋልጧል። ይህ ጥቃት «በመላው ኢትዮጵያ በአማራ ሕዝብ ላይ እየተደረገ ካለው ግፍና ጭካኔ» ጋር ተዳምሮ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን ማዕከሉ ገልጿል። ይህ በሲቪል ክርስቲያኖችና በአማራ ተወላጆች ላይ ያነጣጠረው ተከታታይነት ያለው ስልታዊ ጥቃት፣ በተመድ የዘር ፍጅት መከላከል ድንጋጌና በዓለም አቀፍ የጦር ወንጀሎች መዳኛ ፍርድ ቤት (የሮም ደንቦች) አኳያ ብርቱ የሕግ ጥያቄዎችን የሚያስነሳ መሆኑን ማዕከሉ በጥብቅ አሳስቧል። በጥቃቱ ወቅት የሟቾች አስከሬን ርቆ በሚገኝ ስፍራ መገኘቱንና የኦርቶዶክስ ክርስቲያን ቤተሰቦች ተለይተው ቤቶቻቸው በእሳት መቃጠላቸውን የጠቀሰው ማዕከሉ፣ የተፈጸሙትን ዘግናኝ ድርጊቶች በዝርዝርና በማስረጃ በማስደገፍ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ለእነዚህ ተጠቂ ማኅበረሰቦች ጥበቃ እንዲያደርግና አስቸኳይ እገዛ እንዲያበረክት ጠይቋል። @zena_maezen @zena_maezen

ኢራን ከ‘ሚሳይል ማስወንጨፊያ’ ወደ ኤኮኖሚ እድገት መሸጋገር አለባት አለ :- ጋሊባፍ የኢራን ፓርላማ አፈ-ጉባኤ መሀመድ ባgher ጋሊባፍ ረቡዕ ዕለት በሰጡት መግለጫ፥ እስላማዊቷ ሪፐብሊክ ከግጭትና
ኢራን ከ‘ሚሳይል ማስወንጨፊያ’ ወደ ኤኮኖሚ እድገት መሸጋገር አለባት አለ :- ጋሊባፍ የኢራን ፓርላማ አፈ-ጉባኤ መሀመድ ባgher ጋሊባፍ ረቡዕ ዕለት በሰጡት መግለጫ፥ እስላማዊቷ ሪፐብሊክ ከግጭትና ፍጥጫ ባለፈ ትኩረቷን በኤኮኖሚ ልማት ላይ ማድረግ እንዳለባት አሳስበዋል። ከቻይና ጋር በተያያዙ የኤኮኖሚ ፖሊሲዎች ላይ ከኢራን የንግድ ምክር ቤት ጋር በተደረገ ስብሰባ ላይ ጋሊባፍ ሲናገሩ፡ “የመከላከያ ምሽጉን ‘ሚሳይል ከሚያስወነጭፉት ወጣቶች’ ተረክበን፥ ህዝባችንን ከኤኮኖሚ ጫና ማውጣትና ሀገሪቱን መገንባት አለብን” ብለዋል። ከአሜሪካ ጋር በተደረገው ድርድር የቴህራንን የልዑካን ቡድን የመሩት ጋሊባፍ፥ ቻይና ለኢራን ልዩ የንግድ አጋር መሆኗን ገልጸው፥ ቤጂንግ ቴህራንን “በምሉዕ ትርጉሙ እውነተኛ አጋር” መሆኗን ማመን አለባት ሲሉ አፅንዖት ሰጥተዋል። አፈ-ጉባኤው አክለውም፡ በፋርስ ባህረ ሰላጤ ዳርቻ ካሉ ሀገራት ጋር የሚመሰረት ማንኛውም የጋራ ስብስብ “በእርግጠኝነት” በቻይና እና በኢራን እስላማዊ ሪፐብሊክ ላይ ማዕከሉን ያደረገ እንደሚሆን አስገንዝበዋል። ይህ ንግግራቸው ኢራን ለዓመታት ከተከተለችውና በወታደራዊ ጡንቻ ላይ ካተኮረው አካሄድ ወጥታ፥ ይበልጥ ወደ ቀጣናዊ የኤኮኖሚ ትስስርና ዲፕሎማሲያዊ ሽርክና ለመዞር የምታደርገውን ስትራቴጂካዊ የፖሊሲ ለውጥ አመላካች ሊሆን እንደሚችል በብዙዎች ዘንድ ግምትን ጭሯል። @zena_maezen @zena_maezen

ዩክሬይን ቤላሩስ ላይ በፈጸመችው ጥቃት ስምንት ህፃናት ህይወታቸው አለፈ የዩክሬን የድሮን ጥቃት የእግር ኳስ አካዳሚ ሰልጣኝ ህፃናትን የጫነ አውቶብስ ላይ ጉዳት አድርሷል። ከጥቃቱ የተፈጸመው አውቶቡ
+1
ዩክሬይን ቤላሩስ ላይ በፈጸመችው ጥቃት ስምንት ህፃናት ህይወታቸው አለፈ የዩክሬን የድሮን ጥቃት የእግር ኳስ አካዳሚ ሰልጣኝ ህፃናትን የጫነ አውቶብስ ላይ ጉዳት አድርሷል። ከጥቃቱ የተፈጸመው አውቶቡሱ ከጎሜል ወደ ገለንድዝክ ከተማ እየተጓዘ በነበረበት ወቅት መሆኑን የብርያንስክ ክልል አስተዳዳሪ ዮጎር ኮቫልችክ ተናግረዋል። የተጎጂዎቹ ቁጥጥር በትክክል ማወቅ አለመቻሉን አብራርተዋል። 48 ሰዎችን አሳፍሮ በነበረው አውቶብስ ላይ ዩክሬን "A240" የሰው አልባ አውሮፕላን በመጠቀም ጥቃት ማድረሷ ተገልጿል። @zena_maezen @zena_maezen

የኢትዮጵያ ስም የጣማቸው ትራምፕ አሁንም ስለግድቡ እየለፈፉ ናቸው በህዳሴ ግድቡ ዙሪያ አወዛጋቢ ንግግር የሚያደርጉት የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ፣ በድጋሚ "የግድቡን ጉዳይ አሁንም እናየዋለ
የኢትዮጵያ ስም የጣማቸው ትራምፕ አሁንም ስለግድቡ እየለፈፉ ናቸው በህዳሴ ግድቡ ዙሪያ አወዛጋቢ ንግግር የሚያደርጉት የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ፣ በድጋሚ "የግድቡን ጉዳይ አሁንም እናየዋለን፣ ለመፍታትም ጥረት እናደርጋለን" ሲሉ ተደምጠዋል። በህዳሴ ግድብ ዙሪያ "ድርድር ለማስጀመር" ሁሉ ማቀዳቸውን እየተናገሩ ናቸው። በፈረንሳይ የቡድን 7 ጉባዔ ላይ ከግብጹ ፕሬዝዳንት አብዱልፈታህ አል-ሲሲ ጋር የተገናኙት ትራምፕ፤ የዓባይ ግድብ "ውዝግብንም በድጋሚ ይጀመራል" ሲሉ ተደምጠዋል። ከሁለትዮሽ ውይይት በኋላ “ከግብጹ ፕሬዝዳንት፣ ከጓደኛዬ ጋር በመሆኔ ታላቅ ደስታ ይሰማኛል። እሳቸው በመላው ዓለም የተከበሩ ናቸው... ግንኙነታችንም በግል ደረጃ ለረጅም ጊዜ በጣም ጠንካራ ሆኖ ቆይቷል" ሲሉ ተደምጠዋል። ከአልሲሲ ጋር ጥሩ ወዳጅነት እንዳላቸው የገለፁት ትራምፕ፣ "ህዳሴ ግድብ በኢትዮጵያ ነው የተገነባው" በማለት ገልጸዋል። "ግዙፍ ግድብ" ሲሉ በጠሩት የህዳሴ ግድብ ላይ "መፍትሔ የሚያመጣ ውይይት እናስጀምራለን" ያሉት ፕሬዝዳንቱ “የግድቡን ጉዳይ አሁንም እናየዋለን፣ ለመፍታትም ጥረት እናደርጋለን" ሲሉም ገልጸዋል። "በኢትዮጵያ የተገነባው ግድብ በግብፅ ላይ ከፍተኛ ችግር እያስከተለ ነው" በማለትም የተለመደ ግጭት ቀስቃሽ ንግግር አድርገዋል። ትራምፕ ለአል-ሲሲ ሲናገሩ "እውነቱን ማወቅ ከፈለጉ፣ በኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ በጣም ኢ-ፍትሃዊ በሆነ መንገድ ነው የተያዛችሁት ብዬ አስባለሁ" ሲሉ አነሳስተዋቸዋል። 

በመርካቶ 41 የላስቲክ ከረጢት የጅምላ መደብሮች ታሸጉ የአዲስ አበባ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ከደንብ ማስከበርና ከፖሊስ ጋር በመቀናጀት፣ በመርካቶ ሲኒማ ራስ አካባቢ ወደ ተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች
በመርካቶ 41 የላስቲክ ከረጢት የጅምላ መደብሮች ታሸጉ የአዲስ አበባ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ከደንብ ማስከበርና ከፖሊስ ጋር በመቀናጀት፣ በመርካቶ ሲኒማ ራስ አካባቢ ወደ ተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የፕላስቲክ ከረጢት የሚያሰራጩ 41 የጅምላ አከፋፋይ ድርጅቶችን አሸገ። ይህ ጠንካራ እርምጃ የተወሰደው ለአካባቢ ብክለት መንስኤ የሆኑ የፕላስቲክ ከረጢቶችን አጠቃቀም ለመገደብ የወጣውን የአዋጅ ቁጥር 1383/2017 መነሻ በማድረግ ሲሆን፣ ድርጅቶቹ ክልከላ የተጣለባቸውን የላስቲክ ምርቶች በስፋት ሲያከፋፍሉ እጅ ከፍንጅ በመገኘታቸው ነው ተብሏል። ባለስልጣኑ ይሄንን አስተዳደራዊ እርምጃ ከመውሰድ ጎን ለጎን፣ ከ100 በላይ ለሚሆኑ የአካባቢው አገልግሎት ሰጪ ድርጅቶችና ተቋማት ስለ አዋጁ ዓላማና ስለ ፕላስቲክ ጎጂነት ሰፊ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራ ሰርቷል። ህብረተሰቡና ነጋዴዎች ለአካባቢ ተስማሚ የሆኑ አማራጭ የመገበያያ ቁሶችን እንዲጠቀሙ ጥሪ የቀረበ ሲሆን፣ በቀጣይም በአምራቾች፣ በጅምላና ችርቻሮ አከፋፋዮች እንዲሁም ህግ ጥሰው በሚገኙ ግለሰቦች ላይ ደረጃ በደረጃ ጥብቅ የህግ ማስከበር እርምጃው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ባለስልጣኑ በጽኑ አሳስቧል። @zena_maezen @zena_maezen

የፑቲን ቀንደኛ ተቺ የነበረው ሩሲያዊ አርቲስት ተገደለ የሩሲያውን ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲንን በስዕሎቹ ክፉኛ በመተቸት የሚታወቀውና በስደት በፖላንድ ይኖር የነበረው ታዋቂው ሩሲያዊ አርቲስት ሰምዮን
የፑቲን ቀንደኛ ተቺ የነበረው ሩሲያዊ አርቲስት ተገደለ የሩሲያውን ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲንን በስዕሎቹ ክፉኛ በመተቸት የሚታወቀውና በስደት በፖላንድ ይኖር የነበረው ታዋቂው ሩሲያዊ አርቲስት ሰምዮን ስክሬፔትስኪ (በእውነተኛ ስሙ ሮበርት ኩዞቭኮቭ) በፖላንድ ሉብሊን ከተማ ውስጥ በጥይት ተመትቶ መገደሉን ባለስልጣናት አስታውቀዋል። ሰኞ ዕለት በተፈጸመው በዚህ ጥቃት አጥቂው በአርቲስቱ ላይ ሶስት ጊዜ የተኮሰበት ሲሆን፥ መሬት ላይ ከወደቀም በኋላ በቅርብ ርቀት ሁለት ተጨማሪ ጥይቶችን በመተኮስ ህይወቱ እንዲያልፍ አድርጓል። ከተገደለው አርቲስት ሞት ጋር በተያያዘ ሁለት የቤላሩስ ዜጎች በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተደረገባቸው ይገኛል። ይህ አሰቃቂ ግድያ ከመፈጸሙ ከሶስት ቀናት በፊት፥ ስክሬፔትስኪ በበርሊን በሚገኘው የሩሲያ ኤምባሲ ፊት ለፊት በመገኘት ከፍተኛ የተቃውሞ ሰልፍ አድርጎ ነበር። በወቅቱ በሩሲያ ብሔራዊ ቀን ላይ ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲንንና የቀድሞውን የሶቪየት መሪ ጆሴፍ ስታሊንን በአንድ ላይ የሚያሳይና እንደ ሃይማኖታዊ ስዕል (አይኮን) ተደርጎ የተሳለ አነጋጋሪ የካርቱን ስዕል በመያዝ ተቃውሞውን አሰምቷል። ይህ ደፋር አቋሙና ጥበባዊ ተቃውሞው በክሬምሊን ደጋፊዎች ዘንድ ከፍተኛ ቁጣን ቀስቅሶ እንደነበር ይነገራል። በሩሲያ አልታይ ሪፐብሊክ ውስጥ የተወለደው ሰምዮን ስክሬፔትስኪ፥ በፖለቲካዊ የካርቱን ስዕሎቹ ፑቲንን ብቻ ሳይሆን የቤላሩሱን መሪ አሌክሳንደር ሉካሼንኮን፣ የቼቺንያውን መሪ ራምዛን ካዲሮቭን እና እንደ አሌክሴ ናቫልኒ ያሉ የሩሲያ ተቃዋሚ ፖለቲከኞችን ጭምር ይተች ነበር። በትውልድ ሀገሩ ይደርስበት ከነበረው እንግልት ለመሸሽ ከ2021 ጀምሮ በፖላንድ በስደት ይኖር የነበረ ቢሆንም፥ በመጨረሻ ግን ህይወቱ በዚህ መልኩ በሚያሳዝን ሁኔታ ተቀጥፏል። @zena_maezen

በሊባኖስ የተፈጸመውን ጥቃት ተከትሎ በትራምፕ እና በኔታንያሁ መካከል አለመግባባት መንገሡ ተሰምቷል የእስራኤል ጦር በደቡብ ሊባኖስ አራት ሰዎችን መግደሉን ተከትሎ፣ የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ዶና
በሊባኖስ የተፈጸመውን ጥቃት ተከትሎ በትራምፕ እና በኔታንያሁ መካከል አለመግባባት መንገሡ ተሰምቷል   የእስራኤል ጦር በደቡብ ሊባኖስ አራት ሰዎችን መግደሉን ተከትሎ፣ የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ ላይ ጠንከር ያለ ትችት ሰንዝረዋል። ፕሬዚዳንት ትራምፕ ኔታንያሁ በሊባኖስ ጉዳይ ላይ "ኃላፊነት ሊሰማቸው ይገባል" ብለዋል። ድርጊቱን ተከትሎም የአሜሪካ ኮንግረስ ለእስራኤል ባለው ድጋፍ ዙሪያ አዲስ መከፋፈሎች መታየታቸው ተገልጿል። በሌላ በኩል ኢራን በበኩሏ፤ በቴህራን እና በዋሽንግተን መካከል የመግባቢያ ስምምነት ከተደረገ ወዲህ እስራኤል በሊባኖስ የተደረገውን የተኩስ አቁም ስምምነት 84 ጊዜ ጥሳለች ስትል ከሳለች። ጥቃቶቹ የሚቀጥሉ ከሆነም "ጠንካራ እርምጃ" እንደምትወስድ አስጠንቅቃለች ሲል አልጀዚራ ዘግቧል። በክልሉ ባለው ሌላ ውጥረት፣ የኢራን ድፍድፍ ዘይት የጫነች ሦስተኛ መርከብ በአሜሪካ ባህር ኃይል የተጣለውን የእገዳ መስመር በመጣስ በኦማን ባህረ ሰላጤ ላይ ተጉዛለች። የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራግቺ ከአሜሪካ ጋር የሚደረግ ማንኛውም ስምምነት፤ የታገዱ የኢራን ንብረቶች እንዲለቀቁ፣ የኢኮኖሚ ማዕቀቦች እንዲነሱ እና እስራኤል ከሊባኖስ ሙሉ በሙሉ እንድትወጣ የሚያስገድድ መሆን እንዳለበት ገልጸዋል።   @zena_maezen @zena_maezen

ቻይና ለኢራን እና ለሊባኖስ ሰብአዊ እርዳታ ለመላክ እየተዘጋጀች መሆኗን አስታወቀች። @zena_maezen @zena_maezen
+2
ቻይና ለኢራን እና ለሊባኖስ ሰብአዊ እርዳታ ለመላክ እየተዘጋጀች መሆኗን አስታወቀች። @zena_maezen @zena_maezen

ወላይታ ዞን በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ4 ሰዎች ህይወት ማለፉን ፖሊስ አስታወቀ ከወላይታ ሶዶ ወደ ገሳ ከተማ 50 ሰዎችን አሳፍሮ ይጓዝ የነበረ የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ “ዛሮ ቁልቁለት” ኤልፋ በ
ወላይታ ዞን በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ4 ሰዎች ህይወት ማለፉን ፖሊስ አስታወቀ ከወላይታ ሶዶ ወደ ገሳ ከተማ 50 ሰዎችን አሳፍሮ ይጓዝ የነበረ የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ “ዛሮ ቁልቁለት” ኤልፋ በተባለ አስቸጋሪ መንገድ ላይ ተገልብጧል። በአደጋው የ4 ሰዎች ህይወት ወዲያውኑ ያለፈ ሲሆን፣ በ22 ሰዎች ላይ ከባድ እና በ24 ሰዎች ላይ ቀላል የአካል ጉዳት ደርሷል። የደቡብ ኢትዮጵያ ፖሊስ ኮሚሽን እንደገለፀው፣ ተጎጂዎች ወደ ህክምና ተቋማት ተወስደዋል። ይሁን እንጂ በደረሰው የጉዳት መጠን ምክንያት የሟቾች ቁጥር ሊጨምር እንደሚችል ተገልፇል። የአካባቢው አስቸጋሪ መልክዓ ምድር ለክስተቱ መንስኤ ሳይሆን እንዳልቀረ የተጠቆመ ሲሆን፣ ፖሊስ ስለ አደጋው ዝርዝር ምርመራ እያደረገ ይገኛል። @zena_maezen @zena_maezen

ኢራን በሊባኖስ ላይ የሚሰነዘረው የእስራኤል ጥቃት ከአሜሪካ ጋር የተደረሰውን ስምምነት አደጋ ላይ እየጣለው ነው አለች ኢራን በእስራኤል የሊባኖስ ጥቃቶች ምክንያት “ከባድ ምላሽ” እንደምትሰጥ ያስጠነ
ኢራን በሊባኖስ ላይ የሚሰነዘረው የእስራኤል ጥቃት ከአሜሪካ ጋር የተደረሰውን ስምምነት አደጋ ላይ እየጣለው ነው አለች ኢራን በእስራኤል የሊባኖስ ጥቃቶች ምክንያት “ከባድ ምላሽ” እንደምትሰጥ ያስጠነቀቀች ሲሆን ይህ ጥቃት ከአሜሪካ ጋር የተደረሰውን ስምምነት የሚፈትንና በዶናልድ ትራምፕ እና ቤንጃሚን ኔታንያሁ መካከል ያለውን ግንኙነት የሚያሻክር ሆኗል። አራት ሰዎችን ለህልፈት የዳረገውን የእስራኤል ጥቃት ተከትሎ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጠቅላይ ሚኒስትር ኔታንያሁ “የበለጠ ኃላፊነት እንዲሰማቸው” በይፋ አሳስበዋል። የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራቅቺ ከአሜሪካ ጋር የሚደረገው የመጨረሻ ስምምነት የማዕቀብ መነሳትን፣ የታገዱ የኢራን ንብረቶች መልቀቅን እና የእስራኤል ጦር ከሊባኖስ መውጣትን ማካተት አለበት ብለዋል። በሌላ በኩል ሦስተኛው የኢራን የነዳጅ ጫኝ መርከብ የአሜሪካን የባህር ኃይል እገዳ አልፋ መውጣቷ ተገልጿል። የአሜሪካው ምክትል ፕሬዝዳንት ጄዲ ቫንስ ስምምነቱ “ቀላል” መሆኑን ጠቅሰው ኢራን የኑክሌር መሣሪያ ካላበለጸገች እና ሽብርተኝነትን በገንዘብ መርዳት ካቆመች “እውነተኛ ጥቅሞችን” ልታገኝ እንደምትችል ተናግረዋል። በእስራኤል በኩል ደግሞ በትራምፕ እና ኔታንያሁ መካከል ያለውን አለመግባባት ለመቀነስና የውስጥ ድጋፍን ለማጠናከር ሲባል በሄብሮን ከተማ ላይ የሚደረገው የመሬት ወረራ እና የግዛት ማካተት እንቅስቃሴ መባባሱ ተዘግቧል። @zena_maezen @zena_maezen

ሶማሊላንድ በእስራኤል ኤምባሲ ከፈተች ከሶማሊያ የተነጠለችው ሶማሊላንድ በእስራኤል የመጀመሪያዋን እውቅና ካገኘች ከስድስት ወር በኋላ እየሩሳሌም ላይ ኤምባሲዋን የከፈተችው። የሥራ ጉብኝት እያደረጉ ባ
ሶማሊላንድ በእስራኤል ኤምባሲ ከፈተች ከሶማሊያ የተነጠለችው ሶማሊላንድ በእስራኤል የመጀመሪያዋን እውቅና ካገኘች ከስድስት ወር በኋላ እየሩሳሌም ላይ ኤምባሲዋን የከፈተችው። የሥራ ጉብኝት እያደረጉ ባሉት የአገሪቱ ፕሬዝዳንት አብዲርሀማን መሐመድ አብዱላሂ በምዕራብ እየሩሳሌም ተመርቆ ተከፍቷል። ከፕሬዝዳንቱ ጋር የተነጋገሩት ጠቅላይ ሚኒስትር ቤኒያሚን ኔታኒያሁ "በሕዝቦቻችን መካከል ጥልቅ መንፈሳዊ ግንኙነት" አለ ብለዋል። ይሁን እንጅ ሶማሊላንድን የግዛቷ አካል አድርጋ የምትመለከታት ሞቃዲሾ "በሰሜን ሶማሊያ ከተገንጣይ አስተዳደር ጋር የሚደረግ ግንኙነት ሉዓላዊነቴን እንደመጣስ ይታያል" ብላለች። ባለፈው ታኅሳስ ላይ እስራኤል ለሶማሊላንድ እውቅና መስጠቷ አወዛጋቢ ነበር። ቻይና፣ ቱርክ፣ ሳዑዲ አረቢያ እና የአፍሪካ ህብረትን ጨምሮ በርካታ አገራት እና ድርጅቶች እውቅናውን ተችተዋል። ይሁን እንጂ ከዚህ በኋላ እስራኤል እና ሶማሊላንድ ግንኙነታቸውን እያጠናከሩ ነው። በጎርጎሮሳዊያኑ አዲስ ዓመት ጅማሮ አካባቢ የእስራኤል ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ሳር በሶማሊላንድ ዋና ከተማ ሀርጌሳ ይፋዊ ጉብኝት አድርገዋል። @zena_maezen @zena_maezen

ትራምፕ፤ አሜሪካ በኢራን ላይ የመዋዕለ ንዋይ (ኢንቨስትመንት) የማፍሰስ ግዴታ የለባትም አሉ ማክሰኞ ሰኔ 9 ቀን 2018 ዓ.ም (ጁን 16 ቀን 2026) ኢንሳይደር ፔፐር የፈረንሳይ የዜና ወኪልን (
ትራምፕ፤ አሜሪካ በኢራን ላይ የመዋዕለ ንዋይ (ኢንቨስትመንት) የማፍሰስ ግዴታ የለባትም አሉ ማክሰኞ ሰኔ 9 ቀን 2018 ዓ.ም (ጁን 16 ቀን 2026) ኢንሳይደር ፔፐር የፈረንሳይ የዜና ወኪልን (AFP) ዋቢ አድርጎ እንደዘገበው፤ የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በመካከለኛው ምስራቅ ያለውን ጦርነት ለማቆም ከኢራን ጋር ስምምነት ቢደረግም፣ ዩናይትድ ስቴትስ በኢራን ውስጥ የመዋዕለ ንዋይ የማፍሰስ ምንም ዓይነት "ግዴታ የለባትም" ሲሉ ገልጸዋል። በፈረንሳይ እየተካሄደ ባለው የቡድን 7 (G7) ጉባኤ ላይ ከቀጠሩ አሚር ጋር ከተወያዩ በኋላ መግለጫ የሰጡት ትራምፕ፤ "በኢራን ውስጥ ምንም ዓይነት ገንዘብ አናፈስስም" ብለዋል። የዚህ ስምምነት ዋና ትኩረት ኢራን የኑክሌር መሣሪያ እንዳታገኝ ማድረግ መሆኑን የገለጹት ፕሬዚዳንቱ፣ ኢራን ይህንን ለማድረግ ከሞከረች ግን "ታላቅ መቅሰፍት" (all hell) በሀገሪቱ ላይ እንደሚዘንብባት አስጠንቅቀዋል። @zena_maezen @zena_maezen

በእስራኤል የአሜሪካ አምባሳደር ማይክ ሁካቢ አሜሪካ “ያለ እስራኤል” ልትኖር እንደማትችል ገለጹ። @zena_maezen @zena_maezen
+1
በእስራኤል የአሜሪካ አምባሳደር ማይክ ሁካቢ አሜሪካ “ያለ እስራኤል” ልትኖር እንደማትችል ገለጹ። @zena_maezen @zena_maezen

የአሜሪካና ኢራን ስምምነት ቢታወጅም የእስራኤል ጥቃት በሊባኖስ የሰዎችን ሕይወት ቀጠፈ ማክሰኞ ሰኔ 9 ቀን 2018 ዓ.ም አሜሪካና ኢራን ጦርነቱን በሁሉም ግንባሮች ለማቆም መግባባት ላይ መድረሳቸው ቢገለጽም፣ እስራኤል በደቡባዊ ሊባኖስ ናባቲህ ግዛት በፈጸመችው የድሮን ጥቃት ቢያንስ አራት ሰዎች ተገድለዋል። የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራቅቺ የእስራኤል ጦር ከያዛቸው የሊባኖስ ግዛቶች ሳይወጣ ጦርነቱ ፍጻሜ አያገኝም ሲሉ፣ የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ግን በደቡባዊ ሊባኖስ ወታደራዊ ይዞታቸውን እንደሚቀጥሉ አስታውቀዋል። ከባለፈው መጋቢት ወር ጀምሮ በእስራኤል ጥቃቶች በሊባኖስ የሟቾች ቁጥር 3,826 ደርሷል። @zena_maezen @zena_maezen

የመጨረሻው የኢራን ሻህ ልጅ ሬዛ ፓህላቪ በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የሚደረገው አዲስ ስምምነት 'አውዳሚ ስህተት' ሲሉ አጥብቀው ተቃወሙ ፓህላቪ ዋሽንግተን ከቴህራን ጋር ያደረገችው ስምምነት የምዕ
የመጨረሻው የኢራን ሻህ ልጅ ሬዛ ፓህላቪ በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የሚደረገው አዲስ ስምምነት 'አውዳሚ ስህተት' ሲሉ አጥብቀው ተቃወሙ ፓህላቪ ዋሽንግተን ከቴህራን ጋር ያደረገችው ስምምነት የምዕራባውያን የሞራል እና የፖለቲካ ውድቀት መሆኑን ገልጸዋል። ይህ እርምጃ በኢራን አምባገነን መንግስት የሚሰቃዩትን የኢራን ዜጎች ችላ ያለ ነው ሲሉ ተችተዋል። በተጨማሪም ከ40,000 በላይ ተቃዋሚዎችን በአጭር ቀናት ውስጥ ከገደለ መንግስት ጋር መደራደር ትልቅ ስትራቴጂካዊ ስህተት መሆኑንና ማዕቀቦችን ማላላት መንግስቱ በውጭ ሀገራት የሚያደርገውን የብጥብጥ ተግባር እንደሚያጠናክርለት አስጠንቅቀዋል። በመጨረሻም፣ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ትኩረቱን በቴህራን ባለስልጣናት ላይ ሳይሆን በኢራን ህዝብ የነጻነት ትግል ላይ እንዲያደርግ ጥሪ አቅርበው፣ የዓለም ድጋፍ ቢኖርም ባይኖርም የአገሪቱ አምባገነን ሥርዓት መውደቁ የማይቀር መሆኑን ገልጸዋል። @zena_maezen @zena_maezen

የኢራኑ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አራግቺ ከአሜሪካ ጋር የነበረው ጦርነት ማክተሙን ገለጹ። ነገር ግን ሚኒስትሩ አክለው እንዳሉት፥ እስራኤል በዚህ ጦርነት ወቅት በቁጥጥሯ ስር ካደረገቻቸው የሊባኖስ ግዛቶ
+1
የኢራኑ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አራግቺ ከአሜሪካ ጋር የነበረው ጦርነት ማክተሙን ገለጹ። ነገር ግን ሚኒስትሩ አክለው እንዳሉት፥ እስራኤል በዚህ ጦርነት ወቅት በቁጥጥሯ ስር ካደረገቻቸው የሊባኖስ ግዛቶች ወታደሮቿን ሙሉ በሙሉ ካላስወጣች በስተቀር ጦርነቱ ሙሉ በሙሉ አብቅቷል ለማለት እንደማይቻል አስታውቀዋል። @zena_maezen @zena_maezen

በመገናኛ ብዙኃን አስተያየት በመስጠታቸው የታሰሩት የ76 ዓመቷ አዛውንት በአስቸኳይ እንዲፈቱ «ቮክስ ትግራይ» ጠየቀ የወጡ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት፤ በጋዜጠኞች መብትና ጥበቃ ዙሪያ የሚንቀሳቀሰው
+1
በመገናኛ ብዙኃን አስተያየት በመስጠታቸው የታሰሩት የ76 ዓመቷ አዛውንት በአስቸኳይ እንዲፈቱ «ቮክስ ትግራይ» ጠየቀ የወጡ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት፤ በጋዜጠኞች መብትና ጥበቃ ዙሪያ የሚንቀሳቀሰው «ቮክስ ትግራይ» (Vox Tigray) ባወጣው መግለጫ፣ ሐሳባቸውን በነፃነት በመግለጻቸው የታሰሩ ዜጎችንና የጋዜጠኞችን መታሰር የሚኮንን ጥሪ አቅርቧል። ተቋሙ በተለይም በቅርቡ «ላንዳ ሪፖርት» (Landa Report) ከተባለ ሚዲያ ጋር ቃለ-መጠይቅ ካደረጉ በኋላ የታሰሩት ወይዘሮ ኣኸዛ ሕሉፍ በአስቸኳይ እንዲፈቱ ጠይቋል። በትግራይ ክልል በደቡብ ምስራቅ ዞን እንደርታ ወረዳ ነዋሪ የሆኑት የ76 ዓመቷ አዛውንት ወይዘሮ ኣኸዛ ሕሉፍ፥ በመገናኛ ብዙኃን ቀርበው ሐሳባቸውን በመግለጻቸው ብቻ ሰኔ 8 ቀን 2018 ዓ.ም በቁጥጥር ሥር መዋላቸው ተገልጿል። «ቮክስ ትግራይ» ድርጊቱን በጽኑ በመኮነን፣ በነፃነት ሐሳብን የመግለጽ መብት እንዲከበርና አዛውንቷ ያለምንም ቅድመ-ሁኔታ በአስቸኳይ ከእስር እንዲለቀቁ አሳስቧል። @zena_maezen @zena_maezen

"የአሜሪካ ሰባራ ሳንቲም ወደ ኢራን አይሄድም። 300 ቢሊዮን ዶላር ወይም 24 ቢሊዮን ዶላር ምንም ዓይነት ገንዘብ የለም ”- የአሜሪካ ምክትል ፕሬዝዳንት የአሜሪካ ምክትል ፕሬዚዳንት ጄዲ ቫንስ ኢራ
"የአሜሪካ ሰባራ ሳንቲም ወደ ኢራን አይሄድም። 300 ቢሊዮን ዶላር ወይም 24 ቢሊዮን ዶላር ምንም ዓይነት ገንዘብ የለም ”- የአሜሪካ ምክትል ፕሬዝዳንት የአሜሪካ ምክትል ፕሬዚዳንት ጄዲ ቫንስ ኢራን ከዩናይትድ ስቴትስ ጋር ባደረገቸው ስምምነት የተነሳ "ሰባራ ሳንቲም" ወደ ቴህራን አይሄድም በማለት ተናገሩ። ቫንስ ለፎክስ ኒውስ በሰጡት ቃለ ምልልስ፣ የቀድሞው ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ ለኢራን "ከ1 ቢሊዮን ዶላር በላይ በጥሬ ገንዘብ ሰጥተዋል" ሲሉ ከትራምፕ አስተዳደር ጋር አነጻጽረዋቸዋል። "ኳታር 300 ቢሊዮን ዶላር ለኢራን ትሰጣታለች እንዲሁም 24 ቢሊየን እንዳይንቀሳቀስ የተደረገ የቴህራን ሃብት ይለቀቃል" ስለተባለው ጉዳይ፣ ሲጠየቁ ቫንስ "በመሰረቱ ይህ የኢራናውያን ፕሮፓጋንዳ ነው" ብለዋል። "እየሆነ ያለው የተወሰኑ ግለሰቦች ለአገር ውስጥ ማኅበረሰብ ስምምነቱ በጎ እንደሆነ በተቻለ መጠን ለማሳየት እየሞከሩ ነው" ሲሉም ተናግረዋል። "የአሜሪካ ሰባራ ሳንቲም ወደ ኢራን አይሄድም። 300 ቢሊዮን ዶላር ወይም 24 ቢሊዮን ዶላር ምንም ዓይነት ገንዘብ" ብለው፣ ይሁን አንጂ "ግዴታቸውን የሚወጡ ከሆነ ለኢራን ጥቅም አለው" በማለት ኳታርና ሳዑዲ አረቢያ በኢራን መዋዕለ ነዋያቸውን ሊያፈሱ እንደሚችሉ ጠቁመዋል። @zena_maezen @zena_maezen