ru
Feedback
ዜና ማዕዘን - Breaking

ዜና ማዕዘን - Breaking

Открыть в Telegram

እንኳን ወደ ዜና ማዕዘን - Breaking በደህና መጡ በቻናላችን 📌 ፈጣን ሀገራዊ #መረጃዎች 📺 📌 #ዓለም ዓቀፍ መረጃዎች 📢 📌 አዝናኝ እና አስተማሪ መረጃዎች 🔔 📌 ወቅታዊ ጉዳዮች ሁሉንም በአንድ ታገኛላችሁ 📣 #zena_maezen ለሀሳብ አስተያየት (ads) @zena_maezen_bot

Больше

📈 Аналитический обзор Telegram-канала ዜና ማዕዘን - Breaking

Канал ዜና ማዕዘን - Breaking (@zena_maezen) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 68 423 подписчиков, занимая 937 место в категории Музыка и 449 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 68 423 подписчиков.

Согласно последним данным от 17 июня, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило -2 002, а за последние 24 часа — -84, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 3.45%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 2.87% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 2 361 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 1 965 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 14.

📝 Описание и контентная политика

Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
እንኳን ወደ ዜና ማዕዘን - Breaking በደህና መጡ በቻናላችን 📌 ፈጣን ሀገራዊ #መረጃዎች 📺 📌 #ዓለም ዓቀፍ መረጃዎች 📢 📌 አዝናኝ እና አስተማሪ መረጃዎች 🔔 📌 ወቅታዊ ጉዳዮች ሁሉንም በአንድ ታገኛላችሁ 📣 #zena_maezen ለሀሳብ አስተያየት (ads) @zena_maezen_bot

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 18 июня, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Музыка.

68 423
Подписчики
-8424 часа
-4877 дней
-2 00230 день
Архив постов
አሜሪካና ኢራን ጦርነቱን ለማቆም የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ የመካከለኛው ምስራቅን ቀውስ ሲያባብስ የነበረውን ጦርነት ለማቆም የሚያስችል ባለ 14 ነጥብ የመግባቢያ ስምምነት በአሜሪካው ፕሬዝዳንት
አሜሪካና ኢራን ጦርነቱን ለማቆም የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ የመካከለኛው ምስራቅን ቀውስ ሲያባብስ የነበረውን ጦርነት ለማቆም የሚያስችል ባለ 14 ነጥብ የመግባቢያ ስምምነት በአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ እና በኢራን ፕሬዝዳንት መካከል በዲጂታል ፊርማ በይፋ ጸድቋል። ይህንን ተከትሎም ላለፉት ወራት ተዘግቶ የነበረውና ለአለም አቀፍ የነዳጅ ንግድ ወሳኝ የሆነው የሆርሙዝ ባህረ ሰላጤ ለ60 ቀናት ያህል ምንም አይነት የይለፍ ክፍያ ሳይጠየቅበት ለንግድ መርከቦች ክፍት እንዲሆን ተወስኗል። ስምምነቱ ይፋ መደረጉን ተከትሎም የብሬንት ድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ የ1 በመቶ ቅናሽ ያሳየ ሲሆን፣ ግዙፍ የነዳጅ መርከቦችም የሆርሙዝ ሰርጥን ማቋረጥ ጀምረዋል። በታሪካዊው ስምምነት መሰረት አሜሪካ በኢራን ላይ የጣለቻቸውን "ማንኛውንም አይነት ማዕቀቦች" ሙሉ በሙሉ እንደምታነሳ የተገለጸ ሲሆን፣ ለኢራን መልሶ ግንባታ የሚውል የ300 ቢሊዮን ዶላር እቅድ ተይዟል። በተጨማሪም አሜሪካ የኢራንን የነዳጅ ኤክስፖርት እና የባንክ አገልግሎቶችን የሚገድቡ ማዕቀቦች ላይ ወዲያውኑ ጊዜያዊ እፎይታ ለመስጠት ተስማምታለች። በምላሹም ኢራን ያከማቸችውን የበለጸገ ዩራኒየም በአለም አቀፉ የአቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ (IAEA) ቁጥጥር ስር ሆና የማሟሟት ስራ ለመስራት ፈቃደኝነቷን አረጋግጣለች። @zena_maezen @zena_maezen

"በምድር ላይ ከኖሩት ሁሉ እጅግ ኃያሉ ሰው እኔ ነኝ’" ትራምፕ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ትላንት እኩለ ሌሊት ላይ በትሩዝ ሶሻል የማኅበራዊ ገጻቸው ባስተላለፉት ተከታታይ መልዕክቶች፣ "በዚህች ፕላ
"በምድር ላይ ከኖሩት ሁሉ እጅግ ኃያሉ ሰው እኔ ነኝ’" ትራምፕ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ትላንት እኩለ ሌሊት ላይ በትሩዝ ሶሻል የማኅበራዊ ገጻቸው ባስተላለፉት ተከታታይ መልዕክቶች፣ "በዚህች ፕላኔት ላይ ከተራመዱት ሰዎች ሁሉ እጅግ ኃያሉ ሰው እኔ ነኝ" የሚል ይዘት ያለውን ጽሑፍ በማጋራት ከፍተኛ መነጋገሪያ ሆነዋል። ትራምፕ ያጋሩት ጽሑፍ "የፕሬዝዳንታዊ ታሪክ ምሁር ዴቭ ኪንግ" በተባሉ ሰው የተጻፈ ሲሆን፣ ፕሬዝዳንቱን እንደ ታላቁ እስክንድር፣ ጄንጊስ ካን እና ናፖሊዮን ካሉ ታዋቂ የዓለም ታሪክ መሪዎች ጋር በማነጻጸር ከሁሉም እንደሚበልጡ ይገልጻል። ይህ መግለጫ ይፋ የሆነው ትራምፕ ረቡዕ ዕለት ከአሜሪካ ጋር ለረጅም ጊዜ የዘለቀውን የኢራን ጦርነት ለማቆም የሚያስችለውን ስምምነት በፈረሙ ማግስት ነው። ምንም እንኳን ይህ የሰላም ስምምነት በብዙ ወገኖች ዘንድ ከፍተኛ ትችት ቢሰነዘርበትም፣ ትራምፕ ግን እሳቸው ይህንን ስምምነት ባያደርጉ ኖሮ ዓለም "ከፍተኛ የኢኮኖሚ ቀውስ" ውስጥ ትወድቅ እንደነበር በመግለጽ ውሳኔያቸውን ተከላክለዋል። ጽሑፉን ያዘጋጁት የታሪክ ምሁሩ ዴቭ ኪንግ፣ ትራምፕን እንደ አቲላ ዘ ሁን (Attila the Hun) እና ዊሊያም ዘ ኮንከረር ካሉ ታሪካዊ ኃያላን መሪዎች ጋር ጭምር በማወዳደር የእሳቸው ተፅዕኖ የላቀ እንደሆነ ይሞግታሉ። ይህ የትራምፕ የሌሊት ማኅበራዊ ሚዲያ ፖስት በአሜሪካ ፖለቲካና በዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙኃን ዘንድ አሁንም ከፍተኛ ክርክርና መነጋገሪያነቱን ቀጥሏል። @zena_maezen @zena_maezen

የኢሎን ማስክ ‘Grok AI’ በኢራን ጦርነት ለታለመ ጥቃት አገልግሎት ላይ መዋሉ ተገለጸ የአሜሪካ የፍትህ ሚኒስቴር ባወጣው ህጋዊ ሰነድ መሰረት፣ የኢሎን ማስክ የሰው ሰራሽ አስተዋፅዖ ቴክኖሎጂ የሆ
የኢሎን ማስክ ‘Grok AI’ በኢራን ጦርነት ለታለመ ጥቃት አገልግሎት ላይ መዋሉ ተገለጸ የአሜሪካ የፍትህ ሚኒስቴር ባወጣው ህጋዊ ሰነድ መሰረት፣ የኢሎን ማስክ የሰው ሰራሽ አስተዋፅዖ ቴክኖሎጂ የሆነው ‘Grok’ በኢራን ላይ ለተሰነዘሩ ወታደራዊ ጥቃቶች ማገልገሉ ተረጋግጧል። ይሄ ይፋ የሆነው የ xAI ኩባንያ የዳታ ማዕከል የሚጠቀማቸውን የጋዝ ተርባይኖች አስመልክቶ በቀረበበት የአካባቢ ብክለት ክስ ራሱን ለመከላከል ባቀረበው ሰነድ ላይ ነው። የሀገሪቱ የፍትህ ሚኒስቴር የዳታ ማዕከሉ የኃይል አቅርቦት ከተቋረጠ የአሜሪካ ብሔራዊ ደህንነት አደጋ ላይ እንደሚወድቅ በመግለጽ የፍርድ ቤት ክሱን ተከላክሏል። በፔንታጎን የ AI ኃላፊ በሆኑት በካሜሮን ስታንሊ የተሰጠው በመሀላ የተደገፈ ምስክርነት እንደሚያሳየው፣ ‘Grok’ የተሰኘው የቴክኖሎጂ መተግበሪያ ‘Project Maven’ በተባለው የአሜሪካ ጦር የታለመ ጥቃት ማስተገበሪያ ፕሮግራም ውስጥ በመሳተፍ ላይ ይገኛል። በጥቃቱም ወቅት “Operation Epic Fury” በተባለው ዘመቻ ውስጥ ‘Grok Gov Model’ በ96 ሰዓታት ውስጥ ብቻ 2,000 በሚሆኑ የተለያዩ የኢራን ኢላማዎች ላይ ትልቅ እገዛ ማድረጉ ተገልጿል። ቀደም ሲል አሜሪካ ትጠቀምበት የነበረው ‘Claude’ የተሰኘው የ AI ሞዴል ሙሉ በሙሉ አውቶማቲክ ለሆኑ ወታደራዊ ጥቃቶች እንዳይሰማራ በመከልከሉ ምክንያት መንግስት ውሉን አቋርጦ ወደ ማስክ ቴክኖሎጂ ፊቱን አዙሯል። @zena_maezen @zena_maezen

ግቤን ማሳካት አልቻልኩም ያለው የኢኳቶሪያል ጊኒ መንግስት ፈረሰ ጠቅላይ ሚኒስትር ኦሳ ንሱ ንስዋ የመልቀቂያ ደብዳቤ ማስገባታቸው ተገልጿል። ንስዋ በ2024 ነበር የኢኳቶሪያል ጊኒ ጠቅላይ ሚኒስትር
ግቤን ማሳካት አልቻልኩም ያለው  የኢኳቶሪያል ጊኒ መንግስት ፈረሰ ጠቅላይ ሚኒስትር ኦሳ ንሱ ንስዋ የመልቀቂያ ደብዳቤ ማስገባታቸው ተገልጿል። ንስዋ በ2024 ነበር የኢኳቶሪያል ጊኒ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው የተሾሙት። ምክትል ፕሬዚዳንት ቴዎድሮ ኦብያንግ ንጉየማ ምባሶጎ መንግስት ከያዘው እቅድ 10% ብቻ ማሳካቱን ገልጸዋል። የወቅቱ መንግስት በሙስና መዘፈቅ ለመፍረሱ ምክንያት መሆኑን ጠቁመዋል። ከ1979 ጀምሮ ሀገሪቱን እያስተዳደሩ ያሉት ፕሬዚዳንት ቴዎድሮ ኦብያንግ ከሁለት አመት በፊት በተመሰረተው መንግስት ደስተኛ አለመሆናቸውን በተደጋጋሚ ሲገልጹ ነበር። በአንፃሩ ፕሬዝዳንቱ ቤተሰባዊ ስርዓት በመዘርጋት እየተወቀሱ ይገኛሉ።  @zena_maezen @zena_maezen

ፕሬዚዳንት ሲልቫ ፕሬዚዳንት ትራምፕን አስጠነቀቁ የብራዚል ፕሬዚዳንት ሉላዳ ሲልቫ የአሜሪካውያን አቻቸውን በሀገሪቱ የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ እንዳይገቡ አስጠንቅቀዋል። ብራዚል በመጪው ጥቅምት ወር በምታካ
ፕሬዚዳንት ሲልቫ ፕሬዚዳንት ትራምፕን አስጠነቀቁ የብራዚል ፕሬዚዳንት ሉላዳ ሲልቫ የአሜሪካውያን አቻቸውን በሀገሪቱ የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ እንዳይገቡ አስጠንቅቀዋል። ብራዚል በመጪው ጥቅምት ወር በምታካሂደው ሀገራዊ ምርጫ ፕሬዚዳንት ትራምፕ ለተፎካካሪ ፓርቲዎች በድብቅ ድጋፍ ለማድረግ እያቀዱ መሆኑ ከተገለፀ በኋላ ነው ሲልቫ ማስጠንቀቂያ የሰጡት። ሲልቫ አሜሪካ የቀድሞውን የብራዚል ፕሬዚዳንት ቦልሴናሮን ወደ ስልጣን ለመመለስ ጥረት እያደረገች ነው ሲሉም ወንጅለዋል። ፕሬዚዳንት ትራምፕ ማዕቀቡን በጣሉበት ወቅት ብራዚልን "በፖለቲካ አደገኛ ናት" ብለዋል። @zena_maezen @zena_maezen

ኮሜዲያኑ አልታሰረም ኮሜዲያን ምናለ ያረጋል፣ በዚህ ሳምንት በፀጥታ ኃይሎች ቁጥጥር ስር መዋሉን የተለያዩ የመረጃ ምንጮች ዘግበዋል። ነገር ግን ኮሜዲያን ምናለ ያረጋል ታስሯል ተብሎ የሚሰራጨው መረጃ
ኮሜዲያኑ አልታሰረም ኮሜዲያን ምናለ ያረጋል፣ በዚህ ሳምንት በፀጥታ ኃይሎች ቁጥጥር ስር መዋሉን የተለያዩ የመረጃ ምንጮች ዘግበዋል። ነገር ግን ኮሜዲያን ምናለ ያረጋል ታስሯል ተብሎ የሚሰራጨው መረጃ ፍጹም የተሳሳተና ከእውነት የራቀ እንደሆነ ኖሮ ሬድዮ ሰምቷል። ኮሜዲያን ምናለ በአሁኑ ሰዓት በሀገር ውስጥም አይገኝም ተብሏል። ምናለ ያረጋል የሕዝብን የዕለት ተዕለት ኑሮ፣ አስተዳደራዊ ክፍተቶችን እና የፖለቲካ ውጥረቶችን በሳቅ እና በቁምነገር አዋዝቶ በማቅረብ በብዙዎች ዘንድ ተወዳጅነትን ያገኘ ኮሜዲያን ነው። @zena_maezen @zena_maezen

በ"ፊንቴክ" ኢንቨስትመንት ማጭበርበር የተጠረጠሩ አርቲስቶች እና ቲክቶከሮች ዛሬ ፍ/ቤት ቀረ ሰኔ 11/2018 ፍርድ ቤት ቀረቡ በ"ፊንቴክ" ኢንቨስትመንት ማጭበርበር የተጠረጠሩ አርቲስቶች እና ቲክቶ
በ"ፊንቴክ" ኢንቨስትመንት ማጭበርበር የተጠረጠሩ አርቲስቶች እና ቲክቶከሮች ዛሬ ፍ/ቤት ቀረ ሰኔ 11/2018 ፍርድ ቤት ቀረቡ በ"ፊንቴክ" ኢንቨስትመንት ማጭበርበር የተጠረጠሩ አርቲስቶች እና ቲክቶከሮች ዛሬ ፍ/ቤት ቀረቡ። በ"ፊንቴክ" ኢንቨስትመንት ሽፋን በተፈጸመ መጠነ ሰፊ የማጭበርበር ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር የዋሉ ታዋቂ አርቲስቶች እና ቲክቶከሮች፣ ከ5 ተኛ ተከሳሽ በስተቀር የዋስትና መብታቸው ተከብሮ በውጪ ሆነው ጉዳያቸውን እንዲከታተሉ መወሰኑ ይታወሳል። ዛሬ ሰኔ 11/2018 ዓ.ም የዋስትና መብቱ ተከልክሎ በማረሚያቤት ሆኖ ጉዳዩን የሚከታተለው አምስተኛ ተከሳሽ መንሱር ጀማልን ጨምሮ ሁሉም ተጠርጣሪዎች ፍ/ቤት ቀርበዋል። ዛሬ በዋለው ችሎት ተከሳሾቹ በጠበቆቻቸው አማካኝነት የክስ መቃወሚያ አቅርበዋል። የ1ኛ ተከሳሽ 5 ገፅ ሌሎች ደግሞ እያንዳንዳቸው 6 ገፅ የክስ መቃወሚያ የደረሰው አቃቢ ህግ ዛሬ ምላሽ መስጠት እንደማይችል አሳውቋል። በዚህ መሠረት የፌደራሉ ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ ችሎት አቃቢ ህግ የክስ መቃወሚያውን ተመልክቶ ምላሽ ለመስጠት ለሐምሌ 8/ 2018 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጥቷል። @zena_maezen @zena_maezen

አሜሪካ የህዋሓት ሰዎች ላይ ማዕቀብ ጣለች የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ፣ በሰሜን ኢትዮጵያ እንዲሁም በመላ ቀጠና ያለውን ሰላምና ደህንነት አደጋ ላይ ጥለዋል ባሏቸው የህዝባዊ ወያኔ
አሜሪካ የህዋሓት ሰዎች ላይ ማዕቀብ ጣለች የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ፣ በሰሜን ኢትዮጵያ እንዲሁም በመላ ቀጠና ያለውን ሰላምና ደህንነት አደጋ ላይ ጥለዋል ባሏቸው የህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) አባላት እና የቅርብ ቤተሰቦቻቸው ላይ የቪዛ ገደብ መጣሉን አስታውቀዋል። ውሳኔው የተላለፈው በስደተኞችና ዜግነት አዋጅ (Immigration and Nationality Act) አንቀጽ 212(a)(3)(C) በተሰጣቸው ስልጣን መሰረት መሆኑን የገለጹት ሚኒስትሩ፤ ማዕቀቡ በትግራይ ክልል ያለውን ቀውስ ለመፍታት የሚደረገውን ጥረት በሚያስተጓጉሉ አመራሮች ላይ ያነጣጠረ መሆኑን ገልጸዋል። የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ፣ በህወኃት አመራሮችና በኢትዮጵያ መንግሥት መካከል እየተባባሰ የመጣው ውጥረት የሰሜን ኢትዮጵያን ሰላም ዳግም ስጋት ላይ መጣሉን ጠቅሷል። በተለይም በዚህ ዓመት መጀመሪያ ላይ በትግራይ የፀጥታ ኃይሎች (TSF) እና በኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት (ENDF) መካከል የተከሰተው ቀጥተኛ ግጭት የፕሪቶሪያውን የሰላም ስምምነት ተከትሎ የተገኘውን አንጻራዊ መረጋጋት የሚፈታተን መሆኑ አመልክቷል። አሜሪካ በሰላምና በክብር መኖር የሚፈልገውን የትግራይን ጨምሮ መላውን የኢትዮጵያ ሕዝብ መደገፏን እንደምትቀጥል የገለጸው መግለጫው፤ በክልሉ ሰላምና መረጋጋትን በሚያናጉ አካላት ላይ ተጠያቂነትን ለማስፈን ያሉትን አማራጮች ሁሉ ጥቅም ላይ እንደምታውል አስታውቃለች። የቪዛ ማዕቀብ የተጣለባቸው የህወሓት (TPLF) አመራሮች እና ቤተሰቦቻቸው ስም በይፋ አልተገለጸም። @zena_maezen @zena_maezen

የኢራኑ ፕሬዝዳንት መስዑድ ፔዜሽኪያን ከኢፌዴሪ/አሜሪካ ጋር የተደረገውን ባለ 14 ነጥብ የመግባቢያ ስምምነት (MoU) ሙሉ ሰነድ ይፋ ያደረጉ ሲሆን፥ ሰነዱ ላይ የፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ፊርማ ይ
+1
የኢራኑ ፕሬዝዳንት መስዑድ ፔዜሽኪያን ከኢፌዴሪ/አሜሪካ ጋር የተደረገውን ባለ 14 ነጥብ የመግባቢያ ስምምነት (MoU) ሙሉ ሰነድ ይፋ ያደረጉ ሲሆን፥ ሰነዱ ላይ የፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ፊርማ ይታያል። ይህ ‘የኢስላማባድ የመግባቢያ ስምምነት’ (Islamabad Memorandum of Understanding) የተሰኘው ሰነድ በአሜሪካ እና በኢራን መካከል ያለውን ግጭት በአስቸኳይ ለማቆም፣ የሆርሙዝ የባህር ወሽመጥን ለመክፈት እና ቀጣይ የሰላም ድርድሮችን ለማካሄድ የተደረሰ ታሪካዊ ስምምነት ነው። @zena_maezen @zena_maezen

በዓለም አቀፍ ደረጃ በትምህርት ተቋማት ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶች በከፍተኛ ሁኔታ በጨመሩበት ወቅት ኢትዮጵያ ከፍተኛ ጥቃት ከተመዘገበባቸው አገራት ተርታ ተመደበች ባለፉት ሁለት ዓመታት ውስጥ በትምህርት
በዓለም አቀፍ ደረጃ በትምህርት ተቋማት ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶች በከፍተኛ ሁኔታ በጨመሩበት ወቅት ኢትዮጵያ ከፍተኛ ጥቃት ከተመዘገበባቸው አገራት ተርታ ተመደበች ባለፉት ሁለት ዓመታት ውስጥ በትምህርት ተቋማት ላይ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ጥቃት ከተመዘገበባቸው አገራት መካከል ኢትዮጵያ አንዷ መሆኗን የትምህርት ተቋማትን ከጥቃት ለመጠበቅ የሚሠራው ዓለም አቀፍ ጥምረት (GCPEA) ያወጣው አዲስ ሪፖርት አመላከተ። ድርጅቱ በትምህርት ቤቶች፣ በተማሪዎች እና በአስተማሪዎች ላይ የሚፈጸመው ጥቃት በዓለም ዙሪያ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን አስጠንቅቋል። ተቋሙ በዚህ ሳምንት ይፋ ባደረገው ሪፖርቱ፤ እ.ኤ.አ. በ2024 እና 2025 መካከል በዓለም አቀፍ ደረጃ ቢያንስ 8,566 በትምህርት ላይ የተሰነዘሩ ጥቃቶችን መዝግቧል። ይህም በ2022 እና 2023 ጋር ሲነጻጸር ከ40 በመቶ በላይ ጭማሪ ማሳየቱን ያመለክታል። ሪፖርቱ ኮሎምቢያ፣ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ፣ ኢትዮጵያ፣ ሄይቲ፣ ፍልስጤም እና ዩክሬንን በትምህርት ላይ ከፍተኛ ጥቃት የተመዘገበባቸው አገራት አድርጎ ለይቷቸዋል። @zena_maezen @zena_maezen

"በጣም ዘግይታችሁ እንዳትመጡ፤ ዕድሉ ያመልጣችኋል" - የሶማሌላንድ ፕሬዝዳንት የሶማሌላንድ ፕሬዝዳንት አብዱልራህማን ሙሐመድ አብዱላሂ በሥልጣን ዘመናቸው የመጀመሪያውን ይፋዊ ጉብኝት በእስራኤል አድር
"በጣም ዘግይታችሁ እንዳትመጡ፤ ዕድሉ ያመልጣችኋል" - የሶማሌላንድ ፕሬዝዳንት የሶማሌላንድ ፕሬዝዳንት አብዱልራህማን ሙሐመድ አብዱላሂ በሥልጣን ዘመናቸው የመጀመሪያውን ይፋዊ ጉብኝት በእስራኤል አድርገው፤ በኢየሩሳሌም የሶማሌላንድን የመጀመሪያ ኤምባሲ በይፋ ከፍተዋል። ፕረዚዳንቱ i24 ከተሰኘ ሚዲያ ጋር ባደረጉት ቃለመጠይቅ ሀገራቸው ከሶማሊያ (ሞቃዲሾ)፣ ከኬንያ እና ከበርካታ የአፍሪካ አገራት ቀድማ ነጻነቷን ያገኘች ሀገር መሆኗን ተናግረዋል። ከእስራኤል ጋር ስላለው ወታደራዊ ትብብር የተጠየቁት ፕረዚዳንቱ በአሁኑ ሰዓት የእስራኤል ወታደራዊ ጣቢያ በሀገራቸው ባይኖርም ይህ አማራጭ ግን ሙሉ ለሙሉ ዝግ አለመሆኑን ተናግረዋል። ፕሬዝዳንቱ ሌሎች አገራት የሶማሌላንድን ነጻነት እንዲቀበሉ ጥሪ ያቀረቡ ሲሆን፤ "በጣም ዘግይተው እንዳይመጡ" ሲሉ ተናግረዋል። "ዘግይተው ከመጡ አሁን ያሉትን ታላላቅ የንግድ፣ የኢንቨስትመንት እና የትብብር ዕድሎች ያጣሉ፤ ቀድሞ የመጣ የተሻለውን ዕድል ያገኛል" ሲሉ ገልጸዋል። ከአሜሪካ፣ ከዩናይትድ አረብ ኤምሬቶች እና ኢትዮጵያን ጨምሮ ከሌሎች የክልሉ ሀገራት ጋርም ክፍት የሆነ የዲፕሎማሲ ግንኙነት እንዳላቸው አረጋግጠዋል። ከአፍሪካ ኅብረትም ጋር የዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቱ እንዳልተቋረጠ ያስረዱት ፕረዚዳንቱ ለሁሉም የአፍሪካ ሀገራት መልዕክት መላኩን ነው በቃለመጠይቁ ወቅት ያነሱት። ፕሬዝዳንት አብዱልራህማን ሙሐመድ አብዱላሂ  በእስራኤል እና በሶማሌላንድ ዋና ከተማ ሀርጌሳ መካከል ቀጥተኛ የአየር በረራ በቅርቡ እንደሚጀመር ፕሬዝዳንቱ ሲያረጋግጡ የልብ ህመም ያለባቸው የሶማሌላንድ ህጻናት በዚህ ሳምንት በእስራኤል የህክምና እርዳታ ማግኘት መጀመራቸውን ጠቅሰዋል። @zena_maezen @zena_maezen

መምህሩም ተማሪውም ታሰሩ በሳውላ ከተማ ኩስቲ ቁጥር አንድ ትምህርት ቤት የ8ኛ ክፍል ፈተና ለተማሪ ሊፈተን ከተማሪ ጋር ተመሳስሎ የገባ መምህር እና ተማሪው በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋላቸውን የከተማው
መምህሩም ተማሪውም ታሰሩ በሳውላ ከተማ ኩስቲ ቁጥር አንድ ትምህርት ቤት የ8ኛ ክፍል ፈተና ለተማሪ ሊፈተን ከተማሪ ጋር ተመሳስሎ የገባ መምህር እና ተማሪው በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋላቸውን የከተማው ፖሊስ ጽህፈት ቤት ገለጸ። ተማሪውን ወክሎ ከመምህርነት ስነ-ምግባር ባፈነገጠ ተግባር ላይ ተሳትፏል የተባለውና ከቡልቂ ከተማ ሙሉ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የመጣው መምህር እስራኤል አሰፋ፣ የማንዴላ ርቀት ትምህርት ቤት ተማሪ የሆነውን አብነት እንዳለን ተክቶ ክልላዊ ፈተና ሊፈትን ሲል በተደረገ የኮማንድ ፖስት ክትትል በቁጥጥር ስር ሊውል መቻሉን የገለጹት የከተማው ትምህርት ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ያዕቆብ በተላ ናቸው። ፈተናውን ከኩረጃና ከስርቆት የፀዳ ለማድረግ በተቀመጠው አቅጣጫ መሠረት፣ የኮማንድ ፖስት አባላቱ ድርጊቱን በማጋለጥ ለፖሊስ ጥቆማ በመስጠታቸው ሊፈተን የገባው መምህርና ፈተናውን አሳልፎ የሰጠው ተማሪ በቁጥጥር ስር መዋል መቻላቸውን አስረድተዋል። የሳውላ ከተማ ፖሊስ አዛዥ ተወካይ ምክትል ኢንስፔክተር ሞገስ ሞኔ በበኩላቸው፣ ተማሪውንና መምህሩን በቁጥጥር ስር በማዋል ምርመራ እየተደረገባቸው መሆኑን ጠቁመው በማዕከሉ እየተሰጠ ያለው ፈተና ፍጹም ሰላማዊ እና በተረጋጋ መንገድ መቀጠሉን ተናግረዋል። ፖሊስ በቁጥጥር ስር የዋሉ ተጠርጣሪዎችን ምርመራ በአስቸኳይ አጣርቶ በአቃቤ ህግ በኩል ለፍርድ ቤት አቅርቦ ለማስወሰን እየሰራ መሆኑንም ምክትል ኢንስፔክተር ሞገስ ሞኔ ገልጸዋል። ምንጭ፦ ሳውላ ከተማ መንግሥት ኮሙኒኬሽን @zena_maezen @zena_maezen

የአሜሪካና ኢራን የተኩስ አቁም ስምምነት በፓኪስታን አደራዳሪነት በይፋ ጸደቀ ሐሙስ ሰኔ 11 ቀን 2018 ዓ.ም የአሜሪካ እና የኢራን ፕሬዚዳንቶች የሆርሙዝ ውጥረት ጦርነትን የሚያበቃውን ባለ 14 ነጥብ «የኢስላማባድ የመግባቢያ ሰነድ» በኤሌክትሮኒክስ ከፈረሙ በኋላ፣ ዋና አደራዳሪው የፓኪስታን ጠቅላይ ሚኒስትር ሸህባዝ ሻሪፍ ስምምነቱን በፊርማቸው አጽድቀውታል። ስምምነቱ ወዲያውኑ በተግባር ላይ የዋለ ቢሆንም፣ የቱርክ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሀካን ፊዳን የኢራን ዩራኒየም ዕጣ ፈንታን የመሰሉ ቴክኒካዊ ጉዳዮች ገና አልተቋጩም ብለዋል። በአሜሪካ የሁለቱም ፓርቲ የሕግ መወሰኛ ምክር ቤት አባላት በስምምነቱ ላይ ጥርጣሬና ትችት እያቀረቡ ባሉበት በዚህ ወቅት፣ እስራኤል በደቡባዊ ሊባኖስ በፈጸመችው የድሮን ጥቃት የአንድ ሰው ሕይወት ማለፉ ተዘግቧል። @zena_maezen @zena_maezen

"የመንግስታችን ዋና መለያ ለደሃ መወገን ነው” ከንቲባ አዳነች አቤቤ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር 175 ሺህ አዳዲስ የሥራ ዕድሎችን ለመፍጠር፣ ዝቅተኛ ገቢ ያላቸውን ዜጎች ለመደገፍ እና የአገልግ
"የመንግስታችን ዋና መለያ ለደሃ መወገን ነው” ከንቲባ አዳነች አቤቤ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር 175 ሺህ አዳዲስ የሥራ ዕድሎችን ለመፍጠር፣ ዝቅተኛ ገቢ ያላቸውን ዜጎች ለመደገፍ እና የአገልግሎት አሰጣጥን ለማዘመን ያለመ የክረምት ዕቅዱን ይፋ አድርጓል። ከንቲባ አዳነች አቤቤ ከከፍተኛ አመራሮች ጋር ባደረጉት ስብሰባ እንዳመለከቱት፤ የኮሪደር ልማት እና የክረምት የበጎ ፈቃድ ፕሮጀክቶች ለወጣቶች የሥራ ዕድል የሚፈጥሩ ሲሆን፣ በአሮጌ ቀበሌ ቤቶች ምትክም G+4 እና G+5 የጋራ መኖሪያ ሕንፃዎች በባለሀብቶችና በበጎ ፈቃደኞች ትብብር ይገነባሉ። “የመንግሥታችን ዋና መለያ ለደሃ መወገን ነው” ያሉት ከንቲባዋ፤ የልማት ሥራዎች ሲከናወኑ ዜጎችን በኃይል ማፈናቀል እንዳይኖር አስጠንቅቀዋል። ዕቅዱ የአረንጓዴ አሻራን ወደ 30 በመቶ ማሳደግን የሚያካትት ሲሆን፤ እንግልትና ሙስናን ለመግታትም የመሬት፣ የገቢዎች እና የንግድ ፈቃድ አገልግሎቶች በ90 ቀናት ውስጥ ወደ “መሶብ አንድ ዲጂታል ማዕከል” እንደሚገቡ ተጠቅሷል። @zena_maezen @zena_maezen

ዩናይትድ ስቴትስ እና ኢራን ከተስማሙ በኋላ የነዳጅ ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ ቀነሰ ረቡዕ ዕለት ከታየው ትንሽ የዋጋ ጭማሪ ውጭ፣ ሁለቱ ሀገራት ጦርነቱን ለማቆም እና ቁልፍ የሆነውን የሆርሙዝ ወሽመጥ የባ
ዩናይትድ ስቴትስ እና ኢራን ከተስማሙ በኋላ የነዳጅ ዋጋ  በከፍተኛ ሁኔታ ቀነሰ ረቡዕ ዕለት ከታየው ትንሽ የዋጋ ጭማሪ ውጭ፣ ሁለቱ ሀገራት ጦርነቱን ለማቆም እና ቁልፍ የሆነውን የሆርሙዝ  ወሽመጥ  የባህር ትራንስፖርት መስመርን መልሶ ለመክፈት የሚያስችል የማዕቀፍ ስምምነት ላይ መድረሳቸው ከታወቀ ወዲህ የነዳጅ ዋጋ እየቀነሰ መጥቷል። የአለም አቀፍ መለኪያ የሆነው የብሬንት ድፍድፍ ነዳጅ ሳምንቱን ሲጀምር በአንድ በርሜል በ86.80 ዶላር አካባቢ ይገበያይ የነበር ሲሆን፤ ከስምምነቱ በኋላ የ2 በመቶ ያህል ቅናሽ በማሳየት በ74.80 ዶላር እየተገበያየ ይገኛል። @zena_maezen @zena_maezen

በአሜሪካ እና ኢራን መካከል የተደረሰው ስምምነት በሊባኖስ ያለውን ወታደራዊ ዘመቻ እንዲቆም ማድረግን እንደሚያካትት ተገለፀ በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የተደረገው ስምምነት የመጀመሪያው አንቀጽ እን
በአሜሪካ እና ኢራን መካከል የተደረሰው ስምምነት በሊባኖስ ያለውን ወታደራዊ ዘመቻ እንዲቆም ማድረግን እንደሚያካትት ተገለፀ በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የተደረገው ስምምነት የመጀመሪያው አንቀጽ እንደሚያመለክተው አሜሪካ እና አጋሮቿ ሊባኖስን ጨምሮ በሁሉም ግንባሮች ላይ ወታደራዊ ዘመቻዎች በአስቸኳይ እና በቋሚነት እንዲቆሙ ያሳስባሉ፡፡ ይህ ጉዳይ በግጭቱ ውስጥ ዋነኛ የአለመግባባት መንስኤ ሆኖ የቆየ ሲሆን፤ በሊባኖስ የሚንቀሳቀሰው እና በኢራን የሚደገፈው የታጠቀው ቡድን ሄዝቦላህ እንዲሁም እስራኤል የተኩስ አቁም ቃልኪዳኖችን በመጣስ እርስ በእርስ ሲወነጃጀሉ ቆይተዋል። የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ እስማኤል ባጋኢ ቀደም ብለው በቴሌግራም ገጻቸው ላይ እንደገለጹት፤እስራኤል በሊባኖስ ላይ የምታደርገውን ጥቃት ከቀጠለች ድርጊቱ የመግባቢያ ስምምነቱን እንደመጣስ ይቆጠራል። እንደ ኢራን መንግሥት ቴሌቪዥን ዘገባ የደህንነት ቃል አቀባዩ የእስራኤል ጦር በሊባኖስ መቆየቱ ጦርነቱን ለማቆም የተደረገውን ስምምነት መጣስ ነው ማለታቸውንም ገልጸዋል። የእስራኤል ጦር ትናንት በደቡባዊ ሊባኖስ አዳዲስ ጥቃቶችን የፈጸመ ሲሆን፤ ዛሬ ደግሞ በደቡባዊ ሊባኖስ በተከሰተ ክስተት የቆሰለ አንድ ወታደር መሞቱን አስታውቋል። በትናንትናው ዕለት በፈረንሳይ በተካሄደው የቡድን 7 ጉባኤ ላይ ንግግር ያደረጉት የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በሊባኖስ ሰላም ማስፈን ልንሰራበት የሚገባ ጉዳይ መሆኑን እንረዳለን ብለው ሆኖም ግን ትልቁ ስምምነት የኢራኑ ስምምነት ነው ብለዋል። የእስራኤል መንግሥት ስለ አሜሪካ እና ኢራን ስምምነት መፈረም እስካሁን በይፋ የሰጠው ምላሽ የለም። @zena_maezen @zena_maezen

የዩክሬን ድሮኖች የሞስኮ የነዳጅ ማጣሪያ ላይ ዛሬ በድጋሚ ጥቃት ሰነዘሩ የዩክሬን ድሮኖች በሩሲያ ዋና ከተማ ሞስኮ በሚገኝ የነዳጅ ማጣሪያ ጣቢያ ላይ በዚህ ሳምንት ለሁለተኛ ጊዜ ከባድ ጥቃት ሰንዝረ
+1
የዩክሬን ድሮኖች የሞስኮ የነዳጅ ማጣሪያ ላይ ዛሬ በድጋሚ ጥቃት ሰነዘሩ የዩክሬን ድሮኖች በሩሲያ ዋና ከተማ ሞስኮ በሚገኝ የነዳጅ ማጣሪያ ጣቢያ ላይ በዚህ ሳምንት ለሁለተኛ ጊዜ ከባድ ጥቃት ሰንዝረዋል፡፡ ይህም ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪ ጦርነቱን ለማቆም ከአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ እና ከአውሮፓ መሪዎች ጋር የሰላም ስምምነት ድጋፍ ለማግኘት ውይይት ባደረጉ ማግስት ነው። የሩሲያ ባለስልጣናት በርካታ ድሮኖችን ማክሸፋቸውን ቢገልጹም ማጣሪያው መመታቱን የከተማዋ ከንቲባ ሰርጌይ ሶቢያኒን አረጋግጠዋል። ይህ ጥቃት ቀደም ሲል በነዳጅ እጥረት ስጋት ውስጥ የነበረችው ሩሲያ ለመጀመሪያ ጊዜ በባህር ላይ ነዳጅ ወደ ሀገር ውስጥ ለማስገባት እንድትገደድ አድርጓታል። ለደህንነት ሲባልም የሞስኮው ትልቁ አየር ማረፊያ ለሰዓታት በረራዎችን አቋርጧል። በአጸፋው ሩሲያ በዩክሬን ዋና ከተማ ኪቭ ላይ የባሊስቲክ ሚሳኤል ጥቃቶችን የሰነዘረች ሲሆን፤ በሱሚ ከተማ በተፈጸመ የድሮን ጥቃት የአንድ ሰው ህይወት ማለፉ ተዘግቧል። ቀደም ሲል ሩሲያ በኪቭ ባደረሰችው ጥቃት 1 ሺህ ዓመት ዕድሜ ያስቆጠረ ታሪካዊ ገዳም ላይ ጉዳት ማድረሷ የአውሮፓ መሪዎችን ቁጣ መቀስቀሱ ይታወሳል፡፡ በዲፕሎማሲው ረገድ ፕሬዝዳንት ዘለንስኪ በፈረንሳይ በተካሄደው የጂ7 ስብሰባ ከአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጋር ጦርነቱን በሰላም ለመቋጨት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ውይይት አድርገዋል። ፕሬዝዳንት ትራምፕ ከውይይቱ በኋላ በሰጡት አስተያየት ሁለቱም ወገኖች ስምምነት ላይ ለመድረስ ፍላጎት እንዳላቸው ጠቁመው፤ በአሁኑ ወቅት ሩሲያ በጦርነቱ ላይ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ወታደር እያጣች መሆኑን ገልጸዋል።

የኢራን ፓርላማ አፈ-ጉባኤ ጋሊባፍ አሜሪካ ለስምምነቱ ታማኝ ካልሆነች ኢራንም ስምምነቱን እንደማታከብር አስታወቁ። @zena_maezen @zena_maezen
የኢራን ፓርላማ አፈ-ጉባኤ ጋሊባፍ አሜሪካ ለስምምነቱ ታማኝ ካልሆነች ኢራንም ስምምነቱን እንደማታከብር አስታወቁ። @zena_maezen @zena_maezen

"ተመልሰን ቦምብ ልናዘንብ እንችላለን" - የትራምፕ ዛቻ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ኢራን በስምምነቱ መሰረት ካልተጓዘች አዲስ ጥቃት አመራለሁ ሲሉ ዛቱ፡፡ በቡድን ሰባት ጉባዔ ፈረንሳይ የሚ
"ተመልሰን ቦምብ ልናዘንብ እንችላለን" - የትራምፕ ዛቻ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ኢራን በስምምነቱ መሰረት ካልተጓዘች አዲስ ጥቃት አመራለሁ ሲሉ ዛቱ፡፡ በቡድን ሰባት ጉባዔ ፈረንሳይ የሚገኙት ትራምፕ ከኢራን ጋር የተደረሰው ስምምነት “ገና እንዳልተገባደደ” ጠቅሰው በመግባቢያ ሰነዱ አተገባበር ደስተኛ ካልሆኑ ቴህራን ላይ ጥቃት መፈጸም እንደሚቀጥሉ አስጠንቅቀዋል፡፡ ኢራን ከእስራኤልና አሜሪካ ጋር ስምምነት ላይ ከደረሰች በኋላ በሰጡት የመጀመሪያ አስተያየት "ጥቃቱ በዚሁ ከቀጠለ ጠንካራ ምላሽ የምንሰጥ ይሆናል" ሲሉ ትራምፕ ተደምጠዋል። ፕሬዝዳንቱ "ተመልሰን ቦምብ ልናዘንብ እንችላለን" ሲሉም ዝተዋል። "የመግባቢያ ስምምነቱ አልተጠናቀቀም" ያሉት ትራምፕ "ካልወደድኩት ወታደራዊ እርምጃ እንወስዳለን" ሲሉም የመፍረስ አደጋ እንዳለው ጠቁመዋል። "ስምምነቱ በብዙ ምክንያት አስፈላጊ ነው" ካሉ በኋላ "99.9% የተስማማንበት ኢራን የኑክሌር መሳሪያ እንደማይኖራት ነው" ብለዋል። ኢራን ለመልሶ ግንባታ የሚሆን 300 ዶላር ካሳ ይከፈላታል መባሉን "ውሸት ነው፣ ሳንቲም አናወጣም" ሲሉ አስተባብለዋል።   @zena_maezen @zena_maezen

በትግራይ ክልል ወጣቶችን ለውትድርና የመመልመልና የማሠልጠን ሥራ እየተሠራ መኾኑ ተገለጸ በትግራይ ክልል በኃይል ሥልጣን የያዘው የክልሉ አስተዳደር ወጣቶችን ለተዋጊነት እየመለመለና እያሠለጠነ መኾኑን
በትግራይ ክልል ወጣቶችን ለውትድርና የመመልመልና የማሠልጠን ሥራ እየተሠራ መኾኑ ተገለጸ በትግራይ ክልል በኃይል ሥልጣን የያዘው የክልሉ አስተዳደር ወጣቶችን ለተዋጊነት እየመለመለና እያሠለጠነ መኾኑን የክልሉ ሰላምና ጸጥታ ቢሮ መግለፁን ቢቢሲ ዘግቧል። ቢሮው ወጣቶች በምን ዓይነት ሂደት ተመልምለው ለሥልጠና እንደሚላኩ የሚወስኑት የክልሉ ሲቪል ባለሥልጣናት ብቻ መኾናቸውን አስታውቋል። በሌላ በኩል፣ የዓድዋ ከተማ ሠላምና ጸጥታ ጽሕፈት ቤት በከተማዋ ወጣቶች በግዳጅ ይታፈሳሉ መባሉን ሙሉ በሙሉ ያስተባበለ ሲሆን፤ የምልመላ ሥራው በግዳጅ ሳይሆን፣ በማሳመን ሂደት ላይ ብቻ በተመሠረተ መልኩ እየተከናወነ እንደሚገኝ በይፋ ገልጧል። @zena_maezen @zena_maezen