uz
Feedback
ዜና ማዕዘን - Breaking

ዜና ማዕዘን - Breaking

Kanalga Telegram’da o‘tish

እንኳን ወደ ዜና ማዕዘን - Breaking በደህና መጡ በቻናላችን 📌 ፈጣን ሀገራዊ #መረጃዎች 📺 📌 #ዓለም ዓቀፍ መረጃዎች 📢 📌 አዝናኝ እና አስተማሪ መረጃዎች 🔔 📌 ወቅታዊ ጉዳዮች ሁሉንም በአንድ ታገኛላችሁ 📣 #zena_maezen ለሀሳብ አስተያየት (ads) @zena_maezen_bot

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali ዜና ማዕዘን - Breaking analitikasi

ዜና ማዕዘን - Breaking (@zena_maezen) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 67 996 obunachidan iborat bo'lib, Musiqi toifasida 945-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 447-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 67 996 obunachiga ega bo‘ldi.

26 Iyun, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni -1 782 ga, so‘nggi 24 soatda esa -57 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 3.35% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 2.66% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 2 278 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 1 809 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 12 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
እንኳን ወደ ዜና ማዕዘን - Breaking በደህና መጡ በቻናላችን 📌 ፈጣን ሀገራዊ #መረጃዎች 📺 📌 #ዓለም ዓቀፍ መረጃዎች 📢 📌 አዝናኝ እና አስተማሪ መረጃዎች 🔔 📌 ወቅታዊ ጉዳዮች ሁሉንም በአንድ ታገኛላችሁ 📣 #zena_maezen ለሀሳብ አስተያየት (ads) @zena_maezen_bot

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 27 Iyun, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Musiqi toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

67 996
Obunachilar
-5724 soatlar
-3577 kunlar
-1 78230 kunlar
Postlar arxiv
በአሜሪካ ቁጥጥር ስር ውላ ከነበረች የነዳጅ ጫኝ መርከብ ላይ የተገኙ 22 የኢራን የባህር ላይ ሰራተኞች በፓኪስታን ለሚገኘው የኢራን ቆንስላ ተመላሽ ተደርገዋል። @zena_maezen @zena_maez
+1
በአሜሪካ ቁጥጥር ስር ውላ ከነበረች የነዳጅ ጫኝ መርከብ ላይ የተገኙ 22 የኢራን የባህር ላይ ሰራተኞች በፓኪስታን ለሚገኘው የኢራን ቆንስላ ተመላሽ ተደርገዋል። @zena_maezen @zena_maezen

ከሆርሙዝ ባህረ ሰላጤ 115 መርከቦችና 2,500 መርከበኞች በሰላም ወጡ በአሜሪካ እና ኢራን ጦርነት ምክንያት ቀጠናው ውስጥ ተዘግቶባቸው ከነበሩት መካከል 115 መርከቦችና 2,500 መርከበኞች ባለፉ
ከሆርሙዝ ባህረ ሰላጤ 115 መርከቦችና 2,500 መርከበኞች በሰላም ወጡ በአሜሪካ እና ኢራን ጦርነት ምክንያት ቀጠናው ውስጥ ተዘግቶባቸው ከነበሩት መካከል 115 መርከቦችና 2,500 መርከበኞች ባለፉት ሶስት ቀናት ተኩል ውስጥ በሰላም ወጥተዋል። የተባበሩት መንግሥታት የባሕር ላይ አካል (IMO) ዋና ጸሐፊ አርሴኒዮ ዶሚንጌዝ በኦማን ባሕረ ሰላጤ በደረሰ ጥቃት ሳቢያ ቀሪዎቹን 600 መርከቦች የማስወጣቱን ሥራ ለጊዜው ማቆማቸውን ገልጸዋል። መርከቦቹ የተለመደውን መስመር የማይጠቀሙት በተቀበሩ የባሕር ውስጥ ፈንጂዎች ምክንያት ሲሆን፤ በሰላም ስምምነቱ መሠረት ኢራን ፈንጂዎቹን በ30 ቀናት ውስጥ ለማንሳት ቃል ገብታለች። @zena_maezen @zena_maezen

በሌጎስ ናይጄሪያ ሕንጻ ተደርምሶ የዘጠኝ ሰዎች ሕይወት አለፈ በናይጄሪያ ሌጎስ ከተማ ባለ ሶስት ፎቅ መኖሪያና የንግድ ሕንጻ በመደርመሱ የሁለት ዓመት ሕፃንን ጨምሮ የዘጠኝ ሰዎች ሕይወት ሲያልፍ፥ 2
በሌጎስ ናይጄሪያ ሕንጻ ተደርምሶ የዘጠኝ ሰዎች ሕይወት አለፈ በናይጄሪያ ሌጎስ ከተማ ባለ ሶስት ፎቅ መኖሪያና የንግድ ሕንጻ በመደርመሱ የሁለት ዓመት ሕፃንን ጨምሮ የዘጠኝ ሰዎች ሕይወት ሲያልፍ፥ 27 ሰዎች ደግሞ በተለያየ ደረጃ ጉዳት ደርሶባቸዋል። የአደጋው መንስኤ በምርመራ ላይ ቢሆንም፤ በከተማዋ ጥራት የሌላቸው የግንባታ ቁሳቁሶች አጠቃቀምና የቁጥጥር መላላት ለተደጋጋሚ የሕንጻ መደርመስ አደጋዎች በምክንያትነት ይጠቀሳሉ። የሌጎስ ገዥ ባባጂዴ ሳንዎ-ኦሉ በአካባቢው ባሉ ሌሎች ሕንጻዎች ላይ አስቸኳይ የደህንነት ፍተሻ እንዲደረግ አዘዋል። @zena_maezen @zena_maezen

ኢራን በሆርሙዝ ሰርጥ የሰላም ስምምነቱን በመጣስ በድሮን ጥቃት ፈፅማለች ሲሉ ትራምፕ ገለፁ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ትላንት ይፋ እንዳደረጉት፣ የኢራን ጦር ኃይሎች በስትራቴጂካዊቷ የሆር
ኢራን በሆርሙዝ ሰርጥ የሰላም ስምምነቱን በመጣስ በድሮን ጥቃት ፈፅማለች ሲሉ ትራምፕ ገለፁ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ትላንት ይፋ እንዳደረጉት፣ የኢራን ጦር ኃይሎች በስትራቴጂካዊቷ የሆርሙዝ ሰርጥ በሚያልፉ የንግድ መርከቦች ላይ ቢያንስ 4 የአጥፊ ድሮን ጥቃቶችን ሰንዝረዋል። ከእነዚህም መካከል አንዱ የካሚካዜ ድሮን የአንድን የጭነት መርከብ ወለል መምታቱንና ጉዳት ማድረሱን ገልጸዋል። ​ትራምፕ በፅሁፋቸው “ይህ የሰላም ስምምነቱን በግልፅ የጣሰ ሞኝነት ነው” ሲሉ ድርጊቱን አውግዘዋል። አሜሪካ ቀሪዎቹን ሦስት ድሮኖች መትታ የጣለች ሲሆን፣ ጥቃት የደረሰባት መርከብ ግን ጉዞዋን ቀጥላለች። @zena_maezen @zena_maezen

ህወሓት የሂዩማን ራይትስ ዎችን “የአስገዳጅ ውትድርና” ወቀሳ ሙሉ በሙሉ ውድቅ አደረገ የዓለም አቀፉ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ሂዩማን ራይትስ ዎች፣ ህወሓት ያወጣውንና ዜጎችን በጦርነት እንዲካፈሉ ያስ
ህወሓት የሂዩማን ራይትስ ዎችን “የአስገዳጅ ውትድርና” ወቀሳ ሙሉ በሙሉ ውድቅ አደረገ የዓለም አቀፉ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ሂዩማን ራይትስ ዎች፣ ህወሓት ያወጣውንና ዜጎችን በጦርነት እንዲካፈሉ ያስገድዳል የተባለውን አዲስ አዋጅ በአስቸኳይ እንዲሽር በቅርቡ ባወጣው መግለጫ ጠይቋል። ተቋሙ አዲሱን አዋጅ የኤርትራ መንግስት ወጣቶችን ለአስገዳጅ ወታደራዊ ምልመላ ከሚጠቀምበት ሕግ ጋር ያመሳሰለው ሲሆን፤ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ላይ የተደረገውን ለውጥ ተከትሎ የወጣው ይህ ድንጋጌ የሲቪል ዜጎችን መብት የሚጋፋና ሕጉን የሚቃወሙትን የሚያስቀጣ ነው ሲል ወቅሷል። በጉዳዩ ላይ ምላሽ የሰጡት የህወሓት ቃል አቀባይ አቶ ሚካኤል አስገዶም ግን የዓለም አቀፉን ተቋም መግለጫ “መሬት ላይ ያለውን እውነታ ያላገናዘበና የተጋነነ” በማለት ሙሉ በሙሉ ውድቅ አድርገውታል። ትግራይ የህልውና አደጋ የተጋረጠባት ብሔር መሆኗን የገለጹት ቃል አቀባዩ፣ የሚደረገው ዝግጅት ሊመጣ የሚችለውን አደጋ ለመቀልበስ እንጂ “ሰው ለመግደልና ለማፈን” እንዳልሆነ ተከላክለዋል። አዲሱ አዋጅ በክልሉ ሕጋዊነትን ለማስፈን የወጣ መሆኑን የገለጹት ባለስልጣናቱ፣ የቀረበባቸውን ከፍተኛ የወቀሳ ትችት አጣጥለውታል። @zena_maezen @zena_maezen

አሜሪካ ኢራን ላይ “ከባድ የአየር ጥቃት አደረስኩ” አለች። የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ (ሴንት ኮም) ኢራን በሆርሙዝ ሰርጥ የአራት ሰው አልባ አውሮፕላን (ድሮን ) ጥቃት ማድረሷን ተከትሎ አፀፋዊ ምላሽ
+1
አሜሪካ ኢራን ላይ “ከባድ የአየር ጥቃት አደረስኩ” አለች። የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ (ሴንት ኮም) ኢራን በሆርሙዝ ሰርጥ የአራት ሰው አልባ አውሮፕላን (ድሮን ) ጥቃት ማድረሷን ተከትሎ አፀፋዊ ምላሽ በሆርሙዝ ሰርጥ እና በወሳኝ አካባቢዎች መስጠቱን አሳውቋል። ፎክስ ኒውስ እንዳስነበበው ዋሽንግተን ስድስት የጦር አውሮፕላኖችን  በመጠቀም አራት ዒላማዎችን መትቻለሁ ብላለች።በሆርሙዝ ዳርቻ ባሉ አካባቢዎች እና በገሽም ደሴት ላይ ጥቃት ደርሷል። የኢራን ሚዲያዊች በሲሪክ አካባቢም ከፍተኛ ፍንዳታ መሰማቱን እየዘገቡ ይገኛል።የራዳር እና ሚሳዔል ስርዓቶች ዒላማ መሆናቸውም ተሰምቷል። ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በትሩዝ ሶሻል ሚዲያቸው ላይ ኢራን በንግድ መርከብ ላይ ያደረሰችው ጥቃት ምላሽ ሊሰጠው እንደሚችል ቀደም ሲል ይፋ ማድረጋቸው የሚታወስ ነው። “ኢራን የሰላም ስምምነት ፈርማለች፤እሱን እናከብራለን” ያሉት ምክትል ፕሬዚዳንት ጄዲ ቫንስ “ጥቃትን በጥቃት እንመልሳለን” ብለዋል። የኢራን አብዮታዊ ዘብ ኃይል (IRGC) የአሜሪካን ጥቃት አውግዞ ሁል ጊዜም ቢሆን ዋሽንግተን ቃሏን ታጥፋለች በሚል ከሷል።የኢራን አብዮታዊ ዘብ የአሜሪካን ዒላማዎች በመካከለኛው ምስራቅ መምታቱንም አሳውቋል። ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት ሰዓት ድረስ የደረሰው ጉዳትም ሆነ ፤ኢራን ስለሰጠችው ምላሽ ዝርዝር መረጃ አልተጋራም።ዘገባው የአልጀዚራ እና ሲ ኤን  ኤን ነው።

ኢትዮጵያ ወታደራዊ ምርቶቿን ለጎረቤት ሀገራት መሸጥ ጀመረች ኢትዮጵያ በጸጥታው ዘርፍ የነበራትን የውጭ ጥገኝነት በመቀነስ፣ ቀላልና ከባድ የጦር መሣሪያ ጥይቶችን በሀገር ውስጥ ማምረት ብቻ ሳይሆን ለ
ኢትዮጵያ ወታደራዊ ምርቶቿን ለጎረቤት ሀገራት መሸጥ ጀመረች ኢትዮጵያ በጸጥታው ዘርፍ የነበራትን የውጭ ጥገኝነት በመቀነስ፣ ቀላልና ከባድ የጦር መሣሪያ ጥይቶችን በሀገር ውስጥ ማምረት ብቻ ሳይሆን ለጎረቤት ሀገራት በመላክ አዲስ የውጭ ምንዛሬ ምንጭ መፍጠር መጀመሯን የመከላከያ ሠራዊት ይፋ አድርጓል። ይህ ታሪካዊ እርምጃ ሀገሪቱ በድንገተኛ የጸጥታ ተግዳሮቶች ጊዜ ሊያጋጥማት የሚችለውን የጥይት አቅርቦት እጥረት ሙሉ በሙሉ የሚቀርፍ ከመሆኑም በላይ፣ ቀደም ሲል ለጦር መሣሪያ ግዥ ይወጣ የነበረውን ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ማዳን አስችሏል። ይህ ስኬት የኢትዮጵያን ወታደራዊ የኢንዱስትሪ አቅም አንድ ደረጃ ከፍ ያደረገ ትልቅ እመርታ ተደርጎ ተወስዷል። የመከላከያ ሠራዊት ባጋራው መረጃ፤ ከጥይት ምርት ጎን ለጎን፣ መንግሥት የድሮን (UAV) ቴክኖሎጂን በሀገር ውስጥ የማልማትና የመገጣጠም ሥራን በስፋት እየተገበረ ይገኛል። እነዚህ የድሮን ማዕከላት መቋቋማቸው የመከላከያ ሠራዊቱ የሀገሪቱን የአየር ክልል በአስተማማኝ ሁኔታ እንዲቆጣጠር የረዳው ሲሆን፣ ማንኛውንም የጸጥታ ስጋት በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) እና በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በታገዘ መንገድ በፈጣን ሁኔታ ምላሽ ለመስጠት አስችሎታል። በአጠቃላይ ይህ የቴክኖሎጂ ሽግግርና በራስ አቅም የመደራጀት ጉዞ የኢትዮጵያን የጸጥታ መዋቅር ይበልጥ እያዘመነው ይገኛል ተብሏል። @zena_maezen @zena_maezen

ማያንማር ከ600 ሚሊዮን ዶላር በላይ የሚያወጡ ህገ-ወጥ እጾችን አቃጠለች ይህ እርምጃ የተወሰደው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአለም አቀፍ የእፅ አላግባብ መጠቀም እና ህገ-ወጥ ዝውውር መከላከያ
ማያንማር ከ600 ሚሊዮን ዶላር በላይ የሚያወጡ ህገ-ወጥ እጾችን አቃጠለች ይህ እርምጃ የተወሰደው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአለም አቀፍ የእፅ አላግባብ መጠቀም እና ህገ-ወጥ ዝውውር መከላከያ ቀንን ምክንያት በማድረግ ነው። በያንጎን ከተማ ዳርቻ በተካሄደው ስነ-ስርዓት ከ50 ቶን በላይ ሄሮይን፣ ሜታምፌታሚን፣ ኦፒየም እና ሌሎች እጾች በእሳት የተቃጠሉ ሲሆን፥ ይህም በሀገሪቱ ታሪክ ከተከናወኑት ትልልቅ እጽ የማውደም እርምጃዎች አንዱ ነው። የሀገሪቱ ፀረ-ዕፅ ፖሊስ እንደገለጸው የዘንድሮው እፅ ዋጋ ካለፈው ዓመት በእጥፍ ይበልጣል። ማያንማር በአለም ላይ ከፍተኛ የእፅ አምራች ከሆኑት ሀገራት አንዷ ስትሆን፥ እ.ኤ.አ. በ2021 ከነበረው የወታደራዊ መፈንቅለ መንግስት በኋላ የተከሰተው የእርስ በእርስ ጦርነት እና አለመረጋጋት ለዕፅ ምርት እና ዝውውር በከፍተኛ ሁኔታ መጨመር ምክንያት መሆኑን ባለሙያዎች ይናገራሉ። የወታደራዊው መንግስት የታጠቁ ቡድኖችን በእፅ ንግድ ሲከስስ፣ አንዳንድ ጎሳዎች ግን በበኩላቸው በቁጥጥራቸው ስር ባሉ አካባቢዎች የእፅ ማጥፊያ ዘመቻዎችን እያካሄዱ ነው። @zena_maezen @zena_maezen

በኮንጎ በኢቦላ ወረርሽኝ የሟቾች ቁጥር 300 ደረሰ የኢቦላ ወረርሽኝ በኮንጎ መቀስቀሱ በይፋ ከታወጀበት ከሚያዝያ 15/2026 ጀምሮ 304 ሰዎች መሞታቸውንና 1155 ሰዎች መጠቃታቸውን የሀገሪቱ የጤ
በኮንጎ በኢቦላ ወረርሽኝ የሟቾች ቁጥር 300 ደረሰ የኢቦላ ወረርሽኝ በኮንጎ መቀስቀሱ በይፋ ከታወጀበት ከሚያዝያ 15/2026 ጀምሮ 304 ሰዎች መሞታቸውንና 1155 ሰዎች መጠቃታቸውን የሀገሪቱ የጤና ሚኒስቴር አስታውቋል። የህክምና ክትትል እየተደረገላቸው እንደሚገኝ ሚኒስቴሩ ገልጿል። ከ150 በላይ ሰዎች ከበሽታው ማገገማቸው ተመላክቷል። የአፍሪካ በሽታ መከላከል እና መቆጣጠር ማዕከል (Africa CDC) በበኩሉ ወረርሽኙን ለመግታት 1.4 ቢሊዮን ዶላር ያስፈልጋል ብሏል። በምሥራቅ ኮንጎ ቡንድቡግዮ ግዛት የተቀሰቀሰው የኢቦላ ወረርሽኝ በአሁኑ ወቅት ኢቱሪ፣ ኖርዝ ኪቩ ሳውዝ ኪቩን ጨምሮ በ34 የሀገሪቱ ግዛቶች መስፋፋቱ ተመላክቷል። @zena_maezen @zena_maezen

"ብንወያይ ይሻላል፣ በሂደት ወደ ውይይት መሄድ ያስፈልጋል" - ሉካሽንኮ የቤላሩስ ፕሬዚዳንት አሌክሳንደር ሉካሽንኮ የሩሲያና ክሬን ጦርነት በስምምነት እንዲቋጭ ጠየቁ። "ሰላማዊ መንገድን እንደ አማራ
"ብንወያይ ይሻላል፣ በሂደት ወደ ውይይት መሄድ ያስፈልጋል" - ሉካሽንኮ የቤላሩስ ፕሬዚዳንት አሌክሳንደር ሉካሽንኮ የሩሲያና ክሬን ጦርነት በስምምነት እንዲቋጭ ጠየቁ። "ሰላማዊ መንገድን እንደ አማራጭ መውሰድ አለበት" ብለዋል። ሉካሽንኮ "የዩክሬን ባለስልጣናት የሚያናግሩን በጦርነት ከሆነ ሁኔታው አስከፊ ለውጥ ያመጣል" በማለት አስጠንቅቀዋል። "ሰዎች ብንወያይ ይሻላል፣ በሂደት ወደ ውይይት መሄድ ያስፈልጋል" በማለት ጥሪ አቅርበዋል። ፕሬዚዳንቱ "ከሩሲያ በመቀጠል እኛ ነን ተጋላጭ የምንሆነው" ሲሉ ተናግረዋል። "ሰላምና ሰላም ብቻ" ያሉት ፕሬዚዳንቱ "ግን ዩክሬን እንዳትጫወት ዋስትና እንፈልጋለን" ብለዋል። ቤላሩስ በዩክሬን ጦርነት ከሩሲያ ጎን የቆመች ሲሆን በዚህ አቋሟ ከአውሮፓ ህብረት ማዕቀብ ተጥሎባታል።  @zena_maezen @zena_maezen

Update‼️ በቬንዙዌላው አደጋ የሟቾች ቁጥር 589 መድረሱን የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት አስታወቁ በቬንዙዌላ በደረሰው የመሬት መንቀጥቀጥ የሞቱ ሰዎች ቁጥር 589 መድረሱን የአገሪቱ ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት
Update‼️ በቬንዙዌላው አደጋ የሟቾች ቁጥር 589 መድረሱን የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት አስታወቁ በቬንዙዌላ በደረሰው የመሬት መንቀጥቀጥ የሞቱ ሰዎች ቁጥር 589 መድረሱን የአገሪቱ ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት ዴልሲ ሮዴሪጌዝ አስታውቀዋል። ከአካባቢው በወጡ መረጃዎች እንደ ቢቢሲ አይነት ሚዲያዎች በዘገቡት መሰረት የተጎጂዎች ብዛት ከ4 ሺሕ መብለጡ የተገለጸ ሲሆን፣ ፕሬዝዳንት ዴልሲ ሮዴሪጌዝ ደግሞ 2,980 ሰዎች መጎዳታቸውን አረጋግጠዋል። አደጋው በደረሰ በ34 ሰዓታት ውስጥ በተደረገው ርብርብ በርካቶችን በሕይወት እያሉ ማትረፍ መቻሉን ተናግረዋል። ከፍተኛ ጉዳት የደረሰበት በካሬቢያን የባሕር ዳርቻ አካባቢ የሚገኘው የላ ጓይራ ግዛት ሲሆን፣ ዋና ከተማ ካራካስና በሌሎች ግዛቶችም ሕንጻዎች ተደርምሰዋል፤ ቤቶች እንዳልነበሩ ሆነዋል። ዓለም አቀፍ የእርዳታ ቡድኖች ወደ ደቡባዊ አሜሪካዊቱ ሀገር እየገቡ ነው። ከስዊትዘርላንድ የተላኩ 80 የነፍስ አድን ሠራተኞች እና 18 ቶን ቁሳቁሶች ቬንዙዌላ መድረሳቸው ተነግሯል። @zena_maezen @zena_maezen

በአዲስ አበባ የቤት ኪራይ ዋጋን በህግ ለመገደብ አዲስ የጥናት ውይይት ተካሄደ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤናማ የቤት ኪራይ አሰራርን ለመዘርጋትና በህግ ማዕቀፍ ለመምራት የሚያስችል የግል መኖሪ
+1
በአዲስ አበባ የቤት ኪራይ ዋጋን በህግ ለመገደብ አዲስ የጥናት ውይይት ተካሄደ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤናማ የቤት ኪራይ አሰራርን ለመዘርጋትና በህግ ማዕቀፍ ለመምራት የሚያስችል የግል መኖሪያ ቤት ኪራይ ዋጋ መተመኛ ጥናትን አስመልክቶ የፓናል ውይይት ተካሂዷል። የቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ ቅድስት ወ/ጊዮርጊስ እንደገለጹት፤ ጥናቱ አከራዩ ወቅቱን ያገናዘበ ፍትሃዊ ገቢ እንዲያገኝ እና ተከራዩ ደግሞ ከገቢው ጋር የተመጣጠነ ኪራይ እንዲከፍል ለማስቻል ነው። ይህ የዋጋ ትመና ጥናት በዘፈቀደ የተሰራ ሳይሆን የነዋሪዎችን የመክፈል አቅም ያገናዘበ በመሆኑ በከተማዋ ያለውን የኑሮ ውድነት በመቀነስ ረገድ ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ፋይዳ ይኖረዋል። ይህ ለ2019 በጀት ዓመት የተዘጋጀው የገበያ ዋጋ ጥናት ወደ ተግባር ከመሸጋገሩ በፊት፣ ከሚመለከታቸው ተቋማትና ከህዝብ ተወካዮች ጋር የጋራ መግባባት ለመፍጠር መድረኩ መዘጋጀቱ ተገልጿል። ጥናቱ በከተማዋ ላይ ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ ፋይዳዎች እንዳሉት የተገለጸ ሲሆን፣ ህገ-ወጥና ያልተገባ የኪራይ ጭማሪን በማስቀረት የተረጋጋ የቤት ኪራይ ገበያ ለመፍጠር ያለመ እንደሆነ ተጠቁሟል።

የግብፅ እና የኢራን እግር ኳስ ማህበራት ከእስልምና ሀይማኖታዊ እሴቶቻቸው ጋር የማይጣጣም በመሆኑ በዓለም ዋንጫ ጨዋታቸው ላይ (LGBTQ) ባንዲራዎች እንዳይፈቀዱ ለፊፋ (FIFA) ተቃውሟቸውን አቅር
+1
የግብፅ እና የኢራን እግር ኳስ ማህበራት ከእስልምና ሀይማኖታዊ እሴቶቻቸው ጋር የማይጣጣም በመሆኑ በዓለም ዋንጫ ጨዋታቸው ላይ (LGBTQ) ባንዲራዎች እንዳይፈቀዱ ለፊፋ (FIFA) ተቃውሟቸውን አቅርበዋል። ነገር ግን ሲያትል ጥያቄውን ውድቅ በማድረግ የግብፅ እና የኢራንን ጨዋታ በይፋ "የፕራይድ ጨዋታ" (Pride Match) አድርጋ ሰይማዋለች። @zena_maezen @zena_maezen

ጃፓን ለኢራን፣ ለሊባኖስ እና ለዌስት ባንክ የ15 ሚሊዮን ዶላር ሰብአዊ እርዳታ ልታበረክት ነው። @zena_maezen @zena_maezen
+1
ጃፓን ለኢራን፣ ለሊባኖስ እና ለዌስት ባንክ የ15 ሚሊዮን ዶላር ሰብአዊ እርዳታ ልታበረክት ነው። @zena_maezen @zena_maezen

የ91 ዓመቱ የእስራኤል ጦር አርበኛ በደቡብ ሱዳን የክብር ጄኔራል ማዕረግ ተሰጣቸው ደቡብ ሱዳን በመጀመሪያው የሱዳን የእርስ በርስ ጦርነት ወቅት ለሀገሪቱ የነፃነት ትግል ላደረጉት ከፍተኛ ድጋፍ ለ9
የ91 ዓመቱ የእስራኤል ጦር አርበኛ በደቡብ ሱዳን የክብር ጄኔራል ማዕረግ ተሰጣቸው ደቡብ ሱዳን በመጀመሪያው የሱዳን የእርስ በርስ ጦርነት ወቅት ለሀገሪቱ የነፃነት ትግል ላደረጉት ከፍተኛ ድጋፍ ለ91 ዓመቱ የእስራኤል ጦር አርበኛ ዴቪድ ኡሪ ቤን-ኡዚኤል የክብር ጄኔራልነት ማዕረግ ሸልማለች። ፕሬዝዳንት ሳልቫ ኪር ማዕረጉን በጁባ በሰጡበት ወቅት ቤን-ኡዚኤል “አንያንያ ዋን” የተባለው የነፃነት ንቅናቄ ከእስራኤል ጋር ግንኙነት እንዲመሰርት ላድረጉት አስተዋጽኦ ምስጋና አቅርበዋል። በትግሉ ወቅት እስራኤል ወታደራዊ ስልጠና፣ የህክምና አቅርቦቶች፣ የኮሙዩኒኬሽን መገልገያዎችና ሌሎች የሎጅስቲክስ ድጋፎችን እንድታደርግ የቤን-ኡዚኤል አስተዋጽኦ ከፍተኛ እንደነበር ተጠቁሟል። @zena_maezen @zena_maezen

5 የአውሮፓ ሀገራት የጥገኝነት ጥያቄያቸው ተቀባይነት ያላገኘ ግለሰቦችን ወደ ኬንያ ለመላክ እያሰቡ ነው ጀርመን፣ ኔዘርላንድስ፣ ኦስትሪያ፣ ዴንማርክና ግሪክ፣ የጥገኝነት ጥያቄያቸው ውድቅ የተደረገባቸ
5 የአውሮፓ ሀገራት የጥገኝነት ጥያቄያቸው ተቀባይነት ያላገኘ ግለሰቦችን ወደ ኬንያ ለመላክ እያሰቡ ነው ጀርመን፣ ኔዘርላንድስ፣ ኦስትሪያ፣ ዴንማርክና ግሪክ፣ የጥገኝነት ጥያቄያቸው ውድቅ የተደረገባቸውን ስደተኞች ከአውሮፓ ውጭ ወደሚገኙ ሶስተኛ ሀገራት ለመላክ የሚያስችል አከራካሪ የፍልሰት እቅድ እያጠኑ መሆኑ ተሰምቷል። በአውሮፓ ህብረት የፍልሰት ማሻሻያ ማዕቀፍ ውስጥ እየተመከረበት ባለው በዚህ አዲስ የውሳኔ ሃሳብ መሰረት፣ ማመልከቻቸው ሙሉ በሙሉ ውድቅ የተደረገባቸው ግለሰቦች ወደ ትውልድ ሀገራቸው የሚመለሱበት የመጨረሻ ዝግጅት እስከሚጠናቀቅ ድረስ ከአውሮፓ ውጭ ወደሚገነቡ “የመመለሻ ማዕከላት” እንዲዛወሩ ይደረጋል። ለዚህ የስደተኞች ማቆያ ማዕከልነት ሊመረጡ ይችላሉ ተብለው ከታጩት ሀገራት መካከል ምስራቅ አፍሪካዊቷ ኬንያ በቀዳሚነት ስሟ የተነሳ ሲሆን፣ ከእሷ በተጨማሪም ሩዋንዳ እና ቤኒን በዕጩነት ተካተዋል። ይህ እቅድ በአውሮፓ ህብረት ውስጥ ትልቅ መነጋገሪያና አከራካሪ አጀንዳ እየሆነ የመጣ ሲሆን፣ ስደተኞችን በጊዜያዊነት ወደ ሌላ ሀገር በማዛወር ሂደት ላይ ያሉትን ሰብአዊና ህጋዊ ተግዳሮቶች በተመለከተ በርካታ ጥያቄዎችን እያስነሳ ይገኛል። ከእነዚህ የአውሮፓ ሀገራት መካከል ኔዘርላንድስ እቅዱን ከሚደግፉት መሪ ሀገራት አንዷ ስትሆን፣ በተለይም ኬንያ ለዚህ ፕሮግራም ቁልፍ አጋር ሀገር እንድትሆን ከፍተኛ ፍላጎት እያሳየች እንደሆነ ሪፖርቶች ያመለክታሉ። ስምምነቱ ከጸደቀ ስደተኞችን ወደ ሶስተኛ ሀገር የመላኩ ሂደት በአውሮፓ የፍልሰት ፖሊሲ ላይ ትልቅ ለውጥ እንደሚያመጣ እየተነገረ ሲሆን፣ የኬንያ መንግስት በዚህ ጉዳይ ላይ የሚሰጠው ምላሽ ግን አልታወቀም። @zena_maezen @zena_maezen

655 ሚሊዮን ህዝብ አሁንም በጨለማ ውስጥ ይኖራል - ሪፖርት በ2026 የወጣው አዲሱ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ሪፖርት እንደሚያሳየው፣ በአለማችን ላይ 655 ሚሊዮን ህዝብ አሁንም ድረስ የኤሌክት
655 ሚሊዮን ህዝብ አሁንም በጨለማ ውስጥ ይኖራል - ሪፖርት በ2026 የወጣው አዲሱ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ሪፖርት እንደሚያሳየው፣ በአለማችን ላይ 655 ሚሊዮን ህዝብ አሁንም ድረስ የኤሌክትሪክ አገልግሎት ሳያገኝ በጨለማ ውስጥ ይኖራል። ከዚህ አስደንጋጭ ቁጥር ውስጥ ከ560 ሚሊዮን በላይ የሚሆነው ህዝብ የሚገኘው ከሰሃራ በታች ባሉ የአፍሪካ ሀገራት ውስጥ ሲሆን፣ ይህም ክልሉ ከአለም አጠቃላይ እድገት ወደኋላ መቅረቱን ያሳያል። በተጨማሪም በአለም ዙሪያ ወደ 2 ቢሊዮን የሚጠጋ ህዝብ ለጤና ጎጂ የሆኑ የማብሰያ ቁሳቁሶችንና ነዳጆችን ለመጠቀም የተገደደ ሲሆን፣ ይህም በየአመቱ ለ3 ሚሊዮን ሰዎች ሞት ምክንያት ለሚሆነው የቤት ውስጥ አየር ብክለት ዋነኛ መንስኤ ሆኗል። በአንጻሩ የታዳሽ ኃይል አጠቃቀም በአለም አቀፍ ደረጃ ከ30% በላይ የኤሌክትሪክ ፍጆታን በመሸፈን ከፍተኛ እድገት ቢያሳይም፣ በበለጸጉና በደሃ ሀገራት መካከል ያለው የሃይል አቅርቦት ልዩነት ግን እጅግ በጣም ሰፊ ነው። ለምሳሌ ያህል ከፍተኛ ገቢ ባላቸው ሀገራት የአንድ ሰው የታዳሽ ሃይል ማመንጨት አቅም 1,224 ዋት ሲሆን፣ ዝቅተኛ ገቢ ባላቸው ሀገራት ግን ይህ ቁጥር 33.6 ዋት ብቻ ነው። የዓለም አቀፍ የፋይናንስ ድጋፍም ቢሆን በ2024 ዓ.ም ወደ 24.6 ቢሊዮን ዶላር ቢያድግም፣ አብዛኛው ድጋፍ (80%) በዕዳ ወይም በብድር መልክ የሚሰጥ በመሆኑ ደሃ ሀገራትን ለከፍተኛ የኢኮኖሚ ጫና እየዳረገ ይገኛል። @zena_maezen @zena_maezen

በቬንዙዌላው አደጋ የሟቾች ብዛት 235፣ የተጎጂዎች 4,300 ደረሰ በቬንዙዌላ ዋና ከተማ ካራካስ አቅራቢያ በደረሱ ሁለት ተከታታይ ከባድ የመሬት መንቀጥቀጦች የሞቱ ሰዎች ቁጭር 235 ሲደርስ፣ 4,3
+1
በቬንዙዌላው አደጋ የሟቾች ብዛት 235፣ የተጎጂዎች 4,300 ደረሰ በቬንዙዌላ ዋና ከተማ ካራካስ አቅራቢያ በደረሱ ሁለት ተከታታይ ከባድ የመሬት መንቀጥቀጦች የሞቱ ሰዎች ቁጭር 235 ሲደርስ፣ 4,300 ተጎድተዋል። በካራከስ እና በአቅራቢያው በሚገኛው የባሕር ዳርቻ ከተማ ላጉኣራ በሕንፃዎች ፍርስራሽ የተቀበሩ ሰዎች ለእርዳታ ሲጣሩ ይሰማሉ። በአደጋው በርካታ ሰዎች ሞተዋል ተብሎ ሲገመት፤ ሌሎች ደግሞ ቤት አልባ ወይንም በተጎዱ እና ለአደጋ በተጋለጡ ሕንፃዎች ውስጥ ከመቆየት ይልቅ መንገድ ላይ መሆንን መርጠዋል። አደጋው የደረሰው ዕረቡ ዕለት ቬንዙዌላ ብሔራዊ በዓል እያከበረች በነበረችበት ጊዜ ነው። ይህም ማለት አደጋው የደረሰው ከወትሮ በተለየ በርካታ ሰዎች ቤት ውስጥ እያሉ ነበር። የቬንዙዌላ ብሔራዊ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሆርሄ ሮድሪጉዝ የአገሪቱ ጊዜያዊ ፕሬዝዳንት ዴልሲ ሮድሪጌዝ አስቸኳይ ጊዜ ካወጁ በኋላ የሟቾች ቁጥር መጨመሩን አስታውቀዋል። @zena_maezen @zena_maezen

በጭነት መርከብ ላይ ጥቃት መሰንዘሩን ተከትሎ የተባበሩት መንግሥታት በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ የጀመረውን የማስወጣት ዕቅድ ማቆሙን አስታወቀ የተባበሩት መንግሥታት ዓለም አቀፍ የባህር ላይ ድርጅት በሆ
በጭነት መርከብ ላይ ጥቃት መሰንዘሩን ተከትሎ የተባበሩት መንግሥታት በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ የጀመረውን የማስወጣት ዕቅድ ማቆሙን አስታወቀ የተባበሩት መንግሥታት ዓለም አቀፍ የባህር ላይ ድርጅት በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ተዘግቶባቸው የቆዩ ከ11 ሺህ በላይ መርከበኞችን ለማስወጣት አቅዶት የነበረውን ተግባር በውሃው ላይ በሚጓዝ አንድ የጭነት መርከብ ላይ ጥቃት በመሰንዘሩ ምክንያት ለጊዜው አቋርጧል። የድርጅቱ ዋና ኃላፊ አርሴኒዮ ዶሚንጌዝ እንደገለጹት፤ በርካታ ጀልባዎች ቀደም ብለው እንዲወጡ የተደረገ ቢሆንም ድርጅቱ ግን ‹‹አስፈላጊው የደህንነት ዋስትና›› በተሟላ ሁኔታ መቀጠሉን ማረጋገጥ ይፈልጋል። የብሪታንያ የባህር ላይ ደህንነት ኤጀንሲ እንደዘገበው፤ አንድ መርከብ ከኦማን የዳሂት ወደብ በስተደቡብ ምስራቅ 7.5 ኖቲካል ማይል ርቀት ላይ ‹‹ምንነቱ ባልታወቀ ተተኳሽ›› ተመትቷል። በጥቃቱ ምንም ዓይነት የሰው ጉዳት አልደረሰም። ጥቃቱ የተፈጸመው የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ የባህር ወሽመጡን ለማቋረጥ የሚደረጉ ሙከራዎች ‹‹ተቀባይነት የሌላቸውና ፍጹም አደገኛ›› መሆናቸውንና መርከቦች ከኢራን ጋር ቅንጅት መፍጠር እንዳለባቸው ማስጠንቀቂያ ከሰጠ በኋላ ነው። የአሜሪካ መገናኛ ብዙኃን የሀገሪቱን ባለሥልጣናት ጠቅሰው እንደዘገቡት፤ኢራን በመርከቡ ላይ ጥቃት ሰንዝራለች። ‹‹ቫንጋርድ›› የተባለው የባህር ላይ ስጋት አስተዳደር ተቋም እንደገለጸው፤ የሲንጋፖር ሰንደቅ ዓላማ የያዘችው ‹‹ኤቨር ላቭሊ›› የተባለችው መርከብ ጥቃቱ ቢሰነዘርባትም በወሽመጡ በኩል ጉዞዋን ቀጥላለች። መርከቧ አራት ሌሎች መርከቦችን በቡድን እየመራች እንደነበር ዎል ስትሪት ጆርናል ዘግቧል።

የአውሮፓ ህብረት ለሶማሊያ ዜጎች የሚሰጠውን የቪዛ አገልግሎት ገደበ ህብረቱ እርምጃዉን የወሰደዉ ሶማሊያ በአውሮፓ ህብረት ውስጥ ያለህጋዊ ሰነድ የሚኖሩ ዜጎቿን መልሳ ለመቀበል በቂ ትብብር አላደረገች
+1
የአውሮፓ ህብረት ለሶማሊያ ዜጎች የሚሰጠውን የቪዛ አገልግሎት ገደበ ህብረቱ እርምጃዉን የወሰደዉ ሶማሊያ በአውሮፓ ህብረት ውስጥ ያለህጋዊ ሰነድ የሚኖሩ ዜጎቿን መልሳ ለመቀበል በቂ ትብብር አላደረገችም በሚል እንደሆነ የአውሮፓ ህብረት ያወጣውን መግለጫ ዋቢ አድርጎ ያስቀመጠው የሆርን ኦብዘርቨር ዘገባ ነዉ፡፡ ህብረቱ ሶማሊያ ዜጎቿን ወደ ሀገራቸው የመመለስ እና መልሶ የመቀበል ሂደትን በተመለከተ ከአውሮፓ ህብረት አባል ሀገራት ጋር በቂ ትብብር አላደረገችም የሚል ዉሳኔ ላይ ደርሶ እንደሆነ ዘገባዎች ያሳያሉ። በእነዚህ ጊዜያዊ እርምጃዎች መሰረት የአውሮፓ ህብረት አባል ሀገራት ለሶማሊያ ዜጎች ከአንድ ጊዜ በላይ የመግቢያ ቪዛዎችን አይሰጡም። ከዚህም በተጨማሪ ለሶማሊያ ዜጎች የሚቀርቡ የቪዛ ማመልከቻዎችን ለማጠናቀቅ የሚፈጀው መደበኛ ጊዜ ከ15 የቀን መቁጠሪያ ቀናት ወደ 45 ቀናት ከፍ እንዲል ይደረጋል። እነዚህ እርምጃዎች የአውሮፓ ህብረት የቪዛ ማዕቀፍ ስርአቶች አካል ሲሆኑ፤ ማዕቀፉ በስደት እና ዜጎችን መልሶ በመቀበል ረገድ የሚደረገው ትብብር በቂ እንዳልሆነ በሚታመንበት ጊዜ በቪዛ አሰራሮች ላይ ማስተካከያዎችን ለማድረግ ይፈቅዳል። ምክር ቤቱ እነዚህ ገደቦች ጊዜያዊ መሆናቸውን እና ዓላማቸውም ሶማሊያ ዜጎቿን መልሳ የመቀበል ሂደቶች ላይ የምታደርገውን ትብብር እንድታጠናክር ለማስቻል እንደሆነ ገልጿል። ገደቡ የሚያበቃበት የተለየ ቀን ግን በግልጽ አልተነገረም። @zena_maezen @zena_maezen