ch
Feedback
AACRA

AACRA

前往频道在 Telegram

Addis Ababa City Roads Authority (AACRA) is a government organization under the Addis Ababa City Adminstration. It was established on March 1998 with the aim of realizing sustainable road infrastructure and creating interchangeable road transport to A.A.

显示更多

📈 Telegram 频道 AACRA 的分析概览

频道 AACRA (@addisroads) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 10 866 名订阅者,在 交通 类别中位列第 2 171,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 3 066

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 10 866 名订阅者。

根据 08 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 49,过去 24 小时变化为 -3,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 10.47%。内容发布后 24 小时内通常能获得 7.89% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 1 138 次浏览,首日通常累积 857 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 2

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
Addis Ababa City Roads Authority (AACRA) is a government organization under the Addis Ababa City Adminstration. It was established on March 1998 with the aim of realizing sustainable road infrastructure and creating interchangeable road transport to ...

凭借高频更新(最新数据采集于 09 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 交通 类别中的关键影响点。

10 866
订阅者
-324 小时
-237
+4930
帖子存档
AACRA
10 866
photo content
+1

AACRA
10 866
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ፤ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 30ኛው መደበኛ ስብሰባ ላይ በሰላምና ደህንነት፣ ኢኮኖሚ፣ ጤና፣ ትምህርት፣ የውጭ ግንኙነትን ጨምሮ በሌሎች ዘርፎች ዙሪያ የመንግሥትን አፈጻጸም እና የቀጣይ እቅዶች አብራርተዋል። ‎ ‎የፕሪቶሪያው ስምምነት ጦርነቱን ለማቆም የተደረገ መሆኑን ጠቅሰው፣ በአሁኑ ወቅት በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደርና በክልሉ የሚታዩ አዳዲስ ውጥረቶችን እንዲሁም የክልሉን ሰላም ለማደናቀፍ የሚደረጉ እንቅስቃሴዎችን አንስተዋል። በማኅበራዊ ጉዳዮች ላይ ደግሞ፣ በኢትዮጵያ የሚከሰቱ ግጭቶች የሃይማኖት ወይም የብሔር ሳይሆኑ በፖለቲካና በኢኮኖሚ ጥቅም ሳቢያ የሚነሱ መሆናቸውን ገልጸዋል። በመሆኑም ሕዝቡ የጥላቻ ቅስቀሳዎችን በመቃወም ሃገራዊ ተቋማትን እንዲደግፍ ጥሪ አቅርበዋል። ‎ ‎የሀገር በቀል ኢኮኖሚ ማሻሻያ ፕሮግራም የዋጋ ንረትን ለመቆጣጠር፣ የግሉን ዘርፍ ለማበረታታት፣ ግብርና እና ቱሪዝምን ለማነቃቃት እንዲሁም የውጭ ምንዛሬ ገቢን ለማሳደግ አስተዋጽዖ እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል። በግብርና 29 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በማረስ 1.3 ቢሊዮን ኩንታል ምርት መሰብሰቡን፣ ዘርፉም 7.7 በመቶ ማደጉን ጠቅሰዋል። በኢንዱስትሪ የማኑፋክቸሪንግ አቅም ከ47 በመቶ ወደ 67 በመቶ ማደጉን፣ አዳዲስ ኢንዱስትሪ ፓርኮች መገንባታቸውን እና በሀገር ውስጥ ምርትን በማስፋፋት እስከ 5 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ የውጭ ምንዛሬ መቆጠቡን ገልጸዋል። ‎ ‎የኢትዮጵያ አየር መንገድ 21 ሚሊዮን ተጓዦችን ማጓጓዙን፣ ከ200 በላይ ዓለም አቀፍ ጉባኤዎች በሀገሪቱ መካሄዳቸውን እና የአገልግሎት ዘርፉ 9.8 በመቶ ማደጉን ጠቅሰዋል። በጤና ዘርፍ፤ የሀገር ውስጥ የመድኃኒት ምርት ከ4 በመቶ ወደ 44 በመቶ ማደጉን፣ አዳዲስ ሆስፒታሎች መገንባታቸውን፣ የወባ መከላከል እና የክትባት ተደራሽነት መስፋፋቱን አብራርተዋል። በትምህርት፤ 35 ሺህ የመዋዕለ ሕፃናት ትምህርት ቤቶች እና 35 ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መገንባታቸው የትምህርት ጥራትን ለማሻሻልና ኩረጃን ለማስወገድ እየተደረገ ያለውን ጥረት ያሳያል። በመኖሪያ ቤት ዘርፍ፤ ባለፉት ሰባት ዓመታት 1.2 ሚሊዮን ቤቶች መገንባታቸውን እና በቀጣይ 1.5 ሚሊዮን ተጨማሪ ቤቶች ለመገንባት ዕቅድ መያዙን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ በመቋቋም፣ መጠቀም እና መግራት በተባሉ ሶስት መርሆች ላይ የተመሰረተ መሆኑን ገልጸው በማንኛውም ብሔራዊ ውሳኔ ላይ የውጭ ጣልቃ ገብነት እንደማንቀበል አስረድተዋል። በተጨማሪም የኢትዮጵያ ሉዓላዊነት ሊደፈር እንደማይችልና ይህንን ለማስጠበቅ አቅም እየተገነባ መሆኑን አስታውቀዋል። ‎ ‎በአጠቃላይ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሰላም ማስፈን፣ ኢኮኖሚን ማሻሻል፣ በምግብ ራስን መቻል፣ የትምህርት ጥራትን ማሻሻል፣ ኢንዱስትሪና አገልግሎትን ማሳደግ፣ የሀገሪቱን ሉዓላዊነት በማስከበር እንዲሁም ሌሎች ማኅበራዊ አገልግሎቶችን በማስፋፋት የተገኙ ውጤቶችን በመዘርዘር የቀጣይ ትኩረትም እነዚህን ስኬቶች በማስቀጠል ዘላቂ ልማትና መረጋጋትን ማጠናከር እንደሚሆን አስገንዝበዋል። #የጠሚሩምላሾች #PMOEthiopia

AACRA
10 866
የፓርላማ ቆይታችንን ተከትሎ የችግኝ ተከላ መርሃግብር አከናውነናል። በዚህ የአረንጓዴ ዐሻራ ወቅት ተስፋን መትከላችንን እንቀጥላለን! ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
+4
የፓርላማ ቆይታችንን ተከትሎ የችግኝ ተከላ መርሃግብር አከናውነናል። በዚህ የአረንጓዴ ዐሻራ ወቅት ተስፋን መትከላችንን እንቀጥላለን! ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

AACRA
10 866
ግብርና እና የምግብ ሉዓላዊነትን በተመለከተ፦ በዘንድሮው የምርት ዘመን 29 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በማረስ 1.3 ቢሊዮን ኩንታል ምርት መሰብሰብ መቻሉ እንዲሁም ዘርፉ የ7.7 በመቶ ዕድገት ማስመዝገቡ
ግብርና እና የምግብ ሉዓላዊነትን በተመለከተ፦ በዘንድሮው የምርት ዘመን 29 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በማረስ 1.3 ቢሊዮን ኩንታል ምርት መሰብሰብ መቻሉ እንዲሁም ዘርፉ የ7.7 በመቶ ዕድገት ማስመዝገቡ፤ የኢትዮጵያ ግብርና እያሳየ ላለው መዋቅራዊ ሽግግር ግልጽ ማሳያ ነው። በሀገር አቀፍ ደረጃ የተተገበረው የ‘ሌማት ትሩፋት’ መርሃ-ግብር አስደናቂ ውጤቶችን ያስመዘገበ ሲሆን፣ በተለይም አቮካዶን ወደ ውጭ በመላክ ከአፍሪካ 2ኛ ደረጃን መያዝ መቻሉ ለሀገሪቱ ተጨማሪ ከፍተኛ ገቢ በማስገኘት አስደናቂ ድል እንዲመዘገብ አስችሏል። ከዚህም በላይ ለረጅም ጊዜ በከባድ ድርቅ ይጎዳ የነበረው የቦረና ቀጣና ዛሬ በሰፊ የስንዴ ልማት ተሸፍኖ ማየት መቻሉ የስትራቴጂያዊ ግብርና ስራችንን ስኬታማነት ያረጋግጣል። ምንም እንኳ የዓለም አቀፍ ጫናዎች ቢበዙም፣ የማዳበሪያ እና የነዳጅ ዋጋ ቢንርም፣ በቁርጠኝነትና በጠንካራ ስራ በምግብ ራሳችንን ለመቻልና በአፍሪካ ላይ የተለጠፈውን የረሃብ ታሪክ ለመቀየር በተግባር እየሰራን እንገኛለን፤ ምክንያቱም ምርጫችን ለምኖ መኖር ሳይሆን ሰርቶ ማደር ነው! #የጠሚሩምላሾች #PMOEthiopia

AACRA
10 866
ከ100 በላይ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ሥራ ጀምረዋል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ ላይ ተገኝተው ማብራሪያ የሰጡት ጠቅላይ
+3
ከ100 በላይ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ሥራ ጀምረዋል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ ላይ ተገኝተው ማብራሪያ የሰጡት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፣ በኢትዮጵያ ከ100 በላይ የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎቶች በይፋ ሥራ መጀመራቸውን አስታውቀዋል። የኢትዮጵያን የዲጂታል ጉዞና የቴክኖሎጂ ሽግግር አስመልክተው በሰጡት ሰፊ ማብራሪያ፣ በሀገራችን ከ5 ሚሊዮን በላይ ወጣቶችን በኮደርስ ሥልጠና ላይ በመመዝገብ በዚህም ትልቅ ስኬት መመዝገቡን ገልጸዋል። የቴክኖሎጂ ልማቱ በኢኮኖሚውና በማኅበራዊ ዘርፉ ላይ እያመጣ ያለውን ዘርፈ-ብዙ ለውጥ የጠቀሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ በአሁኑ ወቅት የሞባይል ባንኪንግ አገልግሎት በከፍተኛ ደረጃ እያደገ እንደሚገኝና የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) ዩኒቨርሲቲ መዋቅርም በጥሩ ሁኔታ ላይ መሆኑን አስረድተዋል። አክለውም በተለይም በስታርት አፖች (አዳዲስ የፈጠራ ሥራዎች)፣ በሥራ ዕድል ፈጠራ፣ በገቢ አሰባሰብ እንዲሁም በአጠቃላይ የአገልግሎት አሰጣጥ ሥርዓት ላይ ቴክኖሎጂ ከፍተኛና ስትራቴጂካዊ ሚና እየተጫወተ እንደሚገኝ በአጽንኦት ገልጸዋል።

AACRA
10 866
የትምህርት ዘርፍ ጥራት እና ለውጦችን በተመለከተ፦ የትምህርት ዘርፍ ጥራትን ለማረጋገጥ በተሰሩ ስራዎች ከፍተኛ ለውጥ እየመጣ ነው። ባለፉት ዓመታት ተማሪዎች በራሳቸው ተማምነው ፈተና የሚወስዱበት አሰ
የትምህርት ዘርፍ ጥራት እና ለውጦችን በተመለከተ፦ የትምህርት ዘርፍ ጥራትን ለማረጋገጥ በተሰሩ ስራዎች ከፍተኛ ለውጥ እየመጣ ነው። ባለፉት ዓመታት ተማሪዎች በራሳቸው ተማምነው ፈተና የሚወስዱበት አሰራር ተተግብሯል፤ በዚህም የኩራጃ ባህልን ማስረቀት ተችሏል። ትምህርት ከታች ካልተሠራ ከላይ መሥራት ውጤታማ አያደርግም፤ ለመዋዕለ ህጻናት ማስፋፊያ በተሰጠው ትኩረት 35 ሺህ መዋዕለ ሕጻናትን መገንባት ተችሏል። የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ፣ ኩረጃን ለማስቀረት፣ ትምህርትን በቴክኖሎጂ ለማስፋፋት እየተደረገ ያለው ሙከራ ተስፋ ሰጪ ነው። የአንደኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችም ደረጃቸውን የጠበቁ እጅግ አበረታች ግንባታዎች እየተከናወኑ ይገኛል። #የጠሚሩምላሾች #PMOEthiopia

AACRA
10 866
የጤና ጉዳዮችን በሚመለከት፦ የሀገር ውስጥ የመድኃኒት ማምረት አቅማችንን ከነበረበት 4 በመቶ ወደ 44 በመቶ ማሳደግ ችለናል። ለአጠቃላይ መድኃኒት ግዢ 70 ቢሊዮን ብር፣ ለሕክምና መሣሪያዎች ግዢ ደ
የጤና ጉዳዮችን በሚመለከት፦ የሀገር ውስጥ የመድኃኒት ማምረት አቅማችንን ከነበረበት 4 በመቶ ወደ 44 በመቶ ማሳደግ ችለናል። ለአጠቃላይ መድኃኒት ግዢ 70 ቢሊዮን ብር፣ ለሕክምና መሣሪያዎች ግዢ ደግሞ ከ60 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ አድርገናል። ባለፉት ወራት በርካታ ሆስፒታሎችን መርቀን ለአገልግሎት ያበቃን ሲሆን፣ በሚቀጥሉት ወራት የሚመረቁ ሌሎች ተቋማት ይኖራሉ። ለግንባታ ሂደት ትኩረት ከተሰጣቸው መካከል የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታልን የአልጋ አቅም በአንድ ሺህ ያሳደገው አዲሱ ሕንፃ ይጠቀሳል። በሀገር ውስጥ የሚመረቱ መድኃኒቶችም በዓለም አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት እንዲኖራቸው ተደርገው የተሰሩ ናቸው። ቀጣዩ ትኩረታችን በውጭ ሀገራት የምናያቸውን ዘመናዊና ደረጃቸውን የጠበቁ ሆስፒታሎችን በሀገራችን መገንባት ነው። በሌላ በኩል፣ የወባ በሽታን ለመቀነስ በተደረገው የተቀናጀ ጥረት 14 ሚሊዮን አጎበር የተሰራጨ ሲሆን፣ በ3 ሚሊዮን መኖሪያ ቤቶች ላይ ደግሞ የጸረ-ወባ ኬሚካል ተረጭቷል። በተጨማሪም፣ ቀደም ሲል የክትባት ተደራሽነት ባልነበረባቸው 58 ወረዳዎች ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ ክትባት መስጠት ተችሏል። #የጠሚሩምላሾች #PMOEthiopia

AACRA
10 866
ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያን በተመለከተ የኢትዮጵያን ብልጽግና እና ሉዓላዊነት ለማረጋገጥ የኢኮኖሚ መዋቅሩን በዘመናዊ መንገድ መቅረጽ እና ማሻሻል የሚያስችሏትን ስትራቴጂዎች ቀርጻ ወደ ተግባር ገብ
ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያን በተመለከተ የኢትዮጵያን ብልጽግና እና ሉዓላዊነት ለማረጋገጥ የኢኮኖሚ መዋቅሩን በዘመናዊ መንገድ መቅረጽ እና ማሻሻል የሚያስችሏትን ስትራቴጂዎች ቀርጻ ወደ ተግባር ገብታለች። ግብርናን በቴክኖሎጂ በማዘመንና ቱሪዝምን በማስፋፋት፣ የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥና የውጭ ምንዛሬን ማሳደግ ቀዳሚ ተግባሩ ያደረገው የሀገር በቀል ኢኮኖሚ ማሻሻያ፤ የዋጋ ንረትን መቆጣጠር እና የግል ዘርፉን በማበረታታት መዋቅራዊ ለውጥ ማምጣት ችሏል። ይህ የኢኮኖሚ ለውጥ የዓለም አቀፍ ጫናዎችን የመቋቋም፣ እንቅፋቶችን ወደ ዕድል የመቀየር እና የራስን ብሔራዊ ጥቅም የማስከበር መርሆዎችን በተግባር እያሳየ ይገኛል። #የጠሚሩምላሾች #PMOEthiopia

AACRA
10 866
ኢትዮጵያ ከምስራቅ አፍሪካ በመግዛት አቅም ተመጣጣኝነት ቀዳሚ መሆኗን አይኤምኤፍ ገለፀ! ኢትዮጵያ በመግዛት አቅም ተመጣጣኝነት (Purchasing Power Parity - PPP) ስሌት ከምስራቅ አፍሪ
ኢትዮጵያ ከምስራቅ አፍሪካ በመግዛት አቅም ተመጣጣኝነት ቀዳሚ መሆኗን አይኤምኤፍ ገለፀ! ኢትዮጵያ በመግዛት አቅም ተመጣጣኝነት (Purchasing Power Parity - PPP) ስሌት ከምስራቅ አፍሪካ ቀዳሚ መሆኗን የዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (አይኤምኤፍ) አስታወቀ። የዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም ባወጣው ሪፖርት፣ ኢትዮጵያ በዚሁ የመግዛት አቅም ተመጣጣኝነት ሚዛን 558 ነጥብ 93 ቢሊየን ዶላር የሚያህል ግዙፍ ዓመታዊ አጠቃላይ የአገር ውስጥ ምርት (GDP-PPP) ማስመዝገቧን ጠቅሷል፡፡ በዚህም ኢትዮጵያ ከኬንያ እና ታንዛኒያ በመቅደም ከምስራቅ አፍሪካ በአንደኝነት እንድትቀመጥ አስችሏታል። እነዚህ ሦስቱ ሀገራት (ኢትዮጵያ፣ ኬንያ እና ታንዛኒያ) በጋራ 1 ነጥብ 35 ትሪሊየን ዶላር ዓመታዊ የመግዛት አቅም ተመጣጣኝነት ጥቅል ዓቅም ማስመዘገባቸውን የአይኤምኤፍ ሪፖርት አመልክቷል፡፡ ይህም ከደረጃ 4 እስከ 19 ላይ የሚገኙ በርካታ የቀጠናው ሀገራት በድምሩ ካስመዘገቡት የኢኮኖሚ አቅም የተሻለ ሆኖ መገኘቱን የሪፖርቱ ትንታኔ አመልክቷል።

AACRA
10 866
በ6ኛው የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 30ኛ መደበኛ ስብሰባ ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተነሡ ጥያቄዎች፦ ********************* 👉 የወ
+7
በ6ኛው የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 30ኛ መደበኛ ስብሰባ ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተነሡ ጥያቄዎች፦ ********************* 👉 የወደብ የኅልውናችን ጉዳይ ነው፤ የወደብና የባህር በር ጉዳይ ምን ደረጃ ላይ እንዳለ ቢገልጹልን? 👉 የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሂደት በተያዘለት የጊዜ ሠሌዳ መሠረት ተጠናቅቆ የታለመለትን ሀገራዊ ዓላማ እንዲያሳካ መንግሥት በቀጣይ ምን ዓይነት የሎጂስቲክስ፣ ፖለቲካዊና ተቋማዊ ድጋፍ ያደርጋል? 👉 ተጀምረው ላልተጠናቀቁ እና ታቅደው ላልተጀመሩ ፕሮጀክቶች ምን የታሰበ ነገር አለ? 👉 አነስተኛ ገቢ ላላቸው እና ለመንግሥት ሠራተኞች የኑሮ ጫናን ለመቋቋም ምን ታስቧል፤ ከሚመሠረተው አዲሱ መንግሥት ምን እንጠብቅ? 👉 የተማሪዎች ምገባ ፕሮግራም የሰብዓዊ መብት ጉዳይ ስለሆነ ለሁሉም ክልሎች አስገዳጅ ሆኖ ቢቀርብ? 👉 የመንግሥት መዋቅር ተጠቅሞ በዜጎች ላይ ምዝበራ የሚፈጽሙ አካላት ላይ ገዥው ፓርቲ መዋቅሩን የማጽዳት እና ተጠያቂነትን የማስፈኑን ጉዳይ እንዴት ሊያስተካክለው አስቧል? 👉 ከፀጥታ አኳያ እየተሻሻሉ ያሉ ጉዳይ ቢኖርም፣ አሁንም አንዳንድ ቦታዎች ችግሮች አሉ፤ በዚህ ጉዳይ ላይ ምን መፍትሔ ለመስጠት ታስቧል? 👉 ከነዳጅ ጋር በተያያዘ፦ መንግሥት ለነዳጅ ድጎማ ቢያደርግም የነዳጅ ሽያጭ እና ስርጭት ከብልሹ አሠራር ሊድን አልቻለም። በዚህ ላይ መንግሥት የያዘው መፍትሔ ምንድን ነው? 👉 በትግራይ ክልል ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እና የትግራይ ሕዝብ የሰላም እንዲያገኝ በመንግሥት በኩል እየተደረገ ያለውን ጥረት ቢያሳውቁን? 👉 ሰላምን ወደ ዘላቂ መሠረት ለማሸጋገር ከምሁራን፣ ከፖለቲካ ፓርቲዎች እና ከህዝቡ ምን አይነት ንቁ ተሳትፎ ይጠበቃል? 👉 በትላልቅ ፕሮጀክቶች ምክንያት የሚነሡ ዜጎች

AACRA
10 866
photo content

AACRA
10 866
photo content

AACRA
10 866
የዜጎችን አኗኗር ምቹ እና ዘመናዊ ማድረግ የኮሪደር ልማት መርሃ-ግብራችን ዋነኛ ግብ ነው። ‎ያየነው የአርባ ምንጭ ከተማ የኮሪደር ልማት ፕሮጀክት፤ ዘመናዊ የአስፋልት መንገድ እና መብራቶችን እና ዲ
+9
የዜጎችን አኗኗር ምቹ እና ዘመናዊ ማድረግ የኮሪደር ልማት መርሃ-ግብራችን ዋነኛ ግብ ነው። ‎ያየነው የአርባ ምንጭ ከተማ የኮሪደር ልማት ፕሮጀክት፤ ዘመናዊ የአስፋልት መንገድ እና መብራቶችን እና ዲጂታል ስክሪኖችን ያካተተ ሲሆን በተጠናቀቁት የኮሪደር ስራዎች ላይ አገልግሎቱ ተጀምሯል። ‎ ‎ጥራቱን የጠበቀ ዘመናዊ መሠረተ-ልማትን ከአረንጓዴ ልማት ጋር በማስተሳሰር የከተሞቻችንን ምቹነት የማረጋገጥ ስራችን ተጠናክሮ ይቀጥላል!

AACRA
10 866

AACRA
10 866
የጎርፍ መከላከል ቅድመ-ዝግጅት ሥራዎች ባለሥልጣን መስሪያቤቱ ለሸገር ኤፍ-ኤም ሬዲዮ ከሰጠው ማብራሪያ የተወሰደ

AACRA
10 866
Repost from AACRA

AACRA
10 866
የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ሙህዲን ረሻድ በአዲስ ሚዲያ ኔትወርክ አገልጋይ ፕሮግራም ላይ የሰጡት ማብራሪያ

AACRA
10 866
የእንጦጦ-ቀበና የወንዝ ዳርቻ ልማት ለነዋሪዎች አዲስ የስራ እድልና ንፁህ የመኖሪያ ስፍራ የፈጠረ ነው- የቀበናና አካባቢው ነዋሪዎች

AACRA
10 866
photo content

AACRA
10 866
የእንጦጦ - ቀበና ወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት የዚህ ትውልድ ደማቅ አሻራ፤ የመጪው ትውልድ የልማት ምንዳ!! በአሻጋሪ እሳቤ፣ የጋራ ህልምን ወደ ታላቅ ድል መቀየር እንደሚቻል አዲስ አበባ በተግባር እያሳየች ትገኛለች። በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐብይ አህመድ እና በክብርት ከንቲባ አዳነች አቤቤ የሚመራው፣ «ሰርቶ ማሳየትና ሰርቶ ማሰራት»ን መርሁ ያደረገው ቁርጠኛ አመራር ለከተማችን ዘላቂ ትንሳኤ የማይደበዝዝ ታሪካዊ አሻራውን አሳርፏል። የዚህ ታላቅ ስኬት ማሳያ የሆነውና በአጭር ጊዜ ተጠናቆ ለህዝብ አገልግሎት ክፍት የተደረገው የእንጦጦ _ ቀበና የወንዝ እና የወንዝ ዳርቻ ፕሮጀክት የአዲስ አበባን የቱሪስት መዳረሻነት በማሳደግ ረገድ አዲስ ምዕራፍ ከፍቷል። በዛሬው ዕለት የሀገራችን ታዋቂ የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች፣ ስመ ጥር አርቲስቶችና የብሔራዊ ጥበባት ማህበራት ፕሬዚዳንቶች የእንጦጦ _ ቀበና የወንዝ እና የወንዝ ዳርቻ ፕሮጀክት በመጎብኘት፣ በጥበብና በልማት መጋመድ ዙሪያ ተጨማሪ ተሞክሮና መነሳሳትን ቀስመዋል። 10 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር ርዝመት የያዘው ይህ ፕሮጀክት፣ በአጠቃላይ 87 ነጥብ 6 ሄክታር መሬትን በአረንጓዴ ልማትና በዘመናዊ መሰረተ ልማት ያደሰ ታላቅ ክስተት ነው። ቀደም ሲል በከፍተኛ ብክለት፣ በጎርፍና በአፈር መንሸራተት አደጋ እንዲሁም በፀጥታ ስጋቶች ሳቢያ የአካባቢው ነዋሪዎች ይኖሩበት የነበረውን አስቸጋሪ ህይወት ፕሮጀክቱ ቀይሮታል። ከተፈጥሮ ጋር በተስማማ እና በዘላቂ ልማት እሳቤ የተገነባው ፕሮጀክቱ በውስጡ ለአካል ብቃት እንቅስቃሴና ለእግር ጉዞ የሚሆኑ ውብ መንገዶችና ደረጃቸውን የጠበቁ ድልድዮች፣ ዘመናዊ ቤተ-መጻሕፍት፣ የመሰብሰቢያ አዳራሽ፣ ሰፋፊ ፕላዛዎችና የመዝናኛ ስፍራዎች፣ የስፖርት ማዘውተሪያ ሜዳዎች፣ የህፃናት መጫወቻዎች፣ ዘመናዊ የመኪና ማቆሚያ (ፓርኪንግ) እና ንፁህ የሕዝብ መጸዳጃ ቤቶች፣ መለስተኛ ግድቦች፣ ሰው ሰራሽ ፏፏቴዎች፣ በርካታ የንግድ ሱቆች እንዲሁም ለምግብነት የሚውሉ (የከተማ ግብርናን የሚያበረታቱ) እፅዋት የተካተቱበት ሰፊ የአረንጓዴ ስፍራዎች የያዘ ነው፡፡ በብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅ/ጽ/ቤት የልዩ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ዳርዳር ብርሀኑ ለጉብኝቱ ተሳታፊዎች በሰጡት ማብራሪያ እንዳመለከቱት፤ ለረጅም ዘመናት ትኩረት ተነፍጎት ለብክለትና ለህገ-ወጥ ግንባታዎች ተጋልጦ የነበረው የቀበና ወንዝ አካባቢ ዛሬ በተባበሩ እጆችና በተደመሩ አቅሞች ማራኪና ሳቢ ገጽታን መላበስ ችሏል ብለዋል።