fa
Feedback
🧡❤️መልካም ልቦች💞 ✍️

🧡❤️መልካም ልቦች💞 ✍️

رفتن به کانال در Telegram

🌷 🥀♡♡ ማፍቀር ስትጀምር ከእምነት ጀምር ♡♡🌷 🙏WELLCOM TO 🧡❤️መልካም ልቦች💞 ✍️ ☆በዚህ ቻናል ውስጥ ደስ የሚሉ ☞ የ ፍቅር ቃላቶች፣ ☞ግጥሞች፣ ☞የፍቅር ታሪኮች ያገኛሉ ! t.me/Melkam_liboch1 ● ቻናላችንን SHARE ያድርጉ 🙏

نمایش بیشتر
2 135
مشترکین
+424 ساؚت
+197 عوز
+3630 عوز

در حال بارگیری داده...

ابر برچسب‌ها
هیچ داده‌ای
مشکلی وجود دارد؟ لطفاً صفحه را تازه کنید یا با مدیر پشتیبانی ما تماس بگیرید.
اشارات ورودی و خروجی
---
---
---
---
---
---
جذب مشترکین
ژوئیه '26
ژوئیه '26
+40
در 0 کانال‌ها
ژوئن '26
+78
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مه '26
+91
در 0 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '26
+104
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مارس '26
+160
در 0 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '26
+117
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '26
+128
در 0 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '25
+175
در 0 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '25
+65
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اڊتبع '25
+63
در 0 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '25
+120
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اوت '25
+143
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '25
+73
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '25
+59
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مه '25
+87
در 0 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '25
+111
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مارس '25
+168
در 0 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '25
+143
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '25
+127
در 0 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '24
+121
در 0 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '24
+172
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اڊتبع '24
+114
در 0 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '24
+138
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اوت '24
+188
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '24
+207
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '24
+52
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مه '24
+132
در 0 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '24
+315
در 0 کانال‌ها
تاریخ
رشد مشترکین
اشاعات
کانال‌ها
12 ژوئیه0
11 ژوئیه+5
10 ژوئیه+4
09 ژوئیه+7
08 ژوئیه+3
07 ژوئیه+1
06 ژوئیه+5
05 ژوئیه+1
04 ژوئیه+4
03 ژوئیه+3
02 ژوئیه+5
01 ژوئیه+2
پست‌های کانال
​​​​💞"ጤዛዉ ፍቅሬ"💞 💝ከመልካም ልቦች የቴሌግራም ቻናል የቀረቀ💝 💐💐ክፍል ሰባት (➐)💐💐 ✍✍( በኑዕማን ኢድሪስ )✍✍ - ..... አንዳንድ ጊዜ ተጨማሪ ፈተና ለሌላዉ ችግር መልስ ወይም መፍትሄ ሆኖ ይገኛል፡፡ ምናልባትም የሀምዛ የመኪና አደጋ መድረስ ለሀቢብና ለፎዚያ ትዳር መስተካከልና መሾመር ጥሩ አጋጣሚ ይሆናል፡፡ ማን ያዉቃል.... ፎዚያ ሆስፒታል ስትደርስ በፍጥነትና በሶምሶማ ከመራመዷ የተነሳ እያለከለከችና እጅግ በጣም ደክማ ነበር፡፡ ሀምዛ ከድንገተኛ ክፍል አልጋ ላይ ተንጋሎ ተኝቷል፡፡ እግሩ ክፉኛ ተጎድቷል፡፡ ቶሎ ሆስፒታል በመድረሱ ከሰዉነቱ የሚፈሰዉ ደም በህክምና እርዳታ ሊቆም ችሏል፡፡ ሀቢብ ደግሞ ከጎኑ ተቀምጦ እያወሩ ነበር፡፡ የሚያወሩት ሾለ ሀቢብ ትዳር መበጣበጥ ነበር፡፡ "ከሞትኩም እንኳ የጓደኛዬን ህይወት ደስተኛ አድርጌ፤ ትዳሩን አስምሬለት መሆን አለበት፡፡" ብሎ ለልሹ ቃል ገብቷል፡፡ የጓደኛ ልኩ እንደ ሀምዛ ነዉ፡፡ እራሱን እያጣ ለጓደኛዉ ያስባለል፣ በአደጋ የተጎዳዉን እግሩን እያመመዉ ረስቶት የጓደኛዉን የልብ ህመም ያስታምማል፡፡ ሀቢብ ደግሞ ከዚህ ርዕስ ለመዉጣት የማያደርገዉ ጥረት አልነበረም፡፡ በወሬያቸዉ መካከል "ቆይ ግን መኪያ ሰምታለች?" እያለ ወሬ ያሰናክላል፡፡ (መኪያ የሀምዛ ሚስት ነች)  'እግርህን እንዳያምህ አትገላበጥበት!' እያለ መኝታዉን እንደማስተካከል ያደርጋል፡፡ ሀምዛ ግን ወይ ፍንክች የፎዚያን እንባ ማበስ ሽቷል፡፡ ...... ፎዚያ ሆስፒታል ስትደርስ ይገጥመኛል ብላ ያሰበችዉ ነገር መጥፎ ነበር፡፡ ነገር ግን ያ ያሰበችዉ ነገር ደርሶና ሆኖ ባለማገኘቷ ጌታዋን አመሰገነች፡፡ ሆኖም  የደረሰበት ነገር አስከፊ በመሆኑ በጣም እያዘነች ባሏንና የባሏን ጓደኛ 'አሰላሙዓለይኩም' ብላ ተቀላቀለች፡፡ ..."አልሐምዱሊላህ ሀምዛ ... መኪና አደጋ ሲሉኝ ክፉኛ የተጎዳህ ነበር የመሰለኝ... እንዴት ነህ ግን በአላህ?' ብላ ጠየቀችዉ፡፡ ሀምዛ ስለደረሰበት አደጋና ስለገጠመዉ ሁኔታ ቀለል አድርጎ ለፎዚ ካስረዳት በኃላ... "አንቺ እንዴት ነሽ?" ብሎ ጠየቃት፡፡ ሾለ ደህንነቷ ሲጠይቃት ቤቷ ሰላም እንደሌላት ያዉቋል፡፡ የሀቢብን ባህሪ ጠንቅቆ ስለሚያዉቀዉ ይሄን ለመረዳት አያዳገተዉም፡፡ .... ሀምዛ ቀስበቀስ ወደ ነገሩ እየገባ ሁለቱንም ጥንዶች መከራቸዉ፡፡ 'ትዳርን መተሳሰብ ካልተጨመረበት ህይወታችሁ ሰቆቃ፤ ትዳራችሁ እንደ ህፃን እቃቃ ያደርግባችኃል፡፡ (ሁለቱም ተመስጠዉ ያዳምጡታል፡፡ በተለይ ሀቢብ የጓደኛዉ ምክር ኑዛዜ እስኪመስለዉ ድረስ ልብ ሰጥቶት እየሰማዉ ነበር፡፡) ... ነጋ ጠባ የምትጣሉት ነገር ፍቅራችሁን እያደፈረሰ መቃቃርን ያመጣል፡፡ መናናቅን በስተመጨረሻም የከፋ ደረጃ ያደርሳችኃል፡፡ በተለይ ሀቢብ ዉድ ጓደኛዬ ለትዳርህ ቦታ ስጠዉ፤ ለሚስትህም እንክብካቤ አትንፈጋት፡፡ (ይሄንን ቃል በፎዚ ፊት በመናገሩ ዉስጧን ሀሴት ተሰማት፡፡ ሀምዛ ... ሀቢብን ተቆጥቶና ገስጾ፤ ለፎዚያ ደግሞ ትዕግስት ማደረግ አለብሽ ብሎ ንግግሩን ቋጨ፡፡)..." ..... በመካከላቸዉ ለተወሰነ ደቂቃ ዝምታ ከሰፈነ ቡኃላ ሀምዛ ወደ ፎዚያ ዞረና... "የመኪያ ስልክ ስለማይሰራ ቤት ሂጂና አረጋግተሽ ንገሪያት፡፡ በዚያም ወደ ቤትሽ ሂደሽ አረፍ በይ" አላትና ፎዚ ተነስታ ተሰነባብታ ለመዉጣት ስትሰናዳ ..."ባይሆን ወዱን ባልሽን ተዉበሽ ጠብቂዉ...እ..." ብሎ ሀቢንም ፎዚንም ፈገግ አደረጋቸዉ፡፡ ..... ሀቢብ ..ሀምዛ ላይ የነበረዉን ጥርጣሬ አስወግዶ ሁሉንም ሚስጥር ለመንገር ከዉስጡ ጋር ሙግት ያዘ፡፡ በስተመጨረሻም የሀምዛ የዋህነትና ቅን አሳቢነት አሸንፎት ፎዚን ለምን ሊጠላት እንደቻለ? ለምን የቤታቸዉ ሰላም እንደደፈረሰ? ለምን የበፊት ፍቅሩ እንደተወገደና ለፎዚ ያለዉ ክብር እንደቀነሰ ሊነግረዉ ፈለገ፡፡ ..... "ሀምዛ..." አለዉ አንገቱን ጎንበስ፤ አይኑን ቀለስ፤ አንደበቱን ለሾለሾ አድርጎ፡፡ ሀምዛም ሲጎነጭ የነበረዉን ጁስ ትቶ ..... "ወይዬ ሀቢብ..." ብሎ መለሰለት፡፡ ..... "ሀምዛ በጣም ይቅርታ" አለዉ፡፡ ..... "ለምኑ?" ..... "ጓደኛዬ ... ባልሆነ ነገር ጠርጥሬህ ነበር፡፡ የምትመክረኝን ነገር አልሰማ ብዬ በሌለህበት ባንተ ጉዳይ መጥፎን ሳስብ ነበር፡፡ አሁን ግን በጣም ይቅርታ ተፀፀቻለሁ ሀምዛ..." አለዉና የሀምዛን ይቅርታ ሽቶ ጠየቀዉ፡፡ ..... "ኧረ ጓደኛዬ ... እኔና አንተ ስንት ነገር ያሳለፍን ሰዎች በዚች ትንሽ ነገር ይቀየመኛል ብለህ ፈራህ?? አብሽር ሀቢቢ ... ይቅርታም አያስፈልገዉም፡፡ አንተን ደስስስስ የሚልህ ከሆነ ግን... ልባዊ ይቅርታ አድርጌላሃለሁ፡፡" ብሎ የሀቢብን ልብ አስፈነደቃት፡፡ ዉስጡንም ረሃ ሰጣት፡፡ ይበልጥ በሀቢብ ልብ ዉስጥ ተወዳጅና ምርጥ ጓደኛዉ እንዲሆን አደረገ፡፡ ..... "በጣም አመሰግናለሁ ጓደኛዬ..." ..... "ምንም አይደል ሀቢቢ... (ጁሱን እንደ መጎንጨት ሊያደርግ እያለ)  ... ለመሆኑ ፎዚን እንዲህ የምታደርጋት ለምንድን ነዉ ሀቢቢ?" ብሎ ጠየቀዉ፡፡ ሀቢብም ከዚህ በኃላ ሀምዛን የቤቱ ጠበቃ አድርጎ ስለሳለዉ ምንም ነገር ላይደብቀዉ ለልሹ ቃል ገባ፡፡ ..... "ሀምዛ ... እ ብዙ ነዉ ሚስጥሩ አሁን ግን ከአንተ የምደብቀዉ ምንም ነገር የለም" አለዉና ፎዚን የጠላባትንና የራቀባትን ምክንያት ሊነግረዉ ከተቀመጠበት ቦታ እንደ መደላደል  አለ.... ╔═══❖•🌺🌺•❖═══╗        áŠ­ááˆ 8 ከlike 👍    á‰ áŠ‹áˆ‹    ይ  ቀ  ጥ  ላ  ል‼️ https://t.me/Melkam_liboch1

2
​​​​💞"ጤዛዉ ፍቅሬ"💞 💝በመልካም ልቦች የቴሌግራም ቻናል የቀረበ💝   ክፍል ስድስት (➏)   ✍✍(በኑዕማን ኢድሪስ)✍✍ ፎዚያ ዉስጧን እየጨነቃት፤ ምጥ እንደያዛት ድመት እየተቁነጠነጠች 'ዛሬ ደግሞ ምን ሊለኝ ይሆን' ብላ ራሷን በሀሳብ መወጠኑን ተያያዘችዉ፡፡ ጀመረ አልጀመረ እያለች አይን አይኑን ስታየዉ፡፡ ሀቢብ ደግሞ አንገቱን ወደ መሬት ቀብሮ በተረጋጋ መንፈስ ነገሩን እንዴትና ከየት መጀመረበት እንዳለበት እያሰበ ጣቶቹን ያፋትጋል፡፡ ያለወትሮዉ ያ መኮሳተርና መቆጣቱን አስወግዶታል፡፡ በዚህ መሃል አንገቱን ቀና አደረገና የፎዚያን አይን እያየ."ፎዚ..." አላት፡፡ እሷም ከስንት ጊዜ በኃላ ባሏ ስሟን አቆላምጦ ሲጠራላት በደስታ ብዛት መልሱ ጠፍቷት ልቧ ልትወጣ ደረሰች፡፡ ..."ወይዬ ሀቢቢ! ... ምን ነዉ ችግር አለ እንዴ ሁቢ?" አለችዉ፡፡ በዚህ መካከል ግን ዉስጧን ሚረብሽ ስሜት ዉል አለባት፡፡ 'ሀቢብ ዛሬ ያለወትሮዉ እንዲህ የተረጋጋዉ እንለያይ ሊለኝ ነዉ? ወይንስ ያሳለፍነዉ ከፍቅር የራቀ ህይወት ቆጭቶት በፍቅር ልቤንም ቤቴንም ሊሞላዉ ነዉ?' እያለች የዚህን ጥያቄ መልሷን ከሀቢብ ፊት ላይ ታገኘዉ ይመስል አይኗቿን አይኖቹ ላይ ተክላ ታስተዉለዋለች፡፡ ..."ፎዚዬ ብዙ እየበደልኩሽ እንደሆነ ይገባኛል...፡፡ (ንገግግሩን ቀጠለ ፎዚም ደስታ እየተሰማት ነዉ)  በርግጥ አንቺ ከእኔ የተሻልሽ ነሽ ማለቱ ይከብዳል፡፡ ምክንያቱም የሰርጋችን ...." ንግግሩን ሳይጨርስ ወዲያዉ ስልኩ አቃጨለ "ጢርርር ጢርርር...." ስልኩን ከኪሱ አዉጥቶ ደዋዬን ሲያይ 'Hamza' ይላል፡፡ 'አሁን ተለያይተን አሁን ምን አስደወለዉ' እያለ ስልኩን አነሳዉ፡፡ "ሄሎ..." አለችዉ፡፡ በሀምዛ ስልክ የደወለችዉ ሴት ነበረች፡፡ ሀቢብ ግራ በተጋባ መንፈስ .."ሄሎ..." አላት፡፡."ሀቢብ ነህ?" ብላ ጠየቀችዉ፡፡ ድምጿ መርዶ ልተትናገር እንደሆነ ያስብቃል፡፡ ሀቢብም ከምታወጣዉ ድምፅ የሆነ ችግር እንዳለ ስለተረዳ..."አዎ ሀቢብ ነኝ! ሀምዛ ምን ሆነ?" ብሎ ጠየቃት፡፡ የደወለችዉም ሴት ሀምዛ የመኪና አደጋ ደርሶበት ሆስፒታል እንዳለና ከተደወሉ ስልኮች መጀመሪያ ላይ የሱን ስልክ አግኝታ እንደደወለች ነገረችዉ፡፡ በዚህ ጊዜ ሀቢብ እምጥ ይግባ ስምጥ አልታወቀዉም፡፡ ብቻ "ምን?" ብሎ ከተቀመጠበት ፈትለክ ብሎ ተነሳ፡፡ ፎዚ የሀቢብ ድንጋጤ ግራ ስለገባት እሷም ደንግጣ "ሀቢቢ ማን ናት? ሀምዛ ምን ሆነ? ምንድን ነዉ?" እያለች በጥያቄ ስታጣድፈዉ ለፎዚ ምንም አልመለሰላትም፡፡ ፎዚም ተከትላዉ እስከ ግቢዉ በር ከሮጠች ቡኃላ ... እንደማትደርስበት ስታዉቅ ወደ ቤቷ ተመለሰች፡፡ አሁንም ቢሆን "ሀቢብ ምን ሊነግረኝ ነበር?" እያለች በሀሳብ ራሷን መወጠሩን ተያያዘችዉ፡፡ 'እንደጎዳኝና እንደበደለኝ ያዉቃል፡፡ ነገር ግን ለምን...." ብላ ራሷን ጠየቀች፡፡ አሁንም ሀቢብ ከነገራት ዉስን ቃላቶች ዉስጥ የጥላቻዉን ምክንያት ታገኘዉ ይመስል መፈለግ ያዘች፡፡  "ለምንስ ነዉ ከኔ የተሻልሽ አይደለሽም ያለኝ?.... የሰርጋችን ቀን ምን አጠፋሁኝ? ምን አይነት ችግር አገኘብኝ...?" ጥያቄ በጥያቄ ብቻ፡፡ እንደገና መለስ ብላ  የሀምዛ ሁኔታምና ምን ችግር እንደገጠመዉ አሳስቧታል፡፡ ምክንያቱም ለሀቢብ ምርጥ ጓደኛዉ ነዉ፡፡ ከዚህም በላይ ደግሞ ለትዳሯ የሚያስብላትና በሀቢብና በርሷ መካከል ስምምነት እንዲፈጠር፤ ፍቅራቸዉ እንዲጠነክር የሚተጋ ብቸኛ የልብ ጓደኛና ወዳጃቸዉ ነዉ፡፡ ... ስልኳ ካለበት አነሳችና ወደ ሀቢብ ደወለች፡፡ ስልኩ እየጠራ ነዉ ነገር ግን ስልኩን አያነሳም፡፡ "የደወሉላቸዉ ደንበኛ ጥሪ እያስተላለፉ ነዉ፡፡ እባክዎ ቆየት ብለዉ ይደዉሉ..." የምትለዉ የኮሚኒታተሯ ድምፅ ተሰማት፡፡ ስልኩን ከዘጋች በኃላ ወደ ወደ ሀቢብ መደወሉን ትታ ወደ ሀምዛ ደወለች፡፡ ..."ሄሎ አሰላሙዓለይኩም..." አለች ..."ጤና ይስጥልኝ..." የሚል ምላሽ ተሰጣት፡፡ ሴት ነበረች፡፡ ..."ይቅርታ ሀምዛ የለም እንዴ? የሀቢብ ባለቤት ነኝ" ብላ ማንነቷንም ጭምር ነገረቻትወደ.."ሀምዛ የመኪና አደጋ ደርሶበት ሆስፒታለል ነዉ፡፡" ብላ አረዳቻት፡፡ በሀሳብ ላይ ሀሳብ የሚደራረብባት ፎዚ ድነንጋጤ ተጨምሮባት ..."ምንንን?" ብላ አንባረቀች፡፡ ነርሷም ያለበትን ሆስፒታል ከነገረቻት በኃላ ሆስፒታል ለመሄድ ልብሷን ለመቀየር ወደ መኝታ ክፍሏ ገባች፡፡ ╔═══❖•🍄🍄•❖═══╗        ክፍል 7 ከlike👍 በኋላ   ይ ቀ ጥ ላ ል‼️ https://t.me/Melkam_liboch1
1 400
3
​​​​❣"ጤዛዉ ፍቅሬ"❣ 💝በመልካም ልቦች የቴሌግራም ቻናል የቀረበ💝 🍂ክፍል-➎- አምስት ❥............🍃💐💐🍃..............❥ .... ብዙ የፍቅር አይነቶች ቢኖሩም የሀቢብ አይነት ፍቅር ግን መጀመሪያዉኑም ፍቅር ሊያስብለዉ የሚችል አልነበረም፡፡ ሀምዛ በሀቢብ ንግግር ወደ መናደዱ እየሄደ ነዉ፡፡ ሀምዛ   ሀቢብና ፎዚን ሊያስማማ፤ በሁለት ባለትዳሮች መካከል የነበረን ጥላቻ አስወግዶ እርቅ ለማስፈን ነበር አካሔዱ፡፡ ነገር ግን የሀቢብ ንግግር ወደ ድርድር የሚያስገባ ሳይሆን መቃቃርን የሚፈጥር እንደ ስድቡ 'ርካሽ ቃላትን የሚመርጥ 'ርካሽነቱን የሚያንፀባርቅ ባህሪ አወጣ፡፡ ..."ጓደኛዬ (አለዉ ሀምዛ... ለዘብ ባለ ንግግር) ... እየዉልህ ሀቢብ በርግጥ አንተ ከፎዚ በፊት ብዙ ሴቶችን ታዉቃለህ፤ ከብዙ ሴቶችም ጋር ነበርክ፡፡ እነዚያ ጋር የነበርከዉ ብዙ አመታት ግን ፎዚ ጋር እንዳለህ የትዳር ዘመን የተባረከ ሳይሆን የረከሰ ጊዜ ነበር፡፡ ፎዚ ጋር አዲስ ህይወት ከጀመርክ ሰነባበትክ የመጀመሪያ ሰሞን ደስተኛ ነበርክ፡፡ አሁን ምን ተፈጥሮ ነዉ የተቀየርከዉ ሀቢብ...!?" ብሎ ጠየቀዉ፡፡ ሀምዛ በሚያወራበት ጊዜ ግን የሀቢብ ሀሳቡ በሙሉ በጥላቻ የመረዘዉ ልቡን ተጠቅሞ ጥላቻን እየሰነቀ ነበር፡፡ ....."ሀቢብ!!? ሄይ... ወደ የት ነጎድክ?" አለዉ ከተጓዘበት አለም እየመለሰዉ፡፡ ....."ሀምዛ እየሰማሃኝ ነዉ፡፡ አንተ ፎዚን ልትወዳት ትችላለህ እኔ ግን... እጠላታለሁ?" ሀምዛ የሀቢብ ነገር አዝማሚያ የገባዉ ይመስላል፡፡ ሀቢብ ወሬዉን ቀጠል አደረገና፡፡ ..."ለመሆኑ ከፎዚ ጋር ከመቼ ጀምሮ ነዉ መገናኘት የጀመራችሁት?" ..." ያዉም እኔ ባለቤቷ ሳላዉቅ?? ... እ??" ብሎ ዉስጡ ያለዉን ስሜት ቀስ እያለ ያወጣዉ ጀመር፡፡ "ሀቢብ.." አለዉ ሀምዛ በተምስጦ አይኑን እየተመለከተ ..."የኔና ያንተ ጓደኝነት ዛሬ አልተጀመረም፡፡ ፎዚያን ከማግባትህ በፊት ብዙ ችግሮችንና ፈተናዎችን አሳልፈናል፡፡ አያሌ የደስታ ቀኖችን አብረን ቦርቀናል፡፡ እኔም እነዚያን መልካም ጊዜዎች በማስታወስ የተለመደዉን የጓደኝነቴን ከጎንህ ልሆን ስለፈለኩኝ፣ ትዳርህ የሰመረና በባለቤትህ ደስተኛ እንድትሆን እንጂ ሌላን ነገር አስቤ አልነበረም፡፡" ብሎ መለሰለት በተረጋጋ መንፈስ፡፡ ሀቢብ ግን ለትዳሩ መስመር፣ ለህይወቱ መቃናት የሚጥርለትን ጓደኛዉን ዛቻም ጭምር እየተናገረዉ ነዉ፡፡ ..."ሰማሃኝ ሀምዛ... ምንም እሰብ ምን ከዚያች ሴት ሴት ጋር ያለህ ግንኙነት ጤነኛ አይደለም፡፡" አለዉ፡፡ መደዋወላቸዉንና ግንኙነታቸዉን እንዲያቋርጥ በማስጠንቀቅ፡፡ ..."እሺ ይቅርታ ጓደኛዬ...." ብሎ ከሀቢብ ጋር የያዘዉ ሙግት መፍትሄ እንደሌለዉና እንደማይበገርለት አወቀ፡፡ . . . ..... ፎዚ የቤቱ ስራ አድክሟት  ምንም ሳትተጣጠብ በስራ ልብሷ ቤቷ ቁጭ የማትመለስበት በሚመስል ያለፈ ትዝታዋ ላይ ተተክላ በሀሳብ ባህር ሰምጣለች፡፡ የትዝታን ቅኔ እያዜመች፤ እጆቸቿን አገጯ ላይ እንዳስደገፈች አይኖቿ ላይርገበገቡ ምለዉ የልጅነት ምኟቷን፤ የኮረዳነት ደስታዋን ማስታወስ ይዛለች፡፡ አሁን የተማረረችበትን ህይወት በትዝታ እንኳ ትደሰትበት እንጂ...፡፡ በዚህ መካከል ሀቢብ ከጓደኛዉ ሀምዛ ጋር የነበራቸዉን እሰጥ አገባ ጨርሰዉ ባለመስማማት ተለያይተዉ ወደ ቤቱ መጣ፡፡ ቤቱ እንደደረሰ በሩን ሳያንኳኳ ከፍቶ ገባ፡፡ ፎዚያ ከበሩ ፊት ለፊት ሶፋዉ ላይ ተቀምጣ ሀቢብ በሩን ከፍቶ ሲገባ አላስተዋለችዉም፡፡ ደትዝታን ባህር እየቀዘፈች ነበርና አዮታዉ ሳታየዉ ቀረች፡፡ አይኖቿ ሀቢብን በር ከፍቶ ሲገባ ቢያዩትም ልቧ ከትዝታዋ ጋር ነበርና ሳታስተዉለዉ ቀረች፡፡ 'ልብ ካላዬ አይን አያይም' አይደል ተረቱስ፡፡ ሀቢብ የበሩን እጄታ ይዞ መልሶ ከዘጋ በኃላ እየተንጎራደደ ወደ ፎዚያ ተጠጋ፡፡ እሷ ግን አሁንም አላየችዉም፡፡ ወደ እሷ የሚጠጋዉ ሰዉ ይሁን ሌላ ነገር አላስተዋለችዉም፡፡ ወደ እሷ ተጠግቶ ከተቀመጠችበት ሶፋ ፊት ለፊቷ ካለዉ ሶፋ ተቀምጦ ..."ፎዚ አላት" እሷ ግን አልሰማችዉም፡፡ አዉቃ ዝም እንዳላለችዉና በሀሳብ  እንደተዋጠች በአቀማመጧና ከሁኔታዋ አስተዉላሏል፡፡ እጁን በፊቷ ላይ እየወዘወዘ "ሄይይ ኧረ ፎዚ..." ሲላት ፎዚያ ከእንቅልፏ እንደሚነቃ አይነት ሰዉ ብትት ብላ ..."  እ ሀቢቢ መጥተሃል እንዴ? ልብስ ሳጥብኮ ቆይቼ ድክም ብሎኝ ነዉ፡፡" እያለች ክስም ብሎ የነበረ ፊቷን በፈገግታ አደመቀችዉ፡፡ ሀቢብም ለጠጥ ብሎ ሶፋዉን እንደ መደገፍ እያለ ..."እ ... ነዉ?" ብሎ ወሬዉን አሳጠረዉ፡፡ ..."አዎ! ሁቢ ደግሞ ሶፊ ጋር ደዉዬ ስናወራ ቆዬን" ብላ ስትነግረዉ .."ለምን እሷ ጋር ደወልሽ?" ብሎ ጮኸባት፡፡ (ሶፊያ የሀቢብ እህት፤ የፎዚያ ደግሞ የግቢ ጓደኛዋ ናት!)፡፡ በዚህ ጊዜ ፎዚያ ደንገጥ ብላ ደህና ሆኖ የነበረዉን ለምን አሁን እንዲህ ብዬ ለምን አስከፋሁት ብላ ለራሷ አሰበች፡፡ 'ግን ሶፊ ጋር እንድደዉል ለምን አልፈለገም፡፡' ብላም ራሷን ጠየቀች እንደገና መለስ ብላ 'አይይ እንደፈለገ!' አለች፡፡ ..."ሀቢቢ የስራ ልብሴን ሳልቀይር እንኳ መጣህ... ቆይ ልብስ ቀይሬ ልምጣ" ብላ ከተቀመጠችበት ስተትነሳ ..."ተቀመጭ..." አላት፡፡ ደንገጥ ብላ ..."እ..." አለችዉ፡፡ ..."ተቀመጭ" ብሎ ቃሉን ደገመዉ፡፡ ..."እ...እ እሺ " ብላ ተቀመጠች፡፡ ፊቱ ሳይፈታ እንደተኮሳተረ ቆጣ ብሎ... ..."እንድናወራ የምፈልገዉ ጉዳይ አለ" አላት፡፡ ╔═══❖•🌺🌺•❖═══╗       ክፍል 6 ከ like በኋላ     ይ  ቀ  ጥ  ላ  ል https://t.me/Melkam_liboch1
2 608
4
​​​​❣"ጤዛዉ ፍቅሬ"❣ 💝በመልካም ልቦች የቴሌግራም ቻናል የቀረበ💝 🌿ክፍል አራት (➍)🌿 ጢርርር ... ጢርርርር..." ጥሪዉ (ደዋዩ) ማን እንደሆነ ለማየት ስልኩን ከሱሪዉ ኪስ አወጣና አየ፡፡ "Hamza" ይላል፡፡ ስልኩን ሳያነሳዉ ድምፁን ቀነሰና ጥሪዉን ድምፅ አልባ አደረገዉ፡፡ ንዴቱ ዉስጡን እያላወሰ ነበርና አይኑን ማጉረጥረጡን ቀጠለ፡፡... ..."ማን ነዉ የደወለዉ?" አላት፡፡ እጆቹን ጨብጦ ለቡጢ እያዘጋጃቸዉ፤ ሁኔታዉ ከሚስቱ ፊት ሳይሆን ከደመኛዉ ሊበቀለዉ ከሚፈልገዉ ሰዉ ፊት የቆመ ይመስላል፡፡ ፎዚያ ፈራችዉ፡፡ በዚህ ንዴቱ መምታት ከጀመራት እንደማያቆም ታዉቋት ትርበተበት ገባች፡፡ ወደ'ሷ ጠጋ እያላት ጥያቄዉን ደገመዉ፡፡ ..."ማን ነዉ የደወለዉ?... እ...?..." ፡፡ ምን ብላ ትመልስ?፡፡ ተደዉሎላት ሳይሆን ደዉላ ነዉ፡፡ 'ሀምዛ ነዉ ብለዉስ?.. ከ'ሱ ጋር ይጠረጥረኝ ይሆን?... የሚዋደዱ ጓደኛሞች በ'ኔ ምክንያት ቢጣሉስ?" እያለች ዉስጧን በስጋት ሞላችዉ፡፡ በዚሁ መካከል ሀምዛ ቅድም ደዉሎ ስላልተነሳለት በድጋሚ ለሀቢብ ደወለ ... "ጢርርርር... ጢርርርር...." የፎዚን ንዴት ስልኩ ላይ ሊወጣዉ ይመስል እጆቹን በሃይል ወደ ኪሱ ልኮ ስልኩን አወጣና  አረንጓዴዉን ተጭኖ..." ሄሎ ..." አለ፡፡ ..."ሄሎ ... ሃቢብ ብደዉልልህኮ አታነሳም" የሀምዛ ድምፅ ነበር፡፡ ከመበሳጨቱ የተነሳ ያሁኑ ደዋይ ማን እንደሆነ አላወቀዉም ነበር፡፡ ..."እ... አንተ ነህ እንዴ ሃምዛ..." ..."ስልክ ቁጥሬ ቢጠፋህ መቼም ድምፄ አይጠፋህም!" እሱ ራሱ ሃምዛ መሆኑን እያረጋገጠለት ነበር፡፡ ..."እ...ለማንሳት አልተመቸኝም ነበር" አለዉ፡፡ ..."ከፎዚ ጋር በምን ተጋጭታችሁ ነዉ?" ..."ማን ነገረህ?" ብሎ በቤቱ ዉስጥ አንገቱን አዟዙሮ ተመለከተ፡፡ 'ይሄ ሰዉዬ ተደብቆ እያየኝ ነዉ እንዴ?' ብሎ አሰበ፡፡  መጥፎ የሚሰራ ሰዉ እንኳን ሌላ ሰዉ ራሱንም ይጠራጠራል፡፡ ስራዉ እንደ ቂል አደረገዉ፡፡ ..."ፎዚ አሁን ደዉላልኝ ነበር፡፡"  ስልኩን ከጆሮዉ ስር 'ራቅ እያደረገ ወደ ኃላ እንደማፈግፈግ ብሎ ፎዚን በቆመችበት ትቷት ወደ መኝታ ክፍሉ ተመለሰ፡፡ ..."እና... ምን አባቷ ወደ አንተ አስደወላት..." አለዉ፡፡ የተጠራጠረ ይመስላል፡፡ 'ግንኙነት አላቸዉ ማለት ነዉ' ሲል አሰበ፡፡ 'በዚህ አይነትማ እስከዛሬ የምነግረዉን ለሷ ይነግራት ነበር ማለት ነዉ!' ... 'ቆይ ግን... ምንድን ነዉ ግንኙነታቸዉ?'፡፡ ሀምዛ ማሜን እየመከረዉ ነዉ፡፡ 'አትጣሉ...' እያለ የጓደኝነቱን ይነግረዋል፡፡ ሀቢብ ግን አልሰማዉም፡፡ እንደዉም ይባስ ብሎ ሀምዛን ከፎዚ ጋር መጠርጠር ይዟል፡፡ ካፉ አላወጣዉም እንጂ 'እሰራለሃላችኃለሁ' እያለ ከንፈሩን በቁጭት ይነክሳል፡፡ ..."እሺ በቃ አንጣላም ... ስንገናኝ እናወራለን!" ብሎት ስልኩ ተዘጋ፡፡ ሀቢብ ፎዚን ጠልቷታል እንዳይባል ይቀናባታል፤ ይወዳታል እንዳይባል ደግሞ ያሰቃያታል፡፡ ነገረ ስራዉ ሁሉ 'እሱ እንዲህ ነዉ!' ብሎ ለመወሰን ይከብዳል፡፡ .... ፎዚያ እራሷን ማስጨነቁን ተያያዘችዉ ..'ቆይ ሀቢብ ሊጠላኝ የቻለበት ምክንያት ምን ይሆን?' ብላ እርግጠኛ ሁና መመለስ በማትችለዉ ጥያቄ ራሷን ታፋጣለች፡፡ 'ያ የበፊቱ ፍቅርስ የት ገባ?' ...'ሶፊ ስለ ሀቢብ ጥሩነት እንጂ አንድም ቀን መጥፎነቱን አዉርታኝ አታዉቅም ነበር፡፡ ፍቅር መስጠት እንደሚችል እንጂ ልቡ በጥላቻ የጠቆረ መሆኑን አልነገረችኝም ነበር፡፡' ነበር... ነበር ... ነበር... እያለች እራሷን ወደ ኃላ እየጎተተች ሀቢብን የተዋወቀችበትን የምርቃን ጊዜዋን አማረረች፡፡ ያን በደስታ የተፍነከነከችበትን ቀን ረገመችዉ፡፡ 'ቆይ ግን ምን አጉድየበት ተቀየረ?'.... ጥያቄ በጥያቄ ላይ ብቻ መልሱን አታዉቀዉም፡፡ ብታዉቀዉ ግን ደስ ይላታል፡፡ ምክንያቱም ራሷን በራሷ ያፋጠጠችበትን ጥያቄ መልስ ከተመለሰላት ትዳሯ ይሰምራል፤ ፍቅሯ ያብባል ስለዚህ ለራሷ ለህይወቷ ስትል መሆን ያለባትን ሁና፤ መክፈል ያለባትን መስዋእትነት ከፍላ ደስታዋ እንደገና መለምለም አለበት፡፡ . ... ሀቢብና ሀምዛ ሁሌም ከሚገናኙበት ዘቢብ ካፌ ተገናኝተዉ እየተጨዋወቱ ነዉ፡፡ ሀቢብ ዉስጡ ልቡ በጥላቻ ከመጥቆሩም በላይ ከርፍቷል፡፡ የገዛ ጓደኛዉን ሀምዛን በፊት በሚወዳት ዛሬ ምክንያቱ ባልታወቀ ምክንያት ከሚጠላት ሚስቱ ጋር ጠርጥሮታል፡፡ በጨዋታቸዉ መካከል እየተሳሳቁ ቢያወሩም የሃቢብ ሳቅ የማስመሰል ግልፈጣ፤ የሀምዛ ግን ከልቡ የሚመጣ ነበር፡፡ ሀምዛ ቀስ እያለ ወደ ቁምነገሩ እየተንደረደረ ነዉ፡፡ ..."ታዉቃለህ ግን ሀቢብ?" ..."ምኑን ነዉ የማዉቀዉ?" አለዉ፡፡ ግንባሩን አጨማዶ፡፡ ሀምዛም ቀጥታ ስለ ፀቡ አንስቶ ይበልጥ ከሚያበሳጨዉ ምናልባት ያንን ጣፋጭ የፍቅር ጊዜዉን አስታዉሸዉ ልቡ ቢለዝብ ብሎ አሰበ፡፡ ..."ያንን የፍቅር ጊዜህን፡፡ በፍቅር ክንፍ ብለህ ከፎዚ ዉጭ ማሰብም ሆነ ማለም ያቆምክበት..." እያለ ስለ መልካም የፍቅር ጊዜዉ ሊያስታዉሰዉ ሲሞክር ሀቢብ የሃምዛን ወሬ አቋረጠና... ..."እ... አዎ ትዝ አለኝ!" ብሎ ወሬዉን ከመቀጠሉ በፊት ተንፈስ ሲል ሀምዛ ወደ በፊት አቋሙ ሊመለስልኝ ነዉ በማለት ልቡን ደስታ ተሰምቶት ጥርሶቹ ታዩ፡፡ ፈገግ አለ፡፡ ሀቢብም ያዘዉን ማኪያቱ ፉት ብሎ አፉን በማኪያቶዉ ቃና ካጣጣመ በኃላ ወሬዉን ቀጠለ... ..."እርካሽ መሆኗን ባዉቅ ኑሮ በፍቅር ቅልጥ ባላልኩላት ነበር፡፡" ብሎ ፈግጎ የነበረዉን የሀምዛን ፊት ወዲያዉ አከሰመዉ ╔═══❖•🌺🌺•❖═══╗        ክፍል 5 ከlike👍 በኋላ       ይ  ቀ  ጥ  ላ  ል https://t.me/Melkam_liboch1
2 855
5
​​​​​​❣ጤዛዉ ፍቅሬ"❣ 💝በመልካም ልቦች የቴሌግራም ቻናል የቀረበ💝   💐ክፍል ሶስት 💐   ....ፎዚ 'አሁን ደግሞ ምን አጠፋሁ?' ብላ የሀቢብ ሁኔታ አስጨነቃት፡፡ ከእለት ወደ እለት ለሷ ያለዉ ጥላቻ እየጨመረ መሄዱ ሃሳብ ገባት፡፡ እንዲህ አምራና ተዉባ ስጠብቀዉ 'የኔ ቆንጆ ዛሬ ደግሞ ይበልጥ አምሮብሻል' እንዲላት ነበር የፈለገችዉ፡፡ እሱ ግን ማሞገስ፤ ዉበት ማድነቅ የሚባለዉ ሃሳብ ሊመጣለት ቀርቶ እሷን መሸሽና እንደ ቆሻሻ ይርቃታል፤ ይፀየፋታል፡፡ ለዚህ ነገር መፍትሄ ማበጀት እንዳለባት አምና የሀቢብን የልብ ጓደኛ ሀምዛን ማማከር እንዳለባት ወሰነች፡፡ ምክንያቱም ሀቢብን ወደ ቀድሞዉ ፍቅሩ መመለስ ካልቻለች ትዳራቸዉ ገደል ስር እንደበቀለ ዛፍ በጊዜ ቆይታ ብዛት ተመንጉሎ እንደሚወድቅ ታዉቋታል፡፡ በፀብ የጠነከረ ትዳር፤ በንትርክ የተገነባ ፍቅር፤ በመቃቃር የተዋቀረ መዋደድ እንደሌለ ታዉቃለችና፡ . ... ሀምዛ የሀቢብ የልብ ጓደኛዉ ነዉ፡፡ ሁለቱ ጓደኛሞች (ሀቢብና ሀምዛ) መካከል ሚስጥር የሚባል ነገር የለም፡፡ እናም የሀቢብን የባህሪ መቀየር ሀምዛ ሊያዉቀዉ ይችላል በሚል ስልኳን አነሳችና የሃምዛን ቁጥር ጽፋ ደወለች፡፡ ስልኩ እየጠራ ነዉ፡፡ ሀምዛ ስልኩን አነሳና የፎዚ ጥሪ እንደሆነ በቁጥሩ ስላወቀ... ..." ሄሎ ፎዚ..." አላት፡፡ ..."አሰላሙዓለይኩም ሀምዛ... እንዴት ነህ?" ድምፅዋ ለቅሶዋን አቋርጣ የደወለች ሀዘንተኛ አስመስሏታል፡፡ ..."ወአለይኩም ሰላም ፎዚ ...ምን ሁነሻል?" ብሎ ጠየቃት፡፡ ልትደብቅዉ ያልቻለችዉ የዉስጥ ሀዘን እንዳለባት ያስታዉቅባታል፡፡ ፎዚም እየሆነች ያለችዉንና የሀቢብን የባህሪ መቀየር ለመንገር ስለደወለች ልትደብቀዉ ወይም በዝምታ ልታልፈዉ አልፈለገችም፡፡ ለሃምዛ ከመንገሯ በፊት ግን ዉስጧ ያለዉን ስሜቷን ትንፋሿ ቀድመዉ ነገሩት፡፡ "እህህህህ..." አለች፡፡ ሳታስበዉ ነበር በረጅሙ የተነፈሰችዉ፡፡ ..."ምነዉ ፎዚ?... ከሀቢብ ጋር ተጣላችሁ እንዴ?" ብሎ ከምትቀዝፈዉ የሀሳብ ባህር ዉስጥ አናጠባት፡፡ ..."ሀምዛ... (ብላ ጠራችዉና ለማዳመጥ ዝግጁ እንደሆነ ስታዉቅ ተንፈስ ብላ ንግግሯን ቀጠለች... ) ... ከሀቢብ ጋር እንደምንጣላ ታዉቃለህ እንዴ?" ብላ ጠየቀችዉ፡፡ ሀምዛ ያላሰበዉን ጥያቄ ስትጠይቀዉ ደንገጥ አለና... ..." ፎዚ ... ሀቢብ ጓደኛዬ እንደሆነ ታዉቂ የለ? ሁሌም ቤቱ ዉስጥ ስለተፈጠረዉ ነገር አይደብቀኝም" አላት፡፡ ..." ለምን ተገናኝተን አናወራም?" ብላ የትዳሯን አሳሳቢነትና አስጊ ሁኔታ ላይ እንዳለ ልትነግረዉ ፈለገች፡፡ በዚሁ ቅፅበት ግን ሀቢብ ሌላዉን ሁሉ የስልክ ንግግር ሳይሰማ "ለምን ተገናኝተን አናወራም?" የምትለዋን ቃል ሰይጣን ለጆሮዉ አቀበለዉ፡፡ ..."ምን? ... ከማን ጋር ነዉ የምትገናኘዉ?" ብሎ ጋደም ካለበት አልጋ ዘሎ ተነሳና ፎዚያ ወዳለችበት ክፍል ተጣደፈ፡፡ ልክ እሷ ጋር እንደደረሰ ከሀምዛ ጋር የሚገናኙበትን ቦታና ሰአት ተነጋግረዉ ስልኩን እየዘጋችዉ ነበር፡፡ እሷ ጋር እንደደረሰ አይኖቹ ሊወጡ ምንም አልቀራቸዉም፡፡ አፈጠጠባት፡፡ ፎዚ ፈራችዉ፡፡ ምን ትበለዉ? ምታወራዉ አጣች፡፡ ፊቷ የቆመዉ የምትወደዉና ዛሬ ቢቀየርም ድሮ የሚወዳት ባልሽ አልመስልሽ አላት፡፡ እሷን ለመደብደብ፤ ህይወቷን ለማበሳቆል፤ ትዳሯን ለማተራመስ፤ ኑሮዋን ለማዘባረቅ የተላከ 'ሰይጣን' ተመሰለባት፡፡ ሀቢብም ንዴቱ ምንም ሊያነጋግረዉ አልቻለም፡፡ አይኖቹ የሆነ ኢንች ያክል ቦታቸዉን ለቀዉ ወደ ፊት ወጣ ያሉ ይመስላሉ፡፡ ጉንጮቹ ተለጠጡ፤ ግባሩ ላይ የተጋደሙት መስመሮች የዘጠና አመት አዛዉንት አስመሰሉት፡፡ ኩስትርትር ብሏል፡፡ ሊመታትም ይቃጠዋል፡፡ በዚህ መሃል ጓደኛዉ ሀምዛ ደወለለት ... "ጢርርር ጢርርር..... ❥..........🍃💐💐🍃............❥ ክፍል 4  ከ100like👍 በኋላ   ይ  ቀ  ጥ  ላ  ል https://t.me/Melkam_liboch1
2 751
6
​​​​​​❣" ጤዛው ፍቅሬ"❣ 💝በመልካም ልቦች የቴሌግራም ቻናል የቀረበ💝 🍄ክፍል ሁለት (➋)🍄 ....... የሃቢብ ስድብ በየቀኑ ቢብስም ፎዚ ግን ቁብ ሳሰጠዉ እሱን ከማፍቀር አላስቆማትም ነበር፡፡ እየሰደባት ትወደዋለች፡፡ ከምንም በላይ የማትረሳዉ ነገር ቢኖር... አንድ ቀን ከስራ መመለሻዋ ሰአት ደርሶ ወደ ቤት እየሄደች ስልኳ ከቦርሳዋ ዉስጥ ሆኖ ይጠራ ነበር፡፡ ፎዚ አልሰማችዉም፡፡ በምትሄድበት መንገድ ዳር የነበረዉ ጫጫታና ሁካታ የስልኩን ድምፅ ሊያወጣዉ ስላልቻለ ፎዚ ስልኩን አንስታ ጥሪዉን ሳታስተናግድ ቀረች፡፡ ቤቷ እንደደረሰች ሃገር አማን - ቤቴ ሰላም ብላ የቤቷን የበር ቁልፍ ከፖርሳዋ አዉጥታ ስትሞክር እንዳጋጣሚ ሆኖ በሩ ክፍት ነበር፡፡ ሀቢብ ቀድሞ እንደገባ ስለተረዳች ሀሳቧን ሁሉ በሩ ላይ ጥላ ባሏን በአንዲስ መንፈስ ለመገናኘት በሙሉ ፈገግታና በሚያስቀና ደስታ እየተፍነከነከች የበሩን እጄታ ይዛ ከፈት ስታደርገዉ ያላሰበችዉ ነገር ገጠማት፡፡ ... ጣቶቹ ከብረት የጠነከሩ የሚመስሉ ሸካራ መዳፍ የፎዚ ፊት ላይ አረፈ "ጯ........." አይኗ እስኪሸፈን፤ የጉንጯ ቆዳ እስኪገፈፍ በጥፊ መታት፡፡ በድጋሜ 'ጯ...........'፡፡ ሀቢብ ነበር፡፡ "ለምንድን ነዉ ስልክ ያላነሳሽዉ?" በሚል ጥያቄ አንባረቀባት፡፡ ፎዚ አይኖቿን በግድ ከገለጠቻቸዉ በኃላ በፍርክርክ መዳፎች ጥፊ የቆሰለዉን ጉንጯን በእጆቿ እያሻሸች፤ ለማልቀስ እየዳዳት አይኖቿ በመቅፅብት እምባ አዝለዉ በለሆሳስ ድምፅ ... " ደዉለህ ነበር እንዴ?" አለችዉ፡፡ ሁሌም በመጥፎ ይጠረጥራት ኑሯልና... "አሃ... አንቺ ከማንም ወንድ ጋር እየዘለልሽ አዉቀሽ ያላነሳሽዉን ልትዋሺ ነዉ??" ብሎ ደም ማንባት በቀራቸዉን አይኖቹ አፈጠጠባት፡፡ አይኖቹ ቀልተዉ ነበር አይገልፃቸዉም፡፡ ደም የለበሱ፤ በርበሬ የጎረሱ መስለዋል፡፡ ሞባይሏን ለማዉጣት እጇን ወደ ፖርሳዋ እየሰደደች "ወላሂ አልዋሸሁህም" አለችዉ፡፡ "ዝምም በይ .. ቀጣፊ!" ብሎ ጥፊዉን ሊደግመዉ ቃጣዉ፡፡ . ... ፎዚያ በሃቢብ ከቦክስ ያላነሰ ጥፊ ጉንጯ ላይ ጠባሳ የቀረ ይመስል ይሄን ክስተት አረሳችዉም ነበር፡፡ ይሁን እንጂ ፍቅሩ በልጦ፤ መዉደዷ ገጦ ይበልጥ ነበርና ሁሉንም ይሁን ብላ በተቀበለችበት፤ ፀቡንም ነገሩንም ወደ ፍቅር ለዉጣ ትዳሯን አቆይታለች፡፡ . ...የሀቢብን መጥፎ ጥርጣሬ ለማስወገድ ስትል የድሮዉ ፍቅሩን ቢመልሰዉ ብላ ከምትሰራበት መስሪያ ቤት የመልቀቂያ ደብዳቤ እንኳ ሳታስገባ ለቀቀች፡፡ ምክንያቷ ደግሞ በተደጋጋሚ ከመስሪያ ቤት ወንዶች ጋር ትቀብጫለሽ 'እኔን ቀይረሽኛል' እያለ መዉጫ መግቢያ ሲያሳጣት፤ በቤቷ ዉስጥ ሰላም ሲነሳት 'ወጥቼ እንድሰራ ካልፈለክና ካላስደሰተህ ቤቴ እዉላለሁ' ብላዉ ባሏን ለመንከባከብ ለሀቢብ ካላት ሙሃባ የተነሳ ስራዋን እርግፍ አድርጋ ትታ ቤት ዉላለች፡፡ . ....... ይሄን ዱላና ተዳጋጋሚ የሆነዉ ስድቡ (ቀጣፊ...ዉሸታም...) ሳይከብዳት ዛሬ የተነፈሳት "እርካሽ" ያላት 'ርካሽ' ቃል ፎዚን እያነፋረቀ ያስለቅሳታል፡፡ 'እኔ ነኝ?... እኮ እኔ?... እኔ ነኝ እርካሿ?" እያለች ታላዝናለች፡፡ የኔ ዉድ የሚለዉ ጥሪዉ ባንዴ ተወግዶ፤ የፍቅር ቃላቶች እንደ ስደተኛ ርቆ ተሰዶ ቤታቸዉ የፀብ አዉድማ ሁኗል፡፡ ሰሞኑን ያመጣዉ አዲስ ፀባይ ደግሞ ፎዚን እየተፈታተናትና ትዳር እንዲያንገሻግሻት ሊያደርጋት ምነንም አልቀሯትም፡፡ ለሱ ብላ ስራ እንዳቆመች፤ በፀብ የጠለሸዉን ትዳር ወደ ፍቅር ለመቀየር እየተጋች ባለበት ወቅት......"እኔ ማመጣዉን ተቀምጦ መብላት አይከብድሽም?" ይላት ጀምሯል፡፡ ምንም አትመልስለትም ይልቁንስ በሱ መጥፎ ንግግርና ፀያፍ ተግባሩ ብትማረርም ሀቢብን መንከባከቧ ከእለት ወደ እለት ጨምሯል፡፡ ከስራ መመለሻዉ ሰአት ሲደርስ በሚያማምሩ ልብሶች ተሽቀርቅራ፤ እሱን በሚያማልሉ ነገሮች ተዉባ፤ እሱዉ በመረጠዉ ሽቶ ጠረኗን አዉዳ ትጠብቀዋለች፡፡ ..."... ሀቢቢ እንኳን ደህና መጣህልኝ!" ብላ እቅፏ ዉስጥ ልታስገባዉ እጇን ስትዘረጋ፤ የዘረጋችዉን እጇቿን በእጆቹ ገፍትሮና አመናቅሮ ... ..."አንቺማ በደህና እንድመለስ አትፈልጊም ነበር... ያዉ ተመለስኩ" ብሎ ነገሩን ይጀምረዋል፡፡ አሁንም ግን... ነገሩን ወደ ነገር ቀይራ ቤቱን በፀብ ቦንብ ማጋይት ስለማትፈልግ በሙሉ ፈገግታ ፈግጋ ወደ'ሱ ጠጋ እያለች... ..." ሀቢቢ ንፍቅ ብለኸኛል!" ትለዋለች፡፡እንደምታፈቅረዉ ያዉቃል፡፡ ነገር ግን እሱ ጸቡን ስለሚፈልገዉ የሷ የፍቅር ቃል አይረታዉም፡፡ "ሀቢቢ...፤ የኔ ማር...፤ የኔ ፍቅር...፤ ዉዴ..." እያለች የምትጠራዉ ነገር አይዋጥለትም፡፡ አጠገቡ ከተቀመጠች በኃላ ፀጉሩን እያሻሸች "ምን ሁነህብኝ ነዉ ዉዴ?" አለችዉ፡፡ እጆቿን ከፀጉሩ ላይ እያነሳ "ለምን ትነኪኛለሽ?" ብሎ አይኑን ጎለጎለባት፡፡ ፎዚ ይብስ እንዳይናደድ ብላ ዝም አለችዉ፡፡ ብቻ በስስት እያየችዉ አይኖቿን አይኖቹ ላይ ታንከባልላቸዋል፡፡ ግንባሩ ተጨማዶ ተኮሳትሮና ተቆጥቶ ከተቀመጠበት ምንጥቅ ብሎ ተመናጭቆ ተነሳና ወደ መኝታ ክፍሉ ገባ፡፡ በአስተያየቷ ተናዷል፡፡ የፍቅሯ ሃያልነት አፉን ዘጋዉ እንጂ በስስት የምታዬዉን ሚስቱን "ምን ታፈጫለሽ?" ማለትም አስቦ ነበር ። ❥..........🍃💐💐🍃............❥ ክፍል 3 ከ150 like በኋላ ይ  ቀ  ጥ  ላ  ል‼️ https://t.me/Melkam_liboch1
0
7
​​​​​​❣" ጤዛው ፍቅሬ"❣ 💝በመልካም ልቦች የቴሌግራም ቻናል የቀረበ💝 🍄ክፍል ሁለት (➋)🍄 ....... የሃቢብ ስድብ በየቀኑ ቢብስም ፎዚ ግን ቁብ ሳሰጠዉ እሱን ከማፍቀር አላስቆማትም ነበር፡፡ እየሰደባት ትወደዋለች፡፡ ከምንም በላይ የማትረሳዉ ነገር ቢኖር... አንድ ቀን ከስራ መመለሻዋ ሰአት ደርሶ ወደ ቤት እየሄደች ስልኳ ከቦርሳዋ ዉስጥ ሆኖ ይጠራ ነበር፡፡ ፎዚ አልሰማችዉም፡፡ በምትሄድበት መንገድ ዳር የነበረዉ ጫጫታና ሁካታ የስልኩን ድምፅ ሊያወጣዉ ስላልቻለ ፎዚ ስልኩን አንስታ ጥሪዉን ሳታስተናግድ ቀረች፡፡ ቤቷ እንደደረሰች ሃገር አማን - ቤቴ ሰላም ብላ የቤቷን የበር ቁልፍ ከፖርሳዋ አዉጥታ ስትሞክር እንዳጋጣሚ ሆኖ በሩ ክፍት ነበር፡፡ ሀቢብ ቀድሞ እንደገባ ስለተረዳች ሀሳቧን ሁሉ በሩ ላይ ጥላ ባሏን በአንዲስ መንፈስ ለመገናኘት በሙሉ ፈገግታና በሚያስቀና ደስታ እየተፍነከነከች የበሩን እጄታ ይዛ ከፈት ስታደርገዉ ያላሰበችዉ ነገር ገጠማት፡፡ ... ጣቶቹ ከብረት የጠነከሩ የሚመስሉ ሸካራ መዳፍ የፎዚ ፊት ላይ አረፈ "ጯ........." አይኗ እስኪሸፈን፤ የጉንጯ ቆዳ እስኪገፈፍ በጥፊ መታት፡፡ በድጋሜ 'ጯ...........'፡፡ ሀቢብ ነበር፡፡ "ለምንድን ነዉ ስልክ ያላነሳሽዉ?" በሚል ጥያቄ አንባረቀባት፡፡ ፎዚ አይኖቿን በግድ ከገለጠቻቸዉ በኃላ በፍርክርክ መዳፎች ጥፊ የቆሰለዉን ጉንጯን በእጆቿ እያሻሸች፤ ለማልቀስ እየዳዳት አይኖቿ በመቅፅብት እምባ አዝለዉ በለሆሳስ ድምፅ ... " ደዉለህ ነበር እንዴ?" አለችዉ፡፡ ሁሌም በመጥፎ ይጠረጥራት ኑሯልና... "አሃ... አንቺ ከማንም ወንድ ጋር እየዘለልሽ አዉቀሽ ያላነሳሽዉን ልትዋሺ ነዉ??" ብሎ ደም ማንባት በቀራቸዉን አይኖቹ አፈጠጠባት፡፡ አይኖቹ ቀልተዉ ነበር አይገልፃቸዉም፡፡ ደም የለበሱ፤ በርበሬ የጎረሱ መስለዋል፡፡ ሞባይሏን ለማዉጣት እጇን ወደ ፖርሳዋ እየሰደደች "ወላሂ አልዋሸሁህም" አለችዉ፡፡ "ዝምም በይ .. ቀጣፊ!" ብሎ ጥፊዉን ሊደግመዉ ቃጣዉ፡፡ . ... ፎዚያ በሃቢብ ከቦክስ ያላነሰ ጥፊ ጉንጯ ላይ ጠባሳ የቀረ ይመስል ይሄን ክስተት አረሳችዉም ነበር፡፡ ይሁን እንጂ ፍቅሩ በልጦ፤ መዉደዷ ገጦ ይበልጥ ነበርና ሁሉንም ይሁን ብላ በተቀበለችበት፤ ፀቡንም ነገሩንም ወደ ፍቅር ለዉጣ ትዳሯን አቆይታለች፡፡ . ...የሀቢብን መጥፎ ጥርጣሬ ለማስወገድ ስትል የድሮዉ ፍቅሩን ቢመልሰዉ ብላ ከምትሰራበት መስሪያ ቤት የመልቀቂያ ደብዳቤ እንኳ ሳታስገባ ለቀቀች፡፡ ምክንያቷ ደግሞ በተደጋጋሚ ከመስሪያ ቤት ወንዶች ጋር ትቀብጫለሽ 'እኔን ቀይረሽኛል' እያለ መዉጫ መግቢያ ሲያሳጣት፤ በቤቷ ዉስጥ ሰላም ሲነሳት 'ወጥቼ እንድሰራ ካልፈለክና ካላስደሰተህ ቤቴ እዉላለሁ' ብላዉ ባሏን ለመንከባከብ ለሀቢብ ካላት ሙሃባ የተነሳ ስራዋን እርግፍ አድርጋ ትታ ቤት ዉላለች፡፡ . ....... ይሄን ዱላና ተዳጋጋሚ የሆነዉ ስድቡ (ቀጣፊ...ዉሸታም...) ሳይከብዳት ዛሬ የተነፈሳት "እርካሽ" ያላት 'ርካሽ' ቃል ፎዚን እያነፋረቀ ያስለቅሳታል፡፡ 'እኔ ነኝ?... እኮ እኔ?... እኔ ነኝ እርካሿ?" እያለች ታላዝናለች፡፡ የኔ ዉድ የሚለዉ ጥሪዉ ባንዴ ተወግዶ፤ የፍቅር ቃላቶች እንደ ስደተኛ ርቆ ተሰዶ ቤታቸዉ የፀብ አዉድማ ሁኗል፡፡ ሰሞኑን ያመጣዉ አዲስ ፀባይ ደግሞ ፎዚን እየተፈታተናትና ትዳር እንዲያንገሻግሻት ሊያደርጋት ምነንም አልቀሯትም፡፡ ለሱ ብላ ስራ እንዳቆመች፤ በፀብ የጠለሸዉን ትዳር ወደ ፍቅር ለመቀየር እየተጋች ባለበት ወቅት......"እኔ ማመጣዉን ተቀምጦ መብላት አይከብድሽም?" ይላት ጀምሯል፡፡ ምንም አትመልስለትም ይልቁንስ በሱ መጥፎ ንግግርና ፀያፍ ተግባሩ ብትማረርም ሀቢብን መንከባከቧ ከእለት ወደ እለት ጨምሯል፡፡ ከስራ መመለሻዉ ሰአት ሲደርስ በሚያማምሩ ልብሶች ተሽቀርቅራ፤ እሱን በሚያማልሉ ነገሮች ተዉባ፤ እሱዉ በመረጠዉ ሽቶ ጠረኗን አዉዳ ትጠብቀዋለች፡፡ ..."... ሀቢቢ እንኳን ደህና መጣህልኝ!" ብላ እቅፏ ዉስጥ ልታስገባዉ እጇን ስትዘረጋ፤ የዘረጋችዉን እጇቿን በእጆቹ ገፍትሮና አመናቅሮ ... ..."አንቺማ በደህና እንድመለስ አትፈልጊም ነበር... ያዉ ተመለስኩ" ብሎ ነገሩን ይጀምረዋል፡፡ አሁንም ግን... ነገሩን ወደ ነገር ቀይራ ቤቱን በፀብ ቦንብ ማጋይት ስለማትፈልግ በሙሉ ፈገግታ ፈግጋ ወደ'ሱ ጠጋ እያለች... ..." ሀቢቢ ንፍቅ ብለኸኛል!" ትለዋለች፡፡እንደምታፈቅረዉ ያዉቃል፡፡ ነገር ግን እሱ ጸቡን ስለሚፈልገዉ የሷ የፍቅር ቃል አይረታዉም፡፡ "ሀቢቢ...፤ የኔ ማር...፤ የኔ ፍቅር...፤ ዉዴ..." እያለች የምትጠራዉ ነገር አይዋጥለትም፡፡ አጠገቡ ከተቀመጠች በኃላ ፀጉሩን እያሻሸች "ምን ሁነህብኝ ነዉ ዉዴ?" አለችዉ፡፡ እጆቿን ከፀጉሩ ላይ እያነሳ "ለምን ትነኪኛለሽ?" ብሎ አይኑን ጎለጎለባት፡፡ ፎዚ ይብስ እንዳይናደድ ብላ ዝም አለችዉ፡፡ ብቻ በስስት እያየችዉ አይኖቿን አይኖቹ ላይ ታንከባልላቸዋል፡፡ ግንባሩ ተጨማዶ ተኮሳትሮና ተቆጥቶ ከተቀመጠበት ምንጥቅ ብሎ ተመናጭቆ ተነሳና ወደ መኝታ ክፍሉ ገባ፡፡ በአስተያየቷ ተናዷል፡፡ የፍቅሯ ሃያልነት አፉን ዘጋዉ እንጂ በስስት የምታዬዉን ሚስቱን "ምን ታፈጫለሽ?" ማለትም አስቦ ነበር ። ❥..........🍃💐💐🍃............❥ ክፍል 3 ከ150 like በኋላ ይ  ቀ  ጥ  ላ  ል‼️ https://t.me/Melkam_liboch1
0
8
​​​​​ ❣ጤዛዉ ፍቅሬ🌿❣ 💝በመልካም ልቦች የቴሌግራም ቻናል የቀረበ💝      💘💘ክፍል አንድ💘💘 ❥..........🍃💐💐🍃...... .....የመቀሌ ዩኒቨርሲቲ የአራቱም ካምፓስ ተማሪዎች የምርቃን ፕሮግራም ለመታደም ተማሪዎች ቤተሰቦቻቸዉን ይዘዉ ከታሪካዊዉ ቦታ ተገኝተዋል፡፡ ይህ ቦታ ብዙ ሰዎች ይቺን ሃገር ለመታደግና ለመጠበቅ  ተሰግስጎባት የነበረዉን መዥገር ለመንቀል ለትግል የወጡ ጀግኖች የተቀበሩበት ቦታ 'ሀወልቲ-ሰማእታት' ነዉ፡፡ ተማሪዉቹ ደስታ ዉጧቸዉ ይፍነከነካሉ፡፡ እዚህም እዚያም ከወላጆቻቸዉ ጋር ተቃቅፈዉ ፎቶ የሚነሱ ይስተዋላሉ፤ እቅፍ አበባዎችና ሌሎች ዉድ ዉድ  ስጦታዎች ከወላጅና ከወዳጆቻቸዉ ይነጉዳሉ፡፡ በደስታ ብዛት ጥርሳቸዉ መከደን ያቃታቸዉ ተማሪዎች በዝተዋል፡፡ ከእነዚህ ተመራቂ ተማሪዎች መካከል ደግሞ ፎዚ አንደኛዋ ናት፡፡ ፌሽታ በፌሽታ ሆናለች፡፡ እንኳን ስቃ አኩርፋም እጅግ በጣም ዉብ ናት!፡፡ በዚያ ላይ ደስታዋ ሰዉነቷን፤ ፈገግታዋ ፊቷን አስዉቦት ከቤተሰቦቿ ጋር የሰማእታቱን ሀዉልት እየተጠጉ ፎቶ ይነሳሉ፡፡ ... ትንሽ እህቱን ለማስመረቅ ከአዲስ አበባ ተነስቶ የሰሜኗን ኮከብ መቀሌን የረገጣት ሀቢብ በእህቱ ጓደኛ ዉበት ፈዞ፤ ፍቅሯን አርግዞ ወደ አዲስ አበባ ተመልሷል፡፡ ፎዚ የሀቢብ እህት ጓደኛ በመሆኗ መቀሌ በቆየባቸዉ የአምስት ቀን እድሜ በደንብ ተግባብተዉና ስልክ ተለዋዉጠዉ ነዉ የተመለሰዉ፡፡ ትዉዉቃቸዉ በዚሁ ጀመረ.... ፡ ፡ ....... ሀቢብና ፎዚያ ከተጋቡ ሳምንታቶች ነጉደዉ ወራቶች ተቆጥረዋል፡፡ ፎዚን ከማግባቱ በፊት ለሁለት አመት ያክል ፍቅሩን በዉስጡ አምቆ ይዞት ለአንድ አመት ያክል ደግሞ የፍቅር ጥያቄ እያቀረበላት በመጨረሻም በጌታ ፍቃድ ተጋቡ፡፡ በጣም ይወዳታል፡፡ ሲወዳት ይወዳታል የሚለዉ ቃል ያንሰዋል፡፡ ሲያፈቅራት ያፈቅራታል የሚለዉ የፍቅር ትልቁ ቃል ሀቢብ ለፎዚያ ያለዉን ፍቅር አይገልፀዉም፡፡ ዘመኑን ሙሉ ከርሷ ጋር ሊኖር ምሎ፤ ዘላለም ላይለያት፤ በማንም ላይቀይራት ተገዝቶ ለምኗት አስለምኗት ብዙ መስዋእትነትን ከፍሎ ፎዚን የራሱ የግሉ ሊያደርጋት ችሏል፡፡ አግብቷታል፡፡  ህይወቷን በህይወቱ አቆራኝቱ የሰዉነቱ አምሳል፤ የአካሉ ክፋይ አድርጓታል፡፡ . ....... ፎዚያ የልጅነት ህልሟ ለትዳር ስትደርስ ማግባት የምትፈልገዉ ወንድ በዲኑ የላቀ፤ በትምህርቱ የረቀቀ፤ ጥላቻን አድክሞ፤ ፍቅርን አጣጥሞ መስጠት የሚችል ሰዉ እንዲያገባት ትፈልግ ነበር፡፡  የአካሉ ፍላጭ፤ የችግሩ ተጋፋጭ እንዲያደርጋት መሆን ምኞቷ ነበር፡፡ የፀባዬ ሸጋ፤ የቁመተ ሎጋ ወንዳ ወንድነትን ተላብሶ በሱና የደመቀ፤ በዒባዳ ለጌታዉ የወደቀ ሰዉ እንዲዘዉጃት- የዚያ ሰዉ ሚስት መሆን አቅዷ ነበር፡፡ . ....... ሁሌም ቢሆን አላህ የፈለገዉና የወሰነዉ ተግባር ላይ  ይዉላል እንጂ ሰዉ የፈለገዉን አያገባም፡፡ ሰዉ ያቀደዉን አይኖርም፡፡ ለህይወቱ ስኬት የቀየሰዉን መንገድ አይጓዝበትም፡፡ ሁሉም የአላህ ዉሳኔና የጌታ መሻት ናቸዉ፡፡ በዚህም ፎዚያ የልጅነትን ህልሟን በሚያኮላሽ መልኩ ስትመኘዉን የነበረ ነገር ሁሉ ሳይሳካላት በተቃራኒዉ የሆነዉን ሀቢብን አገባች፡፡ . ...... በርግጥ ሀቢብ የዲን እዉቀትም የለዉም፤ እንዲኖረዉም ጥረት አድርጎ አያዉቅም፡፡ ሶላት ሊሰግድ ቀርቶ የሶላት ጥሪ /አዛን/ ሲሰማ ያንገሸግሸዋል፡፡ ፎዚያ ይሄንን ሁሉ ተግባር ሳታገባዉ በፊት ቀድማ አዉቃ ነበር፡፡ ነገር ግን ... ፎዚን ለማግባትና ላለማጣት የራሱ ማድረግ ስለነበረበት፤ እንቡጥ ፅጌረዳ አይቶ ማለፍ ተስኖት ... 'የዲን እዉቀት የሌለኝ የቤተሰቦቼ አስተዳደግ ነዉ' እያለ ዋሻት፡፡ 'አንቺን የማገባ ከሆነ ግን ፀባዬ ይስተካከላል፤ ሶላት እጀምራለሁ፤ ቁርዓንም እቀራለሁ' ብሎ አሳምኗት የዋኀ ፎዚም ይሁን ብላ አምና ተቀብላዉ 'ባሌ ይስተካከላል፡፡ ቃል የገባልኝን ይፈፅማል' እያለች በባዶ የህልም ሩጫ ትሮጣለች፡፡ ....... በተጋቡ ከጥቂት ሳምንታት ቆይታ በኃላ ነገሩን ጀምሮት እያመሸ መግባት አዘወተረ፡፡ ከእሷ ጋር ላለማደር አልጋ እየለየ መተኛት ከጀመረ ሰነባበተ፡፡ የሚገባትን ክብርና እንክብካቤ ነፍጓት ሳያገባት በፊት ለፎዚ የነበረዉ ፍቅር በሚገርም ፍጥነት አሽቆልቁሎ በገባ በወጣ ቁጥር ባ'ፉ እያከላፈታት፤ አይኑና ፊቱ እየገለመጧት ኑሮን ከሃቢብ ጋር እየኖረች ነዉ፡፡ የሚገርመዉ ግን... ትወደዋለች፡፡ በጣም አፍቀረዋለች፡፡ ባሏን (ሀቢብ) በልቧ ዉስጥ እንደ ንጉስ አንግሳ፤ የፍቅር ካባን አልብሳ እየተንከባከበች ይዘዋለች፡፡ . .......ከእለታት ባንዱ ቀን ፎዚ መኝታ ቤቷ ዉስጥ አልጋዋ ላይ እጥፍጥፍ ብላ ተኝታ የተንተራሰችዉ ትራስ በእንባዋ ርሶ ታጥቦ እንደተጠመዘዘ ጨርቅ ረጥቧል፡፡  ... "እኔ ነኝ እርካሿ?" እያለች በመነፋረቅ አይኖቿን ቀይስር ያገመጠቻቸዉ እስኪመስል ድረስ ታነባለች፡፡ ታለቅሳለች፡፡ 'እርካሽ..." የሚለዉ የሀቢብ ስድብ በአይነ-ህሊናዋ እየተመላለሰ እንደ ገደል-ማሚት ያስተጋባባታል፡፡  "እርካሽ.... እኮ እኔ...እርካሽ....!" ❥..........🍃💐💐🍃............❥ ክፍል 2 ከ200like👍 በኋላ  ይ  ቀ  ጥ  ላ  ል‼️ https://t.me/Melkam_liboch1 ሼር🙏
0
9
ምርጥ ባህሪ🧡✅ --------- ★. ጥቂት አዉራ፡፡ ስታወራ ቀስ ብትል መልካም ነዉ ★. አንድ ቦታ ላይ ብዙ አትታይ፡፡ ስራህ ላይ አተኩር ተግባቢና የተረጋጋ ሰዉ ሁን ★. ማንም ትክክል ነህ እንዲልህ #አትጠብቅ፡፡ ማንም ደጋፊህ እንዲሆን አትጎትጉት ★. ስላለህ ነገር ደጋግመህ እየተናገርክ የመጎረር ስሜትን አስወግድ ★. ምርጥ #አዳማጭና መፍትሄ አምጪ ሁን ★. አደርገዋለሁ ያልከዉን ነገር አድርገዉ ★. በጣም ደስ ሲልህ ወይም በጣም ስታዝን ዉሳኔ #አትወስን! ★. የግል ጉዳይህን ላገኘኸዉ ሰዉ አትናገር ★. ሰዉ ስላንተ የፈለገዉን ቢያስብ ከማንነትህ ጋር አታገናኘዉ ★. ማንንም ለመጉዳት ብለህ ጉድጓድ ከመቆፈርም ይሁን ከማስቆፈር ራስህን አሽሽ ★. የጎዱህንና ‘ምንም የለዉም!’ ብለዉ የራቁህን ሰዎች ስኬታማ በመሆን አሳያቸዉ ★. ሃሳብህን ለማሳመን የሰዎችን ማንነት አትጉዳ፡፡ ትክክክል ብትሆን እንኳን ካመኑ ይመኑህ ካላመኑህ ጊዜዉ ያሳምናቸዋል መልካም ምሽት ምርጦቼ💛 https://t.me/Melkam_liboch1 ሼር አደራ
0
10
🥰 ልስምሽ ዞር ስል 💋                                      ልስምሽ ዞር ስል                  የሳትኩሽ አሳሳት🫣        አልረሳ ብሎኝ ፊቴ ላይ ታትሟል                ልክ እንደ ንቅሳት🤗          ድጋሜ አስበላኝ ይሄ ሞኝ ከንፈሬ   ይኸው ሳማት ስለው ይላል ነው አፍሬ🫣           ምኔ ነው ያስጠላሽ ፊቴ ነው አይኔ👁           ወይ ደግሞ ሊስምሽ ያሰበው                  ያ ሞኙ ከንፈሬ🥺   ምኔን ጠልተሽው ነው እንደዛ ሽል ያልሽኝ😒                   ያ ሞኙ ከንፈሬን💋           ልክ እንደ አበባ ያገረጣሽብኝ😢 ቆይ ምን አስበሽ ነው እንደዛ ሽል ያልሽኝ🤔 🤔🤔🤔🤔🤔🤔🤔🤔🤔🤔🤔🤔🤔🤔🤔🤔 https://t.me/Melkam_liboch1
0