ar
Feedback
AACRA

AACRA

الذهاب إلى القناة على Telegram

Addis Ababa City Roads Authority (AACRA) is a government organization under the Addis Ababa City Adminstration. It was established on March 1998 with the aim of realizing sustainable road infrastructure and creating interchangeable road transport to A.A.

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام AACRA

تُعد قناة AACRA (@addisroads) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 11 086 مشتركاً، محتلاً المرتبة 2 110 في فئة النقل والمرتبة 3 010 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 11 086 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 30 أغسطس, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 162، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 2، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 12.90‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 9.25‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 1 430 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 1 025 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 3.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
Addis Ababa City Roads Authority (AACRA) is a government organization under the Addis Ababa City Adminstration. It was established on March 1998 with the aim of realizing sustainable road infrastructure and creating interchangeable road transport to ...

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 31 أغسطس, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة النقل.

11 086
المشتركون
+224 ساعات
+1367 أيام
+16230 أيام
أرشيف المشاركات
AACRA
11 083
ማስታወቂያ ለረጅም ዓመታት አገልግሎት ሲሰጥ የቆየው የአድዋ ድልድይ በደረሰበት ጉዳት ምክንያት በተጠቃሚዎች ላይ አደጋ እንዳያስከትል፣ መንገዱን መዝጋት አስፈልጓል፡፡ በዚሁ መሠረት ያጋጠመው ችግር በ
ማስታወቂያ ለረጅም ዓመታት አገልግሎት ሲሰጥ የቆየው የአድዋ ድልድይ በደረሰበት ጉዳት ምክንያት በተጠቃሚዎች ላይ አደጋ እንዳያስከትል፣ መንገዱን መዝጋት አስፈልጓል፡፡ በዚሁ መሠረት ያጋጠመው ችግር በጥናትና ዲዛይን የተደገፈ፣ ዘላቂ መፍትሄ እስኪሰጠው ድረስ፤ ከሴቶች አደባባይ ወደ ባልድራስ ትራፊክ መብራት የሚወስደው መንገድ፤ ከዛሬ ነሐሴ 25 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በሁለቱም አቅጣጫ ሙሉ በሙሉ ለትራፊክ እንቅስቃሴ ዝግ ተደርጓል፡፡ በመሆኑም አሽከርካሪዎች አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ ባለሥልጣን መስሪያቤቱ ያሳስባል፡፡ የተሻለ መንገድ፣ ለተሻለች አዲስ አባባ የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለሥልጣን

AACRA
11 083
ዛሬ የከተማ አስተዳደራችንን የቀጣይ አምስት ዓመታት እና የ2019 በጀት ዓመት እቅድ ውይይት መላው የከተማችን አመራሮች በተገኙበት አስጀምረናል። በስድስተኛው ዙር ሀገራዊ ምርጫ ህዝባችን የሰጠንን ሃላፊነት መነሻ ያደረገ ስትራቴጂክ እቅድ ነድፈን ቃላችንን በተግባር ቆጥረን ፈፅመን የከተማችንን ህዝብ ተጠቃሚ እንዲሆን እንዲሁም ከተማችን ደግሞ ተወዳዳሪ እንድትሆን አድርገናል። ይህንኑ መነሻ በማድረግ የከተማችን ነዋሪ እምነት አድሮበት ዳግም መርጦን ሀላፊነት ሰጥቶናል። የዛሬው ውይይትም የከተማችን ነዋሪ የጣለብንን እምነት እና የሰጠንን ሀላፊነት መነሻ ያደረገ፣ በቀጣይ አምስት ዓመታት እና የ2019 በጀት ዓመት የእቅድ ዝርዝር ግቦች ላይ ተወያይተን በማዳበር የባለፉት አምስት ዓመታት አፈፃፀምን በእጥፍ ለማሳደግ ዝግጁነታችንን የምናረጋግጥበት መድረክ ነው። እነዚህን ዝርዝር ውይይቶች ስናደርግ 24/7 የመፈጸም ባህላችንን ይበልጥ በማሳደግ፣ አመራራችን ከፊት ሆኖ የበለጠ እየሮጠ ህዝባችንንና የልማት አጋሮቻችንን በማስተባበርና ተሞክሮዎችን በማስፋት በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት በሀገራዊ ማንሰራራት ውስጥ የአዲስ አበባን የብልፅግና ተምሳሌትነት ለማረጋገጥ እንተጋለን። በተጨማሪም በክረምት የያዝናቸው የ90 ቀን ስራዎች ውስጥ የ60 ቀናት አፈፃፀማችንንም የምንገመግምበት የውይይት መድረክ ነው። ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ! ከንቲባ አዳነች አቤቤ የአዲስ አበባ ከተማ ኮሙኒኬሽን ቢሮ

AACRA
11 083
photo content
+6

AACRA
11 083
የከተማ አስተዳደራችንን የቀጣይ አምስት ዓመታት እና የ2019 በጀት ዓመት እቅድ ውይይት መላው የከተማችን አመራሮች በተገኙበት አስጀምረናል። በስድስተኛው ዙር ሀገራዊ ምርጫ ህዝባችን የሰጠንን ሃላፊነ
+6
የከተማ አስተዳደራችንን የቀጣይ አምስት ዓመታት እና የ2019 በጀት ዓመት እቅድ ውይይት መላው የከተማችን አመራሮች በተገኙበት አስጀምረናል። በስድስተኛው ዙር ሀገራዊ ምርጫ ህዝባችን የሰጠንን ሃላፊነት መነሻ ያደረገ ስትራቴጂክ እቅድ ነድፈን ቃላችንን በተግባር ቆጥረን ፈፅመን የከተማችንን ህዝብ ተጠቃሚ እንዲሆን እንዲሁም ከተማችን ደግሞ ተወዳዳሪ እንድትሆን አድርገናል። ይህንኑ መነሻ በማድረግ የከተማችን ነዋሪ እምነት አድሮበት ዳግም መርጦን ሀላፊነት ሰጥቶናል። የዛሬው ውይይትም የከተማችን ነዋሪ የጣለብንን እምነት እና የሰጠንን ሀላፊነት መነሻ ያደረገ፣ በቀጣይ አምስት ዓመታት እና የ2019 በጀት ዓመት የእቅድ ዝርዝር ግቦች ላይ ተወያይተን በማዳበር የባለፉት አምስት ዓመታት አፈፃፀምን በእጥፍ ለማሳደግ ዝግጁነታችንን የምናረጋግጥበት መድረክ ነው። እነዚህን ዝርዝር ውይይቶች ስናደርግ 24/7 የመፈጸም ባህላችንን ይበልጥ በማሳደግ፣ አመራራችን ከፊት ሆኖ የበለጠ እየሮጠ ህዝባችንንና የልማት አጋሮቻችንን በማስተባበርና ተሞክሮዎችን በማስፋት በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት በሀገራዊ ማንሰራራት ውስጥ የአዲስ አበባን የብልፅግና ተምሳሌትነት ለማረጋገጥ እንተጋለን። በተጨማሪም በክረምት የያዝናቸው የ90 ቀን ስራዎች ውስጥ የ60 ቀናት አፈፃፀማችንንም የምንገመግምበት የውይይት መድረክ ነው። ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ! ከንቲባ አዳነች አቤቤ የአዲስ አበባ ከተማ ኮሙኒኬሽን ቢሮ

AACRA
11 083
የአራዳ የበጎነት መንደር ግንባታ በታቀደለት ፍጥነትና ጥራት እየተከናወነ ይገኛል በአዲስ አበባ አራዳ ክፍለ ከተማ የተጀመረው የአራዳ በጎነት መንደር የግንባታ ፕሮጀክት በከፍተኛ ፍጥነት ላይ መሆኑ ተ
+3
የአራዳ የበጎነት መንደር ግንባታ በታቀደለት ፍጥነትና ጥራት እየተከናወነ ይገኛል በአዲስ አበባ አራዳ ክፍለ ከተማ የተጀመረው የአራዳ በጎነት መንደር የግንባታ ፕሮጀክት በከፍተኛ ፍጥነት ላይ መሆኑ ተገለጸ። የአራዳ የበጎነት መንደር የአቅመ ደካሞችና የሀገር ባለውለታዎች የመኖሪያ ቤት ግንባታ ሰኔ 15/2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ መጀመሩ ይታወሳል። ቀደም ሲል የደሳሳ ጎጆዎች መገኛና ለመኖር ምቹ ያልነበሩ አካባቢዎችን በመቀየር፣ በርካታ ዜጎችን ችግር ለመቅረፍ የታለመው ይህ ግዙፍ የበጎነት ተግባር በአጭር ጊዜ ውስጥ አበረታች ምዕራፍ ላይ መድረሱን አዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ ባደረገው ቅኝት ታዝቧል። የፕሮጀክቱ አማካሪ ድርጅት ተወካይ ኢንጂነር በሪሁን ደርቤ ፤ የፕሮጀክቱ ግንባታ ከተጀመረ 54 ቀናት ማስቆጠሩን አስታውቀዋል። ግንባታው በሁለት ዙሮች የተከፈለ መሆኑን የገለጹት ኢንጂነር በሪሁን፣ አንደኛው ዙር ከብሎክ 1 እስከ 3 ያሉ ብሎኮች ግንባታ የተጀመረበት ነው ብለዋል፡፡ ሁለተኛው ዙር ደግሞ ከብሎክ 4 እስከ 15 ያሉትን ብሎኮች አካቶ እየተገነባ እንደሚገኝ ጠቁመዋል። በአንደኛው ዙር ግንባታቸው የተጀመሩት ስትራክቸራል ሥራዎች ሙሉ በሙሉ የተጠናቀቁ ሲሆን የብሎክ ዎርክ እና የልስን ሥራዎችም እስከ አምስተኛ ፎቅ እየተከናወኑ ይገኛሉ ብለዋል። የግንባታ ሂደቱ በ24/7 የስራ ባሕል በከፍተኛ ጥራት እና ፍጥነት እየተከናወነ መሆኑን የገለጹት ኢንጂነር በሪሁን ፤ ይህ ስኬት እንዲመዘገብ የባለሙያዎች ቁርጠኝነት እና ቅንጅታዊ አሰራር ወሳኝ ሚና እንደተጫወተ ጠቁመዋል፡፡ በሌላ በኩል ስለግንባታው ሃሳብ የሰጡት ከአየሰና ባጫ ተቋራጭ ተወካይ ኃይለሚካኤል ዋቆሽ፣ የፊኒሺንግ፣ የቡሎኬት ግንባታ እና የልስን ስራዎችም በፍጥነት እየተከናወን መሆኑን ገልጸዋል። AMN

AACRA
11 083
የተሽከርካሪ ማቆሚያ ተርሚናልና የንግድ ማዕከል እና ፕላዛ ምርቃት ሥነ-ስርዓት ያስተላለፉት መልዕክት ከንቲባ አዳነች አቤቤ

AACRA
11 083
ፋና ዘገባ የመንገድ ሀብት አጠቃቀም አስመልክቶ የተከናወኑ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎች

AACRA
11 083
በአዲስ አበባ የተገነቡት ዘመናዊ የተሽከርካሪ ማቆሚያዎች የተገልጋዩን እንግልት የሚቀንሱ ናቸው - ኢ/ር አያልነሽ ሃ/ማርያም በአዲስ አበባ የተገነቡት ዘመናዊ የተሽከርካሪ ማቆሚያዎች የተገልጋዩን እን
+7
በአዲስ አበባ የተገነቡት ዘመናዊ የተሽከርካሪ ማቆሚያዎች የተገልጋዩን እንግልት የሚቀንሱ ናቸው - ኢ/ር አያልነሽ ሃ/ማርያም በአዲስ አበባ የተገነቡት ዘመናዊ የተሽከርካሪ ማቆሚያዎች የተገልጋዩን እንግልት የሚቀንሱ መሆናቸውን የአዲስ አበባ ከተማ የዲዛይንና ግንባታ ሥራዎች ቢሮ ኃላፊ ኢ/ር አያልነሽ ሃ/ማርያም ገለጹ፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ የትራንስፖርት ሥርዓትን ወደ ተቀናጀና ዘመናዊ አሠራር የሚያሸጋግሩ መሠረተ ልማቶችን የማስፋፋት ሥራዎች ተጠናክረው ቀጥለዋል። ኢንጂነር አያልነሽ ሃብተ ማርያም እንደገለጹት፤ አዲስ ተመርቀው ለአገልግሎት ክፍት የተደረጉት የተሽከርካሪ ማቆሚያ እና ተርሚናሎች የህብረተሰቡን እንግልት በከፍተኛ ሁኔታ የሚቀንሱ ናቸው። እያንዳንዳቸው በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የተደራጁ፣ ሙሉ በሙሉ ደህንነታቸው የተጠበቀ እና ለተገልጋዩ ህብረተሰብ ልዩ ምቾትን የሚያጎናጽፉ ናቸውም ብለዋል፡፡ በውስጣቸው የታክሲ እና አውቶብስ ተርሚናሎች፣ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ቻርጀሮች እንዲሁም የህዝብ መዝናኛ ስፍራዎች ተካተዋል። በተጨማሪ የንግድ ሱቆች፣ ካፊቴሪያ እና ሬስቶራንቶች፣ የልጆች መጫወቻ እና ማረፊያ ስፍራዎች እንዲሁም ምቹ የተሳፋሪ መጠበቂያ ስፍራዎች ተሟልተዋል። ተርሚናሎቹ አሳንሰሮችን እና ንጹህ መጸዳጃ ቤቶችን እንዲሁም የደህንነት እና አደጋ ቅድመ መከላከያ ስርዓቶችን ያካተቱም ናቸው፡፡ ፕሮጀክቶቹ በሙሉ አቅማቸው ወደ አገልግሎት ሲገቡ በከተማዋ ጤናማ እና ደህንነቱ የተጠበቀ የተሽከርካሪ ፍሰት እና የእግረኛ እንቅስቃሴ እንዲኖር ከማስቻላቸውም ባሻገር ለከተማዋ የ«ስማርት ሲቲ» ውጥን እውን መሆን ጉልህ ሚና ይጫወታሉ።

AACRA
11 083
የጨረታ ማስታወቂያ፡- የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለሥልጣን የተለያዩ ፕሮጀክቶችን የዲዛይን ክለሳና ግንባታ ቁጥጥር ስራዎች የሚሰሩ አማካሪ መሀንዲሶችን በጨረታ አወዳድሮ ለመቅጠር የወጣ ማስታወቂያ
+2
የጨረታ ማስታወቂያ፡- የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለሥልጣን የተለያዩ ፕሮጀክቶችን የዲዛይን ክለሳና ግንባታ ቁጥጥር ስራዎች የሚሰሩ አማካሪ መሀንዲሶችን በጨረታ አወዳድሮ ለመቅጠር የወጣ ማስታወቂያ

AACRA
11 083
+2
የጨረታ ማስታወቂያ፡- የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለሥልጣን የተለያዩ ፕሮጀክቶችን የዲዛይን ክለሳና ግንባታ ቁጥጥር ስራዎች የሚሰሩ አማካሪ መሀንዲሶችን በጨረታ አወዳድሮ ለመቅጠር የወጣ ማስታወቂያ

AACRA
11 083
በመዲናዋ የጎርፍ ተጋላጭነትን ለማስቀረት ቅንጅታዊ ሥራዎች እየተከናወኑ ናቸው AMN - ነሐሴ 20/2018 ዓ.ም አዲስ አበባን በክረምት ወራት ከሚከሰቱ የጎርፍ፣ የመሬት መንሸራተት እና የፍሳሽ ቱቦ መዘጋት አደጋዎች ለመከላከል መጠነ ሰፊ የንቅናቄ ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ። የከተማዋ የጎርፍ አደጋ ተጋላጭነቶች እንደ መልክአ ምድራዊ አቀማመጥ፣ የመንገዶች አገነባብ ጉድለቶች፣ በወንዝ ዳርቻዎች የሚደረጉ ሕገወጥ ግንባታዎች፣ የፍሳሽ ማስወገጃዎች በአግባቡ አለመሰራት እንዲሁም ወንዞች በደለልና በቆሻሻ መደፈን ዋና ዋና ምክንያቶች መሆናቸው በጥናት ተለይቷል። ይህን ስጋት ለመቅረፍ የአዲስ አበባ የእሳትና ድንገተኛ አደጋ ኮሚሽን ከከተማዋ መንገዶች ባለሥልጣን እና ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ሰፊ የማስተካከያ ሥራዎችን አከናውኗል። በወንዝ ዳርቻዎች ጎርፍ ወደ መኖሪያ አካባቢዎች እንዳይገባ የሚከላከሉ የድጋፍ ግንቦች እየተገነቡ ሲሆን፣ በደለልና በቆሻሻ የተደፈኑ የፍሳሽ ማስወገጃ ቱቦዎችን የማጽዳት፣ የመጠገን እና የማስፋፋት ሥራዎች ተጠናክረው ቀጥለዋል። ከዚህ ባለፈም ነዋሪዎችን ያሳተፉ የአካባቢ ፅዳት ንቅናቄዎች በመካሄድ ላይ ይገኛሉ። የአካባቢ ፅዳትና ውበት የመንግሥት ኃላፊነት ብቻ ሳይሆን የሁሉም ነዋሪ የጋራ ተግባር በመሆኑ፣ በንቅናቄው የተሳተፉት ነዋሪዎች የጎርፍ መውረጃ ቱቦዎችንና አካባቢያቸውን ከቆሻሻ በማፅዳት የዝናብ ውሃ ፍሰት እንዳይስተጓጎል አድርገዋል። ይህ የነዋሪዎች ንቁ ተሳትፎ ንፁህ ፣ ውብና ለኑሮ ምቹ የሆነች ከተማን በጋራ ለመፍጠር ያለውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ ነው። የከተሞች ዘመናዊነትና ምቹነት ተፈጥሯዊ አደጋዎችን በሚቋቋሙበት አቅም የሚለካ በመሆኑ፣ ህብረተሰቡ አሁንም ቆሻሻዎችን በአግባቡ በማስወገድ እና የፍሳሽ ቱቦዎችን ከቆሻሻ ነፃ በማድረግ የየበኩሉን ኃላፊነት መወጣቱን ሊያጠናክር ይገባል። AMN

AACRA
11 083
photo content
+4

AACRA
11 083
photo content
+1

AACRA
11 083
የመንገድ ጥገና ሥራ ማጠናቀቂያ መግለጫ የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለሥልጣን፤ ከአያት 49 ወደ ፊጋ በሚወስደው መንገድ ላይ 72 ድልድይ አካባቢ የመንገድ ጥገና ሥራ ለማካሄድ ከሰኞ ነሐሴ 18 ቀ
የመንገድ ጥገና ሥራ ማጠናቀቂያ መግለጫ የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለሥልጣን፤ ከአያት 49 ወደ ፊጋ በሚወስደው መንገድ ላይ 72 ድልድይ አካባቢ የመንገድ ጥገና ሥራ ለማካሄድ ከሰኞ ነሐሴ 18 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ መንገዱ በከፊል ለትራፊክ እንቅስቃሴ ዝግ እንደሚደረግ ማሳወቁ ይታወሳል። በዚሁ መሠረት በክረምቱ ወቅት በአካባቢው ይከሰት የነበረውን የጎርፍ አደጋ ስጋት በጊዜያዊነት መቅረፍ የሚያስችል አሰቸኳይ የጥገና ሥራ በማጠናቀቅ፤ ከነገ ረቡዕ ነሐሴ 20 ቀን 2018 ዓ.ም ንጋት ጀምሮ መንገዱ ሙሉ በሙሉ ለትራፊክ እንቅስቃሴ ክፍት የሚደረግ መሆኑን ከወዲሁ ያሳውቃል። የመንገዱ ተጠቃሚዎች ለጥገና ሥራው መቀላጠፍ ላበረከቱት አውንታዊ አስተዋጽኦ ባለሥልጣን መስሪያ ቤቱ በዚህ አጋጣሚ ልባዊ ምስጋናውን ያቀርባል። በዚህ አካባቢ በተደጋጋሚ እያጋጠመ ያለውን የጎርፍ አደጋ ስጋት በዘላቂነት ለመፍታት የሚያስችል የግንባታ ሥራ በቀጣዮቹ 3 ወራት ውስጥ የሚጀመር መሆኑን ከወዲሁ ሲገልፅ ከፍ ባለ አክብሮት ነው። የተሻለ መንገድ፣ ለተሻለች አዲስ አበባ የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለሥልጣን

AACRA
11 083
በአንድነት እንቁም፤ በቁርጠኝነት እንስራ፤ የእናት ሀገራችንን ከፍታ እናረጋግጥ! #Ethiopia #PMOEthiopia

AACRA
11 083
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች ፤ እንኳን ለ1 ሺህ 501ኛው የነቢዩ መሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) የመውሊድ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! በዓሉን ስናከብር እንደከዚህ ቀደሙ የተቸገሩ ወገኖችን በመርዳት፤ ለ
+1
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች ፤ እንኳን ለ1 ሺህ 501ኛው የነቢዩ መሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) የመውሊድ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! በዓሉን ስናከብር እንደከዚህ ቀደሙ የተቸገሩ ወገኖችን በመርዳት፤ ለሌላቸው በማካፈል፣ የታረዙትን በማልበስ፣ የታመሙትን በመጠየቅ እንዲሆን እመኛለሁ። በድጋሚ እንኳን አደረሳችሁ - ኢድ ሙባረክ! ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ! ከንቲባ አዳነች አቤቤ

AACRA
11 083
እንኳን ለ1501ኛው የነቢዩ መሐመድ(ሰዐወ) የመውሊድ በዓል አደረሳችሁ የነቢዩ መሐመድ ታሪክ ትውልድን ለበጎ ከሚቀርጹ ታሪኮች መካከል አንዱ ነው፡፡ የተጠሩበትን ዓላማ ማክበር፤ ለተጠሩበት ዓላማ ዋጋ መክፈል፤ የተጠሩበትን ለሌሎች ማካፈል፤ የተጠሩበትን አክብሮ መኖር - እነዚህ ሁሉ ሺ መጻሕፍት የሚወጧቸው ትምህርቶች ናቸው፡፡ ነቢዩ የተጠሩበትን ዓላማ በሚገባ ስለተገነዘቡ አክብረው ኖረዋል፡፡ የተጠሩት ለተራና ርካሽ ነገር እንዳልሆነ ተገንዝበዋል፡፡ የተጠሩት ትውልድን ለመቅረጽና ታሪክን ለመቀየር መሆኑን አምነዋል፡፡ ያንንም በቃላቸው፣ በሥራቸውና በኑሯቸው አክብረውት ነኖረዋል፡፡ ለታላቅ ሀገራዊ ዓላማ ተጠርተናል ብለን የምናምን ከሆነ ይህ የነቢዩ ሕይወት ታላቅ ትምህርት ይሆነናል፡፡ የተጠራንበትን ዓላማ በንግግራችን፣ በሥራችንና በሕይወታችን እንግለጠው፡፡ ነቢዩ ለተጠሩበት ዓላማ ዋጋ ከፍለዋል፡፡ ከቦታቸው ተሰደዋል፤ ምግብና መጠለያ ተነፍገዋል፤ ከቤተሰቦቻቸው ተለይተዋል፡፡ ለሞት በሚያበቁ ፈተናዎች ውስጥ አልፈዋል፡፡ ጦርነት ተከፍቶባቸዋል፡፡ ነገር ግን ሁሉንም በአላህ ኃይል አሸንፈዋል፡፡ ክብር ያለ መከራ አይገኝምና፡፡ እውነተኛ ሰው ለዓላማው እንደ ነቢዩ መሐመድ(ሰዐወ)ዋጋ ይከፍላል፡፡ ዓላማው የሚያስገኘውን ክብርና ጥቅም ብቻ ሳይሆን ዓላማው የሚያስከፍለውን መሥዋዕትነት ለመክፈል ዝግጁ ይሆናል፡፡ ነቢዩ መሐመድ(ሰዐወ) ከአላህ የደረሳቸውን መልእክት ለራሳቸው ብቻ አላስቀሩም፡፡ የተጠሩበትን ለሌሎች ለማካፈል ተግተዋል፡፡ መጀመሪያ በጣት ለሚቆጠሩ ሰዎች፣ በኋላም ለቅርብ ሱሐባዎች፣ በመጨረሻም ለዓለም መልእክቱን አዳርሰዋል ፡፡ እሳቸው የዘሩት ዘር እያፈራና እየጎመራ ተጉዟል፡፡ ዓላማችንን እኛ ማወቃችንና ማመናችን ብቻ ጥቅም የለውም፡፡ ሌሎች እንዲያውቁና እንዲያምኑ ልክ እንደነቢዩ ተገትተን መድከም አለብን፡፡ የነቢዩን መውሊድ ስናከብር ከሕይወታቸው እየተማርን፤ የተማርነውንም ለሀገረ መንግሥት ግንባታችን እየተጠቀምን እንዲሆን አደራ እላለሁ፡፡ በድጋሚ መልካም የመውሊድ በዓል ይሁንልን። ኢትዮጵያ በልጆቿ ጥረት ታፍራና ተከብራ ለዘላለም ትኑር!! ፈጣሪ ኢትዮጵያና ሕዝቦቿን ይባርክ! ነሐሴ 19 ቀን 2018 ዓ.ም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

AACRA
11 083
photo content

AACRA
11 083
ባለሥልጣን መስሪያቤቱ በተለያዩ የከተማዋ አካባቢዎች የትራፊክ ፍሰትን ለማሻሻል የአስፋልት ጥገና ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል ፡፡ ከነዚህም መካከል ዘነበወርቅ አደባባይ በክረምቱ ዝናብ እና በአገልግሎ
ባለሥልጣን መስሪያቤቱ በተለያዩ የከተማዋ አካባቢዎች የትራፊክ ፍሰትን ለማሻሻል የአስፋልት ጥገና ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል ፡፡ ከነዚህም መካከል ዘነበወርቅ አደባባይ በክረምቱ ዝናብ እና በአገልግሎት ብዛት ተቦርቡሮ የነበረ የአስፋልት መንገድ ጥገና ተደርጎለት የተሻለ የትራፊክ እንቅስቃሴ እየሰጠ ይገኛል

AACRA
11 083
የግንባታ ስራ ጨረታ ማስታወቂያ፡ የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለስልጣን "ከ ኮካ -ገዳመ እየሱስ መሳለሚያ የአስፋልት መንገድ ግንባታ የግንባታ ሥራዎች " በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል።
+9
የግንባታ ስራ ጨረታ ማስታወቂያ፡ የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለስልጣን "ከ ኮካ -ገዳመ እየሱስ መሳለሚያ የአስፋልት መንገድ ግንባታ የግንባታ ሥራዎች " በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል። ፍላጎት ያላቸው ተቋራጮች በሙሉ ከታች ባለው የeGP system ሊንክ በመግባትና አስፈላጊውን መረጃ በመሙላት መሳተፍ ይችላሉ። Construction Works Tender Notice: The Addis Ababa City Roads Authority invites eligible contractors through an Open Tender for the Construction Works of Coca - Gedame Eyesus - Mesalemia Asphalt Road Project. Qualified firms can participate by registering and submitting all required information through the official eGP System link below. Procurement Reference No.: AACRA-ICB-W-0007-2019-BID-Open eGP System Link: https://production.egp.gov.et/egp/bids/report/tendering/fea30a5e-b8f7-4e3a-8bff-a88fac1684fb/open