ዜና ማዕዘን - Breaking
እንኳን ወደ ዜና ማዕዘን - Breaking በደህና መጡ በቻናላችን 📌 ፈጣን ሀገራዊ #መረጃዎች 📺 📌 #ዓለም ዓቀፍ መረጃዎች 📢 📌 አዝናኝ እና አስተማሪ መረጃዎች 🔔 📌 ወቅታዊ ጉዳዮች ሁሉንም በአንድ ታገኛላችሁ 📣 #zena_maezen ለሀሳብ አስተያየት (ads) @zena_maezen_bot
نمایش بیشتر📈 تحلیل کانال تلگرام ዜና ማዕዘን - Breaking
کانال ዜና ማዕዘን - Breaking (@zena_maezen) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 67 445 مشترک است و جایگاه 959 را در دسته موسیقی و رتبه 461 را در منطقه أثيوبيا دارد.
📊 شاخصهای مخاطب و پویایی
از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 67 445 مشترک جذب کرده است.
بر اساس آخرین دادهها در تاریخ 08 ژوئیه, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر -1 566 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -55 بوده و همچنان دسترسی گستردهای حفظ شده است.
- وضعیت تأیید: تأیید نشده
- نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 3.23% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 2.58% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب میکند.
- دسترسی پستها: هر پست به طور میانگین 2 181 بازدید دریافت میکند. در اولین روز معمولاً 1 740 بازدید جمعآوری میشود.
- واکنشها و تعامل: مخاطبان بهطور فعال حمایت میکنند؛ میانگین واکنش به هر پست 10 است.
📝 توضیح و سیاست محتوایی
نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاههای شخصی توصیف میکند:
“እንኳን ወደ ዜና ማዕዘን - Breaking በደህና መጡ
በቻናላችን
📌 ፈጣን ሀገራዊ #መረጃዎች 📺
📌 #ዓለም ዓቀፍ መረጃዎች 📢
📌 አዝናኝ እና አስተማሪ መረጃዎች 🔔
📌 ወቅታዊ ጉዳዮች ሁሉንም በአንድ ታገኛላችሁ 📣
#zena_maezen
ለሀሳብ አስተያየት (ads) @zena_maezen_bot”
به لطف بهروزرسانیهای پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 09 ژوئیه, 2026)، کانال همواره بهروز و دارای دسترسی بالاست. تحلیلها نشان میدهد مخاطبان بهطور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته موسیقی تبدیل کردهاند.
در حال بارگیری داده...
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 09 ژوئیه | 0 | |||
| 08 ژوئیه | 0 | |||
| 07 ژوئیه | 0 | |||
| 06 ژوئیه | 0 | |||
| 05 ژوئیه | 0 | |||
| 04 ژوئیه | 0 | |||
| 03 ژوئیه | 0 | |||
| 02 ژوئیه | 0 | |||
| 01 ژوئیه | 0 |
| 2 | የሀማስ አስተዳደር መፍረስ
። ። ። ። ። ። ። ። ። ።
ሃማስ የጋዛ አስተዳደሩን ማፍረሱን አስታወቀ።
ሃማስ ለአሜሪካ መራሹ የፍለስጤም ሽግግር ኮሚቴ መንግስቱን አሳልፎ ለመስጠት ዝግጁ ነኝ ብሏል።
በድርድር ሂደቱ ውስጥ እስራኤል ቁልፍ ነጥብ አድርጋ የምትወስደው ተጥቅ የመፍታትን ጉዳይ ግን ሃማስ በመግለጫው ላይ አላካተተውም።
እስራኤል ጥቃቷን በዚህ አጋጣሚ አጠናክራ የምትቀጥል ከሆነ ከፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጋርም በድጋሜ አለመግባባት ውስጥ ትገባለች ተብሏል።
ሃማስ እስራኤል በስምምነቱ መሰረት እንድትንቀሳቀስ ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ጥሪ ማቅረቡንም የሃማስ አስተዳደር ሚዲያ ቢሮ ሀላፊ ኢስማኤል አል -ትህዋብታ አረጋግጠዋል።
ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ያቋቆሙት የሰላም ቦርድ ስራውን እንዲሰራ በር ተከፍቷል ቢባልም እስራኤል ጥያቄ እያነሳች በማንሳት ላይ ናት።
የእስራኤሉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ሳዓር የሃማስን መግለጫም ውድቅ አድርገውታል።
ሀማስ የተቋቋመው ኮሚቴ ወደ ስራ እንዲገባ በር የከፈተው ትጥቅ ላለመፍታት መንገድ ለማፈላለግ ነው ብለዋል ሚኒስትሩ።
ሃማስ ጋዛን ከፈረንጆቹ 2007 አንስቶ እያስተዳደረ እንደሚገኝ ይታወቃል።
ዘገባው የሲ ኤን ኤን እና ቢ ቢ ሲ ነው።
@zena meazen | 1 805 |
| 3 | በደቡብ አፍሪካ በፀረ ስደተኞች ተቃውሞ ሁለት ዜጎቿ መገደላቸውን ናይጄሪያ አስታወቀች
👉 ናይጄሪያ በዜጎቿ ላይ ለደረሰው ኪሳራ አስልታ ካሳ እንደምትቀበል ዝታለች
ናይጄሪያ፣ "የውጭ ዜጎች ያለ አግባብ ኢላማ እየተደረጉ ባለቡት በዚህ ወቅት" በደቡብ አፍሪካ ሁለት ዜጎቿ መገደላቸውን ይፋ አድርጋለች። የናይጄሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ፣ ኤሜካ ቻርለስ ኢሮግቡ ሰኔ 28 ቀን በፖሊስ መኮንኖች "አስፈሪ የምርመራ ዘዴዎችን በመጠቀም" እንደተገደለ ገልፀዋል። ማንነታቸው ያልታወቁ አጥቂዎች ደግሞ የሱቁ ባለቤት የሆነውን ሙሳ ዩናና ጆን በተመሳሳይ ቀን እንደገደሉት ገልጿል።
የደቡብ አፍሪካ ዋና ከተማ ፕሪቶሪያ ባለስልጣናት እስካሁን ምንም አይነት አስተያየት በጉዳዩ ላይ አልሰጡም። የናይጄሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እንደገለጸው ክስተቶቹ ያጋጠመው በደቡብ አፍሪካ ውስጥ ከሌሎች የአፍሪካ አገራት የመጡ ወደ 25,000 የሚጠጉ ዜጎች በስደተኛ ጠል እንቅስቃሴ ወደ አገራቸው እንዲመለሱ ምክንያት ሆኗል። በደቡብ አፍሪካ የሚገኙ ተቃዋሚዎች መንግስት ህገወጥ ስደትን ለመግታት የበለጠ ጥረት እንዲያደርግ አሳስበዋል።
የውጭ ዜጎች ስራችንን እየወሰዱ እና ከህዝብ አገልግሎቶች ፍትሃዊ ባልሆነ መንገድ እየተጠቀሙ ነው ብለዋል።ናይጄሪያ ከደቡብ አፍሪካ ለወጡ ዜጎቿ ካሳ እንደምትጠይቅ ገልጻለች፣ አቡጃ ከናይጄሪያውያን የተዘረፉ የንግድ ድርጅቶችና ንብረቶች መመዝገብ መጀመሯን አክላለች። | 2 068 |
| 4 | بدون متن... | 1 |
| 5 | ሲኖትራክ ከባጃጅ ጋር በመጋጨታቸው የሰባት ሰዎች ሕይወት አለፈ
በባጃጁ ከነበሩት ስምንት ሰዎች ሰባቱ ሲሞቱ ውስጡ የነበረች ህፃን ብቻ ምንም ጉዳት ሳይደርስባት ተርፍለች
በአዓዊ ብሔረሠብ አስተዳደር ዞን ባንጃ ወረዳ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የሰባት ሰዎች ሕይወት ሲልፍ አደጋው የደረሰው ሲኖትራክና ከባለ ሶስት እግር ባጃጅ በመጋጨታቸው መሆኑን የወረዳው ፖሊስ አስታውቋል።
የባንጃ ወረዳ ፖሊስ ፅህፈት ቤት ኃላፊ ዋና ኢንስፔክተር የሻንበል ገበየሁ እንደገለፁት ሰኔ 27 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ ስምንት ሰዓት ላይ ስምንት ሰዎችን አሳፍሮ ከቅዳ ማጃ ከተማ ወደ አስኩና በመጓዝ ላይ የነበረ ባለ ሶስት እግር ተሽከርካሪ ባጃጅ ከእንጅባራ ከተማ ወደ ቅዳ ባንጃ ሲጓዝ ከነበረ ሲኖ ትራክ ጋር በመጋጨቱ አደጋው አጋጥማል ብለዋል።
የባለ ሶስት እግር አሽከርካሪ ውስጥ የነበሩ ሰባት ሰዎች ሕይወታቸውን ያጡ ሲሆን አንዲት ሕፃን በአስገራሚ ሁኔታ ከዚሕ አደጋ ምንም ሳትሆን መትረፏ ተገልጿል።
በዚህ አደጋ አምስት ሴቶችና ሁለት ወንዶች ሕይወታቸውን ያጡ ሲሆን መንገድ ላይ የነበሩ ሁለት እግረኞች ከባድ የአካል ጉዳት ደርሶባቸው ወደ ባንጃ ወረዳ ጤና ጣቢያ ተልከው ሕክምና ላይ እንዳሉ ዋና ኢንስፔክተር የሻምበል ገበየሁ ጨምረው ገልፀዋል።
#zena@Zena_Maezen | 2 283 |
| 6 | ትምህርት መስከረም 5 ይጀመራል!
የትምህርት ሚኒስቴር በመላው ሀገሪቱ ወጥነት ያለው የማስተማር ሂደት እንዲኖር ለማስቻል ያዘጋጀውን የ2019 ዓ.ም አጠቃላይ የትምህርት ዘመን ዓመታዊ የጊዜ ሰሌዳ (ካላንደር) ለክልሎች እና ለከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮዎች አስተላልፏል።
በወጣው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት፦
- ከነሐሴ 26 እስከ ጳጉሜ 5 ቀን 2018 ዓ.ም ይከናወናል።
- መስከረም 5 ቀን 2019 ዓ.ም በይፋ ትምህርት ይጀምራል።
@zena_maezen
@zena_maezen | 4 178 |
| 7 | በአማራ ክልል ባለፉት 11 ወራት ከ69 ሺህ በላይ የጋብቻ ምዝገባ ተከናወነ
ያልተመዘገበ ጋብቻ በተለይም በሴቶችና በህፃናት መብት ላይ የህግ ችግሮችን ሊያስከትል ይችላል።በመሆኑም ሁሉም ጥንዶች ጋብቻቸውን በህጋዊ መንገድ እንዲያስመዘግቡ የግንዛቤ ማስጨበጫዎችን ሲሰጥ መቆየቱን የአማራ ክልል ሲቪል እና ምዝገባ አገልግሎት አስታውቋል ።
በአገልግሎቱ የእቅድና በጀት ክትትልና ግምገማ ዳይሬክቶሬት አቶ ዋለ ቅዱስ ከብስራት ሬዲዮ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደተናገሩት በክልሉ ባለፉት 11 ወራት 99 ሺህ 670 የጋብቻ ምዝገባ ለማከናወን ታቅዶ ነበር።
በዚህም የዕቅዱን 70 በመቶ ማሳካት መቻሉን ተናግረው በወቅታዊ ፣በዘገየ እና የጊዜ ገደቡ ባለፈ ምዝገባ ከ69 ሺህ በላይ ጋብቻዎችን መመዝገብ መቻሉን አስረድተዋል።ህጋዊ የጋብቻ ምዝገባ በተለይም በውርስ ፣በንብረት ክፍፍል ፣በልጆች መብትና በሌሎች የፍትሀ ብሄር ጉዳዮች ላይ የሚከሰቱ አለመግባባቶችን ለመቀነስ ጉልህ ሚና እንደሚጫወት አቶ ዋለ ጨምረው ለ ሚዳችን ተናግረዋል።
| 3 405 |
| 8 | በአዲስ አበባ ከተማ የደንብ መተላለፍ በ81.3 በመቶ ቀንሷል ተባለ
የአዲስ አበባ ከተማ የደንብ ማስከበር ባለስልጣን የ2018 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈፃፀም ግምገማን አከናውኗል።
ተቋሙ በቴክኖሎጂ አጠቃቀም፣ በሕግ ማስከበር፣ በተቋም ግንባታ እና በሰው ኃይል አቅም ማሳደግ ረገድ ከፍተኛ ርቀት መጓዙን
የባለስልጣኑ የኮሚኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ የምስራች ግርማ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።
ከዚህ ቀደም በቀን ለ12 ሰዓታት ብቻ አገልግሎት ይሰጥ የነበረው የ9995 የጥሪ መስመርን ወደ ዲጂታል በመቀየር በአሁኑ ወቅት በአምስት ቋንቋዎች የ24 ሰዓት ሙሉ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል ብለዋል።
በቀን እስከ 300 የሚደርሱ ጥቆማዎችን በመቀበል ከሕዝብ በሚገኝ መረጃ መሰረት ውጤት እየተመዘገበ ይገኛል። በኮሪደር ልማት የተሰሩ መሰረተ ልማቶችን ከመጠበቅ አንፃር ተቋሙ የተለያዪ ስራዎችን እየሰራ እንደሚገኝ ገልፀው ፤ ከመሬት አስተዳደር ጋር በተያያዘ ወደ መሬት ባንክ የገቡ መሬቶችን ሙሉ በሙሉ ማስከበር ተችሏል ሲሉ አስረድተዋል ።
ከ9ኙ የደንብ ጥሰቶች ከጎዳና ንግድ፣ ከደረቅና ፈሳሽ ቆሻሻ አወጋገድ፣ ከሕገ-ወጥ ማስታወቂያ እና ከሌሎች ጉዳዮች ጋር በተያያዘ በርካታ ስራዎችን ማከናወን ተችሏል።በዚህም ካለፈው ዓመት ጋር ሲነፃፀር በ81.3 በመቶ ብልጫ ያለው ውጤት መመዝገቡን አቶ የምስራች ግርማ ጨምረው ለጣቢያችን ገልፀዋል። | 2 973 |
| 9 | በአሜሪካ ቁጥጥር ስር ውላ ከነበረች የነዳጅ ጫኝ መርከብ ላይ የተገኙ 22 የኢራን የባህር ላይ ሰራተኞች በፓኪስታን ለሚገኘው የኢራን ቆንስላ ተመላሽ ተደርገዋል።
@zena_maezen
@zena_maezen | 4 905 |
| 10 | ከሆርሙዝ ባህረ ሰላጤ 115 መርከቦችና 2,500 መርከበኞች በሰላም ወጡ
በአሜሪካ እና ኢራን ጦርነት ምክንያት ቀጠናው ውስጥ ተዘግቶባቸው ከነበሩት መካከል 115 መርከቦችና 2,500 መርከበኞች ባለፉት ሶስት ቀናት ተኩል ውስጥ በሰላም ወጥተዋል።
የተባበሩት መንግሥታት የባሕር ላይ አካል (IMO) ዋና ጸሐፊ አርሴኒዮ ዶሚንጌዝ በኦማን ባሕረ ሰላጤ በደረሰ ጥቃት ሳቢያ ቀሪዎቹን 600 መርከቦች የማስወጣቱን ሥራ ለጊዜው ማቆማቸውን ገልጸዋል።
መርከቦቹ የተለመደውን መስመር የማይጠቀሙት በተቀበሩ የባሕር ውስጥ ፈንጂዎች ምክንያት ሲሆን፤ በሰላም ስምምነቱ መሠረት ኢራን ፈንጂዎቹን በ30 ቀናት ውስጥ ለማንሳት ቃል ገብታለች።
@zena_maezen
@zena_maezen | 3 978 |
| 11 | በሌጎስ ናይጄሪያ ሕንጻ ተደርምሶ የዘጠኝ ሰዎች ሕይወት አለፈ
በናይጄሪያ ሌጎስ ከተማ ባለ ሶስት ፎቅ መኖሪያና የንግድ ሕንጻ በመደርመሱ የሁለት ዓመት ሕፃንን ጨምሮ የዘጠኝ ሰዎች ሕይወት ሲያልፍ፥ 27 ሰዎች ደግሞ በተለያየ ደረጃ ጉዳት ደርሶባቸዋል።
የአደጋው መንስኤ በምርመራ ላይ ቢሆንም፤ በከተማዋ ጥራት የሌላቸው የግንባታ ቁሳቁሶች አጠቃቀምና የቁጥጥር መላላት ለተደጋጋሚ የሕንጻ መደርመስ አደጋዎች በምክንያትነት ይጠቀሳሉ። የሌጎስ ገዥ ባባጂዴ ሳንዎ-ኦሉ በአካባቢው ባሉ ሌሎች ሕንጻዎች ላይ አስቸኳይ የደህንነት ፍተሻ እንዲደረግ አዘዋል።
@zena_maezen
@zena_maezen | 3 390 |
| 12 | ኢራን በሆርሙዝ ሰርጥ የሰላም ስምምነቱን በመጣስ በድሮን ጥቃት ፈፅማለች ሲሉ ትራምፕ ገለፁ
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ትላንት ይፋ እንዳደረጉት፣ የኢራን ጦር ኃይሎች በስትራቴጂካዊቷ የሆርሙዝ ሰርጥ በሚያልፉ የንግድ መርከቦች ላይ ቢያንስ 4 የአጥፊ ድሮን ጥቃቶችን ሰንዝረዋል።
ከእነዚህም መካከል አንዱ የካሚካዜ ድሮን የአንድን የጭነት መርከብ ወለል መምታቱንና ጉዳት ማድረሱን ገልጸዋል።
ትራምፕ በፅሁፋቸው “ይህ የሰላም ስምምነቱን በግልፅ የጣሰ ሞኝነት ነው” ሲሉ ድርጊቱን አውግዘዋል።
አሜሪካ ቀሪዎቹን ሦስት ድሮኖች መትታ የጣለች ሲሆን፣ ጥቃት የደረሰባት መርከብ ግን ጉዞዋን ቀጥላለች።
@zena_maezen
@zena_maezen | 2 846 |
| 13 | ህወሓት የሂዩማን ራይትስ ዎችን “የአስገዳጅ
ውትድርና” ወቀሳ ሙሉ በሙሉ ውድቅ አደረገ
የዓለም አቀፉ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ሂዩማን ራይትስ ዎች፣ ህወሓት ያወጣውንና ዜጎችን በጦርነት እንዲካፈሉ ያስገድዳል የተባለውን አዲስ አዋጅ በአስቸኳይ እንዲሽር በቅርቡ ባወጣው መግለጫ ጠይቋል። ተቋሙ አዲሱን አዋጅ የኤርትራ መንግስት ወጣቶችን ለአስገዳጅ ወታደራዊ ምልመላ ከሚጠቀምበት ሕግ ጋር ያመሳሰለው ሲሆን፤ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ላይ የተደረገውን ለውጥ ተከትሎ የወጣው ይህ ድንጋጌ የሲቪል ዜጎችን መብት የሚጋፋና ሕጉን የሚቃወሙትን የሚያስቀጣ ነው ሲል ወቅሷል።
በጉዳዩ ላይ ምላሽ የሰጡት የህወሓት ቃል አቀባይ አቶ ሚካኤል አስገዶም ግን የዓለም አቀፉን ተቋም መግለጫ “መሬት ላይ ያለውን እውነታ ያላገናዘበና የተጋነነ” በማለት ሙሉ በሙሉ ውድቅ አድርገውታል። ትግራይ የህልውና አደጋ የተጋረጠባት ብሔር መሆኗን የገለጹት ቃል አቀባዩ፣ የሚደረገው ዝግጅት ሊመጣ የሚችለውን አደጋ ለመቀልበስ እንጂ “ሰው ለመግደልና ለማፈን” እንዳልሆነ ተከላክለዋል። አዲሱ አዋጅ በክልሉ ሕጋዊነትን ለማስፈን የወጣ መሆኑን የገለጹት ባለስልጣናቱ፣ የቀረበባቸውን ከፍተኛ የወቀሳ ትችት አጣጥለውታል።
@zena_maezen
@zena_maezen | 2 770 |
| 14 | አሜሪካ ኢራን ላይ “ከባድ የአየር ጥቃት አደረስኩ” አለች።
የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ (ሴንት ኮም) ኢራን በሆርሙዝ ሰርጥ የአራት ሰው አልባ አውሮፕላን (ድሮን ) ጥቃት ማድረሷን ተከትሎ አፀፋዊ ምላሽ በሆርሙዝ ሰርጥ እና በወሳኝ አካባቢዎች መስጠቱን አሳውቋል።
ፎክስ ኒውስ እንዳስነበበው ዋሽንግተን ስድስት የጦር አውሮፕላኖችን በመጠቀም አራት ዒላማዎችን መትቻለሁ ብላለች።በሆርሙዝ ዳርቻ ባሉ አካባቢዎች እና በገሽም ደሴት ላይ ጥቃት ደርሷል።
የኢራን ሚዲያዊች በሲሪክ አካባቢም ከፍተኛ ፍንዳታ መሰማቱን እየዘገቡ ይገኛል።የራዳር እና ሚሳዔል ስርዓቶች ዒላማ መሆናቸውም ተሰምቷል።
ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በትሩዝ ሶሻል ሚዲያቸው ላይ ኢራን በንግድ መርከብ ላይ ያደረሰችው ጥቃት ምላሽ ሊሰጠው እንደሚችል ቀደም ሲል ይፋ ማድረጋቸው የሚታወስ ነው።
“ኢራን የሰላም ስምምነት ፈርማለች፤እሱን እናከብራለን” ያሉት ምክትል ፕሬዚዳንት ጄዲ ቫንስ “ጥቃትን በጥቃት እንመልሳለን” ብለዋል።
የኢራን አብዮታዊ ዘብ ኃይል (IRGC) የአሜሪካን ጥቃት አውግዞ ሁል ጊዜም ቢሆን ዋሽንግተን ቃሏን ታጥፋለች በሚል ከሷል።የኢራን አብዮታዊ ዘብ የአሜሪካን ዒላማዎች በመካከለኛው ምስራቅ መምታቱንም አሳውቋል።
ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት ሰዓት ድረስ የደረሰው ጉዳትም ሆነ ፤ኢራን ስለሰጠችው ምላሽ ዝርዝር መረጃ አልተጋራም።ዘገባው የአልጀዚራ እና ሲ ኤን ኤን ነው። | 3 133 |
| 15 | ኢትዮጵያ ወታደራዊ ምርቶቿን ለጎረቤት ሀገራት መሸጥ ጀመረች
ኢትዮጵያ በጸጥታው ዘርፍ የነበራትን የውጭ ጥገኝነት በመቀነስ፣ ቀላልና ከባድ የጦር መሣሪያ ጥይቶችን በሀገር ውስጥ ማምረት ብቻ ሳይሆን ለጎረቤት ሀገራት በመላክ አዲስ የውጭ ምንዛሬ ምንጭ መፍጠር መጀመሯን የመከላከያ ሠራዊት ይፋ አድርጓል። ይህ ታሪካዊ እርምጃ ሀገሪቱ በድንገተኛ የጸጥታ ተግዳሮቶች ጊዜ ሊያጋጥማት የሚችለውን የጥይት አቅርቦት እጥረት ሙሉ በሙሉ የሚቀርፍ ከመሆኑም በላይ፣ ቀደም ሲል ለጦር መሣሪያ ግዥ ይወጣ የነበረውን ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ማዳን አስችሏል። ይህ ስኬት የኢትዮጵያን ወታደራዊ የኢንዱስትሪ አቅም አንድ ደረጃ ከፍ ያደረገ ትልቅ እመርታ ተደርጎ ተወስዷል።
የመከላከያ ሠራዊት ባጋራው መረጃ፤ ከጥይት ምርት ጎን ለጎን፣ መንግሥት የድሮን (UAV) ቴክኖሎጂን በሀገር ውስጥ የማልማትና የመገጣጠም ሥራን በስፋት እየተገበረ ይገኛል። እነዚህ የድሮን ማዕከላት መቋቋማቸው የመከላከያ ሠራዊቱ የሀገሪቱን የአየር ክልል በአስተማማኝ ሁኔታ እንዲቆጣጠር የረዳው ሲሆን፣ ማንኛውንም የጸጥታ ስጋት በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) እና በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በታገዘ መንገድ በፈጣን ሁኔታ ምላሽ ለመስጠት አስችሎታል። በአጠቃላይ ይህ የቴክኖሎጂ ሽግግርና በራስ አቅም የመደራጀት ጉዞ የኢትዮጵያን የጸጥታ መዋቅር ይበልጥ እያዘመነው ይገኛል ተብሏል።
@zena_maezen
@zena_maezen | 2 570 |
| 16 | ማያንማር ከ600 ሚሊዮን ዶላር በላይ የሚያወጡ ህገ-ወጥ እጾችን አቃጠለች
ይህ እርምጃ የተወሰደው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአለም አቀፍ የእፅ አላግባብ መጠቀም እና ህገ-ወጥ ዝውውር መከላከያ ቀንን ምክንያት በማድረግ ነው።
በያንጎን ከተማ ዳርቻ በተካሄደው ስነ-ስርዓት ከ50 ቶን በላይ ሄሮይን፣ ሜታምፌታሚን፣ ኦፒየም እና ሌሎች እጾች በእሳት የተቃጠሉ ሲሆን፥ ይህም በሀገሪቱ ታሪክ ከተከናወኑት ትልልቅ እጽ የማውደም እርምጃዎች አንዱ ነው።
የሀገሪቱ ፀረ-ዕፅ ፖሊስ እንደገለጸው የዘንድሮው እፅ ዋጋ ካለፈው ዓመት በእጥፍ ይበልጣል።
ማያንማር በአለም ላይ ከፍተኛ የእፅ አምራች ከሆኑት ሀገራት አንዷ ስትሆን፥ እ.ኤ.አ. በ2021 ከነበረው የወታደራዊ መፈንቅለ መንግስት በኋላ የተከሰተው የእርስ በእርስ ጦርነት እና አለመረጋጋት ለዕፅ ምርት እና ዝውውር በከፍተኛ ሁኔታ መጨመር ምክንያት መሆኑን ባለሙያዎች ይናገራሉ።
የወታደራዊው መንግስት የታጠቁ ቡድኖችን በእፅ ንግድ ሲከስስ፣ አንዳንድ ጎሳዎች ግን በበኩላቸው በቁጥጥራቸው ስር ባሉ አካባቢዎች የእፅ ማጥፊያ ዘመቻዎችን እያካሄዱ ነው።
@zena_maezen
@zena_maezen | 2 511 |
| 17 | በኮንጎ በኢቦላ ወረርሽኝ የሟቾች ቁጥር 300 ደረሰ
የኢቦላ ወረርሽኝ በኮንጎ መቀስቀሱ በይፋ ከታወጀበት ከሚያዝያ 15/2026 ጀምሮ 304 ሰዎች መሞታቸውንና 1155 ሰዎች መጠቃታቸውን የሀገሪቱ የጤና ሚኒስቴር አስታውቋል።
የህክምና ክትትል እየተደረገላቸው እንደሚገኝ ሚኒስቴሩ ገልጿል። ከ150 በላይ ሰዎች ከበሽታው ማገገማቸው ተመላክቷል።
የአፍሪካ በሽታ መከላከል እና መቆጣጠር ማዕከል (Africa CDC) በበኩሉ ወረርሽኙን ለመግታት 1.4 ቢሊዮን ዶላር ያስፈልጋል ብሏል።
በምሥራቅ ኮንጎ ቡንድቡግዮ ግዛት የተቀሰቀሰው የኢቦላ ወረርሽኝ በአሁኑ ወቅት ኢቱሪ፣ ኖርዝ ኪቩ ሳውዝ ኪቩን ጨምሮ በ34 የሀገሪቱ ግዛቶች መስፋፋቱ ተመላክቷል።
@zena_maezen
@zena_maezen | 2 213 |
| 18 | "ብንወያይ ይሻላል፣ በሂደት ወደ ውይይት መሄድ ያስፈልጋል" - ሉካሽንኮ
የቤላሩስ ፕሬዚዳንት አሌክሳንደር ሉካሽንኮ የሩሲያና ክሬን ጦርነት በስምምነት እንዲቋጭ ጠየቁ። "ሰላማዊ መንገድን እንደ አማራጭ መውሰድ አለበት" ብለዋል።
ሉካሽንኮ "የዩክሬን ባለስልጣናት የሚያናግሩን በጦርነት ከሆነ ሁኔታው አስከፊ ለውጥ ያመጣል" በማለት አስጠንቅቀዋል።
"ሰዎች ብንወያይ ይሻላል፣ በሂደት ወደ ውይይት መሄድ ያስፈልጋል" በማለት ጥሪ አቅርበዋል። ፕሬዚዳንቱ "ከሩሲያ በመቀጠል እኛ ነን ተጋላጭ የምንሆነው" ሲሉ ተናግረዋል።
"ሰላምና ሰላም ብቻ" ያሉት ፕሬዚዳንቱ "ግን ዩክሬን እንዳትጫወት ዋስትና እንፈልጋለን" ብለዋል።
ቤላሩስ በዩክሬን ጦርነት ከሩሲያ ጎን የቆመች ሲሆን በዚህ አቋሟ ከአውሮፓ ህብረት ማዕቀብ ተጥሎባታል።
@zena_maezen
@zena_maezen | 2 473 |
| 19 | Update‼️
በቬንዙዌላው አደጋ የሟቾች ቁጥር 589 መድረሱን የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት አስታወቁ
በቬንዙዌላ በደረሰው የመሬት መንቀጥቀጥ የሞቱ ሰዎች ቁጥር 589 መድረሱን የአገሪቱ ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት ዴልሲ ሮዴሪጌዝ አስታውቀዋል።
ከአካባቢው በወጡ መረጃዎች እንደ ቢቢሲ አይነት ሚዲያዎች በዘገቡት መሰረት የተጎጂዎች ብዛት ከ4 ሺሕ መብለጡ የተገለጸ ሲሆን፣ ፕሬዝዳንት ዴልሲ ሮዴሪጌዝ
ደግሞ 2,980 ሰዎች መጎዳታቸውን አረጋግጠዋል።
አደጋው በደረሰ በ34 ሰዓታት ውስጥ በተደረገው ርብርብ በርካቶችን በሕይወት እያሉ ማትረፍ መቻሉን ተናግረዋል።
ከፍተኛ ጉዳት የደረሰበት በካሬቢያን የባሕር ዳርቻ አካባቢ የሚገኘው የላ ጓይራ ግዛት ሲሆን፣ ዋና ከተማ ካራካስና በሌሎች ግዛቶችም ሕንጻዎች ተደርምሰዋል፤ ቤቶች እንዳልነበሩ ሆነዋል።
ዓለም አቀፍ የእርዳታ ቡድኖች ወደ ደቡባዊ አሜሪካዊቱ ሀገር እየገቡ ነው። ከስዊትዘርላንድ የተላኩ 80 የነፍስ አድን ሠራተኞች እና 18 ቶን ቁሳቁሶች ቬንዙዌላ መድረሳቸው ተነግሯል።
@zena_maezen
@zena_maezen | 2 094 |
| 20 | በአዲስ አበባ የቤት ኪራይ ዋጋን በህግ ለመገደብ አዲስ የጥናት ውይይት ተካሄደ
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤናማ የቤት ኪራይ አሰራርን ለመዘርጋትና በህግ ማዕቀፍ ለመምራት የሚያስችል የግል መኖሪያ ቤት ኪራይ ዋጋ መተመኛ ጥናትን አስመልክቶ የፓናል ውይይት ተካሂዷል።
የቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ ቅድስት ወ/ጊዮርጊስ እንደገለጹት፤ ጥናቱ አከራዩ ወቅቱን ያገናዘበ ፍትሃዊ ገቢ እንዲያገኝ እና ተከራዩ ደግሞ ከገቢው ጋር የተመጣጠነ ኪራይ እንዲከፍል ለማስቻል ነው። ይህ የዋጋ ትመና ጥናት በዘፈቀደ የተሰራ ሳይሆን የነዋሪዎችን የመክፈል አቅም ያገናዘበ በመሆኑ በከተማዋ ያለውን የኑሮ ውድነት በመቀነስ ረገድ ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ፋይዳ ይኖረዋል።
ይህ ለ2019 በጀት ዓመት የተዘጋጀው የገበያ ዋጋ ጥናት ወደ ተግባር ከመሸጋገሩ በፊት፣ ከሚመለከታቸው ተቋማትና ከህዝብ ተወካዮች ጋር የጋራ መግባባት ለመፍጠር መድረኩ መዘጋጀቱ ተገልጿል። ጥናቱ በከተማዋ ላይ ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ ፋይዳዎች እንዳሉት የተገለጸ ሲሆን፣ ህገ-ወጥና ያልተገባ የኪራይ ጭማሪን በማስቀረት የተረጋጋ የቤት ኪራይ ገበያ ለመፍጠር ያለመ እንደሆነ ተጠቁሟል። | 2 239 |
