fa
Feedback
AACRA

AACRA

رفتن به کانال در Telegram

Addis Ababa City Roads Authority (AACRA) is a government organization under the Addis Ababa City Adminstration. It was established on March 1998 with the aim of realizing sustainable road infrastructure and creating interchangeable road transport to A.A.

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام AACRA

کانال AACRA (@addisroads) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 11 115 مشترک است و جایگاه 2 100 را در دسته حمل و نقل و رتبه 3 006 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 11 115 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 19 سپتامبر, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 159 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 7 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 13.33% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 8.22% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 1 482 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 914 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 3 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
Addis Ababa City Roads Authority (AACRA) is a government organization under the Addis Ababa City Adminstration. It was established on March 1998 with the aim of realizing sustainable road infrastructure and creating interchangeable road transport to ...

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 20 سپتامبر, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته حمل و نقل تبدیل کرده‌اند.

11 115
مشترکین
+724 ساعت
+237 روز
+15930 روز
آرشیو پست ها
AACRA
11 111
photo content
+9

AACRA
11 111
የሰንበት እረፍትዎን ከቤተሰቦ:ከልጆቾና ከወዳጅ ዘመድዎ ጋር በመሀል ፒያሳ በአራዳ ፖርክ ያድርጉ:-
የሰንበት እረፍትዎን ከቤተሰቦ:ከልጆቾና ከወዳጅ ዘመድዎ ጋር በመሀል ፒያሳ በአራዳ ፖርክ ያድርጉ:-

AACRA
11 111
photo content
+7

AACRA
11 111
አዲስ አበባ የኮሪደር ልማቷን ከስማርት ሲቲ ጋር በማቀናጀት የወጣቶችን ጥያቄ የሚመልሱ ዓለም አቀፍ የስፖርት ውድድሮች የሚካሄዱባት ማዕከል እየሆነች ነው። መዲናችን አዲስ አበባ ዘመናዊ የኮሪደር ልማትን ከስማርት ሲቲ ፅንሰ-ሀሳብ ጋር በማቀናጀት በፍጥነት በመለወጥ ላይ ትገኛለች። ይህ ከተማዋን የማዘመንና የመሠረተ ልማት ግንባታ ስራ የወጣቶችን ሁለንተናዊ ፍላጎትና ጥያቄ በሚመልስ መልኩ እየተከናወነ የሚገኝ ሲሆን አዲስ አበባን ዓለም አቀፍ መስፈርቶችን ያሟሉ ትልልቅ አህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ የስፖርት ውድድሮች የሚካሄዱባት ተመራጭ መዲና አድርጓታል። በመዲናዋ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በህብረተሰቡ በተለይም በወጣቱ ዘንድ ከፍተኛ ተወዳጅነትን እያገኘ የመጣው የቅልቅል ማርሻል አርት (MMA) ውድድር የዚህ አዲስ የለውጥ ምዕራፍ ማሳያ ሆኗል። ስፖርቱ በወጣቶች ዘንድ ያለውን ከፍተኛ ፍላጎትና ስሜት ከመመለሱ ባሻገር፤ ስነ-ሥርዓትን፣ ጽናትንና ስፖርታዊ አቅምን የታነፀ አዲስ ትውልድ በመገንባት ረገድ የጎላ ድርሻ እየተወጣ ይገኛል። ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ ውድድሮች በመዲናዋ መካሄዳቸውም የወጣቶቻችንን ክህሎት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ትልቅ እድል ፈጥሯል። ከተማዋ ከሚክስድ ማርሻል አርት (MMA) ውድድሮች በተጨማሪ በርካታ ዓለም አቀፍና አህጉራዊ የስፖርት ሁነቶችን በብቃት ማስተናገድ ጀምራለች። ዘመናዊ የስፖርት መሰረተ ልማቶች መስፋፋታቸው፣ የኮሪደር ልማቱ የፈጠረው ጽዳትና ውበት እንዲሁም የሆቴልና የትራንስፖርት አገልግሎቶች መዘመን አዲስ አበባን የኦሊምፒክ ደረጃ ያላቸው ውድድሮችና የምስራቅ አፍሪካ ዋና የስፖርት ማዕከል እያደረጋት ይገኛል። ይህ ሁለንተናዊ የልማትና የስፖርት እንቅስቃሴ አዲስ አበባ ለነዋሪዎቿ፣ በተለይም ለወጣቶቿ ምን ያህል ምቹ፣ ሳቢ እና ተስፋ ሰጪ እየሆነች መምጣቷን በተግባር የሚያሳይ ነው። በዚህም ወጣቶች በስፖርቱ ዘርፍ ያላቸውን እውቀትና ክህሎት የሚያወጡበት፣ ጤናማ የአኗኗር ዘይቤን የሚያደብሩበት እና በከተማቸው ልማት ንቁ ተሳታፊ የሚሆኑበት ሰፊ እድል እየተፈጠረላቸው ይገኛል።

AACRA
11 111
በኮሪደር መሰረተ ልማት እርጅናዋ የተገፈፈ አዲስ አበባ:-
+3
በኮሪደር መሰረተ ልማት እርጅናዋ የተገፈፈ አዲስ አበባ:-

AACRA
11 111
በትጋትና ጥረት የተወለደ አዲስ የማንሰራራት ንጋት! አዲስ አበባ ለነዋሪዎቿ ምቹ፣ ጽዱ፣ ተወዳዳሪና ዘመናዊ እንድትሆን ለማድረግ ከተማ አስተዳደሩ አቅዶ በሰራው ሥራ ዘርፈ ብዙ ለውጦች ተመዝግበዋል። በከተማዋ የተገነቡት ሜጋ ፕሮጀክቶችና የልማት ኢኒሼቲቮች የህዝቡን የልማትና የተጠቃሚነት ጥያቄ ከመመለስ ባሻገር ከተማዋ እንድታንሰራራ እና ለሌሎች ከተሞች የብልጽግና ፋና ወጊ እንድትሆን አስችሏታል። ባለፉት አምስት ዓመታት ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ያደረጉ ከ60 ሺህ በላይ ፕሮጀክቶች ተጠናቀው ወደ አገልግሎት የገቡ ሲሆን በ2018 ዓ.ም ብቻ ከ20ሺህ በላይ ፕሮጀክቶች መጠናቀቅ ችለዋል። ይህ በ24/7 የሥራ ባህል የተተገበረው የፕሮጀክት አፈጻጸም ለከተማዋ ማንሰራራት ጉልህ ድርሻ ተጫውቷል። በከተማዋ ባለፉት አምስት ዓመታት የተገነቡ የመንገድ መሰረተ ልማቶች ለከተማዋ ዘመናዊነትን ከማላበስ በዘለለ ነዋሪው ደህንነቱ ተጠብቆ እንዲንቀሳቀስ ምቹ መደላድል ፈጥረዋል። የመንገድ ኔትዎርክ ሽፋንና ጥራትን በማሳደግ የትራንስፖርት እንቅስቃሴው እንዲሳለጥ አድርጓል። በከተማዋ ምንም ያልነበሩ የትራንስፖርት ቴርሚናሎችና መኪና ማቆሚያዎች በበርካታ ቦታዎች ተገንብተው ህብረተሰቡን ከእንግልትና ከአደጋ መታደግ ችለዋል። የነዋሪዎችን አስከፊ አኗኗር ለማሻሻል ታቅዶ የተተገበረው የከተማ ማደስ ሥራም አዲስ አበባ ፈጥና እንድታንሰራራና ባለፉት ጊዜያት “አይቻልም” ተብሎ የተዘጋውን አዲስ አበባን የመለወጥ ውጥን ወደ ተግባር እንዲቀየር አስችሏል። ከተማዋ ለኑሮ ምቹ፣ ለጤና ተስማሚ እንድትሆን ብክለትን ለመቀነስ በተሰራው የአረንጓዴ ልማት ሥራ የከተማዋ የአረንጓዴ ሽፋን ከ2.8 በመቶ ወደ 24 በመቶ አድጓል። በተጨማሪ ለከተማዋ ጽዳት በተሰጠው ትኩረት አዲስ አበባ ከ10 ጽዱ የአፍሪካ ከተሞች አንዷ መሆን ችላለች። በአዲስ አበባ የተመዘገቡ የመሰረተ ልማት ስኬቶች ለነዋሪዎቿ ዘመናዊ አገልግሎት ከመስጠታቸው በተጨማሪ ከተማዋን ከቱሪስት መተላለፊያነት ወደ ቱሪስት መዳረሻነት እንድትሸጋገር አስችሏታል። በኮንፍረንስ ቱሪዝም በ2018 ዓ.ም. ብቻ ከ220 በላይ ዓለም አቀፍ እና አህጉር አቀፍ ስብሰባዎችን በማስተናገድ አዲስ አበባ ማንሰራራቷን አስመስክራለች።

AACRA
11 111
photo content
+6

AACRA
11 111
ፋና ዘገባ የ2018 በጀት አመት አፈጻጸጸም እና የ2019 በጀት አመት ዕቅድ ከባለድርሻ አካላት ጋር የውይይት መድረክ

AACRA
11 111
photo content
+5

AACRA
11 111
ለዓለም ከተሞች ምሳሌ የሆነች ከተማ - አዲስ አበባ አዲስ አበባ ዝቅተኛ የአደጋ ተጋላጭ የሆነች፥ ደህንነቷ የተጠበቀና የአየር ንብረት ለውጥን የምትቋቋም ከተማ በሚል ከአፍሪካ ቀዳሚ ከዓለም ሁለተኛ ከተማ ሆና ተቀምጣለች። የጂኦስፓሻል ኩባንያ አልፋ ጂኦ በዋነኝነት በሶስት መመዘኛዎች የአዲስ አበባ ከተማን የመዘነ ሲሆን አካላዊ የአየር ንብረት ለውጥ፥ አደጋ ተጋላጭነት፤ሊገጥሙ ለሚችሉ አደጋዎች አስተዳደር እና ፖሊሲ ምላሽ እንዲሁም የአየር ንብረት ለውጥ የማላመድ እርምጃዎች ላይ በማተኮር ነው ምዘናው የተካሄደው። በእነዚህ መመዘኛዎች አዲስ አበባ ከተማ ከ72 ከተሞች ጋር ተወዳድራ ሁለተኛ ደረጃን በመያዝ ለዓለም ከተሞች ምሳሌ ሆናለች፡፡ በዓለም የስልጣኔ ቁንጮ የተባሉትን እንደነ ፓሪስ እና ለንደን የመሳሰሉት ከተሞች አስከትላ በዓለም ላይ የአየር ንብረት ተጋላጭነት የምትቋቋም ከተማ በሚል ከአሜሪካዋ ቺካጎ ቀጥሎ በቁንጮ ላይ የተቀመጠችው አዲስ አበባ በኮሪደር እና የመንዝ ዳርቻ ልማት ያከናወነችው ስራዎች እና የዘረጋቻቸው ዘመናዊ መሰረተ ልማቶች በዚህ ደረጃ እንድትቀመጥ አስችሏታል፡፡ አዲስ አበባ የዓለም ቀልብ የምትስብ ለነዋሪዎቿ ምቹ ከተማ ብቻ አይደለችም ከምቹነት ባለፈ የአደጋ ተጋላጭነቷ ዝቅተኛ የሆነች፥ ደህንነቷ የተጠበቀ የአየር ንብረት ለውጥን የምትቋቋም ከተማ ናት ፡፡ በዓለምአቀፉ ጂኦስፓሻል ኩባንያ አልፋ ጂኦ (Alpha Geo) ለአዲስ አበባ የተሰጠው ማረጋገጫ ለፖሊሲ አውጪዎች፤ ኢንቬስተሮች እና የመሰረተ ልማት ባለቤቶች አዲስ አበባ ከተማ በተመለከተ የውሳኔ ሀሳቦች ለመስጠት እጅጉን ጠቃሚ ነው፡፡ በዓለም ላይ የሚገኙ ከተሞች ፈጣን የህዝብ ቁጥር ጭማሪን እያስተናገዱ ሲሆን ይህ የሕዝብ ቁጥር በፍጥነት ማደግ አዳዲስ ፍላጎቶችን ይዞ የሚመጣ ሲሆን በዚያው መጠን ደግሞ ከተሞች ለሚፈጠሩ አዳዲስ ፍላጎቶች ፈጣን ምላሽ መስጠት ይገባቸዋል፡፡ በዚህ መርህ የተቃኘው የአዲስ አበባ ከተማ የወንዝ እና የኮሪደር ልማት ስራ ከተማዋ በዓለማቀፍ ደረጃ እውቅና እንዲቸራት እያደረገ ሲሆን በ8 ወንዞች 59 ኪሎ ሚትር ርዝመት ያለው የአዲስ አበባ የወንዝ ዳርቻ ልማት ለበርካታ ችግሮች ሁሉን አቀፍ ምላሽ የሰጠ ነው፡፡ ወንዞችን ማልማት ከመዋብ ባለፈ ዘርፈ ብዙ ጥቅሞች አሉት፤ የወንዞችን መበከል ይከላከላል፣ የጎርፍ አደጋን ይቀንሳል፣ የከተማዋን የሙቀት መጠን ይቀንሳል፥ ነዋሪዎች ንጹህ አየር የሚያገኙበትን፣ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ የሚያደርጉበትን እና አዕምሮአቸውን የሚያድሱበትን ዕድል ይፈጥራል።

AACRA
11 111
የመንገድ መከፈትን ለመግለፅ የተላለፈ ማስታወቂያ ከቦሌ ሚካኤል ወደ ጎርጎሪዎስ አደባባይ በሚወስደው መንገድ ላይ የሚገኘውን ድልድይ ለመጠገን ከጳጉሜ 2 ቀን 2018 ዓ.ም ምሽት ጀምሮ መንገዱ ለትራፊክ እንቅስቃሴ በከፊል ዝግ መደረጉ ይታወሳል። በዚሁ መሰረት የጥገና ሥራው የተጠናቀቀ ስለሆነ፤ ከዛሬ መስከረም 7 ቀን 2019 ዓ.ም ጀምሮ፣ ከጎርጎሪዎስ አደባባይ ወደ ቦሌ ሚካኤል እና ተቃራኒ አቅጣጫ የሚወስደው መንገድ፣ ለቀላል ተሽከርካሪዎች ብቻ ለትራፊክ እንቅስቃሴ ክፍት ተደርጓል። በድልድዩ ላይ በተደጋጋሚ የሚያጋጥመውን የመቦርቦር ችግር በዘላቂነት ለመፍታት፣ በቀጣይ ወራት በጥናትና ዲዛይን የተደገፈ ተጨማሪ የማጠናከሪያ ግንባታ የሚከናወን ይሆናል። የተሻለ መንገድ፣ ለተሻለች አዲስ አበባ፤ የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለሥልጣን ወቅታዊና ፈጣን ከተማ አቀፍ መንገድ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለሥልጣን ማህራዊ ሚዲያ መድረኮችን ይቀላቀሉ፦ https://linktr.ee/aacracom?utm_source=linktree_profile_share&ltsid=513a17d0-08ca-4c83-a9f4-d64df599f68f

AACRA
11 111
photo content

AACRA
11 111
ለመስቀልና የኢሬቻ በዓላት ድምቀት የመንገድ ዘርፍ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች በመከናወን ላይ ናቸው የበዓላቱን አከባበር አስመልክቶ በተዘጋጀው ሰነድ ላይም የሠራተኞች ውይይት ተካሂዷል መስከረም 7 ቀን
+4
ለመስቀልና የኢሬቻ በዓላት ድምቀት የመንገድ ዘርፍ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች በመከናወን ላይ ናቸው የበዓላቱን አከባበር አስመልክቶ በተዘጋጀው ሰነድ ላይም የሠራተኞች ውይይት ተካሂዷል መስከረም 7 ቀን 2019 ዓ.ም (አ.አ.ከ.መ.ባ)፡- የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለሥልጣን በመስከረም ወር ለሚከበሩት የመስቀልና የኢሬቻ በዓላት ድምቀት በመንገድ ዘርፍ የሚጠበቁ የቅድመ ዝግጅት ሥራ እያከናወነ ይገኛል፡፡ ባለሥልጣን መስሪያ ቤቱ በዓላቱ በሚከበሩባቸው አካባቢዎች፤ ጥገና የሚያስፈልጋቸውን የአስፋልት መንገዶችን እና ሌሎች የመንገድ መሰረተ ልማቶችን በማስተካከል ላይ ነው። ይህ በእንዲህ እንዳለ፤ የባለሥልጣን መሥሪያቤቱ አመራርና ሠራተኞች፤ የ2019 የመስቀልና የኢሬቻ በዓላትን በድምቀት ለማክበር በተዘጋጀው ሰነድ ላይ ውይይት አካሂደዋል፡፡ በውይይት መድረኩ ላይ መልዕክት ያስተላለፉት የባለሥልጣኑ የኦፕሬሽን ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር ታካለ ሉሌና፤ መጪዎቹ የመስቀልና የኢሬቻ በዓላት ባህላዊና ሐይማኖታዊ ይዘታቸው ተጠብቆ በሠላም እንዲከበሩ፣ የህብረተሰቡ አካል የሆነው የተቋሙ ሠራተኛ የበኩሉን አውንታዊ ሚና እንዲወጣ አሳስበዋል፡፡

AACRA
11 111
የአቅመ ደካማ ወገኖች የማዕድ ማጋራት መርሃ ግብር በተስፋ የምገባ ማዕከል ቁጥር 4

AACRA
11 111
አዲስ አበባ የእህትማማች ከተሞች ትስስርን በማስፋት ከዓለም ከተሞች ጋር ያላትን ግንኙነት እያሳደገች ነው፡፡ አዲስ አበባ በተለያዩ ዘርፎች የጋራ ትብብርን ለማጠናከር በምታደርገው ጥረት ባለፉት አምስት ዓመታት የከተማዋ የእህትማማች ከተሞች ትስስር ከ20 ወደ 30 ከተሞች አድጓል፡፡ አዲስ አበባ ባላት ታሪክ እና አሁን ላይ እያስመዘገበችው ባለው ሁለንተናዊ ለውጥ በርካታ የዓለም ከተሞች የእህትማማችነት ግንኙነቱን እያሳደጉ ይገኛሉ፡፡ ይህ ከከተሞች ጋር የሚኖር ስትራቴጂካዊ ግንኙነት አዲስ አበባ ከዓለም አቀፍ ከተሞች ጋር ያላትን ዲፕሎማሲያዊ እና ኢኮኖሚያዊ ትስስርን ያሳድጋል፡፡ በተጨማሪም ዘመናዊ የከተማ ልማት ልምዶችን እና ምርጥ ተሞክሮዎችን ለመለዋወጥ እጅግ ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል፡፡ የአዲስ አበባ ለውጥ ዛሬ በሁሉም መልኩ የእይታ ማዕከል እንድትሆን አድርጓታል፡፡ ዓለምዓቀፍ ተቋማቶች ስብሰባዎቻቸውን አዲስ አበባ ላይ ለማድረግ ቀዳሚ ምርጫቸውን አድርገዋል፡፡ በ2018 በጀት ዓመት ብቻ 221 ዓለም አቀፍ እና አህጉር አቀፍ ኮንፈረንሶች በአዲስ አበባ ተካሂደዋል። አዲስ አበባ ወደ ስማርት ሲቲ (ዘመናዊ ከተማ) ለመቀየር በምታደርገው ተከታታይ ጥረትና በምታስመዘግባቸው ስኬቶች በርካታ ዓለም አቀፍ ሽልማቶችንና እውቅናዎችንም አግኝታለች። ከእነዚህ እውቅናዎች መካከልም በሪዮዲጀነሪዮ የተቀበለችው የምገባ ኘሮግራም ሽልማት፡ በደቡብ ኮሪያ የተበረከተውና ለከተማዋ አመራር እውቅና የሰጠው የሴኡል ስማርት ከተማ ሽልማት (2024)፡ ለቆሻሻ አወጋገድ ስርዓት መሻሻል በቦነስአይረስ የተሰጠው እውቅና፡ የC40 ከተሞች የብሉምበርግ ሽልማት፡ በናይሮቢ ኬንያ በተካሄደው የአፍሪካ ስማርት ከተሞች ኢንቨስትመንት ሰሚት የተሰጠው የአፍሪካ ምርጥ ስማርት ከተማ ሽልማት (2024)፡ አዲስ አበባ በመንገድ ደህንነትና ፍጥነት ማስተዳደር ላይ ባስመዘገበችው ውጤት በዓለም አቀፍ የከተሞች የዘርፉ ውድድር የወርቅ ሜዳሊያ ተሸላሚ የሆነችባቸው ተጠቃሽ ናቸው፡፡ እነዚህ ዓለም አቀፍ እውቅናዎች የከተማዋን ሁለንተናዊ መልካም ገጽታ በዓለም መድረክ ላይ በግልጽ ያሳዩ ታላላቅ ስኬቶች ናቸው።

AACRA
11 111
photo content
+8

AACRA
11 111
photo content

AACRA
11 111
ለአዲሱ ዓመት እንኳን በሰላም ፣በጤና እና በፍቅር አደረሰን ! አደረሳችሁ! የዘመን መለወጫ በዓል፣ ከምንም በላይ የብሩህ ተስፋ፣ የአብሮነት ፣ የሰላምና የእርቅ እንዲሁም የመልካም ይሁንልን። አዲስ አመት ለኛ ኢትዮጵያውያን ከአሮጌው ወደ አዲስ አመት የሚደረግ ሽግግር ብቻ አይደለም። ይልቁንም፣ ከአንድ የለውጥና የእድገት ምዕራፍ ወደሌላ የላቀ ምዕራፍ የተሸጋገርንበት የዘመን ድልድይ ጭምር ነው፡፡ በአዲስ ዓመት አዲስ ተስፋ፣ ሰላም፣ ፍቅር፣ አብሮነት፣ አዲስ ራዕይ፣ ትጋት፣ ለውጥ፣ ፅናት ውጤትና ብልፅግና ብለን የምንነሳበት ነው፡፡ ዘመን ይመጣል ደግሞም ይሄዳል፡፡ የሄደው ተመልሶ አይመጣም፡፡ ዋናው ቁምነገሩ በተሰጠን ዘመን ጥሎን የማይሄድ አሻራ ማኖር ነው። አዲስ አበባ ያረጁ ገጾታዎችን ከአሮጌዉ ዘመን ጋር ሸኝታ፣ እንደ ከአዲሱ ዘመን እየታደሰች አዲስ እና አበባ ሆናለች። ትናንት ያከናወናቸው የህዝብን ህይወት በተጨባጭ የሚቀይሩ ፣ ከተማዋን ማስዋብና ማሳመር ብቻ ሳይሆን ዜጎቿን የማትዘነጋ ከተማ መሆኗን ያረጋገጥንባቸው ሰው ተኮር ስራዎች ለዝቅተኛ ማህበረብ ክፍሎች ጉድለታቸውን የሸፈኑ፣ የደካሞችን እንባ ያበሱ፣ የተረሱትን ያስታወሱ ስራዎች ከሰጠን የህሊና እርካታ በላይ ከተጋን ከዚህ የላቀ የዜጎቻችንን ህይወት እንደምንቀይር ያረጋገጥንባቸው ናቸው፡፡ ይህ ውጤት እንዲሁ በከንቱ አልመጣም፡፡ ሁላችን ባሳየነው ትብብርና ቅንጅት፣ ትብብርና ድጋፍ እውን የሆነ መላው የከተማዋ ነዋሪዎች፣ በየደረጃው የሚገኘው የልማት አጋሮች፣ አመራር፣ ሰራተኞች፣ የልትአጋሮቻቸን የሆኑ ባለ ሀብቶች፣ወጣቶች ሴቶች እናቶችና አባቶች፣ በአብሮነት በመረባረብ በጋራ ያመጣው የድል ፍሬ ነው። በእርግጥም ስንተባበር እንችላለን! አዲሱ አመት፣ በሰራናቸው ስራዎች ሳንኩራራ ጊዜያችንን ሳናባክን ዛሬ ላይ ቆመን ለነገ አሻግረን በመመልከት፣ ከትናንት ስኬቱን በላይ ጉድለቱ ተምረን ለላቀ ውጤት ለመትጋት ቃል የምንገባበት ነው፡፡ ኢትዮጵያ ሀገራችን፣ እኛ ልጆቿ እስከተሳሰብን ድረስ፣ ለሁላችን የሚበቃ ፀጋ የታደለች፣ ተፈጥሮ የባረካት ከኛ አልፎ ለሌላም የምትተርፍ ሀገር ናት፡፡ በመሆኑም፣ አዲሱን ዘመን ስንቀበል ለከፋፋይ ትርክቶች ምንም ዓይነት ቦታ ሳንሰጥ፤ የወንድማማችነትና የእህትማማችነት ስሜታችንን በማጎልበት የፀናችና የበለፀገች የምትታፈር ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ! በህብረብሔራዊ አንድነት እንቁም፤ በሰላም እንጽና፤ በሥራ እንትጋ፤ በፍቅር እንተባበር፤ እርስበርሳችን እንከባበር፣ ኢትዮጵያንም ወደ ከፍታዋ እንምራ! በድጋሚ አዲሱ ዘመን የሰላም፣ የፍቅር፣ የእርቅ፣ የብልፅግናና የላቀ እመርታ ዓመት እንዲሆንልን ከልብ እመኛለሁ። ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ! ከንቲባ አዳነች አቤቤ

AACRA
11 111
photo content
+4

AACRA
11 111
photo content
+9