ar
Feedback
🧡❤️መልካም ልቦች💞 ✍️

🧡❤️መልካም ልቦች💞 ✍️

الذهاب إلى القناة على Telegram

🌷 🥀♡♡ ማፍቀር ስትጀምር ከእምነት ጀምር ♡♡🌷 🙏WELLCOM TO 🧡❤️መልካም ልቦች💞 ✍️ ☆በዚህ ቻናል ውስጥ ደስ የሚሉ ☞ የ ፍቅር ቃላቶች፣ ☞ግጥሞች፣ ☞የፍቅር ታሪኮች ያገኛሉ ! t.me/Melkam_liboch1 ● ቻናላችንን SHARE ያድርጉ 🙏

إظهار المزيد
2 116
المشتركون
-524 ساؚات
+97 أيام
+2430 أيام

جاري تحميل البيانات...

سحابة العلامات
لا توجد بيانات
هل تواجه مشاكل؟ يرجى تحديث الصفحة أو الاتصال بمدير الدعم الخاص بنا.
الإشارات الواردة والصادرة
---
---
---
---
---
---
جذب المشتركين
يونيو '26
يونيو '26
+77
في 0 قنوات
مايو '26
+91
في 0 قنوات
Get PRO
أبريل '26
+104
في 0 قنوات
Get PRO
مارس '26
+160
في 0 قنوات
Get PRO
فبراير '26
+117
في 0 قنوات
Get PRO
يناير '26
+128
في 0 قنوات
Get PRO
ديسمبر '25
+175
في 0 قنوات
Get PRO
نوفمبر '25
+65
في 0 قنوات
Get PRO
أكتوبع '25
+63
في 0 قنوات
Get PRO
سبتمبر '25
+120
في 0 قنوات
Get PRO
أغسءس '25
+143
في 0 قنوات
Get PRO
يوليو '25
+73
في 0 قنوات
Get PRO
يونيو '25
+59
في 0 قنوات
Get PRO
مايو '25
+87
في 0 قنوات
Get PRO
أبريل '25
+111
في 0 قنوات
Get PRO
مارس '25
+168
في 0 قنوات
Get PRO
فبراير '25
+143
في 0 قنوات
Get PRO
يناير '25
+127
في 0 قنوات
Get PRO
ديسمبر '24
+121
في 0 قنوات
Get PRO
نوفمبر '24
+172
في 0 قنوات
Get PRO
أكتوبع '24
+114
في 0 قنوات
Get PRO
سبتمبر '24
+138
في 0 قنوات
Get PRO
أغسءس '24
+188
في 0 قنوات
Get PRO
يوليو '24
+207
في 0 قنوات
Get PRO
يونيو '24
+52
في 0 قنوات
Get PRO
مايو '24
+132
في 0 قنوات
Get PRO
أبريل '24
+315
في 0 قنوات
التاريخ
نمو المشتركين
الإشارات
القنوات
29 يونيو0
28 يونيو0
27 يونيو+3
26 يونيو+6
25 يونيو+2
24 يونيو+4
23 يونيو+3
22 يونيو+4
21 يونيو+3
20 يونيو+4
19 يونيو0
18 يونيو+2
17 يونيو+5
16 يونيو+3
15 يونيو+3
14 يونيو+2
13 يونيو+1
12 يونيو+2
11 يونيو+2
10 يونيو+3
09 يونيو+1
08 يونيو+2
07 يونيو+4
06 يونيو+3
05 يونيو+4
04 يونيو+2
03 يونيو+2
02 يونيو+6
01 يونيو+1
منشورات القناة
​​​​❣"ጤዛዉ ፍቅሬ"❣ 💝በመልካም ልቦች የቴሌግራም ቻናል የቀረበ💝 🍂ክፍል-➎- አምስት ❥............🍃💐💐🍃..............❥ .... ብዙ የፍቅር አይነቶች ቢኖሩም የሀቢብ አይነት ፍቅር ግን መጀመሪያዉኑም ፍቅር ሊያስብለዉ የሚችል አልነበረም፡፡ ሀምዛ በሀቢብ ንግግር ወደ መናደዱ እየሄደ ነዉ፡፡ ሀምዛ   ሀቢብና ፎዚን ሊያስማማ፤ በሁለት ባለትዳሮች መካከል የነበረን ጥላቻ አስወግዶ እርቅ ለማስፈን ነበር አካሔዱ፡፡ ነገር ግን የሀቢብ ንግግር ወደ ድርድር የሚያስገባ ሳይሆን መቃቃርን የሚፈጥር እንደ ስድቡ 'ርካሽ ቃላትን የሚመርጥ 'ርካሽነቱን የሚያንፀባርቅ ባህሪ አወጣ፡፡ ..."ጓደኛዬ (አለዉ ሀምዛ... ለዘብ ባለ ንግግር) ... እየዉልህ ሀቢብ በርግጥ አንተ ከፎዚ በፊት ብዙ ሴቶችን ታዉቃለህ፤ ከብዙ ሴቶችም ጋር ነበርክ፡፡ እነዚያ ጋር የነበርከዉ ብዙ አመታት ግን ፎዚ ጋር እንዳለህ የትዳር ዘመን የተባረከ ሳይሆን የረከሰ ጊዜ ነበር፡፡ ፎዚ ጋር አዲስ ህይወት ከጀመርክ ሰነባበትክ የመጀመሪያ ሰሞን ደስተኛ ነበርክ፡፡ አሁን ምን ተፈጥሮ ነዉ የተቀየርከዉ ሀቢብ...!?" ብሎ ጠየቀዉ፡፡ ሀምዛ በሚያወራበት ጊዜ ግን የሀቢብ ሀሳቡ በሙሉ በጥላቻ የመረዘዉ ልቡን ተጠቅሞ ጥላቻን እየሰነቀ ነበር፡፡ ....."ሀቢብ!!? ሄይ... ወደ የት ነጎድክ?" አለዉ ከተጓዘበት አለም እየመለሰዉ፡፡ ....."ሀምዛ እየሰማሃኝ ነዉ፡፡ አንተ ፎዚን ልትወዳት ትችላለህ እኔ ግን... እጠላታለሁ?" ሀምዛ የሀቢብ ነገር አዝማሚያ የገባዉ ይመስላል፡፡ ሀቢብ ወሬዉን ቀጠል አደረገና፡፡ ..."ለመሆኑ ከፎዚ ጋር ከመቼ ጀምሮ ነዉ መገናኘት የጀመራችሁት?" ..." ያዉም እኔ ባለቤቷ ሳላዉቅ?? ... እ??" ብሎ ዉስጡ ያለዉን ስሜት ቀስ እያለ ያወጣዉ ጀመር፡፡ "ሀቢብ.." አለዉ ሀምዛ በተምስጦ አይኑን እየተመለከተ ..."የኔና ያንተ ጓደኝነት ዛሬ አልተጀመረም፡፡ ፎዚያን ከማግባትህ በፊት ብዙ ችግሮችንና ፈተናዎችን አሳልፈናል፡፡ አያሌ የደስታ ቀኖችን አብረን ቦርቀናል፡፡ እኔም እነዚያን መልካም ጊዜዎች በማስታወስ የተለመደዉን የጓደኝነቴን ከጎንህ ልሆን ስለፈለኩኝ፣ ትዳርህ የሰመረና በባለቤትህ ደስተኛ እንድትሆን እንጂ ሌላን ነገር አስቤ አልነበረም፡፡" ብሎ መለሰለት በተረጋጋ መንፈስ፡፡ ሀቢብ ግን ለትዳሩ መስመር፣ ለህይወቱ መቃናት የሚጥርለትን ጓደኛዉን ዛቻም ጭምር እየተናገረዉ ነዉ፡፡ ..."ሰማሃኝ ሀምዛ... ምንም እሰብ ምን ከዚያች ሴት ሴት ጋር ያለህ ግንኙነት ጤነኛ አይደለም፡፡" አለዉ፡፡ መደዋወላቸዉንና ግንኙነታቸዉን እንዲያቋርጥ በማስጠንቀቅ፡፡ ..."እሺ ይቅርታ ጓደኛዬ...." ብሎ ከሀቢብ ጋር የያዘዉ ሙግት መፍትሄ እንደሌለዉና እንደማይበገርለት አወቀ፡፡ . . . ..... ፎዚ የቤቱ ሾል አድክሟት  ምንም ሳትተጣጠብ በስራ ልብሷ ቤቷ ቁጭ የማትመለስበት በሚመስል ያለፈ ትዝታዋ ላይ ተተክላ በሀሳብ ባህር ሰምጣለች፡፡ የትዝታን ቅኔ እያዜመች፤ እጆቸቿን አገጯ ላይ እንዳስደገፈች አይኖቿ ላይርገበገቡ ምለዉ የልጅነት ምኟቷን፤ የኮረዳነት ደስታዋን ማስታወስ ይዛለች፡፡ አሁን የተማረረችበትን ህይወት በትዝታ እንኳ ትደሰትበት እንጂ...፡፡ በዚህ መካከል ሀቢብ ከጓደኛዉ ሀምዛ ጋር የነበራቸዉን እሰጥ አገባ ጨርሰዉ ባለመስማማት ተለያይተዉ ወደ ቤቱ መጣ፡፡ ቤቱ እንደደረሰ በሩን ሳያንኳኳ ከፍቶ ገባ፡፡ ፎዚያ ከበሩ ፊት ለፊት ሶፋዉ ላይ ተቀምጣ ሀቢብ በሩን ከፍቶ ሲገባ አላስተዋለችዉም፡፡ ደትዝታን ባህር እየቀዘፈች ነበርና አዮታዉ ሳታየዉ ቀረች፡፡ አይኖቿ ሀቢብን በር ከፍቶ ሲገባ ቢያዩትም ልቧ ከትዝታዋ ጋር ነበርና ሳታስተዉለዉ ቀረች፡፡ 'ልብ ካላዬ አይን አያይም' አይደል ተረቱስ፡፡ ሀቢብ የበሩን እጄታ ይዞ መልሶ ከዘጋ በኃላ እየተንጎራደደ ወደ ፎዚያ ተጠጋ፡፡ እሷ ግን አሁንም አላየችዉም፡፡ ወደ እሷ የሚጠጋዉ ሰዉ ይሁን ሌላ ነገር አላስተዋለችዉም፡፡ ወደ እሷ ተጠግቶ ከተቀመጠችበት ሶፋ ፊት ለፊቷ ካለዉ ሶፋ ተቀምጦ ..."ፎዚ አላት" እሷ ግን አልሰማችዉም፡፡ አዉቃ ዝም እንዳላለችዉና በሀሳብ  እንደተዋጠች በአቀማመጧና ከሁኔታዋ አስተዉላሏል፡፡ እጁን በፊቷ ላይ እየወዘወዘ "ሄይይ ኧረ ፎዚ..." ሲላት ፎዚያ ከእንቅልፏ እንደሚነቃ አይነት ሰዉ ብትት ብላ ..."  እ ሀቢቢ መጥተሃል እንዴ? ልብስ ሳጥብኮ ቆይቼ ድክም ብሎኝ ነዉ፡፡" እያለች ክስም ብሎ የነበረ ፊቷን በፈገግታ አደመቀችዉ፡፡ ሀቢብም ለጠጥ ብሎ ሶፋዉን እንደ መደገፍ እያለ ..."እ ... ነዉ?" ብሎ ወሬዉን አሳጠረዉ፡፡ ..."አዎ! ሁቢ ደግሞ ሶፊ ጋር ደዉዬ ስናወራ ቆዬን" ብላ ስትነግረዉ .."ለምን እሷ ጋር ደወልሽ?" ብሎ ጮኸባት፡፡ (ሶፊያ የሀቢብ እህት፤ የፎዚያ ደግሞ የግቢ ጓደኛዋ ናት!)፡፡ በዚህ ጊዜ ፎዚያ ደንገጥ ብላ ደህና ሆኖ የነበረዉን ለምን አሁን እንዲህ ብዬ ለምን አስከፋሁት ብላ ለልሡ አሰበች፡፡ 'ግን ሶፊ ጋር እንድደዉል ለምን አልፈለገም፡፡' ብላም ራሷን ጠየቀች እንደገና መለሾ ብላ 'አይይ እንደፈለገ!' አለች፡፡ ..."ሀቢቢ የስራ ልብሴን ሳልቀይር እንኳ መጣህ... ቆይ ልብስ ቀይሬ ልምጣ" ብላ ከተቀመጠችበት ስተትነሳ ..."ተቀመጭ..." አላት፡፡ ደንገጥ ብላ ..."እ..." አለችዉ፡፡ ..."ተቀመጭ" ብሎ ቃሉን ደገመዉ፡፡ ..."እ...እ እሺ " ብላ ተቀመጠች፡፡ ፊቱ ሳይፈታ እንደተኮሳተረ ቆጣ ብሎ... ..."እንድናወራ የምፈልገዉ ጉዳይ አለ" አላት፡፡ ╔═══❖•🌺🌺•❖═══╗       áŠ­ááˆ 6 ከ like በኋላ     á‹­  ቀ  ጥ  ላ  ል https://t.me/Melkam_liboch1

2
​​​​❣"ጤዛዉ ፍቅሬ"❣ 💝በመልካም ልቦች የቴሌግራም ቻናል የቀረበ💝 🌿ክፍል አራት (➍)🌿 ጢርርር ... ጢርርርር..." ጥሪዉ (ደዋዩ) ማን እንደሆነ ለማየት ስልኩን ከሱሪዉ ኪስ አወጣና አየ፡፡ "Hamza" ይላል፡፡ ስልኩን ሳያነሳዉ ድምፁን ቀነሰና ጥሪዉን ድምፅ አልባ አደረገዉ፡፡ ንዴቱ ዉስጡን እያላወሰ ነበርና አይኑን ማጉረጥረጡን ቀጠለ፡፡... ..."ማን ነዉ የደወለዉ?" አላት፡፡ እጆቹን ጨብጦ ለቡጢ እያዘጋጃቸዉ፤ ሁኔታዉ ከሚስቱ ፊት ሳይሆን ከደመኛዉ ሊበቀለዉ ከሚፈልገዉ ሰዉ ፊት የቆመ ይመስላል፡፡ ፎዚያ ፈራችዉ፡፡ በዚህ ንዴቱ መምታት ከጀመራት እንደማያቆም ታዉቋት ትርበተበት ገባች፡፡ ወደ'ሷ ጠጋ እያላት ጥያቄዉን ደገመዉ፡፡ ..."ማን ነዉ የደወለዉ?... እ...?..." ፡፡ ምን ብላ ትመልስ?፡፡ ተደዉሎላት ሳይሆን ደዉላ ነዉ፡፡ 'ሀምዛ ነዉ ብለዉስ?.. ከ'ሱ ጋር ይጠረጥረኝ ይሆን?... የሚዋደዱ ጓደኛሞች በ'ኔ ምክንያት ቢጣሉስ?" እያለች ዉስጧን በስጋት ሞላችዉ፡፡ በዚሁ መካከል ሀምዛ ቅድም ደዉሎ ስላልተነሳለት በድጋሚ ለሀቢብ ደወለ ... "ጢርርርር... ጢርርርር...." የፎዚን ንዴት ስልኩ ላይ ሊወጣዉ ይመስል እጆቹን በሃይል ወደ ኪሱ ልኮ ስልኩን አወጣና  አረንጓዴዉን ተጭኖ..." ሄሎ ..." አለ፡፡ ..."ሄሎ ... ሃቢብ ብደዉልልህኮ አታነሳም" የሀምዛ ድምፅ ነበር፡፡ ከመበሳጨቱ የተነሳ ያሁኑ ደዋይ ማን እንደሆነ አላወቀዉም ነበር፡፡ ..."እ... አንተ ነህ እንዴ ሃምዛ..." ..."ስልክ ቁጥሬ ቢጠፋህ መቼም ድምፄ አይጠፋህም!" እሱ ራሱ ሃምዛ መሆኑን እያረጋገጠለት ነበር፡፡ ..."እ...ለማንሳት አልተመቸኝም ነበር" አለዉ፡፡ ..."ከፎዚ ጋር በምን ተጋጭታችሁ ነዉ?" ..."ማን ነገረህ?" ብሎ በቤቱ ዉስጥ አንገቱን አዟዙሮ ተመለከተ፡፡ 'ይሄ ሰዉዬ ተደብቆ እያየኝ ነዉ እንዴ?' ብሎ አሰበ፡፡  መጥፎ የሚሰራ ሰዉ እንኳን ሌላ ሰዉ ራሱንም ይጠራጠራል፡፡ ስራዉ እንደ ቂል አደረገዉ፡፡ ..."ፎዚ አሁን ደዉላልኝ ነበር፡፡"  ስልኩን ከጆሮዉ ስር 'ራቅ እያደረገ ወደ ኃላ እንደማፈግፈግ ብሎ ፎዚን በቆመችበት ትቷት ወደ መኝታ ክፍሉ ተመለሰ፡፡ ..."እና... ምን አባቷ ወደ አንተ አስደወላት..." አለዉ፡፡ የተጠራጠረ ይመስላል፡፡ 'ግንኙነት አላቸዉ ማለት ነዉ' ሲል አሰበ፡፡ 'በዚህ አይነትማ እስከዛሬ የምነግረዉን ለሷ ይነግራት ነበር ማለት ነዉ!' ... 'ቆይ ግን... ምንድን ነዉ ግንኙነታቸዉ?'፡፡ ሀምዛ ማሜን እየመከረዉ ነዉ፡፡ 'አትጣሉ...' እያለ የጓደኝነቱን ይነግረዋል፡፡ ሀቢብ ግን አልሰማዉም፡፡ እንደዉም ይባስ ብሎ ሀምዛን ከፎዚ ጋር መጠርጠር ይዟል፡፡ ካፉ አላወጣዉም እንጂ 'እሰራለሃላችኃለሁ' እያለ ከንፈሩን በቁጭት ይነክሳል፡፡ ..."እሺ በቃ አንጣላም ... ስንገናኝ እናወራለን!" ብሎት ስልኩ ተዘጋ፡፡ ሀቢብ ፎዚን ጠልቷታል እንዳይባል ይቀናባታል፤ ይወዳታል እንዳይባል ደግሞ ያሰቃያታል፡፡ ነገረ ስራዉ ሁሉ 'እሱ እንዲህ ነዉ!' ብሎ ለመወሰን ይከብዳል፡፡ .... ፎዚያ እራሷን ማስጨነቁን ተያያዘችዉ ..'ቆይ ሀቢብ ሊጠላኝ የቻለበት ምክንያት ምን ይሆን?' ብላ እርግጠኛ ሁና መመለስ በማትችለዉ ጥያቄ ራሷን ታፋጣለች፡፡ 'ያ የበፊቱ ፍቅርስ የት ገባ?' ...'ሶፊ ስለ ሀቢብ ጥሩነት እንጂ አንድም ቀን መጥፎነቱን አዉርታኝ አታዉቅም ነበር፡፡ ፍቅር መስጠት እንደሚችል እንጂ ልቡ በጥላቻ የጠቆረ መሆኑን አልነገረችኝም ነበር፡፡' ነበር... ነበር ... ነበር... እያለች እራሷን ወደ ኃላ እየጎተተች ሀቢብን የተዋወቀችበትን የምርቃን ጊዜዋን አማረረች፡፡ ያን በደስታ የተፍነከነከችበትን ቀን ረገመችዉ፡፡ 'ቆይ ግን ምን አጉድየበት ተቀየረ?'.... ጥያቄ በጥያቄ ላይ ብቻ መልሱን አታዉቀዉም፡፡ ብታዉቀዉ ግን ደስ ይላታል፡፡ ምክንያቱም ራሷን በራሷ ያፋጠጠችበትን ጥያቄ መልስ ከተመለሰላት ትዳሯ ይሰምራል፤ ፍቅሯ ያብባል ስለዚህ ለራሷ ለህይወቷ ስትል መሆን ያለባትን ሁና፤ መክፈል ያለባትን መስዋእትነት ከፍላ ደስታዋ እንደገና መለምለም አለበት፡፡ . ... ሀቢብና ሀምዛ ሁሌም ከሚገናኙበት ዘቢብ ካፌ ተገናኝተዉ እየተጨዋወቱ ነዉ፡፡ ሀቢብ ዉስጡ ልቡ በጥላቻ ከመጥቆሩም በላይ ከርፍቷል፡፡ የገዛ ጓደኛዉን ሀምዛን በፊት በሚወዳት ዛሬ ምክንያቱ ባልታወቀ ምክንያት ከሚጠላት ሚስቱ ጋር ጠርጥሮታል፡፡ በጨዋታቸዉ መካከል እየተሳሳቁ ቢያወሩም የሃቢብ ሳቅ የማስመሰል ግልፈጣ፤ የሀምዛ ግን ከልቡ የሚመጣ ነበር፡፡ ሀምዛ ቀስ እያለ ወደ ቁምነገሩ እየተንደረደረ ነዉ፡፡ ..."ታዉቃለህ ግን ሀቢብ?" ..."ምኑን ነዉ የማዉቀዉ?" አለዉ፡፡ ግንባሩን አጨማዶ፡፡ ሀምዛም ቀጥታ ስለ ፀቡ አንስቶ ይበልጥ ከሚያበሳጨዉ ምናልባት ያንን ጣፋጭ የፍቅር ጊዜዉን አስታዉሸዉ ልቡ ቢለዝብ ብሎ አሰበ፡፡ ..."ያንን የፍቅር ጊዜህን፡፡ በፍቅር ክንፍ ብለህ ከፎዚ ዉጭ ማሰብም ሆነ ማለም ያቆምክበት..." እያለ ስለ መልካም የፍቅር ጊዜዉ ሊያስታዉሰዉ ሲሞክር ሀቢብ የሃምዛን ወሬ አቋረጠና... ..."እ... አዎ ትዝ አለኝ!" ብሎ ወሬዉን ከመቀጠሉ በፊት ተንፈስ ሲል ሀምዛ ወደ በፊት አቋሙ ሊመለስልኝ ነዉ በማለት ልቡን ደስታ ተሰምቶት ጥርሶቹ ታዩ፡፡ ፈገግ አለ፡፡ ሀቢብም ያዘዉን ማኪያቱ ፉት ብሎ አፉን በማኪያቶዉ ቃና ካጣጣመ በኃላ ወሬዉን ቀጠለ... ..."እርካሽ መሆኗን ባዉቅ ኑሮ በፍቅር ቅልጥ ባላልኩላት ነበር፡፡" ብሎ ፈግጎ የነበረዉን የሀምዛን ፊት ወዲያዉ አከሰመዉ ╔═══❖•🌺🌺•❖═══╗        ክፍል 5 ከlike👍 በኋላ       ይ  ቀ  ጥ  ላ  ል https://t.me/Melkam_liboch1
2 855
3
​​​​​​❣ጤዛዉ ፍቅሬ"❣ 💝በመልካም ልቦች የቴሌግራም ቻናል የቀረበ💝   💐ክፍል ሶስት 💐   ....ፎዚ 'አሁን ደግሞ ምን አጠፋሁ?' ብላ የሀቢብ ሁኔታ አስጨነቃት፡፡ ከእለት ወደ እለት ለሷ ያለዉ ጥላቻ እየጨመረ መሄዱ ሃሳብ ገባት፡፡ እንዲህ አምራና ተዉባ ስጠብቀዉ 'የኔ ቆንጆ ዛሬ ደግሞ ይበልጥ አምሮብሻል' እንዲላት ነበር የፈለገችዉ፡፡ እሱ ግን ማሞገስ፤ ዉበት ማድነቅ የሚባለዉ ሃሳብ ሊመጣለት ቀርቶ እሷን መሸሽና እንደ ቆሻሻ ይርቃታል፤ ይፀየፋታል፡፡ ለዚህ ነገር መፍትሄ ማበጀት እንዳለባት አምና የሀቢብን የልብ ጓደኛ ሀምዛን ማማከር እንዳለባት ወሰነች፡፡ ምክንያቱም ሀቢብን ወደ ቀድሞዉ ፍቅሩ መመለስ ካልቻለች ትዳራቸዉ ገደል ስር እንደበቀለ ዛፍ በጊዜ ቆይታ ብዛት ተመንጉሎ እንደሚወድቅ ታዉቋታል፡፡ በፀብ የጠነከረ ትዳር፤ በንትርክ የተገነባ ፍቅር፤ በመቃቃር የተዋቀረ መዋደድ እንደሌለ ታዉቃለችና፡ . ... ሀምዛ የሀቢብ የልብ ጓደኛዉ ነዉ፡፡ ሁለቱ ጓደኛሞች (ሀቢብና ሀምዛ) መካከል ሚስጥር የሚባል ነገር የለም፡፡ እናም የሀቢብን የባህሪ መቀየር ሀምዛ ሊያዉቀዉ ይችላል በሚል ስልኳን አነሳችና የሃምዛን ቁጥር ጽፋ ደወለች፡፡ ስልኩ እየጠራ ነዉ፡፡ ሀምዛ ስልኩን አነሳና የፎዚ ጥሪ እንደሆነ በቁጥሩ ስላወቀ... ..." ሄሎ ፎዚ..." አላት፡፡ ..."አሰላሙዓለይኩም ሀምዛ... እንዴት ነህ?" ድምፅዋ ለቅሶዋን አቋርጣ የደወለች ሀዘንተኛ አስመስሏታል፡፡ ..."ወአለይኩም ሰላም ፎዚ ...ምን ሁነሻል?" ብሎ ጠየቃት፡፡ ልትደብቅዉ ያልቻለችዉ የዉስጥ ሀዘን እንዳለባት ያስታዉቅባታል፡፡ ፎዚም እየሆነች ያለችዉንና የሀቢብን የባህሪ መቀየር ለመንገር ስለደወለች ልትደብቀዉ ወይም በዝምታ ልታልፈዉ አልፈለገችም፡፡ ለሃምዛ ከመንገሯ በፊት ግን ዉስጧ ያለዉን ስሜቷን ትንፋሿ ቀድመዉ ነገሩት፡፡ "እህህህህ..." አለች፡፡ ሳታስበዉ ነበር በረጅሙ የተነፈሰችዉ፡፡ ..."ምነዉ ፎዚ?... ከሀቢብ ጋር ተጣላችሁ እንዴ?" ብሎ ከምትቀዝፈዉ የሀሳብ ባህር ዉስጥ አናጠባት፡፡ ..."ሀምዛ... (ብላ ጠራችዉና ለማዳመጥ ዝግጁ እንደሆነ ስታዉቅ ተንፈስ ብላ ንግግሯን ቀጠለች... ) ... ከሀቢብ ጋር እንደምንጣላ ታዉቃለህ እንዴ?" ብላ ጠየቀችዉ፡፡ ሀምዛ ያላሰበዉን ጥያቄ ስትጠይቀዉ ደንገጥ አለና... ..." ፎዚ ... ሀቢብ ጓደኛዬ እንደሆነ ታዉቂ የለ? ሁሌም ቤቱ ዉስጥ ስለተፈጠረዉ ነገር አይደብቀኝም" አላት፡፡ ..." ለምን ተገናኝተን አናወራም?" ብላ የትዳሯን አሳሳቢነትና አስጊ ሁኔታ ላይ እንዳለ ልትነግረዉ ፈለገች፡፡ በዚሁ ቅፅበት ግን ሀቢብ ሌላዉን ሁሉ የስልክ ንግግር ሳይሰማ "ለምን ተገናኝተን አናወራም?" የምትለዋን ቃል ሰይጣን ለጆሮዉ አቀበለዉ፡፡ ..."ምን? ... ከማን ጋር ነዉ የምትገናኘዉ?" ብሎ ጋደም ካለበት አልጋ ዘሎ ተነሳና ፎዚያ ወዳለችበት ክፍል ተጣደፈ፡፡ ልክ እሷ ጋር እንደደረሰ ከሀምዛ ጋር የሚገናኙበትን ቦታና ሰአት ተነጋግረዉ ስልኩን እየዘጋችዉ ነበር፡፡ እሷ ጋር እንደደረሰ አይኖቹ ሊወጡ ምንም አልቀራቸዉም፡፡ አፈጠጠባት፡፡ ፎዚ ፈራችዉ፡፡ ምን ትበለዉ? ምታወራዉ አጣች፡፡ ፊቷ የቆመዉ የምትወደዉና ዛሬ ቢቀየርም ድሮ የሚወዳት ባልሽ አልመስልሽ አላት፡፡ እሷን ለመደብደብ፤ ህይወቷን ለማበሳቆል፤ ትዳሯን ለማተራመስ፤ ኑሮዋን ለማዘባረቅ የተላከ 'ሰይጣን' ተመሰለባት፡፡ ሀቢብም ንዴቱ ምንም ሊያነጋግረዉ አልቻለም፡፡ አይኖቹ የሆነ ኢንች ያክል ቦታቸዉን ለቀዉ ወደ ፊት ወጣ ያሉ ይመስላሉ፡፡ ጉንጮቹ ተለጠጡ፤ ግባሩ ላይ የተጋደሙት መስመሮች የዘጠና አመት አዛዉንት አስመሰሉት፡፡ ኩስትርትር ብሏል፡፡ ሊመታትም ይቃጠዋል፡፡ በዚህ መሃል ጓደኛዉ ሀምዛ ደወለለት ... "ጢርርር ጢርርር..... ❥..........🍃💐💐🍃............❥ ክፍል 4  ከ100like👍 በኋላ   ይ  ቀ  ጥ  ላ  ል https://t.me/Melkam_liboch1
2 751
4
​​​​​​❣" ጤዛው ፍቅሬ"❣ 💝በመልካም ልቦች የቴሌግራም ቻናል የቀረበ💝 🍄ክፍል ሁለት (➋)🍄 ....... የሃቢብ ስድብ በየቀኑ ቢብስም ፎዚ ግን ቁብ ሳሰጠዉ እሱን ከማፍቀር አላስቆማትም ነበር፡፡ እየሰደባት ትወደዋለች፡፡ ከምንም በላይ የማትረሳዉ ነገር ቢኖር... አንድ ቀን ከስራ መመለሻዋ ሰአት ደርሶ ወደ ቤት እየሄደች ስልኳ ከቦርሳዋ ዉስጥ ሆኖ ይጠራ ነበር፡፡ ፎዚ አልሰማችዉም፡፡ በምትሄድበት መንገድ ዳር የነበረዉ ጫጫታና ሁካታ የስልኩን ድምፅ ሊያወጣዉ ስላልቻለ ፎዚ ስልኩን አንስታ ጥሪዉን ሳታስተናግድ ቀረች፡፡ ቤቷ እንደደረሰች ሃገር አማን - ቤቴ ሰላም ብላ የቤቷን የበር ቁልፍ ከፖርሳዋ አዉጥታ ስትሞክር እንዳጋጣሚ ሆኖ በሩ ክፍት ነበር፡፡ ሀቢብ ቀድሞ እንደገባ ስለተረዳች ሀሳቧን ሁሉ በሩ ላይ ጥላ ባሏን በአንዲስ መንፈስ ለመገናኘት በሙሉ ፈገግታና በሚያስቀና ደስታ እየተፍነከነከች የበሩን እጄታ ይዛ ከፈት ስታደርገዉ ያላሰበችዉ ነገር ገጠማት፡፡ ... ጣቶቹ ከብረት የጠነከሩ የሚመስሉ ሸካራ መዳፍ የፎዚ ፊት ላይ አረፈ "ጯ........." አይኗ እስኪሸፈን፤ የጉንጯ ቆዳ እስኪገፈፍ በጥፊ መታት፡፡ በድጋሜ 'ጯ...........'፡፡ ሀቢብ ነበር፡፡ "ለምንድን ነዉ ስልክ ያላነሳሽዉ?" በሚል ጥያቄ አንባረቀባት፡፡ ፎዚ አይኖቿን በግድ ከገለጠቻቸዉ በኃላ በፍርክርክ መዳፎች ጥፊ የቆሰለዉን ጉንጯን በእጆቿ እያሻሸች፤ ለማልቀስ እየዳዳት አይኖቿ በመቅፅብት እምባ አዝለዉ በለሆሳስ ድምፅ ... " ደዉለህ ነበር እንዴ?" አለችዉ፡፡ ሁሌም በመጥፎ ይጠረጥራት ኑሯልና... "አሃ... አንቺ ከማንም ወንድ ጋር እየዘለልሽ አዉቀሽ ያላነሳሽዉን ልትዋሺ ነዉ??" ብሎ ደም ማንባት በቀራቸዉን አይኖቹ አፈጠጠባት፡፡ አይኖቹ ቀልተዉ ነበር አይገልፃቸዉም፡፡ ደም የለበሱ፤ በርበሬ የጎረሱ መስለዋል፡፡ ሞባይሏን ለማዉጣት እጇን ወደ ፖርሳዋ እየሰደደች "ወላሂ አልዋሸሁህም" አለችዉ፡፡ "ዝምም በይ .. ቀጣፊ!" ብሎ ጥፊዉን ሊደግመዉ ቃጣዉ፡፡ . ... ፎዚያ በሃቢብ ከቦክስ ያላነሰ ጥፊ ጉንጯ ላይ ጠባሳ የቀረ ይመስል ይሄን ክስተት አረሳችዉም ነበር፡፡ ይሁን እንጂ ፍቅሩ በልጦ፤ መዉደዷ ገጦ ይበልጥ ነበርና ሁሉንም ይሁን ብላ በተቀበለችበት፤ ፀቡንም ነገሩንም ወደ ፍቅር ለዉጣ ትዳሯን አቆይታለች፡፡ . ...የሀቢብን መጥፎ ጥርጣሬ ለማስወገድ ስትል የድሮዉ ፍቅሩን ቢመልሰዉ ብላ ከምትሰራበት መስሪያ ቤት የመልቀቂያ ደብዳቤ እንኳ ሳታስገባ ለቀቀች፡፡ ምክንያቷ ደግሞ በተደጋጋሚ ከመስሪያ ቤት ወንዶች ጋር ትቀብጫለሽ 'እኔን ቀይረሽኛል' እያለ መዉጫ መግቢያ ሲያሳጣት፤ በቤቷ ዉስጥ ሰላም ሲነሳት 'ወጥቼ እንድሰራ ካልፈለክና ካላስደሰተህ ቤቴ እዉላለሁ' ብላዉ ባሏን ለመንከባከብ ለሀቢብ ካላት ሙሃባ የተነሳ ስራዋን እርግፍ አድርጋ ትታ ቤት ዉላለች፡፡ . ....... ይሄን ዱላና ተዳጋጋሚ የሆነዉ ስድቡ (ቀጣፊ...ዉሸታም...) ሳይከብዳት ዛሬ የተነፈሳት "እርካሽ" ያላት 'ርካሽ' ቃል ፎዚን እያነፋረቀ ያስለቅሳታል፡፡ 'እኔ ነኝ?... እኮ እኔ?... እኔ ነኝ እርካሿ?" እያለች ታላዝናለች፡፡ የኔ ዉድ የሚለዉ ጥሪዉ ባንዴ ተወግዶ፤ የፍቅር ቃላቶች እንደ ስደተኛ ርቆ ተሰዶ ቤታቸዉ የፀብ አዉድማ ሁኗል፡፡ ሰሞኑን ያመጣዉ አዲስ ፀባይ ደግሞ ፎዚን እየተፈታተናትና ትዳር እንዲያንገሻግሻት ሊያደርጋት ምነንም አልቀሯትም፡፡ ለሱ ብላ ስራ እንዳቆመች፤ በፀብ የጠለሸዉን ትዳር ወደ ፍቅር ለመቀየር እየተጋች ባለበት ወቅት......"እኔ ማመጣዉን ተቀምጦ መብላት አይከብድሽም?" ይላት ጀምሯል፡፡ ምንም አትመልስለትም ይልቁንስ በሱ መጥፎ ንግግርና ፀያፍ ተግባሩ ብትማረርም ሀቢብን መንከባከቧ ከእለት ወደ እለት ጨምሯል፡፡ ከስራ መመለሻዉ ሰአት ሲደርስ በሚያማምሩ ልብሶች ተሽቀርቅራ፤ እሱን በሚያማልሉ ነገሮች ተዉባ፤ እሱዉ በመረጠዉ ሽቶ ጠረኗን አዉዳ ትጠብቀዋለች፡፡ ..."... ሀቢቢ እንኳን ደህና መጣህልኝ!" ብላ እቅፏ ዉስጥ ልታስገባዉ እጇን ስትዘረጋ፤ የዘረጋችዉን እጇቿን በእጆቹ ገፍትሮና አመናቅሮ ... ..."አንቺማ በደህና እንድመለስ አትፈልጊም ነበር... ያዉ ተመለስኩ" ብሎ ነገሩን ይጀምረዋል፡፡ አሁንም ግን... ነገሩን ወደ ነገር ቀይራ ቤቱን በፀብ ቦንብ ማጋይት ስለማትፈልግ በሙሉ ፈገግታ ፈግጋ ወደ'ሱ ጠጋ እያለች... ..." ሀቢቢ ንፍቅ ብለኸኛል!" ትለዋለች፡፡እንደምታፈቅረዉ ያዉቃል፡፡ ነገር ግን እሱ ጸቡን ስለሚፈልገዉ የሷ የፍቅር ቃል አይረታዉም፡፡ "ሀቢቢ...፤ የኔ ማር...፤ የኔ ፍቅር...፤ ዉዴ..." እያለች የምትጠራዉ ነገር አይዋጥለትም፡፡ አጠገቡ ከተቀመጠች በኃላ ፀጉሩን እያሻሸች "ምን ሁነህብኝ ነዉ ዉዴ?" አለችዉ፡፡ እጆቿን ከፀጉሩ ላይ እያነሳ "ለምን ትነኪኛለሽ?" ብሎ አይኑን ጎለጎለባት፡፡ ፎዚ ይብስ እንዳይናደድ ብላ ዝም አለችዉ፡፡ ብቻ በስስት እያየችዉ አይኖቿን አይኖቹ ላይ ታንከባልላቸዋል፡፡ ግንባሩ ተጨማዶ ተኮሳትሮና ተቆጥቶ ከተቀመጠበት ምንጥቅ ብሎ ተመናጭቆ ተነሳና ወደ መኝታ ክፍሉ ገባ፡፡ በአስተያየቷ ተናዷል፡፡ የፍቅሯ ሃያልነት አፉን ዘጋዉ እንጂ በስስት የምታዬዉን ሚስቱን "ምን ታፈጫለሽ?" ማለትም አስቦ ነበር ። ❥..........🍃💐💐🍃............❥ ክፍል 3 ከ150 like በኋላ ይ  ቀ  ጥ  ላ  ል‼️ https://t.me/Melkam_liboch1
3 113
5
​​​​​​❣" ጤዛው ፍቅሬ"❣ 💝በመልካም ልቦች የቴሌግራም ቻናል የቀረበ💝 🍄ክፍል ሁለት (➋)🍄 ....... የሃቢብ ስድብ በየቀኑ ቢብስም ፎዚ ግን ቁብ ሳሰጠዉ እሱን ከማፍቀር አላስቆማትም ነበር፡፡ እየሰደባት ትወደዋለች፡፡ ከምንም በላይ የማትረሳዉ ነገር ቢኖር... አንድ ቀን ከስራ መመለሻዋ ሰአት ደርሶ ወደ ቤት እየሄደች ስልኳ ከቦርሳዋ ዉስጥ ሆኖ ይጠራ ነበር፡፡ ፎዚ አልሰማችዉም፡፡ በምትሄድበት መንገድ ዳር የነበረዉ ጫጫታና ሁካታ የስልኩን ድምፅ ሊያወጣዉ ስላልቻለ ፎዚ ስልኩን አንስታ ጥሪዉን ሳታስተናግድ ቀረች፡፡ ቤቷ እንደደረሰች ሃገር አማን - ቤቴ ሰላም ብላ የቤቷን የበር ቁልፍ ከፖርሳዋ አዉጥታ ስትሞክር እንዳጋጣሚ ሆኖ በሩ ክፍት ነበር፡፡ ሀቢብ ቀድሞ እንደገባ ስለተረዳች ሀሳቧን ሁሉ በሩ ላይ ጥላ ባሏን በአንዲስ መንፈስ ለመገናኘት በሙሉ ፈገግታና በሚያስቀና ደስታ እየተፍነከነከች የበሩን እጄታ ይዛ ከፈት ስታደርገዉ ያላሰበችዉ ነገር ገጠማት፡፡ ... ጣቶቹ ከብረት የጠነከሩ የሚመስሉ ሸካራ መዳፍ የፎዚ ፊት ላይ አረፈ "ጯ........." አይኗ እስኪሸፈን፤ የጉንጯ ቆዳ እስኪገፈፍ በጥፊ መታት፡፡ በድጋሜ 'ጯ...........'፡፡ ሀቢብ ነበር፡፡ "ለምንድን ነዉ ስልክ ያላነሳሽዉ?" በሚል ጥያቄ አንባረቀባት፡፡ ፎዚ አይኖቿን በግድ ከገለጠቻቸዉ በኃላ በፍርክርክ መዳፎች ጥፊ የቆሰለዉን ጉንጯን በእጆቿ እያሻሸች፤ ለማልቀስ እየዳዳት አይኖቿ በመቅፅብት እምባ አዝለዉ በለሆሳስ ድምፅ ... " ደዉለህ ነበር እንዴ?" አለችዉ፡፡ ሁሌም በመጥፎ ይጠረጥራት ኑሯልና... "አሃ... አንቺ ከማንም ወንድ ጋር እየዘለልሽ አዉቀሽ ያላነሳሽዉን ልትዋሺ ነዉ??" ብሎ ደም ማንባት በቀራቸዉን አይኖቹ አፈጠጠባት፡፡ አይኖቹ ቀልተዉ ነበር አይገልፃቸዉም፡፡ ደም የለበሱ፤ በርበሬ የጎረሱ መስለዋል፡፡ ሞባይሏን ለማዉጣት እጇን ወደ ፖርሳዋ እየሰደደች "ወላሂ አልዋሸሁህም" አለችዉ፡፡ "ዝምም በይ .. ቀጣፊ!" ብሎ ጥፊዉን ሊደግመዉ ቃጣዉ፡፡ . ... ፎዚያ በሃቢብ ከቦክስ ያላነሰ ጥፊ ጉንጯ ላይ ጠባሳ የቀረ ይመስል ይሄን ክስተት አረሳችዉም ነበር፡፡ ይሁን እንጂ ፍቅሩ በልጦ፤ መዉደዷ ገጦ ይበልጥ ነበርና ሁሉንም ይሁን ብላ በተቀበለችበት፤ ፀቡንም ነገሩንም ወደ ፍቅር ለዉጣ ትዳሯን አቆይታለች፡፡ . ...የሀቢብን መጥፎ ጥርጣሬ ለማስወገድ ስትል የድሮዉ ፍቅሩን ቢመልሰዉ ብላ ከምትሰራበት መስሪያ ቤት የመልቀቂያ ደብዳቤ እንኳ ሳታስገባ ለቀቀች፡፡ ምክንያቷ ደግሞ በተደጋጋሚ ከመስሪያ ቤት ወንዶች ጋር ትቀብጫለሽ 'እኔን ቀይረሽኛል' እያለ መዉጫ መግቢያ ሲያሳጣት፤ በቤቷ ዉስጥ ሰላም ሲነሳት 'ወጥቼ እንድሰራ ካልፈለክና ካላስደሰተህ ቤቴ እዉላለሁ' ብላዉ ባሏን ለመንከባከብ ለሀቢብ ካላት ሙሃባ የተነሳ ስራዋን እርግፍ አድርጋ ትታ ቤት ዉላለች፡፡ . ....... ይሄን ዱላና ተዳጋጋሚ የሆነዉ ስድቡ (ቀጣፊ...ዉሸታም...) ሳይከብዳት ዛሬ የተነፈሳት "እርካሽ" ያላት 'ርካሽ' ቃል ፎዚን እያነፋረቀ ያስለቅሳታል፡፡ 'እኔ ነኝ?... እኮ እኔ?... እኔ ነኝ እርካሿ?" እያለች ታላዝናለች፡፡ የኔ ዉድ የሚለዉ ጥሪዉ ባንዴ ተወግዶ፤ የፍቅር ቃላቶች እንደ ስደተኛ ርቆ ተሰዶ ቤታቸዉ የፀብ አዉድማ ሁኗል፡፡ ሰሞኑን ያመጣዉ አዲስ ፀባይ ደግሞ ፎዚን እየተፈታተናትና ትዳር እንዲያንገሻግሻት ሊያደርጋት ምነንም አልቀሯትም፡፡ ለሱ ብላ ስራ እንዳቆመች፤ በፀብ የጠለሸዉን ትዳር ወደ ፍቅር ለመቀየር እየተጋች ባለበት ወቅት......"እኔ ማመጣዉን ተቀምጦ መብላት አይከብድሽም?" ይላት ጀምሯል፡፡ ምንም አትመልስለትም ይልቁንስ በሱ መጥፎ ንግግርና ፀያፍ ተግባሩ ብትማረርም ሀቢብን መንከባከቧ ከእለት ወደ እለት ጨምሯል፡፡ ከስራ መመለሻዉ ሰአት ሲደርስ በሚያማምሩ ልብሶች ተሽቀርቅራ፤ እሱን በሚያማልሉ ነገሮች ተዉባ፤ እሱዉ በመረጠዉ ሽቶ ጠረኗን አዉዳ ትጠብቀዋለች፡፡ ..."... ሀቢቢ እንኳን ደህና መጣህልኝ!" ብላ እቅፏ ዉስጥ ልታስገባዉ እጇን ስትዘረጋ፤ የዘረጋችዉን እጇቿን በእጆቹ ገፍትሮና አመናቅሮ ... ..."አንቺማ በደህና እንድመለስ አትፈልጊም ነበር... ያዉ ተመለስኩ" ብሎ ነገሩን ይጀምረዋል፡፡ አሁንም ግን... ነገሩን ወደ ነገር ቀይራ ቤቱን በፀብ ቦንብ ማጋይት ስለማትፈልግ በሙሉ ፈገግታ ፈግጋ ወደ'ሱ ጠጋ እያለች... ..." ሀቢቢ ንፍቅ ብለኸኛል!" ትለዋለች፡፡እንደምታፈቅረዉ ያዉቃል፡፡ ነገር ግን እሱ ጸቡን ስለሚፈልገዉ የሷ የፍቅር ቃል አይረታዉም፡፡ "ሀቢቢ...፤ የኔ ማር...፤ የኔ ፍቅር...፤ ዉዴ..." እያለች የምትጠራዉ ነገር አይዋጥለትም፡፡ አጠገቡ ከተቀመጠች በኃላ ፀጉሩን እያሻሸች "ምን ሁነህብኝ ነዉ ዉዴ?" አለችዉ፡፡ እጆቿን ከፀጉሩ ላይ እያነሳ "ለምን ትነኪኛለሽ?" ብሎ አይኑን ጎለጎለባት፡፡ ፎዚ ይብስ እንዳይናደድ ብላ ዝም አለችዉ፡፡ ብቻ በስስት እያየችዉ አይኖቿን አይኖቹ ላይ ታንከባልላቸዋል፡፡ ግንባሩ ተጨማዶ ተኮሳትሮና ተቆጥቶ ከተቀመጠበት ምንጥቅ ብሎ ተመናጭቆ ተነሳና ወደ መኝታ ክፍሉ ገባ፡፡ በአስተያየቷ ተናዷል፡፡ የፍቅሯ ሃያልነት አፉን ዘጋዉ እንጂ በስስት የምታዬዉን ሚስቱን "ምን ታፈጫለሽ?" ማለትም አስቦ ነበር ። ❥..........🍃💐💐🍃............❥ ክፍል 3 ከ150 like በኋላ ይ  ቀ  ጥ  ላ  ል‼️ https://t.me/Melkam_liboch1
1
6
​​​​​ ❣ጤዛዉ ፍቅሬ🌿❣ 💝በመልካም ልቦች የቴሌግራም ቻናል የቀረበ💝      💘💘ክፍል አንድ💘💘 ❥..........🍃💐💐🍃...... .....የመቀሌ ዩኒቨርሲቲ የአራቱም ካምፓስ ተማሪዎች የምርቃን ፕሮግራም ለመታደም ተማሪዎች ቤተሰቦቻቸዉን ይዘዉ ከታሪካዊዉ ቦታ ተገኝተዋል፡፡ ይህ ቦታ ብዙ ሰዎች ይቺን ሃገር ለመታደግና ለመጠበቅ  ተሰግስጎባት የነበረዉን መዥገር ለመንቀል ለትግል የወጡ ጀግኖች የተቀበሩበት ቦታ 'ሀወልቲ-ሰማእታት' ነዉ፡፡ ተማሪዉቹ ደስታ ዉጧቸዉ ይፍነከነካሉ፡፡ እዚህም እዚያም ከወላጆቻቸዉ ጋር ተቃቅፈዉ ፎቶ የሚነሱ ይስተዋላሉ፤ እቅፍ አበባዎችና ሌሎች ዉድ ዉድ  ስጦታዎች ከወላጅና ከወዳጆቻቸዉ ይነጉዳሉ፡፡ በደስታ ብዛት ጥርሳቸዉ መከደን ያቃታቸዉ ተማሪዎች በዝተዋል፡፡ ከእነዚህ ተመራቂ ተማሪዎች መካከል ደግሞ ፎዚ አንደኛዋ ናት፡፡ ፌሽታ በፌሽታ ሆናለች፡፡ እንኳን ስቃ አኩርፋም እጅግ በጣም ዉብ ናት!፡፡ በዚያ ላይ ደስታዋ ሰዉነቷን፤ ፈገግታዋ ፊቷን አስዉቦት ከቤተሰቦቿ ጋር የሰማእታቱን ሀዉልት እየተጠጉ ፎቶ ይነሳሉ፡፡ ... ትንሽ እህቱን ለማስመረቅ ከአዲስ አበባ ተነስቶ የሰሜኗን ኮከብ መቀሌን የረገጣት ሀቢብ በእህቱ ጓደኛ ዉበት ፈዞ፤ ፍቅሯን አርግዞ ወደ አዲስ አበባ ተመልሷል፡፡ ፎዚ የሀቢብ እህት ጓደኛ በመሆኗ መቀሌ በቆየባቸዉ የአምስት ቀን እድሜ በደንብ ተግባብተዉና ስልክ ተለዋዉጠዉ ነዉ የተመለሰዉ፡፡ ትዉዉቃቸዉ በዚሁ ጀመረ.... ፡ ፡ ....... ሀቢብና ፎዚያ ከተጋቡ ሳምንታቶች ነጉደዉ ወራቶች ተቆጥረዋል፡፡ ፎዚን ከማግባቱ በፊት ለሁለት አመት ያክል ፍቅሩን በዉስጡ አምቆ ይዞት ለአንድ አመት ያክል ደግሞ የፍቅር ጥያቄ እያቀረበላት በመጨረሻም በጌታ ፍቃድ ተጋቡ፡፡ በጣም ይወዳታል፡፡ ሲወዳት ይወዳታል የሚለዉ ቃል ያንሰዋል፡፡ ሲያፈቅራት ያፈቅራታል የሚለዉ የፍቅር ትልቁ ቃል ሀቢብ ለፎዚያ ያለዉን ፍቅር አይገልፀዉም፡፡ ዘመኑን ሙሉ ከርሷ ጋር ሊኖር ምሎ፤ ዘላለም ላይለያት፤ በማንም ላይቀይራት ተገዝቶ ለምኗት አስለምኗት ብዙ መስዋእትነትን ከፍሎ ፎዚን የራሱ የግሉ ሊያደርጋት ችሏል፡፡ አግብቷታል፡፡  ህይወቷን በህይወቱ አቆራኝቱ የሰዉነቱ አምሳል፤ የአካሉ ክፋይ አድርጓታል፡፡ . ....... ፎዚያ የልጅነት ህልሟ ለትዳር ስትደርስ ማግባት የምትፈልገዉ ወንድ በዲኑ የላቀ፤ በትምህርቱ የረቀቀ፤ ጥላቻን አድክሞ፤ ፍቅርን አጣጥሞ መስጠት የሚችል ሰዉ እንዲያገባት ትፈልግ ነበር፡፡  የአካሉ ፍላጭ፤ የችግሩ ተጋፋጭ እንዲያደርጋት መሆን ምኞቷ ነበር፡፡ የፀባዬ ሸጋ፤ የቁመተ ሎጋ ወንዳ ወንድነትን ተላብሶ በሱና የደመቀ፤ በዒባዳ ለጌታዉ የወደቀ ሰዉ እንዲዘዉጃት- የዚያ ሰዉ ሚስት መሆን አቅዷ ነበር፡፡ . ....... ሁሌም ቢሆን አላህ የፈለገዉና የወሰነዉ ተግባር ላይ  ይዉላል እንጂ ሰዉ የፈለገዉን አያገባም፡፡ ሰዉ ያቀደዉን አይኖርም፡፡ ለህይወቱ ስኬት የቀየሰዉን መንገድ አይጓዝበትም፡፡ ሁሉም የአላህ ዉሳኔና የጌታ መሻት ናቸዉ፡፡ በዚህም ፎዚያ የልጅነትን ህልሟን በሚያኮላሽ መልኩ ስትመኘዉን የነበረ ነገር ሁሉ ሳይሳካላት በተቃራኒዉ የሆነዉን ሀቢብን አገባች፡፡ . ...... በርግጥ ሀቢብ የዲን እዉቀትም የለዉም፤ እንዲኖረዉም ጥረት አድርጎ አያዉቅም፡፡ ሶላት ሊሰግድ ቀርቶ የሶላት ጥሪ /አዛን/ ሲሰማ ያንገሸግሸዋል፡፡ ፎዚያ ይሄንን ሁሉ ተግባር ሳታገባዉ በፊት ቀድማ አዉቃ ነበር፡፡ ነገር ግን ... ፎዚን ለማግባትና ላለማጣት የራሱ ማድረግ ስለነበረበት፤ እንቡጥ ፅጌረዳ አይቶ ማለፍ ተስኖት ... 'የዲን እዉቀት የሌለኝ የቤተሰቦቼ አስተዳደግ ነዉ' እያለ ዋሻት፡፡ 'አንቺን የማገባ ከሆነ ግን ፀባዬ ይስተካከላል፤ ሶላት እጀምራለሁ፤ ቁርዓንም እቀራለሁ' ብሎ አሳምኗት የዋኀ ፎዚም ይሁን ብላ አምና ተቀብላዉ 'ባሌ ይስተካከላል፡፡ ቃል የገባልኝን ይፈፅማል' እያለች በባዶ የህልም ሩጫ ትሮጣለች፡፡ ....... በተጋቡ ከጥቂት ሳምንታት ቆይታ በኃላ ነገሩን ጀምሮት እያመሸ መግባት አዘወተረ፡፡ ከእሷ ጋር ላለማደር አልጋ እየለየ መተኛት ከጀመረ ሰነባበተ፡፡ የሚገባትን ክብርና እንክብካቤ ነፍጓት ሳያገባት በፊት ለፎዚ የነበረዉ ፍቅር በሚገርም ፍጥነት አሽቆልቁሎ በገባ በወጣ ቁጥር ባ'ፉ እያከላፈታት፤ አይኑና ፊቱ እየገለመጧት ኑሮን ከሃቢብ ጋር እየኖረች ነዉ፡፡ የሚገርመዉ ግን... ትወደዋለች፡፡ በጣም አፍቀረዋለች፡፡ ባሏን (ሀቢብ) በልቧ ዉስጥ እንደ ንጉስ አንግሳ፤ የፍቅር ካባን አልብሳ እየተንከባከበች ይዘዋለች፡፡ . .......ከእለታት ባንዱ ቀን ፎዚ መኝታ ቤቷ ዉስጥ አልጋዋ ላይ እጥፍጥፍ ብላ ተኝታ የተንተራሰችዉ ትራስ በእንባዋ ርሶ ታጥቦ እንደተጠመዘዘ ጨርቅ ረጥቧል፡፡  ... "እኔ ነኝ እርካሿ?" እያለች በመነፋረቅ አይኖቿን ቀይስር ያገመጠቻቸዉ እስኪመስል ድረስ ታነባለች፡፡ ታለቅሳለች፡፡ 'እርካሽ..." የሚለዉ የሀቢብ ስድብ በአይነ-ህሊናዋ እየተመላለሰ እንደ ገደል-ማሚት ያስተጋባባታል፡፡  "እርካሽ.... እኮ እኔ...እርካሽ....!" ❥..........🍃💐💐🍃............❥ ክፍል 2 ከ200like👍 በኋላ  ይ  ቀ  ጥ  ላ  ል‼️ https://t.me/Melkam_liboch1 ሼር🙏
2 987
7
ምርጥ ባህሪ🧡✅ --------- ★. ጥቂት አዉራ፡፡ ስታወራ ቀስ ብትል መልካም ነዉ ★. አንድ ቦታ ላይ ብዙ አትታይ፡፡ ስራህ ላይ አተኩር ተግባቢና የተረጋጋ ሰዉ ሁን ★. ማንም ትክክል ነህ እንዲልህ #አትጠብቅ፡፡ ማንም ደጋፊህ እንዲሆን አትጎትጉት ★. ስላለህ ነገር ደጋግመህ እየተናገርክ የመጎረር ስሜትን አስወግድ ★. ምርጥ #አዳማጭና መፍትሄ አምጪ ሁን ★. አደርገዋለሁ ያልከዉን ነገር አድርገዉ ★. በጣም ደስ ሲልህ ወይም በጣም ስታዝን ዉሳኔ #አትወስን! ★. የግል ጉዳይህን ላገኘኸዉ ሰዉ አትናገር ★. ሰዉ ስላንተ የፈለገዉን ቢያስብ ከማንነትህ ጋር አታገናኘዉ ★. ማንንም ለመጉዳት ብለህ ጉድጓድ ከመቆፈርም ይሁን ከማስቆፈር ራስህን አሽሽ ★. የጎዱህንና ‘ምንም የለዉም!’ ብለዉ የራቁህን ሰዎች ስኬታማ በመሆን አሳያቸዉ ★. ሃሳብህን ለማሳመን የሰዎችን ማንነት አትጉዳ፡፡ ትክክክል ብትሆን እንኳን ካመኑ ይመኑህ ካላመኑህ ጊዜዉ ያሳምናቸዋል መልካም ምሽት ምርጦቼ💛 https://t.me/Melkam_liboch1 ሼር አደራ
2 580
8
🥰 ልስምሽ ዞር ስል 💋                                      ልስምሽ ዞር ስል                  የሳትኩሽ አሳሳት🫣        አልረሳ ብሎኝ ፊቴ ላይ ታትሟል                ልክ እንደ ንቅሳት🤗          ድጋሜ አስበላኝ ይሄ ሞኝ ከንፈሬ   ይኸው ሳማት ስለው ይላል ነው አፍሬ🫣           ምኔ ነው ያስጠላሽ ፊቴ ነው አይኔ👁           ወይ ደግሞ ሊስምሽ ያሰበው                  ያ ሞኙ ከንፈሬ🥺   ምኔን ጠልተሽው ነው እንደዛ ሽል ያልሽኝ😒                   ያ ሞኙ ከንፈሬን💋           ልክ እንደ አበባ ያገረጣሽብኝ😢 ቆይ ምን አስበሽ ነው እንደዛ ሽል ያልሽኝ🤔 🤔🤔🤔🤔🤔🤔🤔🤔🤔🤔🤔🤔🤔🤔🤔🤔 https://t.me/Melkam_liboch1
2 606
9
​​💖 ኤልዳና  💞 💝ልብ አንጠልጣይ የ ፍቅር ታሪክ በመልካም ልቦች የቴሌግራም ቻናል ተዘጋጅቶ የቀረበ💝           ክፍል 3⃣4⃣ የመጨረሻው ክፍል ዝም ዝም ዝም ተባባልን ትንሽ ቆየና አንዳንዴ አንቺ ከለፋሽለት ዋጋ ከከፈልሽለት ፍቅር ይልቅ እጣ ፈንታሽ በልጦ ይገኛል እጣ ፈንታ ሚባለው ነገር ለካ እውነት ነው አይገርምሽም ያን ያህል ቀን ካንቺጋ ስናድር አላረገዝሽም መከላከያም አልተጠቀምሽም አንድ ቀን ከቃልጋ አደርኩ ለዛውም በስተት እሷ ግን አረገዘች በዛ አሰረችኝ እናቴን መስመር ባታስዢልኝ ባታግዣትና አሪፍ ሁኔታ ላይ ሆና ባጠብቀኝ ኖሮ እራሴን ሳላስተዳድር ለሷም ሸክም እሆንባት ነበር አሁን ግን ቢያንስ ለልጄ መኖር አያቅተኝምአለ። አንቸ ባበጀሽው ባስተካከልሽው መንገድ ላይ እኔ ከሚስቴና ከልጄጋ ልጓዝበት ነው። አንዳንድ ስተቶች አንዴ ከሆኑ ቡሀላ መስተካከያ የላቸውም ከረፈደ እረፈደ ነው። አብሮ የኖረን ሰው መሸኘት ባንድ ቀን ያውም ባንድ ጀንበር ማጣትን የሚያህል ለሰው ልጅ ምን አለ የሚከብድ ነገር የሚለውን ዘፈን አዳመጥሽው ታቂያለሽ ብሎ ተነስቶ ጥሎኝ ሄደ። . . . . ዛሬ ከሶስት አመት ቡሀላ መኪናዬ ውስጥ ቁጭ ብዬ ባሌን (ዴቭን)እየጠበኩ እዩና ቃል ከግራና ከቀኝ ልጃቸውን ይዘው ከሱፐርማርኬት ሲወጡ አየኋቸውና የመጀመሪያ ፍቅር ጠባሳ ነው  ልተውህ ልርሳህ ብትይው አይረሳም  ልብሽ ላይ ተጣብቆ ይቀራል ያለኝንና  ለሶስት አመታት ከልቤ ያደረኩትን ፍልሚያ ከእውነት መሆኑን  አስታውሼ ብቻዬን  ፈገግ አልኩ ።።። ተ ፈ ፀ መ (ኤልዳና በእውነተኛ ታሪክ ላይ የተመሰረተ  ልብ አንጠልጣይ ታሪክ ነው። አንዳንዴ ትክክለኛ ህይወታችን የአማረኛ ፊልም ይመስል ሁሌም የተዋበ መጨረሻ የለውም አንዳንዴ ከህይወትጋ እንድንታገል  ሚያስገዱድን ብዙ ሁኔታዎች አሉ ። ከአቅም በላይ ማፍቀር ብቻውን አብሮ ለመኖር በቂ አይደለም ) አብራችሁን ስለነበራች ከልብ እናመሰግናለን በቀጣይ በሌላ ቆንጆ ታሪክ እስከምንገናኝ መልካም ጊዜ❤️ አንብበው ሲጨርሱ Like ማድረግ አይርሱ። https://t.me/Melkam_liboch1
3 287
10
አቀዋለሁ ግን የመጨረሻ አንድ ውሳኔ ማስተላለፍ ስላለብኝ ነው እዚህ አንቺና ዴቭን የጠራኋችሁ አለኝ። በቃ ነፍሴ ባፌ ልትወጣ ደረሰች አባቴ የእስከዛሬው ጥፋቱ አልበቃ ብሎ ጭራሽ ነፍሰ ገዳይ ሆነ የምሰማው የማየው ግራ ገባኝ አባቴ ከዛ በላይ ማውራት ስላልቻለ የዴቭ አባት ቀበል አረገና በቃ አሁን የሚሰጥሽ ወረቀት ላይ ፈርሙ አንቺና ዴቭ ከዛሬ ጀምሮ ባልና ሚስት ትሆናላችሁ አባትሽ ያለውን ነገር በሙሉ በዴቭ ስም አድርጎታል አንቺ እሱን ስታገቢው በሙሉ የጋራ ይሆናል ማለት ነው አለኝ። እኔ በፎፁም አልፈርምም አልኩኝ። አባቴ በጥፊ ሞቅ አደረገኝና ፈጠን ብለሽ ፈርሚ አሁኑኑ ያዘዝኩሽን አድርጊ ገና እድሜ ልኬን ልበሰብስ እንደሆነ እየነገርኩሽ ማን ስለሆንሽ ነው ማትፈርምው አንቺስ ተይው እናትሽና እህትሽ አያሳዝኑሽም እኔ አምስት ሳንቲም ሳላስቀር በሱ ስም አድርጌዋለሁ ምትታዘዙት ላይ በሙሉ ፈርሙ ከዛ እኔ እጄን አሰጣለሁ አለኝ። እጄ እየተንቀጠቀጠ የሰጡኝ ወረቀት ላይ እንዳለ ፈረምኩኝ አባቴ በእንባ ታጅቦ ከተሰናበተኝ ቡሀላ ወደ ውጭ ወጣና ተከትሎኝ ለመጣው ፖሊስ እጁን ሊሰጥ ሲል ሲቭል ፖሊሶች ባንዴ ፍስስ አሉ። አባቴም በፍርድ ቤት የሁለት ሰው ህይወት በማጥፋት ወንጀል የእድሜ ልክ እስራት ተፈረደበት። እኔና ዴቭም ባልና ሚስት ሆንን በተቻለኝ መጠን ሀላፊነትን ለመውሰድና ለማስተዳደር እንድችል እያንዳንዷን ነገር ያለማምደኝ ጀመር ከየተወለድኩበትንና ያደኩበትን ቤት ለእናቴ በስሟ አዞርንላት። ለታናሽ እህቴም መደበቅ ስለማንችል የእናቷን መሞት አረዳናት እናቴ ከጎኗ ሆና ከእናትም በላይ ተንከባከበቻት። እዩ ለመመረቅ ሶስት ወር ሲቀረው ከመሬት ተነስቶ አኮረፈኝ በቃ ዘጋኝ በምንም አይነት ስልክ ደውዬ ላገኘው አልቻልኩም ቢቸግረኝ እናቱገ ሄጄ የሆነውን ነገር እንድትጠይቅልኝ ለመንኳት በሷ ስልክ ደውለን አነሳውና የኔን ድምፅ ሲሰማ ይዘጋዋል ። እኔ ግን ተስፋ ሳልቆርጥ የምርቃቱን ድግስ ከእናቱ እኩል ደገስኩለት እዛው እያደርኩ እየዋልኩ ስራውን ሰራራን ምርቃቱ ቀን ደረሰ እናቱና ዴቭ ወደግንደር ሄደው  ስለነበር እኔ የቤቱን ነገር ጨራርሼ ጠበኳቸው እሱ ግን ምንም ሳያፍር ቤት ሲመጣ ቃልን እጇን ይዟት ገባ ምን እየተካሄደ እንዳለ እንዳለ ግራ ገባኝ እኔ እየሮጥኩ ወደ ጓዳ ገባሁና ለዴቭ ምን እየተፈጠረ እንዳለ ጠየኩት እሱ ዝም አለኝ ። ከሰው መሀል አንዴ ላውራህ ብዬ እጁን ይዥ ወሰድኪትና እዩ ምን እየተካሄደ ነው ጤነኛ አደለህም እንዴ ቃል እዚህ ምን ትሰራለች አልኩት አታሰቢ ቤተሰቦቿም እየመጡ ነው ብሎ ገፍትሮኝ ወጣ ምርቃቱ ተካሄደ ከምሳ ፕሮግራር ቡሀላ እዩ ቆም አለና ሁላችሁንም  አመሰግናለሁ ዛሬ እንግዲ ለምወዳት ልጅ ቀለበት ማሰር እፈልጋለሁ ቃል ነይ ወደመድረክ ብሎ እጁን ዘረጋላት ቀለበቱን አደረገላትና ብድግ ብሎ እንግዲህ በቅርቡም የልጅ አባት ልታደርገኝ ነው ይሄንን ክብር ስለሰጠሽኝ አመሰግንሻለሁ ብሎ ንግግር አደረገ  እናቱን አመስግኖ ንግግሩን ቋጨው ....... ክፍል ሰላሳ አራት #የመጨረሻው ክፍል ከ 200 like👍 በኋላ ይቀጥላል...  ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ # Like👍 #Share #Add ማድረግ አይርሱ።       ‌‌‌‌‌‌‌      ይ 🀄️ላ🀄️ሉን https://t.me/Melkam_liboch1
3 056
11
💖 ኤልዳና💞   ‍ ​ 💝ልብ አንጠልጣይ የ ፍቅር ታሪክ በመልካም ልቦች የ ቴሌግራም ቻናል ተዘጋጅቶ የቀረበ💝           ክፍል 3⃣3⃣ አባቴ እናቴን ሳይፈታት እኔም እህት እያለችኝ አንድ ቀን እንኳን ሳላያት እዩም የግቢ ትምህርቱን ለማጠናቀቅ 6 ወር እኔም እንደዛው ወራቶች ቀርተውት ዴቭም ካወኩት ቀን አንስቶ አንድ ቀን ፀባዩ ሳይቀየር እናቴም ውስጧ ያለው ንዴት እየበዛ ሲሄድ በግልፅ ፊቷ ላይ መታየት ጀምሮ የእዩም እናት ገበያዋን አጧጡፋ ሱቋን አስፋፍታ ለልጇ ምርቃት ድግሷን እንዴት በሰፊው እንደምትደግስ ከምርቃቱ ቡሀላ ስለሰርጋችን ብቻ እንድናስብ  እየተመካከርን ጊዜያቶች ተቆጠሩ። ሰኞ ክላስ ስላልነበረኝ ቤት ተኝቼ ከእዩጋ በvedio call እያወራን ፂም ማውጣት መጀመሩን አስመልክቶ ሙድ እየያዝኩበት ጠዋት የበላው ምግብ እንዳልተስማማው እየነገረኝ ድንገት ቃል መጣችና vedio ውስጥ ገባች ከጎኑ ቁጭ ስትል የሆነ ሴጣን ካጠገቡ የተቀመጠ ያህል ጋደም ካልኩበት ብድግ አልኩና በቃ ቻው ጊዜያችሁን አልሻም አልኩት እዩ እየተበሳጨ ያምሻል እንዴ ኤልዱ ቃልኮ ስለኔና ስላንቺ አውቃለች እንደውም ማታ ስላንቺ አንስተን ምን ያህል እንደማፈቅርሽ እየነገርኳት ነበር እንደውም የምርቃቴ ቀን ፕሮሚስ ላስርልሽ እንዳሰብኩ ስነግራት በምን መልኩ እንደምናደርገው እያወራን ነበር አንቺ ግን ለሰርፕራይዝ እንኳን አትሆኚም ይኸው አስለፈለፍሽኝ አለኝ። ባንዴ ፊቴ ሁላ በራ አፌን አፍኜ እየሳኩ እሺ በቃ አልሰማሁም አሉ እኔ ስለቀለበት ምንም ማቀው ነገር የለም እሺ በቃ የዛን ቀን እንደማያቅ ሰው እደነግጣለሁ አልኩት እሱ ግን ንዴቱ ስላልበረደለት ኤልዱ ግን ይሄን ቅናትሽን አቁሚ ቅናት ቤት ያፈርሳል ትለኝ ነበር እናቴ ነግሬሻለሁ ብሎ አስጠነቀቀኝና ወሬያችንን አፈቅርሻለሁ አፈቅርሀለሁ ተባባልን ተቋጨ እንዴት ደስ ብሎኝ እንደነበር ፈጣሪ ያውቃል ቀለበቱን ያደረገልኝ ያህል እጄን እያየሁ ፍንድቅድቅ አልኩና ለእናቴ ሄጄ ነገርኳት ያድርግልሽ ልጄ ይገባሻል አለችኝ ደስ እያላት። በነጋታው ዴቭ መጣና ክላስ አደረሰኝ ስወጣ እንድደውልለት ነግሮኝ ተመልሶ ሄደ ። እኔም ስጨርስ ደወልኩለትና እስኪመጣ ካፌ ቁጭ አልኩኝ አንድ የክላሴ ልጅ መጥቶ ካጠገቤ ቁጭ አለ እኔም ሰላምታ አቀረብኩለትና ዝም ብዬ ተቀመጥኩ እየተቅለሰለሰ የሆነ ነገር ላወራሽ ነበር ማለቴ እእእ በቃ ድምፁ ሁላ ተቆራረጠ እኔ ምን ሊያወራኝ ነው ብዬ እያሰብኩ ችግር የለም ሳትፈራ አውራኝ ምን ሆነህ ነው አልኩት። ያው ብዙ ጊዜ ልነግርሽ ብዬ እየፈራሁ ነው ዛሬ ግን ጓደኞቼ አስገድደውኝ ነው ማለት እኔ ካየሁሽ ቀን ጀምሮ አፍቅሬሻለሁ አብረን ብንሆን ደስ ይለኛል አለ። ለምን እንደሆነ አላቅም ሳቄ መጣ እሱ ፊት ላለመዋረደና ላለመሸማቀቅ አስቤ ዋጥ አደረኩትና እኔ ከሀይስኩል ጀምሮ የምወደው ፍቅረኛ አለኝ አሁን ስመረቅ ቀለበት ላስር ነው ይቅርታ እሺ ብዬ ተነስቼ ወጣሁ ደግነቱ ዴቭም ደርሶ ስለነበር ብዙ አልቆምኩም መኪና ውስጥ ከገባሁ ቡሀላ ግን ሳቄን ለቀቀኩት ልጁ ያለኝን ከነ አባባሉ እያስመሰልኩ ነገርኩትና ከዴቭጋ እየተሳሳቅን ቤት ደረስን ። ሌላ ጊዜ ከውጭ ሚመለሰው ዴቭ ተከትሎኝ ቤት ድረስ ገባና ቁጭ አለ እናቴን ልጥራት ቆይ ብዬ ወደክፍሏ ወጣሁ ከሆነች ልጅጋ ተቃቅፋ ተኝታለች እንዴ እማ ማናት ያቀፍሻት ልጅ ካፌ ሳልጨርሰው ዝም እንድል በእጇ ምልክት ሰጠችኝና ቀስ ብላ ተነስታ መጥታ ወደታች ወረድን ምንድነው እማ ማናት አልኳት ቡሀላ ነግርሻለሁ አባትሽ ደውሎልሽ ነበር እንዴ አለችኝ አረ አልደወለልኝም ምነው እማ አልኳት ዴቭ ላንተስ ደውሎልህ ነበር ? አዎ ቅድም ደውሎ ቤት እስክመጣ ጠብቀኝ እንዳትሄድ ብሎኝ ነበር ምነው ችግር አለ እንዴ አላት። አላቅም ግን የሆነ ሰላም ያልሆነ ነገር አለ አለችና እናቴ ቁጭ አለች። እኔ ስለልጅቷ ማንነት አስሬ ስጠይቃት ኤልዱ ደሞ ድርቅ ካልሽ መመለሻ የለሽም እህትሽ ናት አለችኝ ።ማለት ?? በቃ እህትሽ ናት ኤልዱ አንቺም አታስጨንቂኝ ልቤ ባፌ ልትወጣ ነው አለችና ተመልሳ ወደክፍሏ ወጣች እኔ ምን ልትሰራ መጣች ብዬ ድርቅ ብዬ ቀረሁ። ለምን እንደሆነ ባላውቅም ተናደድኩባት ልክ አባቴን የቀማች ያህል ብቻ ምን ልትሰራ እሷ እዚህ መጣች ግራ ገባኝ። ነገሮች ልክ አደሉም ምንድነው የተፈጠረው አባትሽ በፅሁፍ መልእክት እየላከልኝ ነው አለኝ ዴቭ ። እኔ ምን አቃለሁ አብሬህ አልነበርኩ እንዴ አልኩት እንዲሁ እንደተጨነቅንና ውዝግብ እንዳልን ከምሽቱ ሁለት ሰአት ሆነ እስከዛ ሰአት ድረስ እናቴ ከክፍሏ አልወጣችም። ማታ ሁለት ሰአት ላይ በራችን በጣም በሀይል ተደበደበ እኔ በድንጋጤ ዴቭን ጥብቅ አድርጌ ያዝኩት እናቴ በምን ቅፅበት ከላይ እንደመጣች ሳላውቅ መጣችና ኤልዳና አፍጥኝው አፍጥኝው እላይ ውጭና እህትሽጋ ሁኚ አለችኝ ወደላይ ወጥቼ ሚሆነውን መከታተል ጀመርኩ እህቴ ስሟ ሜሎና ነው ሳያት ትራስ እቅፍ አድርጋ ቁጭ በላ እያየችኝ ነው በጣም ቆንጆ ናት አይኗ ቡኒ ነው ሳያት አሳሳችኝ ላቅፋት ፈልጌ ቀድንጋጤ ውስጥ ስለነበርኩ ማቀፍ አልቻልኩም ወዲያው ፖሊሶች ያለንበትን ክፍል ከፍተው ገቡና እያንዳንዱን ነገር መፈተሽ ጀመሩ ። እናቴ ሁለታችንንም አቅፋን አይዟችሁ ተረጋጉ እሺ ብላ አይናችንን ጨፈነችን ቤቱ ትርምስሥምሱ ወጣ ምን እየፈለጉ እንደሆነ ማናችንም አልገባንም ነበር። ቡሀላ ላይ እናቴ ወደታች ወረደችና ተመልሳ መጣች ፊቷ ቅይይር ብሎ ሰውነቷን መቆጣጠር አቅቷት ሳያት ልቤ መምታት ጀመረ ቀስ ብዬ ወደሷ ተጠጋሁና ምን እንደተፈጠረ ጠየኳት በሹክሹክታ አባትሽ ትልቅ ወንጀል ፈፅሟል ልጄ አሁን እህትሽን አጫውቻት ዴቭ አደራ ዛሬ ከኛጋ እደር ከዚህ ክፍል እንዳትወጣ አለችውና ሌሊቱን ሙሉ አንዳችንም እንቅልፍ ሳይወስደን በጭንቀት ተወጥረን ነጋልን ጠዋት ወደውጪ ስመለከት ፖሊሶች በር ላይ ቆመዋል ። ትንሽ ቆይቶ ተነሽ ኤልዳና ለባብሺ እኛ ቤት እንድንሄድ አባትሽ አዞናል አለኘና ተያይዘን ወጣን ፖሊሶቹ ወዴት እነሰደሆነ ጠየቁን ነገርናቸው አንዱ ፖሊስ ከኋላችን በመኪና ይከታተለን ጀመር እኔና ዴቭ እነሱጋ ስንደርስ አባቱ ሳሎን ቁጭ ብሎ አገኘነው ኑ ተከተሉኝ ብሎ ወደላይ ይዞን ወጣ በር ይሁን ግድግዳ አይለይም ግን ሲነካው ግድግዳው እንደበር ተከፍቶ አባቴ ውስጥ ቁጭ ብሎ አገኘሁት ሚስጥራዊ ክፍላቸው መሆኑንም ተረዳሁ። አባቴን እንዳገኘሁት አቀፍኩትና አባ ምንድነው የተፈጠረው ምን ሆነህ ነው እንደዚህ የገረጣኸው አይንህ ምን ሆኖ ነው ያበጠው ምን ወንጀል ነው የሰራኸው ብዬ በጥያቄ አጣደፍኩት። እሱ ነይ ልጄ ተረጋጊና አጠገቤ ቁጭ በይ ብሎ አስቀመጠኝና እየውልሽ እኔ ካሁን ቡሀላ አብሬሽ የለሁም እኔ እንደሞትኩ ቁጠሪው ሀላፊነቱን ባንቺ ላይ ጥያለሁ ከእንግዲህ ልጅነት የለም ህይወትሽ ውስጥ ቆፍጣና ውሳኔ ያላት ጠንካራ ሴት ሁኝልኝ አለኝ የስንብት ንግግር በሚመስል መልኩ እኔ እየተርበተበትኩ አባ ንገረኝ ለምንድነው እንደዚህ ምትለው አልኩት??? ​​ልጄ እኔ ነፍሰ ገዳይ ሆኛለሁ  እህትሽን ከትምህርት ቤት የማመጣት እኔ ነበርኩ አጋጣሚ ሆኖ ትናትና አስተማሪዎች ድንገተኛ ስብሰባ ስለሚያደርጉ ናና ውሰዳት ብለው 6.30 ላይ ደውለውልኝ ወደትምህርት ቤት ሄድኩና ልጄን ይዤ ወደቤት ተመለስኩ ስመለስ ግን እታች ማንም ስላልነበር  ሚስቴን ልጠራት ወደመኝታ ቤቴ ወጣሁ  ከሌላ ወንድጋ እርቃኗን ተቃቅፋ ተኝታ ሳያት ሁለቱንም በሽጉጥ እዛው ደፍቻቸው ልጄን ይዤ ከዛ አካባቢ ጠፋሁና ቤት ይዣት መጣሁ የእናትሽ ግፍ ዋጋዬን ሰጠኝ እኔ ማምለጥ አልችልም
2 037