en
Feedback
🧡❤️መልካም ልቦች💞 ✍️

🧡❤️መልካም ልቦች💞 ✍️

Open in Telegram

🌷 🥀♡♡ ማፍቀር ስትጀምር ከእምነት ጀምር ♡♡🌷 🙏WELLCOM TO 🧡❤️መልካም ልቦች💞 ✍️ ☆በዚህ ቻናል ውስጥ ደስ የሚሉ ☞ የ ፍቅር ቃላቶች፣ ☞ግጥሞች፣ ☞የፍቅር ታሪኮች ያገኛሉ ! t.me/Melkam_liboch1 ● ቻናላችንን SHARE ያድርጉ 🙏

Show more
2 128
Subscribers
-224 hours
-267 days
-3130 days
Attracting Subscribers
September '26
September '26
+4
in 0 channels
August '26
+69
in 0 channels
Get PRO
July '26
+101
in 0 channels
Get PRO
June '26
+78
in 0 channels
Get PRO
May '26
+91
in 0 channels
Get PRO
April '26
+104
in 0 channels
Get PRO
March '26
+160
in 0 channels
Get PRO
February '26
+117
in 0 channels
Get PRO
January '26
+128
in 0 channels
Get PRO
December '25
+175
in 0 channels
Get PRO
November '25
+65
in 0 channels
Get PRO
October '25
+63
in 0 channels
Get PRO
September '25
+120
in 0 channels
Get PRO
August '25
+143
in 0 channels
Get PRO
July '25
+73
in 0 channels
Get PRO
June '25
+59
in 0 channels
Get PRO
May '25
+87
in 0 channels
Get PRO
April '25
+111
in 0 channels
Get PRO
March '25
+168
in 0 channels
Get PRO
February '25
+143
in 0 channels
Get PRO
January '25
+127
in 0 channels
Get PRO
December '24
+121
in 0 channels
Get PRO
November '24
+172
in 0 channels
Get PRO
October '24
+114
in 0 channels
Get PRO
September '24
+138
in 0 channels
Get PRO
August '24
+188
in 0 channels
Get PRO
July '24
+207
in 0 channels
Get PRO
June '24
+52
in 0 channels
Get PRO
May '24
+132
in 0 channels
Get PRO
April '24
+315
in 0 channels
Date
Subscriber Growth
Mentions
Channels
07 September+1
06 September0
05 September0
04 September+2
03 September+1
02 September0
01 September0
Channel Posts
🌙 ጨረቃ ና ናፍቆት ♥️ እቱ የጥንቲቱ😊 የጥርስሽ ንጣቱ የጉንጭሽ ቅላቱ  🥰 ውል ይለኛል ዛሬም የገላሽ ሙቀቱ  የእግሮችሽ ኮሽታ  የፍቅርሽ ሹክሹክታ 😘  ያ የሣቅሽ ዜማ የበዛው ክትክታ  ይሠማኛል ዛሬም ናፍቆት ሲበረታ 😊 እቱ የጥንቲቱ  አንቺም ትዝ ካለሽ ካለብሽ ናፍቆቱ ይህ ነው መዳኒቱ 🤗 ባስለመድኩሽ ሰዓት ባለሽበት ቦታ  ቀና በይ ላንድ አፍታ እኔም ባለሁበት ባስለመድሽኝ ሰዓት ዓይኖቼን አቅንቼ ጨረቃን አይቼ  ልግባ ተፅናንቼ ❤️ አንቺም በዚያች አፍታ  ጨረቃዋን ፈክታ  ካየሻት ተጽናኚ  በይ ቃሌን እመኚ ❤️ ምንም ብንራራቅ ካንድ ሰማይ ሼር ነን 🙏😘 https://t.me/Melkam_liboch1

2
​​... "እኔምኮ አስቤዉ ነበር ሀቢቢ?" አለችዉ። ... "ብቸኝነት እንዳይሰማትና ደስታ እንዳይርቃት ምን እናድርግ የኔ ቆንጆ?" እያለ መፍትሄ ትነገረዉ ዘንድ በአይኖቹም ጭምር ተማጸናት። መኪያ ዝም አለች። ሀምዛም የሚስቱን አይን አይኗን እያየ ዝም ብሎ ከሷ መልስ ይጠባበቅ ጀመር።... በመካከላቸዉ ለተወሰኑ ደቂቃዎች ዝምታ ከሰፈነ በኃላ መኪያ በሷና በሀምዛ አጠገብ የሚያወሩትን ፤ የሚነጋገሩትን የሚሰማቸዉ ሰዉ አለመኖሩን ካረጋገጠች በኃላ ወደ'ሱ ጠጋ አለች። ... "ሀምዚ... ፎዚን ግን ለምን አታገባትም?" ስትለዉ ሀምዛ ጆሮዉን ማመን አቅቶት በመቅጽበት ወደ'ሷ ዘወር ብሎ..."ምንንን?" አላት። ... በዚህ መካከል አንድ የሰፈሩ ሽማግሌ ጮኽ ብለዉ መናገር ጀመሩ። ... ".... ልጆቼ ነገ በአኼራ ሰዉ ከሚወደዉ ሰዉ ጋር ነዉ የሚቀሰቀሰዉ። እናም ፎዚያ ልጄ! ... አላህ እናንተን ለዘላለም ላትለያዩ በጀነት ሊያኖራችሁ ይችላል። ለሱም ቢሆን ዱዓ ብታደርጊለት እንጂ ለቅሶና ሀዘን አይበጀዉም። ..." እያሉ ብዙ ከመከሯቸዉ በኃላ ንግግራቸዉን ጨረሱ የፎዚያ ፍቅርም ልክ እንደ ጧት ጤዛ በጅምር ቀረ ... 💞💞💞 ተፈፀመ💞💞💞 በሌላ ምርጥ ታሪክ እሰከምንገናኝ መልካም ጊዜ❤️ https://t.me/Melkam_liboch1 https://t.me/Melkam_liboch1
895
3
💞"ጤዛዉ ፍቅሬ"💞 💝በመልካም ልቦች የቴሌግራም ቻናል የቀረበ💝 ክፍል አስራ አምስት (15) 💖የመጨረሻዉ ክፍል💖 (ኑዕማን ኢድሪስ) . .... ሆስፒታሉ በትራፊክ ፖሊሶችና ቆመዉ ክስተቱን በሚመለከቱ ሰዎች ተሞልቷል። ሁሉም ጭንቅላታቸዉን በሁለት እጃቸዉ ይዘዉ የተጎጂዉን መትረፉን ይሁን መሞቱን በጉጉት ይጠባበቃሉ። ... ከሰዎቹ መካከል ግን የፎዚያ የተለየ ነበር። ከዚያ ሁሉ ሰዎች ጉልበቷ ሀይሎ የድገተኛ ክፍሉን በር ገንጥላ ለመግባት ትታገላለች። እሷን ለመያዝና ለማረጋጋት የተወሰኑ ሰዎች እየታገሏት ነዉ። ከነዚያ ሰዎች መካከል ግን መኪያ የለችም። ለባሏ ጓደኛዉ ምን እንደሆነ ለመንገር ሀምዛ ወደተኛበት ጠባቧ ክፍል ሩጫ በቀረዉ ሶምሶማ ደረጃዉን ሽቅብ እየወጣች ነዉ። ባሏ ያለበት ክፍል ገብታ ጉዱን ልታረዳዉ ተቻኩላለች። ስትሮጥ እንኳ ምንም አልደከማትም። ክፍሏ ጋር እንደደረሰች የበሩን እጀታ ይዛ በሀይል ከፈተችዉ። ትንሽ እንቅልፍ ቢጤ ሸለብ አድርጎት በሰሰመን ዉስጥ የነበረዉ ሀምዛ የበሩን በሀይል አከፋፈት ሰምቶ ተዘግተዉ የነበሩ አይኖቹን ወደ በሩ በለጠጣቸዉ ። በሩን በሃይል ገፍታ ፤ ከፍታ የገባችዉ መኪያ ነበረች። ነገር ግን ስትለየዉ በሰላም የወጣችዉ መኪያ ሳትሆን ሁሉ ነገሯ ተቀያይሮ ፤ ድንጋጤና ፍራሃት ግንባሯ ላይ ሸንተር ሰርተዋል። ልቧ በአፏ ልትቀጣ ደርሳ ድዉ ድዉ ትላለች። በአይኗቿ እንባ እያዘነበች ነበር። .. " እህ እህ..." እያለች ልትናገር የፈለገችዉን ትንፍሿ ይዉጥባታል። ሀምዛ ጋደም ካለበት አልጋ ከወገቡ ቀና አለና ተቀምጦ... "መኪ ምን ሆነሽ ነዉ?" ብሎ የድንጋጤዉን ጮኸ። መኪያ እየተከታተለ የሚወጣዉን ትንፋሿን ገታ አድርጋ... "ሀቢብ ... ሀቢብ..." ስትለዉ የሀምዛ ፊት ባንዴ ተቀያየረ ፊቱን ቅጭም አድርጎ ..." ሀቢብ ምን ሆነ?" አላት። .... "የመኪና አደጋ ደርሶበት ... እዚህ" እያለች ጣቷን ወደኃላዋ እንደመቀሰር ስታደርግ ሀምዛ ከተኛበት አልጋ ላይ ምንጥቅ ብሎ ተነሳ። መኪያ ባለችበት እንደቆመች ክፍሉን ለቆ ወደ ድንገተኛ ክፍል በቸርኬዉ ተፈተለከ። መኪያም የባሏን በእግሩ መራመድ ሳታስተዉል ከኃላዉ ተከታትላዉ ሀቢብ ወደተኛበት ድንገተኛ ክፍል ተሯሯጡ። የሆስፒታሉን ደረጃ ተንደርድረዉ ወረዱት ከማለት ይልቅ ዘለዉ ባ'ንዴ ከሰዎቹ አጠገብ ደረሱ ማለት ይቀላል። ሀምዛ የእግሩን መጎዳት ረስቶት በሩጫ ከድንገተኛ ክፍል ሲደርስ የተሰበሰቡት ሰዎች የጸጥታ አዋጅ የታወጀ ይመስል ጸጥ ብለዋል። ከሰዎቹ መካከል ግን በሴቶች ተከባ ማልቀስ የምትችልበት ሀይል አጥታ አይኗ እንደፈጠጠ በደረቁ የምትንሰቀሰቅ ፤ ከናፍሮቿ ዉሃ ካገኙ ሳምንታት ያስቆጠሩ ይመስል ዝናብ ጥሎበት እንደደረቀ ዋልካ መሬን የተሰነጣጠቀባት ሴት ተመለከተ - ፎዚያ ነበረች። ... ሀምዛ ሰዉነቱን በሞላ ከዚህ በፊት ተሰምቶት የማያዉቅ የሀዘን ስሜት መላ አካላቱን ሲያዳርሰዉ ተሰማዉ። ፎዚን በተቀመጠችበት አለፍ አለና ወደ ድንገተኛ ክፍሉ ተጠግቶ በመስተዋት የተገጠመዉን በር ወደ ዉስጥ ያሳየዉ ዘንድ አይኖቹን ቀረብ አድርጎ ሲመለከት በነጭ ጨርቅ መላ አካላቱ የተሸፈነ አስክሬን ተመለከተ። - ሀቢብ ስለመሆኑ አልተጠራጠረም። ምንም እንኳ ሁሉም አካሉ የተሸፈነ ቢሆንም ቁመቱ ሀቢብ መሆኑን ይናገራል። "ሞቷል?" ሲል ከአንደበቱ ቃል አወጣ። አጠገቡ ቆሞ የነበረ አንድ ሰዉ እሱን የጠየቀዉ መስሎት "አዎ ሞቷል" ብሎ መለሰለት። ሰማይ ፤ ምድሩ የተቀላቀሉበት መሰለዉ። አይኑ ፍጥጥ ፤ ደሙ ቀጥ አለበት። የስንት ጊዜ ጓደኛዉ ፤ ክፉ ደጉን አብረዉ ያሳለፉ ፤ ደስታንና ሀዘንን በጋራ አብረዉ የወጡት ፤ እንደ'ራሱ የሚወደዉ ጓደኛዉ እሱን ለመጠየቅ ወደ ሆስፒታል  ሲመጣ መንገድ ላይ ቀረ። ላይመለስ ምድርን ተሰናበተ። . .... ፎዚያ ትእግስት አሳጥቷታል። የህይወት አጋሯ ፤ ከራሷ አስበልጣ የምትወደዉ ሀቢብ ሞቷል። ሳትወድ በግዷ አምና ተቀብላለች። ከዚህ በኃላ ሀቢብን በድጋሜ አታገኘዉም። ፍቅሯ እንደ ጧት ጤዛ ሆኖ ቀረ። ያ እንክብካቤና ደስታ በጅምር ቀረ። ዉስጧ ተብሰከሰከ ፤ ያ የዉበት ጸዳል የሆነዉ ፊቷ ሀዘን የሚባል መጥሮ ነገር ፤ ሞት የሚባል የማይለመድ ክስተት ጥላዉን አጥልተዉበት ከጥቀርሻም በላይ ጠቆረ። እንደ ማለዳ ወፍ ዜማዎች የሚያምረዉ ድምጿ ተኩረፈረፈ ፤ ልሳኗ ተዘጋ። ሀቢብን በስስት የምታይበት አይኖቿ .. በርበሬ የተቦካበት ሙሃቻ ይመስል ቀይ ሆነ። ... ... በዚህ ምድር እጅግ ከባዱ ነገር የሚወዱትን ሰዉ መለየት ነዉ። ፎዚያ ግን ያን ሁሉ የችግር ወቅት ከሀቢብ ላለመለየት ታግሳና ችላ ኖራ ነበር። የሰቆቃዉ ህይወት አልፎ የደስታዉ ዘመን ሲመጣ ደስታዋን የሚያጠፋ ፤ ፍቅሯን የሚያከስም ነገር ተፈጠረ።... ሀቢብ ሞተ!!! . . . ... የሀቢብ የቀብር ስነ ስርአት ከተፈጸመ ዛሬ ሦስተኛ ቀኑን አስቆጠረ። ፎዚያ ሊያስተዛዝኗት በሚመጡ ሰዎች ተከባለች። ሁሉም 'አብሽሪ' ይሏታል። ሞት በሁሉም ሰዉ ላይ ያለ ነዉ። እኛም ተራችንን ጠባቂዎች እንጂ ይህችን ምድር ለዝንታለም አንኖርባትም። አድርን የማንዉልባት ፤ ዉለን የማናድርበት ጠፊ አለም ናት!። እያሉ ይመክሯታል። እሷ እንደሆነ ሀቢብን ብቻ ሳይሆን ፍቅሯንም ከባሏ ጋር አብራ ቀብረዋለች። አንድ ቀን በትክክል ያጣጣመችዉን ፍቅር በድጋሜ ሳታገኘዉ መንገድ ላይ ቀርቶባል። የሚደፈያስተዛዝኗት ሰዎች ያወራሉ እንጂ እሷ ሀሳቧ ሁሉ ከሟች ባሏ ጋር ነዉ። . . ... ሀምዛና መኪያ ከአንድ ጥግ ተቀምጠዉ ፎዚያን አሻግረዉ ይመለከቷታል። ዉበቷ ሀያ አራት በሙሉ እንደ ጨረቃ ሲያበራ የነበረችዉ ፎዚ ሳትሆን ሀዘን እንዳይሆኑ አድርጓታል። ሀምዛ ወደ ፎዚያ ተጠግቶ ሊያስተዛዝናት ፤ ሊያጽናናት ድፍረቱን አጣ። እሷ ዘንድ ሂዶ ስለ ሀቢብ አንስቶ 'አብሽሪ' ቢላት ሁለታቸዉም አይኖቻቸዉ በእንባ እንደሚሞሉና ትዕግስት እንደሚያጡ ዉስጡ ነግሮታል። በተቀመጠበት ሆኖ አሻግሮ እያያት ስለ'ሷ የወደፊት ህይወት 'ብቸኝነትና ሀዘን' እንደሚበረታባት ሲያስብ እንዴት አድርጎ ሊረዳት እንደሚችል ማስተንተን ጀመረ። ... የሱ ህይወት አያስጨንቀዉም። ምክንያቱም ቤቱ በደስታና በፍቅር የተሞላ ነዉ። እግሩም ቢሆን ደህና ነዉ። ለተወሰነ ጊዜ ክራንች ተጠቅሞ ይበልጥ ደህና ሲሆን የእስከዛሬዉን ሙሉዉን ሀምዛ እንደሚሆን ተነግሮታል ~ አልሐምዱሊላህ!!። አሁን የሚያስጨንቀዉ ጉዳይ የፎዚያ ነዉ። ስለሷ ያስባል... ያስባል.... 'ብቸኝነቷን እንዴት እንደሚያስወግድላት ፤ ከዚህ በኃላ እንዴት ደስተኛ እንደምትሆን እያሰላሰለ በሃሳብ ነጉዷል።... ጭል.....ጥ ብሏል።.....። በዚህ መሃል መኪያ ዘወር ብላ ስታየዉ ትካዜ ዉስጥ እንደሆነ አስተዋለች። ... "ሀምዚ .. ሀምዚ የነሰ..." ብላ ጠራችዉ። ... "ወይዬ መኪዬ.." ሲል መለሰላት። ... "ምን እያሰብክ ነዉ?" ብላ ከአይኖቹ ስለምን እንደሚያስብ ታዉቅ ይመስል ትክ ብላ አየችዉ። ... "መኪዬ የፎዚ የወደፊት ሁኔታ ግን አላሰሳሰበሽም?" ብሎ መልሶ እሷኑ ጠየቃት። መኪያም ስለፎዚያ ሁኔታ እያሰበች ነበር። ነገር ግን መፍትሄ ሳታገኝ ቀርታ ዝምታን መርጣ ነበር።
786
4
​​​💞ጤዛዉ ፍቅሬ 💞 💝በመልካም ልቦች የቴሌግራም ቻናል የቀረበ💝 🌹🌹ክፍል አስራ አራት🌹🌹 ✍✍(ኑዕማን ኢድሪስ)✍✍ ... ከቤት እንደወጣ ከኃላዉ ከተል አለችና "ሀቢቢ..." አለችዉ። ጅምር ፍቅሯን አቋርጦባት ከቤት ሲወጣ አላስቻላትም። ግድ ስለሆነ እንጂ ከመንገዱ ብታስቀረዉ ደስ ባላት ነበር። እርምጃዉን ገታ አድረጎ ወደ ኃላ ዘወር አለና .."ወይዬ ፎዚቲ ..." አላት። ... "ልብሴን ልቀያይርና አብረን እንሂድ" አለችዉ አብራዉ ሂዳ አብራዉ መመለስ አሰኛት። ድጋሜ የማታገኘዉ ፤ እንደወጣ የሚቀር ይመስል ሆዷ ባ ባ። ፍርሃት ፍርሃት አላት። በቆመበት ፈግጎ .. "ፎዚዬ አንቺ ልብስ እስከምትቀይሪኮ እዚሁ ይመሻል። እኔ ቶሎ ደርሼ ብመለስ አይሻልም?" አላት። ... "አልቆይምኮ ሀቢቢ .. ቶሎ ቀያይሬ ልምጣ" አለችዉ እንደ መሽኮርመም እያደረጋት። ... "እረሳሸዉዴ ሁቢ? ... (እንደ መሳቅ እያደረገዉ) ... አንቺኮ ልብስ ለመቀየር ገና ሸዋር ቤት መግባት አለብሽ። ከዚያ ደግሞ ያ የፈረደበት መስታወት ፊት መገተር አለብሽ ሃሃ..." ... "ሂድ አንተ ደግሞ .." እያለች ወደ'ሱ ቀረብ አለችና ..."አደራ ሀቢቢ ራስህን ጠብቅ" አለችዉ። ... "አታስቢ የኔ ቆንጆ" ... "በመንገድህ ላይ አደራ.. የዛሬ ሾፌሮች እንደሆኑ መንጃ ፍቃዳቸዉ ካርቶን ቀደዉ የሚያድሏቸዉ ይመስል አብዛኞቹ ህጋዊ አይደሉም።..." እያለች አደጋ እንዳይገጥመዉ በመፍራት ብዙ አስጠነቀቀችዉ። እሱም ፈገግታዉ ከፊቱ ሳይለየዉ የምትነገረዉን ሁሉ በጽሞና ሰማት። ... "እወድሃለሁ የኔ ዉብ..." ብላ በቆመበት ሂዳ ጥምጥም ብላ አቀፈችዉ። እንደወጣ ይቀራል ተብላ የተነገራት ፤ ፍቅርሽ በጅምሩ ይቀራል ተብላ ሹክ የተባለች ይመስል ዉስጧን ባር ባር አላት። ሀቢብም ያቀፈችዉን ሚስቱን እሱም አቀፋት። የሷ አስተቃቀፍ ግን ይለያል!። ... "በቃ ወደ ቤት ግቢ ፎዚዬ እኔም ቶሎ ልሂድ" አላት። ሀቢብ .. በድኑ እሷ ዘንድ ይቁም እንጂ አሁን ሀሳቡ ሁሉ ሀምዛ ላይ ሆኗል። ቆየሁበት እያለ መጨነቅ ይዟል። ከእቅፉ ዉስጥ ሲያወጣት እሷ ግን የጠመጠመችበትን እጇን አላላቀቀችም። 'ይሄን ያክል ፍቅር ርቧት ነበር ማለት ነዉ' ሲል አሰበ። ፍቅር ከምንም ነገር በላይ ይርባል። ከጥም በላይም በጣም ይጠማል። ገንዘብ ያላቸዉ ሰዎች ሁሉ በገንዘባቸዉ የማያገኙት ነገር ቢኖር እዉነተኛ ደስታንና ፍጹምነት የተሞላበት ፍቅርን ነዉ። ፍቅር ከጤናም በላይ ዉድ የሆነ ነገር ነዉ። ምክንያቱም በህይወት ያለ ሰዉ ሁሉ ማፍቀር አይችልም። ምናልባት ሊያፈቅር ቢችል እንኳ አንዳንድ ሰዎች መጥፎነትን ያፈቅራሉ ፤ ጥላቻን ይቀባሉ ፤ ክፉነትን ይመርጣሉ። ነገር ግን በተቃራኒዉ ማፍቀር የሚችሉ ነገሮች ሁሉ ህይወት አላቸዉ። በህይወት መኖርን ትርጉም የሚሰጠዉ ነገር ንጹህ ፍቅር ሲታከልበት ፤ ደስታ ሲጨመርበት ነዉ። ፎዚያ የእስከዛሬ ትርጉም የሌለዉ ህይወቷን ፤ ያለፈዉ ከደስታ የራቀዉ ኑሯዋን ዛሬ በፍቅር ስለተዋበላት ያን የፍቅር ንጉስ መቀናጆዋን በቀላሉ ልትለቀዉ አልቻለችም። በሽንጡ በኩል ሰድዳ ጥምጥም ያደረገችበትን እጇን ቀስ ብሎ አላቀቃቸዉ። ..."ፎዚዬ ቶሎ እመለሳለሁ። ከዚያ ስትመኚዉን የነበረዉን ሁሉ እያደረግን ጣፋጭ የፍቅር ጊዜን እናሳልፋለን - እሺ!" አላት። እንደሚያባብሉት ህጻን ልጅ እሺታዋን በአንገቷና በይኗ ገለፀችለት። የግራ ጉንጯን ሳም አድርጎ ሲሄድበት ወደነበረበት አቅጣጫ ዙሮ መንገዱን ጀመረ። ፎዚያም ጀርባዉን ሰጥቷት የሚሄደዉን ባሏን ከአይኗ እስከሚጠፋ ድረስ በስስት እየተመለከተችዉ ሸኘችዉ። . . .... "መኪዬ.." አላት አይኖቹን በመስኩቱ ወዲያ ማዶ የሚታየዉን ግትር ህንጻ እየተመለከተ። 'ወይ' አለችዉ በተቻኮለ አይነት። .... "መኪዬ አሁን ሀቢብ ሲመጣ ተቻኩለሽ ዶክተሩ ምን እንዳለኝ እንዳትነግሪዉ - እሺ" ብሎ በተኛበት ቦታ እንዳለ አንገቱን መለስ አድርጎ ወደ'ሷ ተመለከተ። መኪያም እንደዚህ ያለበትን ምክንያት ለማወቅ ያክል ..."ለምን ሀምዚ?" ብላ በተቀመጠችበት ቦታ እንደመደላደል እያለች ጠየቀችዉ። ... "ሀቢብ እንዲደነግጥ አልፈልግም። እኔዉ ቀስ ብዬ አረጋግቼ እነግረዋለሁ!" ሲላት የባሏን ትዕዛዝ ጥሳ የማታዉቀዉ መኪያ 'እሺ አልነግረዉም' ብላ ሀሳቡን በይሁንታ ተቀበለች። . . ... ሀቢብ ስለማን እንደሚያስብ ግራ ገብቶታል። አንዴ ስለ ቤቱ ፤ ቀጠል አድርጎም ሰሞኑን ስላቋረጠዉ ስራና ስለ አመለ ቢሱ የቅርብ አለቃዉ ፤ በመሃል ደግሞ ስንቅር የሚልበት .. ሆስፒታል ዉስጥ ክፉኛ እግሩን ተጎድቶ ስለተኛዉ ጓደኛዉ - ሀምዛ ... በሀሳብ ዉጥር ብሏል። ሁሉም 'እሱን ተወዉ' 'እሱን ተወዉና ስለ'ኔ እሰብ እያሉ የሚከፋፈሉት ፤ የሚቦጫጨቁት መሰለዉ። እግሮቹን እሱ ሳይሆን የሚያዛቸዉ ሀሳብ ከኃላዉ ሆኖ እንደ ጋሪ የሚገፋዉ እስኪመስለዉ ድረስ ራሱን አያዉቅም። . . ... ፎዚያ ባሏን በአይኗ ከሸኘች በኃላ ወደ ቤቱ ገባች። ሀቢብ ከቤት ከወጣ ጀምሮ ሀሳብ አይሉት ሰበብ የጭንቀት ናዳ አእምሮዋ ላይ ሰፈረባት። የትጥበት ግዴታዋን ለመወጣት ወደ ሸዋር ቤት ከገባች በኃላ ዉሃዉን በሃይል ከፍታ መታጠብ ጀመረች። ... ከፀጉሯ ኩልል ብሎ የሚወርደዉ ዉሃ በግንባሯ ላይ ተንከባሎ ቅንድቧን አልፎ አይኗ ዉስጥ ሊገባ ሲል አይኖቿን ከደነቻቸዉ - ጨፈነች። በዚህ መካከል ህልም አይሉት ቅዥት በአይነ ህሊናዋ አስደንጋጭ ክስተት ተመለከተች። ከራሷ በላይ የምትወደዉ ባሏ ሀቢብ የእጅ ስልኩን በእጁ ይዞ ስልክ እያነጋገረ አስፖልት በመሻገር ላይ ሳለ የመኪናዉን ፍጥነት መቆጣጠር ያቃተዉ አንድ ሾፌር ሀቢብ በሚሻገርበት መንገድ በፍጥነት መኪናዉን ሲያሽከረክር ተመለከተች። "ሀቢ...ብ" ብላ በቅጽበት የከደነቻቸዉን አይኖቿን ገልጣ በጎኗ በኩል የተንጠለጠለዉን ፎጣ አነሳች። ፎጣዉን በትክክል ሳታሸርጠዉ (ሳታገለድመዉ) ተቻኩላ ከሸዋር ቤት ወጣች።ሰዉነቷ እየተንቀጠቀጠ ነበር። ያየችዉ ክስተት በአይነ ህሊናዋ ሳይሆን በእዉኗ እስኪመስላት ድረስ ያጣፋችዉን ፎጣ በአንድ እጇ ጨምድዳ እንደያዘች ገላዋ ራደ - ተብረከረከች። ስልኳን አነሳችና ወደ ሀቢብ ደወለች። ╔═══❖•💕💕•❖═══╗    ክፍል 15 የመጨረሻው ክፍል ከ250like👍 በኋላ ይቀጥላል ‼️ ╚═══❖•💕💕•❖═══ https://t.me/Melkam_liboch1
1 374
5
​​💞​ጤዛዉ ፍቅሬ"💞 💝በመልካም ልቦች የቴሌግራም ቻናል የቀረበ💝 🌻🌻ክፍል አስራ ሶስት🌻🌻 ✍✍( ሰሊና )✍✍ .... አንድ ሀሳብ በአንድ ግለሰብ ዉስጥ ዉሎ ካደረ ለሰዉዬዉ ጭንቀትን እንጂ ሌላ ምንንም አያተርፍም። ይሄን ደግሞ ሀቢብ በራሱ ላይ ያረጋገጠዉ ነገር ነዉ። ጉድለት አለብሽ ፤ ሙሉ አልነበርሽም 'ለምን' ተብላ የምትጠየቀዉ ፎዚያ ሆና ሳለች ከእሷ በላይ ግን እሱ ተጨንቋል። 'የትኛዉ አጠያየቅ ትክክል ነዉ?' እያለ በማሰብ ላይ ሳለ በሀሳብ መንጎዱን ያስተዋለችዉ ፎዚያ ... ... "ንገረኛ ሀቢቢ ... '' ስትለዉ ደንገጥ አለና ..'እ' አለ። ... "የፈለግከዉን ጠይቀኝ ሁቢ ... ማወቅ ያለብክን ሁሉ ... እነግረሃለሁ። ካንተ ምንም ምደብቀዉ ነገር የለኝም።" አለችዉ። እሱ እንደሆነ አፉን ይዞታል። ቅንነቷና መልካምነቷ አንደበቱን አሳስሮታል። ፍቅር አሰጣጧ ልቡን ምንም ሳያስቀር እንዲሰጣት አስገድዷታል። ምክንያቱም ፎዚያ ሲበዛ ብልህ ናት። ዛሬ ሲቀርባትና ሲወዳት ብቻ ሳይሆን ያኔም በትድራቸዉ ላይ የጨለማን ጽልመት ሲያጠላበት ፤ እንደ አባቱ ገዳይ ሲጠላትና ሲያመናጭቃት በነበረችበት ጊዜ እንኳን እሱን ከማፍቀር አልቦዘነችም ነበር። ሲወጣም ሆነ ሲገባ እንክብካቤ በማብዛት ፤ ያንን ክፉ ፊት ተቋቁማ ፤ በክፉ ንግግሩ ዉስጧ እየደማ በመቻልና በመታገስ ትዳሯን በቋፍም ቢሆን አቆይታለች። በተለይ የአንዱ ቀን ስድቡ ልቧን ላይሽር የሰበረበት እለት የሚረሳ አልነበረም። "ርካሽ" ሲላት ስቅስቅ ብላ ያለቀሰችበት። በዉሃ ታጥቦ እንደተጠመዘዘ ጨርቅ የተንተራሰችዉ ትራስ ልብስ በእንባዋ ሲርስ የነበረችበት። ... አሁን ግን... ያንን ሁሉ ወደ ጎን ትታ ባሏ የሚሰጣትን ፍቅር መኮምኮምና ዉስጡን የሚያስጨንቀዉን ፤ ማወቅ የሚፈልገዉን እዉነቱን ነግራ ቀሪ ህይወቷን በደስታ ማሳለፍ ፤ ትዳሯን ሙሀባ ዉስጥ ነክራ የኑሮን ጥፍጥና ማጣጣም ፣ የዱንያን ፈተና በድል መወጣት - እዉን ልታደርግ የምትፈልግዉ ህልሟ ነዉ። .... "ፎዚዬ ..." አላት በድጋሜ። ስሟን እያቋላመጠ ፤ አስሬ እያቆለጳጰሰ ከመጥራት ዉጭ ደፍሮ የሚጠይቃት ሀሞቱ ፈሰሰበት። .... "ወይዬ ዉዴ... አታስጨንቀኛ! ,, የፈለከዉን ጠይቀኝ እኔ ምንም ቅር አይለኝም።" እያለች እንደ ህጻን ልጅ ታደፋፈረዉ ያዘች። ዉስጡ ታምቆ የቆየዉን የሀሳብ ክምር በሞቃት ትንፋሹ 'ኡፍፍፍ ...' ብሎ ካወጣ በኃላ ... .... "ፎዚዬ መጀመሪያ ያገባሁሽ ሰሞን ላንቺ ያለኝ ፍቅር ወደር የማይገኝለትና በቀላሉ የማይተመን ነበር። እመኒኝ ማሬ...! አሁንም ያ ስሜት ዉስጤ ላይ አለ...." አይን አይኑን እያየች ጆሯዋንም ልቧንም ከፍታ ከማዳመጥ ዉጭ የሚጠይቃትንና ማወቅ ያለበት ነገር ምን እንደሆነ በዉል አላወቀችዉም። ... ንግግሩን ቀጥሏል.... "ሀቢብቲ... በጣም ነዉ የምወድሽ ፤ ከልቤም አፈቅርሻለሁ። ነገር ግን ... አንድ ዉስጤን የሚከነክነኝ ነገር አለ። የማስበዉ ሀሳብ ፤ ስላንቺ የምገምተዉ ... እንደ ሰደድ እሳት ዉስጥ ዉስጤን እየፈጀ ከሚጨርሰኝ አዉጥቼዉ በግልጽ ልጠይቅሽ እፈልጋለሁ።..." ሲናገር እዉነትም የሆነ ዉስጡን የሚረብሸዉ ነገር እንዳለ ያስታዉቅበታል። ለሷ ፍቅር እንዳይሰጣትና እንዲጠላት ያደረገዉ አሁን የሚነግራት ነገር እንደሆነ አላጣችዉም። ይበልጥ ለማወቅ ጓጓች። ዉስጥን በሚያራራ ሁኔታ ድምጿን ቀነስ አድርጋ በለሆሳስ ... "ምንድን ነዉ እሱ የኔ ዉድ? ምንድን ነዉ ዉስጥህን የሚከነክንህ?..." አለችዉ። ... "ፎዚቲ አንቺ ከ'ኔ በብዙ ነገር ትሻያለሽ። በዚህም ላንቺ የነበረኝ ቦታ እጅግ የገነነ ነበር። በመኃል ግን ስሰጥሽ የነበረዉን ፍቅር ትቼ ፤ ሚስቴ በመሆንሽም ሁሉ ስማረር ነበር። ይሄ ሁሉ የሆነዉ ግን ባንድ ምክንያት ነዉ።..." አሁን ላይ ከሀተታዉ ይበልጥ መስማት የፈለገችዉ 'ሊጠላባት የቻለዉን ምክንያት ስለነበር..."እኮ ምንድን ነዉ ምክንያትህ?" ብላ በንግግሩ መሃል ገባች። ከዚህ በኃላ ወሬ መቀየርም አይችልም። ዳር ላይ ስለደረሰ ሊጠይቃት የሚፈልገዉን በግልጽ ሊጠይቃት ወሰነ። እንደምንም ከራሱ ጋር ታገለና "ክብረ..." ብሎ ቃሉን ሳይጨርሰዉ ስልኩ ጠራ ..."ዝ... ዝ... ዝ..." ንግግሩን አቋረጠና የደዋዩን ማንነት ሲያይ በስልኩ ላይ 'Hamza' ብሎ የመዘገበዉ ስልክ ቁጥር የጓደኛዉ ሀምዛ ነበር። ፎዚያ ዉስጧን የቁጣ ክርቢት ንዴቷን ጫረዉ። ቅስሟ የተሰበረ ያክል አንገቷን ወደ ታች ደፋችና በእጇ መዳፍ አገጯን ደገፍ አደረገች። ... "ኦህ ፎዚ... ለነሀምዛ ቆየሁባቸዉ!" ብሎ ሊያነጋግር የሚያስችለዉን ቁልፍ ተጭኖ .."ሄሎ" አለ። ፎዚን በተቀመጠችበት ትቷት ስልኩን እያነጋገረ ቁም ሳጥኑ ወዳለበት ክፍል ገባ። . ... 'ምን ሊጠይቀኝ ነበር?' ብላ ሀቢብ ገና ከቤት ሳይወጣ ጭንቀቷን ጀመረችዉ። 'እስከ'ዛሬ ትዳሬን የበጠበጥኩት እኔዉ 'ራሴ ነኝ ማለት ነዉ?' እያለች ያሳለፋቸዉና የተጓዘችበት ከሰላም የራቀችበትን መንገድ እያስታወሰች ራሷን ትረግም ገባች። 'ቆይ ግን ምክንያቱ ምን ነበር? ክብረ ብሎ የጀመረዉ ምን ሊል ነበር??" 'የምን ክብር ነዉ?' ... በዚህ መሃል ሀቢብ ልብሱን ልብሶ ከዉስጥ ብቅ አለ። ፎዚም ተነሳችና ወደ'ሱ ተጠጋች። ... "ሀቢቢ ..." አለችዉ። አሁን ፈርታለች። ሀቢብ ደግሞ ግማሽ ያክሉን የሀሳብ ቁልል ወደ'ሷ ንዶ ስላጋባባት ትንሽ ረፍት የተሰማዉ ይመስላል። ሀሳቡን ሙሉ ለሙሉ ባይገልጽላትም ስለጀመረዉ ከሀምዛ ዘንድ ሲመለስ መጨረስ እንደሚችልና ተነጋግረዉ ችግራቸዉን እንደሚፈቱት አምኗል። ... "ወይዬ የኔ ቆንጆ ..." ብሎ ፀጉሯን ባንድ እጁ እንደመዳበስ አደረጋት። እሷም የሸሚዙን ኮሌታ እንደማስተካከል እያደረገች አይኖቿን አይኖቹ ላይ አንከባለለቻቸዉ። ╔═══❖•💕💕•❖═══╗ ክፈል14   ከ100like👍 በኋላ ይቀጥላል‼️ ╚═══❖•💕💕•❖═══╝ https://t.me/Melkam_liboch1
1 890
6
https://t.me/Melkam_liboch1
2 016
7
​​💞ጤዛዉ ፍቅሬ"💞 💝በመልካም ልቦች የቴሌግራም ገፅ የቀረበ💝 🍂🍂ክፍል አስራ ሁለት🍂🍂 ✍✍(ኑዕማን ኢድሪስ) ...."ሙሀመድ ነቢና ኡሙሁ አሚና አቡሁ አብደላህ..." የሚለዉ የፎዚያ የስልክ መጥሪያ እስከ ንዝረቱ 'ዝ... ዝ... ዝ...." እያለ የነሀቢብ ፍቅር ማድመቂያ መስሏል። ጆሯቸዉ ከአፍንጫቸዉና ከከናፍሮቻቸዉ መካከል ሾልኮ በሚወጣዉ ሞቃት ትንፍሽ ተደፍኗል። . .... ሀቢብ የፎዚያን ስሜት እየጠበቀ ከጠበቀችዉ በላይ አስደስቷታል። የደስታን ማማ አፈናጧታል። ጋደም ባለበት ፎዚን በቀኝ እጁ ወደ ደረቱ አስጠግቶ አቅፏት በግራ እጁ ያሰረዉን ሰአት ተመለከተ። ከቀኑ 11:25 ይላል። .."ያ አላህ ፎዚዬ ..." አለና ፎዚን ከእቅፉ ዉስጥ አዉጥቶ ተነሳ። እሷም በግንባሯ በኩል ወርዶ የተዘናፈለዉን ጸጉሯን በእጇ ወደ ኃላዋ መለስ እያደረገች ቀስ ብላ ጋደም ካለችበት ሶፋ እየተነሳች.... "ምን ሆንክብኝ ሀቢቢ?" አለችዉ። ..."ሀምዛን እስካሁን ሳልጠይቀዉ!" አላትና እየተቻኮለ ወደ ሸዋር ቤት አመራ። ፎዚያም ሰአቱ ስንት እንደሆነ ለማወቅ ተንተርሳዉ ከነበረችበት ትራስ ስር ስልኳን አዉጥታ ተመለከተች። ስንት ሰአት እንደሆነ ካወቀች በኃላ ቁጥሩን የማታዉቀዉ ስልክ ሰባት ጊዜ ደጋግሞ ተደዉሎባት ነበር። . . . .... "ግን ሀቢብ ምን ሆኖ ነዉ?" ንዴቷን ፊቷ ላይ አንጸባርቃ እየነገረችዉ ነበር። ...."መኪዬ ስለመምጣቱ ሳይሆን ስለደህንነቱ ተጨነቂ ... እሺ!" አላት ሀምዛ። ቀጠል አድርጎም ..."ሀቢብ ደህና ከሆነ ይመጣል። ለጓደኛዬ ዱዓ የማደርግለት በመንገዱ ላይ እንቅፋት እንዳያገኘዉና የ'ኔ እጣ እንዳይደርሰዉ ነዉ።" ብሎ በረዥሙ ትንፋሹን አወጣ። የ'ሱ ቅጽበታዊ አደጋ ለዘላለም ጎደሎ አድርጎ እንዳስቀረዉ ሁሉ ለጓደኛዉ ሀቢብም ይሄ ነገር እንዳይገጥመዉ በመመኘት ነበር። ...." እሱስ ልክ ነህ! ወጥቶ መቅረትም አለ።" አለች መኪያ። ይሄ መልሷ ለሀምዛም ይሆናል። ምክንያቱም ሀምዛ የደረሰበት ዱንያ ላይ ካሉ አደጋዎች ፤ ምድር ላይ ካሉ ችግሮች እጅግ በጣም ትንሹ ሊሆን ይችላል። ምክንያቱም 'ጫማ የለኝም ብለህ አትዘን እግር የሌላቸዉ አሉና!' አይደል ተረቱስ። ከቤታቸዉ እንደወጡ ያልተመለሱ ስንቶች አሉ - መንገድ ላይ በሚገጥማቸዉ አደጋ ህይወታቸዉ ላትመለስ ይከነፈችባቸዉ። ወይም ወደቤታቸዉ ሲመለሱ ቤታቸዉ አልሆኑ ሆኖ ቤት ንብረታቸዉን ፤ ሚስት ልጆቻቸዉን በአደጋ አጥተዉ ህይወት የጨለመችባቸዉ እልፍ ሰዎች እንዳሉ የማይካድ ሀቅ ነዉ። ከነዚህ ሁሉ ፈተናዎች ምናልባትም የሀምዛ ቀላሉ ነበር። 'ወጥቶ መቅረትም አለ' ስትለዉ እዉነት መሆኑን ለማረጋገጥ ያክል ራሱን በአዎንታ ወደ ታችና ወደ ላይ ከፍ ዝቅ አድርጎ ነቀነቀ። . ..."ለይሰል ገሪቡ... ገሪብ አሽ-ሻሚ ወል የመኒ ወላኪነል ገሪበ ... ገሪብ ወለህዲ ወል ከፈኒ ዛሬ የሌሉ ከኛ ጋራ... ትናንት አብረዉን የኖሩ ከመሬት በታች የገቡ ...የተጫናቸዉ አፈሩ እሩቅ አስበዉ በተስፋ... ዳሩ ግን ባጭር የቀሩ የራቁን የረሳናቸዉ ብዙ ወንድሞች ነበሩ....." የሚለዉ የሙሀመድ አወል ነሽዳ ከመኪያ ፖርሳ ዉስጥ ተሰማ - ስልኳ እየጠራ ነበር። ነሽዳዉ አቋርጡኝ አቋርጡኝ አይልም። በተስረቅራቂ ድምፁ ያዜማዉ ነሽዳ ቢሰማ የማይጠገብና የማይሰለች ነዉ። ይበልጥ ከሚያወሩት ርዕስ ጋር ስለገጠመ ተመሰጡብኝ ፤ አስተንትኑብኝ እንጂ ዝጉኝ አይልም - መካሪና ገሳጭ የሆነ ነሽዳ ነበር። መኪያ የፖርሳዋን መቆፊያ ዚፑን ከከፈተች በኃላ ስልኩን አወጣች። ..."የፎዚያ ቁጥር ነዉ" አለችዉ። ሀምዛም አንገቱን መለስ አድርጎ አያት። አንሽዉና አናግሪያት ማለቱ ነበሩ። አይኖቹ እንጂ ልሳኖቹ አላናገራትም። ..."ሄሎ አሰላሙዓለይኩም" አለች መኪያ። ከወዲያ ማዶ ሆና የምታወራዉ ፎዚ የሰላምታዉን መልስ ከመለሰች በኃላ የመኪያን ስልክ ቁጥር ስላላወቀች ማንነቷን ጠየቀቻት። ..."መኪያ ነኝ ፎዚ.. የሀቢብ ስልክ አይሰራም አንቺም አልመለሽልኝም። ችግር አለ እንዴ ፎዚ!?" ብላ ጠየቀቻት። ሀምዛን የሚያስጨንቀዉና የሚያሳስበዉ የሀቢብንና የፎዚያን ወደ ሆስፒታል መምጣት ሳይሆን ደህንነታቸዉንና በመካከላቸዉ እርቅ መስፈኑን፤ በፍቅር አንድ መሆናቸዉን ነዉ። የሄን የምታዉቀዉ መኪያ ሀምዛ በሚፈልገዉ መልኩ ፎዚያን እያናገረቻት ነዉ። በዚህ መካከል ሀቢብ ከሸዋር ቤት ሰዉነቱን በፎጣ እየጠረገ ወጣ። ፎዚያ ለመኪያ የምትነግራት ምክንያት ስላጣች ሀቢብ ከሸዋር እስኪወጣ ተጠባብቃ መኪያን እንዲያናግራት ስልኩን አቃበለችዉ። አንገቱን ወደ ላይና ወደ ታች እየነቀነቀ 'ማን ነዉ?' በሚል አይነት ሁኔታ ጠየቃት። ድምጿን ከፍ ሳታደርግ ከንፈሯንና ምላሷን ብቻ በማንቀሳቀስ ... "መ....ኪ....ያ ...ና...ት" አለችዉ። . ..."መኪ አሰላሙአለይኪ እንዴት ነሽ?" ብሎ ሞቅ ያለ ሰላምታ አቀረበላት። የጓደኛዉን ጉድ አላወቀ ... ... "ወአለይኩም ሰላም ደህና ነህ?" በማለት መልሳ የሱን ደህንነቱን ጠየቀችዉ። የሷን ደህንነት ግን አልነገረችዉም። ምክንያቱም ደህና አይደለችም!። ባሏ በሚሰቃዬዉ ህመም የሷም ዉስጧ ታሟል። ... "አልሀምዱሊላህ ... ሀምዛ እንዴት ነዉ!?" ለመጠየቅ ያክል እንጂ ከሀምዛ ከተለዬ ብዙም አልቆየም። ሀቢብን ከሆስፒታል ወደ ቤቱ አላህ የወሰደዉ የሀምዛን አስደንጋጭ ዜና እንዳይሰማና ከፎዚያ ጋር ጣፋጭ የሆነ የፍቅር ጊዜን እንዲያሳልፍ ሽቶ ይመስላል። ... መኪያ ጭንቀትና ሀሳብ ያሞቀዉን ትንፋሿን በረጅሙ 'ኡህህህፍፍፍ...." ብላ አወጣች። ያወጣዉ ትንፋሽ በጣም ከመሞቁ የተነሳ ፊት ለፊቱ የፕላስቲክ ፌስታል ቢያገኝ ለማጨማድድ የሚያንስ አልነበረም። ... "አልሐምዱሊላህ ያዉ ነዉ..." ... "መጣሁ በቃ መኪ .. ብዙ አትጨነቂ" አላት። መኪያ መንታ ሀሳብ ዉስጥ ሆና ተወዛገበች 'ልንገረዉ ወይንስ ሲመጣ ይሻላል?' እያለች ከራሷ ጋር ስትወያይ ... ሀቢብ "ቻዉ መኪ" ብሎ ስልኩን ዘጋዉ። . ... ፎዚያ አይን አይኑን እያየችዉ ነበር። ዘወር ብሎ ሲመለከታት ሶፋዉ ላይ ተቀመጣ ትቁለጨለጫለች። የሆነ ነገር እንዲላትና እንደሚወዳት እንዲነግራት ፈልጋለች። ... "የኔ ቆ..ን..ጆ...." ብሎ ከተቀመጠችበት ጎን ሂዶ ተቀመጠ። ... "ወይዬ ሁቢ" ስትለዉ ወደ ደረቱ አስጠግቶ እቅፍፍ.. አደረጋት። ፍጹም ሰላም ፤ ልዩ ደስታና ዘላለማዊ ሀሴት በይቅርታ ዉስጥ እንደ ወንዝ ዥረት በዝቶ ይገኛል። ይቅርታ ህመምን ያሽላል ፤ ዉሳኔንና ህግን ያሽራል። የዚህ ዉድ ነገር ባለቤቶች ግን ጠንካራ ሰዎች ናቸዉ። ፎዚ ደግሞ በዚህ አትታማም። እንኳን እሱዉ ይቅርታ ጠይቋትና ራሷ ሂዳ ይቅርታ ላድርግልህ ፍቅራችንን እናድስ እያለች ደጅ የምትጠና ልበ ብርቱ ሴት ናት። ... "እስከዛሬ ላደረግኩሽ ፣ ላስቀየምኩሽና ለበደልኩሽ ሁሉ ከልብ የሆነ ይቅርታሽን እፈልጋለሁ።" አላት። በአይኖቹ አይኖቿን እያየ ዉስጧን ሰርስሮ ልቧ ድረስ ዘልቋል። አሁን አንደበታቸዉ ብቻ ሳይሆን ልባቸዉም ሌላ ዉይይት ይዟል። ሀቢብ ድንግል ያልነበረችበት ምክንያት ምን እንደሆነ ከይቅርታዉ በኃላ ሊጠይቃት ወስኗል። ግን ደግሞ 'እንዳዲስ በግድ ያገኘሁትን ፍቅር የማይሆን ጥያቄ ጠይቄ ባስቀይማትስ' ብሎ ፈራ። 'እሷስ በጥያቄዬ ተናዳብኝ መጥፎ መልስ ብትመልስልኝ የሚታገስ ልብ ይኖረኝ ይሆን?' ሙግቱ ከራሱ ጋር ነዉ። ይሄን እያሰበ ፎዚያ ትክ ብላ ስታዬዉ ቆይታ.... "ሀቢቢ የኔ ዉድ..."  አለችዉ። ክፍል 13 ከ50 👍 like በኋላ ይቀጥላል‼️ ╚═══❖•💕💕•❖═══╝
1 940
8
​​​​​​💞"ጤዛዉ ፍቅሬ💞 💝በመልካም ልቦች የቴሌግራም ቻናል የቀረበ💝 🍂🍂ክፍል አስራ አንድ🍂🍂 ✍✍(ኑዕማን ኢድሪስ)✍✍ . .... "ወይዬ ሀቢቢ..." አለችዉ። በአይኖቿ አይኖቹን ስታይ የመጀመሪያዉን ሀቢብ ሆኖ አገኘችዉ። ፍቅርን እንጂ ጸብን የማያዉቀዉ ሀቢብ! - ፍፁም ተቀይሯል። ያን መጥፎ ባህሪ አስወግዶ ወደራሱ ማንነት ተመልሷል። ..ያን ጣፋጭ ጠረን ካገኘዉ ቆይቷል። ፍቅሯን ሁሌም ባትነፍገዉም በራሱ ሽሽት ግን ገላዋን ከማቀፍ ፤ ጸጉሯን እየደባበሰ ከንፈሯን ከመሳም ርቆ ኑሯል። ሁለቱም ተርበዋል። ከየት እንደሚጀምርና እንዴት ሊያስደስታት እንደሚችል ተደናግሮታል። ......"ታዉቂልሽ ማሬ?" አላት። ......"ምኑን ሀቢቢ?" ......"ልቤ ማፍቀር ከሚችለዉ በላይ እንደማፈቅርሽ!" ድምጹ ልስልስ ያለ ለጆሮ የማይጎረብጥ ፤ ሀሴትን የሚያፈናጥጥ በመሆኑ ዉስጧ በፌሽታ ተሞላ። አይታዉ የማታዉቀዉ አለም ዉስጥ የገባች መሰላት። ምንም ጠራራ ፀሐይ የወጣበት ከቀኑ ስምንት ሰአት ቢሆንም የቤቱ በርና መስኮቶች ተዘጋግተዉ ቤቱ ጨልሟል። እንደተከዘ ህፃን ልጅ ቡዝዝ ፍዝዝ ብላ የምትበራዉ መብራት ፎዚን በዉብት ላይ ዉበት አክሎላታል። .... እጆቿን አንገቱ ላይ ጣል አድርጋቸዉ እሱም ቀጭን ወገቧን በእጆቹ ይዞ ጣፋጭ ጠረኗን እየማገ አንገቷ ስር ዉትፍ ብሏል።.... . . .... ነርሶቹ ሀምዛን አይተዉት ከሄዱ በኃላ በመኪያና በሀምዛ መካከል የዝምታ አዋጅ የተጣለባቸዉ እስኪመስል ድረስ ተኮራርፈዉ ዝምታ በመካከላቸዉ ነግሷል። ቀደም ብሎ ዶክተሩ መኪያን አስጠርቷት የሀምዛ እግሮች ወደ ቀድሞ ሁኔታዉ መመለስ እንደማይችልና ቀሪ ህይወቱን ዊልቸር ላይ ሆኖ እንደሚያሳልፍ አርድቷታል። አላርፍ ያለች ነርስ ደግሞ በማያገባት ጥልቅ ብላ...."አይይ ይሄ እግር ቢቆረጥ እንጂ ከዚህ በኃላ እንኳ አያገለግልም።" ብላ በሁለቱም ፊት ላይ ጨለማ ጥላዉን እንዲያጣላ ፈረደችባቸዉ። ሁለቱም ተፈራርተዋል። መኪያ ቀና ብላ ሀምዛን ስታዬዉ ከአጠገቧ የሀምዛ ዛቱ እንጂ ሙሉ ሆኖ ከአጠገቧ እንደሌለ ፊቱ ላይ ተመለከተች። ..."ይሄዉልህ ዉዴ...." ብላ ጸጥታ የነገሰችበትን ክፍል ፈራ ተባ እያለች ምናልባት ከሰማኝ ብላ ንግግሯን ጀመረች። ነገር ግን ሀምዛ አልነቃም። የሚጓዝበት አለም የማይገፋ ፤ የሚሄድበት መንገድ የማያልቅ ፤ የሚቀዝፈዉ ዉቅያኖስ ክንድን የሚፈትን... ማዶን ተሻግሮ ሲመለከተዉ እንደ ሀረግ ዉስብስቡ የበዛ ሆኖ ታየዉ። ....."ጠንካራ አልነበርክ'ዴ ዉዴ? ለምን በቀላሉ ትሸነፋለህ?" እያለች የዉስጧን ህመም ፤ የባሏን ጉዳትና ስቃይ በዉስጧ አምቃ ይዛ እሱን ለማበረታታት ተቀምጣ ከነበረበት እግርጌዉ ወደ ራስጌዉ ተጠጋች። ....."ትዕግስት ማድረግኮ አለብህ ሁቢ ... ደግሞስ አላህ የወሰነዉና እሱ የፈለገዉን የሚያደርግ የሚያደርግ ጌታ መሆኑን ዘንግተህዉ ነዉ?" በእጇቿ የሀቢብን አገጭ ይዛ ወደ'ሷ አዞረችዉ። ፊቱ ኩስምን ፤ ሰዉነቱ ምንምን ብሏል። "ሀቢቢ አናግረኛ!!... አላህ እንደሚወድህ ለምን ትረሳለህ? እሱ የወደደዉን ባሪያዉን ወንጀሉን ሊያብስለት ሲፈልግ አይደል የሚፈትነዉ። ያ የሚሆነዉ ደግሞ ተወዳጁ የአላህ ባሪያ በሚደርስበት ፈተና ላይ ሶብር ሲያደርግ ነዉ። ሶብር...!!።" ታወራለች እንጂ ከልቡ አልሰማትም ፤ ከዉስጡ አላዳመጣትም። እንደምታወራ እንጂ ምን እንደምታወራ ፤ ስለምን እንደምታወራና ለምን እንደምታወራ በዉል አያዉቀዉም። "ሀምዛ... ሀምዛ" አለችዉ። በተዳከመ ድምጽ "ወይ መኪ" አላት። ...."እስኪ ለሀቢብ ደዉልልት" አለችዉ። ምናልባት ይሄን ትካዜ ሀቢብ መጥቶ ቢያጽናናዉና ስለሌላ ጉዳይ እያወራዉ የተወሰነ ቢረሳዉ ብላ በመመኘት ነዉ። ሀምዛ "እሺ" አላትና ወደ መስኮቱ አቅጣጫ አንቱን ቀለበስ አደረገ። .... "ደዉልለታ ሀምዛ" እሺ አባባሉ እሷን ላለመቃረን አንጂ ለመደወል እንዳልሆነ ገብቷታታል። ..."እንደዉም እኔ እደዉልለታለሁ" ብላ የእጅ ቦርሳዋን ፍለጋ ተነሳች። እሱ ግን የምትናገረዉንና የምታዘዉን ከማዳመጥ ዉጭ ምንም አይነት ምላሽ አልሰጣትም። ስልኳን ከቦርሳዋ አወጣችና የሀቢብን ቁጥር ተጫነች 091471። የደወሉላለቸዉ ደንበኛ........ "ኤጭ ይቺ ደግሞ...." ብላ ብላ ስልኩን ዘጋችዉና እንደገና ደወለች። . . .... ሀቢብና ፎዚ የጦፈ ፍቅር ዉስጥ ናቸዉ። አንዳቸዉ አንዳቸዉ ላይ ተለጣጥፈዉ አንድ አካል ፤ አንድ አምሳል እስኪመስሉ ድረስ ተቃቅፈዋል። በመካከላቸዉ ማስቲሽ ያጣበቃቸዉ እስኪመስል ድረስ ሙቀቱ አቆራኝቷቸዋል። የፎዚ ትንፋሽ ቁርጥ ቁርጥ እያለ ስሙን በየመሀሉ ትጠራዋለች። የሀቢብ ስም በሙሉዉ ቢጠራም የተቆላመጠ ይመስላል። ሀቢብ... ሀቢቢ... ሁቢ የሀቢብ ወላጆች ለፎዚያ መጥራት እንዲመቻት ተመካክረዉ ያወጡለት እስኪመስል ድረስ ገርቶላታል። ሀቢብ ከዚህ በፊት ፎዚን የማያዉቃት መስሎ እስኪሰማዉ ድረስ ጣፍጭ ሆናለታለች። ፀጉሯን እየደባበሰ ፤ መላ አካላቶቿን በጣቹ እያመሰ የቱን ስሞ የቱን እንደሚተወዉ ግር አለዉ። ከናፍሮቿ....፤ ጉንጮቿ....፤ የአንገቷ ጠረን ... እያንዳንዱ ገላዋን ማር የተቀባችዉ ይመስል የሀቢብ ከናፍሮች ፎዚን አልጠግባት ብለዋል። አንዱን እየሳመ ፤ አንዱን እየላሰ እንደተቃቀፉ ከፎዚ ኃላ ከነበረዉ ሶፋ ላይ ተያይዘዉ ወደቁ።.... . . . ..... መኪያ የሀቢብ ስልክ ባለመስራቱ እንደመበሳጨት ብላለች። "ቆይ አሁን ስለኩን ለምን ዘጋዉ?" ብላ የሀምዛን አይኖች አየቻቸዉ። ሀምዛም "በፎዚያ ሞክሪ..." አላትና ያቋረጠዉ ህልም እንዳለ አይኖቹን ግጥም አደረጋቸዉ። ትእግስት በማጣትና ተስፋ በመቆረጥ መካከል እንዳለ ሁኔታዉን አይቶ መገመት አያዳግትም። ነገር ግን መኪያም ተመሳሳይ ስሜት ዉስጥ በመሆኗ የሀቢብን መምጣትና ሀምዛን እንዲያበረታዉ ተመኘች እንጂ የሀምዛን ሁኔታ ለመረዳት አቀበት ሆኖባታል። ከብዷታል። .... "የፎዚን ስልክ ቁጥርኮ አላዉቀዉም" አለችዉ። .... "09 23   " ብሎ ነገራት። መኪያም ወደ ፎዚ ስልክ ደወለች። . . . ..... "ሙሀመድ ነቢና ኡሙሁ አሚና አቡሁ አብደላህ....." እያለ የሚጠራዉ የፎዚያ ስልክ አቃጨለ። ነገር ግን ሀቢብም ፣ ፎዚያም አልሰሙትም። የጋለ ስሜት ዉስጥ ናቸዉ። እንኳን የስልክ ጥሪና አጠገባቸዉ ብየዳጠቤት ቢከፈት የግላይንደር ድምጽ የሚያነቃቸዉ አይመስሉም። ለሀቢብ ከዚህ ድምጽ በላይ በለሰለሰ ድምጿ 'ሁቢ' የምትለዉ የፎዚያ ጥሪ ገኖ ይሰማዋል። ይሳሳማሉ ... እ.... እ.... . . . ...."አትመልስም" አለችዉ። ...."ተይዉ በቃ ምልክቱንጨስታየዉ መልሳ ትደዉላለች" ...." ቆይ ደግሜ ልደዉል..." አለችና በድጋሜ ደወለች። . . "ሙሀመድ ነቢና ኡሙሁ አሚና አቡሁ አብደላህ...." ╔═══❖•💕💕•❖═══╗      ክፍል12 ከ 80 👍like በኋላ ይቀጥል ‼️ ╚═══❖•💕💕•❖═══╝ https://t.me/Melkam_liboch1
2 096
9
​​​​💞"ጤዛዉ ፍቅሬ"💞 🌸🌸ክፍል አስር (10)🌸🌸 💝በመልካም ልቦች የቴሌግራሞ ቻናል የቀረበ💝 ✍✍(ኑዕማን ኢድሪስ)✍✍ -----------------((()))---------------- ..... ፎዚያ ከወትሮዋ ይበልጥ ደምቃለች። ሰሞኑን በትካዜ ከስሞ የነበረዉን ዉበቷን በአዲስ መንፈስ እንዳዲስ ወደ ቀድሞ እሷነቷ መልሰዋለች። ፊትለፊቷ በተገተረዉ መስታወት ራሷን እየተመለከተች ከዉበቷ ጋር ሙግት ይዛለች። 'ለሀቢብ ከዚህ የበለጥኩኝ ሆኜ መጠበቅ አለብኝ' በማለት የምትቀባባዉ አይነቱ በልክ ፤ አለባበሷ ስልክክ ያለች ወጣት ኮረዳ አስመስሏታል። እዉነታዉም ቢሆን ሀቢብ የተዘበራረቀ ህይወትን እንድትኖር ፈረደባት፤ ኑሮን እንድትጠላዉ አደረጋት እንጂ እሷ ገና አንዲት ፍሬ ነበረች። .... ቅንድቧን ስትኳለዉ አይኖቿ የሷን ዉበት ብቻ ሳይሆን ቤቱን ጨረቃ የወጣበት እስኪመስል ድረስ ግርማ ሞገስ አላበሰችዉ። ከንፈሮቿ እንኳን ስመዋት በማየት ብቻ ጣፋጭ እንደሆኑ መገመት እስኪያስችል ድረስ .... ጉንጮቿ ፤ መላ አካላቷ ነፍስን የሚጠግን የዉበት ቁንጮ ሆናለች። የቀራት የለም ቤቱን አድምቃ ፤ ራሷን አሸብርቃ ዉድ ባሏን መጠባበቅ ይዛለች። . .... ሀቢብ የግቢዉን በር ኪሱ በነበረዉ ቁልፍ ከፍቶ ገባ። ሙቤ የነገረዉ ነገር በልቡ ዉስጥ መንታ ሀሳቦች እንዲፈጥሩ አድርጎታል። 'ለማን ለመዋብ ነዉ የገዛችዉ?' ሲል መጥፎ ጥርጣሬን ፈጥሯል። ይሄን ከንቱ ሀሳብ የሀቢብ ልብ ሳይሆን ፍቅረኛሞችን ለመለያየት ፤ ትዳርን ለመበተን የሚወጥነዉ የርኩሱ ሰይጣን ሀሳብ ይመስላል። "አላህስ (ሱ.ወ) ጠላታችን እንደሆነ ነግሮን የለ?" . .... ፎዚ የዉድ ባሏን መምጣት በጉጉት እየጠበቀች ሳሎኑ ዉስጥ መንጎራደድ ይዛለች። ሀቢብም የግቢዉ በር አልፎ ከቤቱ ዋናዉ በር ስር ቆሞ በሩን ለማንኳኳት እጁን ሲዘነዝር አንዳች ሀይል አፍንጫዉን ጎትቶ የሸሚዙን ኮሌታ አንቆ ወደ ዉስጥ የሚያስገባዉ መሰለዉ። የቤቱ ጠረን ገና በሩቁ ይጣራ ነበር። ድግሱ ለሱ እንደሆነ ገባዉ። ፎዚያ በጥሩ መንፈስ ፤ ልቧንም ቤቷንም በፍቅር ሞልታ እየጠበቀችዉ እንደሆነ ተረዳ። ይሄን የመሰለ ልዩ ዝግጅት እጅና እግሩን (እሱነቱን) ብቻ ይዞ ሊገባ አልፈለገም። ይሄን የመሰለ ልዩ ዝግጅት በተኮሳተረ ፊት ገብቼ ሊደፈርስ አይገባም ብሎ ተጠናዉቶት የነበረዉን አጉል ጥርጣሬ አስወግዶ ፊቱን በፈገግታ ሞልቶ ወደ ቤት የመግባት ሀሳቡን ቀይሮ ወደ ኃላ ዞሮ መንገድ ጀመረ። . .... በጉጉት የምጠብቀዉ ሀቢብ (ባሏ) አልመጣላትም። ዘገየባት። ስልኳን አነሳችና ደወለችለት። "ነህኑ ቀዉሙን አዓዘነላህ ነህኑ ቀዉሙን አዓዘነላህ ህዝቦች ነን ያላቀን አላህ...." የሚለዉ የአልፋቲሁን ነሽዳ ከከሱ ዉስጥ እንደሆነ የሀቢብ ስልክ አቃጨለ። ...."ምንድን ነዉ የምሰጥህ?" አለዉ ሙቤ። ...."ቆይ አንዴ ሙቤ...." ብሎ ስልኩን ከኪሱ አዉጥቶ ለማነጋገር የሚያስችለዉን ቁልፍ ተጭኖ ማነጋገር ጀመረ። ፎዚያ ሰላምታዉን ካስቀደመች ቡኃላ ... "ምን ሁነህብኝ ነዉ ሀቢቢ ሀምዛ አልተሻለዉም'ዴ?" አለችዉ። .... "መኪያ መጥታለታለች ፎዚ?" ስሟን ሲያቆላምጥላት ዉስጧ በደስታ ማእበል ተናወጠ። .... "እና አንተ...." ብላ ንግግሯን ሳትጨርስ "ደርሻለሁ ፎዚዬ እየመጣሁኝ ነዉ" አላት። . ...."አንተ አትናገርም እንዴ? ምንድን ነዉ የምሰጥህ?" አለዉ ጮኾ። ስልኩ ተዘግቶ ስለነበር ፎዚያ የሙቤን ድምጽ አልሰማችዉም። ...."እስኪ ለቆንጆ ሴት የሚሆን ቆንጆ ስጦታ...." ብሎ ትእዛዙን ሳይጨርስ ቀድሞ የሀቢብን አመል የሚያዉቀዉ ሙቤ..."አንተ አሁንም ሌላ ሴት ጋር ትሄዳለህ? ፎዚን የመሰለች ቆንጆ የት ትተህ ሌላ ቆንጆ ትፈልጋለህ??" ብሎ ጮኸበት። የሙቤን ቁጣ ሲሰማ ፈገግ አለና ..."ሙቤ እስኪ ተረጋጋ!" አለዉ። .... "ምን ያረጋጋኛል? ሚስትህ ቆንጆ ሆና...." ሀቢብ አላስጨረሰዉም። .... "እኮ ስጦታዉ'ኮ ለሷ ነዉ" ብሎ ቶሎ አፉን አዘጋዉ። ሙቤ ሀቢብን ከፎዚያ በፊት ያዉቀዋል። ያለፈ አመሉ ቤቱ ሴት ማመላለስ ነበር ስራዉ። ዛሬ የያዛትን እስከ ነገ አያቆያትም ነበር። እሷን አባሮ ሌላ ሴት መተካት የሚታወቅበት ተግባሩ ነበር። ይሄንን ስለሚያዉቅ በሚስኪኗ ፎዚ ላይ እንዲህ አይነት የዘቀጠ ትግባር እንዲፈጽም አልፈቀደለትም። . .... ከአንድ አይሉ ሁለት ስጦታዎችን ገዝቶ ይዟል። ታፍኖ የኖረዉን የፎዚን ልብ ሊያስቦርቃት ሽቷል። በዚሁ አጋጣሚም ዉስጡ የሚብሰለሰለዉን ጥያቄ ሊያፈርጠዉና በትዳሩ ዉስጥ ግልጽነት የሚባለዉን መርህ ሊያሰፍን አንግቦ ተነስቷል። "የክብረ ንጽህናዋን ጉዳይ...." ይሄ ነገር ዉስጡን ሰላም እንዲነሳዉ አልፈቀደም። መፍትሄ ሊያበጅለትና የጥላቻዉና የመቃቃሩ ጉዳይ ዛሬ እንደሚያበቃለት በዉስጡ ደምድሞ ጨርሷል። . ..... "ኳ ኳ ኳ" በሩን አያንኳኳ ነዉ። የ'ሱን መምጣት በጉጉት ስትጠባበቅ የነበረችዉ ፎዚያ ተቀምጣበት ከነበረችበት ሶፋ ምንጥቅ ብላ ተነሳችና እየተንደረደረች ወደ በሩ አመራች። ..."ማን ነዉ?" አለች። ሀቢብ ስለመሆኑ አላጣችዉም መጠየቅ ስላለባት ብቻ ጠየቀች። ሀቢብ ፎዚንና እሱን የጋረዳቸዉ በር ስር እንደቆመ በተስረቅራቂ ድምጿ ልቡ ራደ። ያ ማራኪ ድምጿ እሱነቱን ገዛዉ ፤ እጅ ወደ ላይ አስባለዉ። ...."እኔ ነኝ ፎዚ...!" አላት። ፎዚያ የሀቢብ ድምጽ መሆኑን ስታዉቅ ሰዉነቷን አንዳች ስሜት ነዘራት። በሩን እንደከፈተች ጥምጥም ብላበት ከንፈሮች ልትገምጣቸዉ ተመኘች። ሀሳቧን እንደገና መለስ አደረገችና 'ሀቢብ ለዚህ ዝግጁ ባይሆንስ?..' ብላ እያሰበች በሩን ቀስ ብላ በቄንጥ ከፈተችዉ። "አሰላሙዓለይኩም ሀቢቢ" ፈገግታዋና ፈገግታዉ አንድ ላይ ሲጋጩ ጸሐይ ከመዉጫዋ መንታ ሆና የወጣች መሰለ። ሰላምታዋን መለሰላትና በጀርባዉ ደብቆት የነበረዉን ቀይ አበባ ለስጦታ ዘረጋላት። "የኔ ቆንጆ... " ብሎ አይኖቹን ሲያቅለሰልሳቸዉ ፎዚ ማመን አቃታት። በድንጋጤ እጆቿን ወደ ከናፍሮቿ አድርቃ "ያ አላህህህህ.... " አለች። .... እሷም በምላሹ "ሀቢቢ..." ብላ የተዘረጋላትን የፍቅራችንን እናድስ ዉብ አበባ ተቀበለችዉ። ሀቢብም ወደ ፎዚ አንድ እርምጃ ቀረብ አለና እቅፉ ዉስጥ አስገባት። በእግሩ በሩን ገፋ አድርጎ ከከረመዉ በኃላ ዉብ ከንፈሯን በስሱ ሳም አደረጋት። ፎዚ ለመጀመሪያ ጊዜ የተሳመች እስኪመስላት ድረስ ስልምልም አለችና ከደረቱ ላይ ልጥፍ አለች። ...."ፎዚዬ የኔ ዉድ....." ከእቅፉ ዉስጥ እንዳለች እያንሾካሾከ ሲጠራት ህልም እስኪመስላት ድረስ ወደ ላይ ቀና አለችና አይን አይኑን እያየች "ወይዬ ሁቢ..." አለችዉ። ╔═══❖•💕💕•❖═══╗      ክፍል 11 ከ👍 like በኋላ  ይቀጥላል ‼️ ❥............🍃👑👑🍃..............❥ በፍጥነት እንዲቀጥል like ፈጠን! https://t.me/Melkam_liboch1
2 219
10
​​​​💞''ጤዛዉ ፍቅሬ'💞 💝በመልካም ልቦች የቴሌግራም ቻናል የቀረበ💝 💐💐ክፍል -9💐💐 ✍✍(ኑዕማን ኢድሪስ)✍✍ ---------------------------------------------- Like እና Share አድርጋችሁ ጀምሩ ---------------------------------------------- ..... 'ሀምዛ... ሀምዛዬ... የኔ ዉድ...' እያለች እጇን እያወናጨፈች ሀምዛ ወደተኛበት አልጋ ሮጠች። ሁለቱ ጓደኛሞች ከልባቸዉ የሆነ ዉይይት ይዘዉ ስለነበር የክፍሉን በር ከፍታ ስትገባ ስላላስተዋሏት 'ሀምዛ' የሚለዉን የመኪያን ጥሪ ሲሰዉ ሀምዛ በተኛበት ፤ ሀቢብ በተቀመጠበት ቦታ ሆነዉ ደንዝዘዉ ቀሩ፤ ክዉ አሉ። ከበሩ አስከ አልጋዉ ያለችዉ ክፍተት መኪያን የአስር ሺ ሜትር ተወዳዳሪ አትሌት አስመስሏታል። ከሰዉነቷ ሁሉ ቀድሞ እንደ ባንድራ የሚዉለበለበዉ እጇ ሀምዛን ለማቀፍ ፤ የሀምዛን ገላ ለመዳበስ ሽተዋል። .... ሀቢብ ከተቀመጠበት የአልጋዉ ጠርዝ ተነስቶ "ተረጋጊ መኪያ... ምንም'ኮ አልሆነም... አይዞሽ" እያለ ያባብላት ይዟል። እሷ ግን ባሏ አልጋ ላይ ተንጋሎ ስታይ የሞት ጽዋን የሚቀዳጅ እንጂ ተሽሎት የሚነሳ አልመስላት ብሏል። ሀምዛም ..."መኪዬ ደህና ነኝኮ ለምን እንደዚህ ትሆኛለሽ?" ብሎ ሲያናግራት ቀና ብላ አየችዉና "ደህና ነህ የኔ ቆንጆ" እያለች በለስላሳ መዳፎቿ አንዴ አይኑን ከዚያም ጉንጮቹን ትደባብሰዉ ገባች። ... "የኔ ቆንጆ መጀመሪያዉኑም አንች ሶብር አጥተሽ መጣሽ እንጂ እኔኮ ደህና ነበርኩ" ብሎ ይበልጥ ደህንነቱን አረጋገጠላት። ሀቢብም ቀጠል አድርጎ "... ሶብሪ መኪ! ትንሽ ጭረት'ጂ ያጋጠመዉ በጣም ደህና ነዉ" ብሎ አከለላት። የተወሰነ ተረጋግታ ወደ ቀድሞዋ እሷነቷ ተመልሳ ስለክስተቱና ስለሁኔታዉ ጠየቀችዉ። "ቀላል ነዉ...." ብሎ ጀመረና ለፎዚያ እንደነገራት አድርጎ አስረዳት። ....... ሀቢብ እሱ ተረስቶ ባልና ሚስቶቹ ብቻዉን ሲያወሩ 'የምን መፋጠጥ ነዉ?' በሚል አይነት "በሉ እናንተ ተጫወቱ እኔንም ሚስቴ ትጠብቀኛለች!" ብሎ ከተቀመጠበት ተነሳ። ፎዚን ሚስቴ በማለቱ ሀምዛ ደስ አለዉ። ጓደኛዉ የተስተካከለለት ያክል መስሎ ተሰማዉ። ነገር ግን በል ቻዉ ብሎ ቶሎ ሊሰናበተዉ ስላልፈለገ "እኔምኮ ሚስት አለችኝ ማንን ለማስቀናት ፈልገህ ነዉ?" ብሎ እንደመቀለድ ሲያደርገዉ ሀቢብም አጸፋዉን ለመመለስ ያክል ወደ መኪያ እየተመለከተ ..."ሚስቱ ጓደኛዬን አደራ እሺ! በደንብ አስታሚዉ" ብሎ ሁለቱንም በፌዝ ኮርኮም አደረጋቸዉ። መኪያም የዋዛ አለነበረችም ኖሯልና "እንደዉም ቶሎ ዉጣ በሽታዉ እንዳይብስበት ክክክክ..." እያለች በአሽሙር ቢጤ ጎንተል አደረገችዉ። "አሃሃ በሽታዉ እኔ ነኝ ማለት ነዉ!? በሉ ቻዉ" ብሎ ተሰናብቶ ወጣ። . . .... ፎዚያ ሆስፒታል ዉስጥ ሀምዛ የመከራት ነገር ዉስጧ ገብቷል። በሀቢብ በጣም ብዙ ጊዜ ተስፋ ልትቆርጥ ቋፍ እየደረሰች 'እስኪ ዛሬን ልየዉ' በሚል ተስፋ ዛሬን ደርሳለች። አሁን ደግሞ የሀምዛ ምክር ተስፋዋን ይበልጥ አለመለመላት ፤ ፍቅሯን የመለሰላት አስኪመስላት ድረስ መንፈሷን ጠገነላት። መኝታ ቤቷ ዉስጥ እንደ አክሱም ሀዉልት የተገተረዉን ቁም ሳጥኗን ከፍታ የቱን ለብሼ ተዉቤ ልጠብቀዉ ፤ ጸጉሬን እንዴት አድርጌ ላስይዘዉ እያለች 'ተዉበሽ ጠብቂዉ' የሚለዉ የሀምዛ ቃል እንደ ገደል ማሚት በጭንቅላቷ ወስጥ እያቃጨለ እንደተቀጠረ ሰአት ያስታዉሳት ይዟል። .. .... ጠጠር የመሰለችዉ ድንጋይ ስታደናቅፈዉ ከእንቅልፉ እንደተቀሰቀሰ ሰዉ ብትት አለ። ታክሲ የሚሳፈርበትንም ቦታ አልፎት ብዙ ተጉዟል። ለካ መንገዱን ሁሉ ስለ ፎዚ ነበር የሚያስበዉ። ስለ'ሷ ብቻ ነበር የሚያልመዉ... እስካሁን ለመወሰን የከበደዉም ጉዳይ አለ። 'ፎዚን ክብረ ንጽህና አላገኘባትም' ቢሆንም ግን እሱ ራሱም የሚመሰክረዉ ነገር አለ 'ፎዚን በጣም ያፈቅራታል ከልቡ ይወዳታል' እና በዚህ አይነት ሁኔታ እንዴት ፎዚን እተዋታለሁ? የሚለዉ ሙግት ሀቢብን በአንድ ሀሳብ የሚከራከሩ ሁለት አካሎች አድርገዉታል። "ቆይ ከክብርና ከፍቅር የቱ ይበልጣል?" ሁለት ወሳኝ የሆኑ ነገሮች ከፊቱ ተጋርጠዉበታል። በዉስጡ ሙግት ገጥመዉበታል። ይሄንኑ በማሰብና በማሰላሰል ላይ እያለ ብዙ ተጎዞ ከሰፈሩ ደረሰ። ወደ ቤቱ ከመግባቱ በፊት ሰፈሩ አከባቢ የምትገኝ ትንሽዬ የኮስሞቲክስ ሱቅ ገባ። በሃሳብ የተኮፋተረ ከንፈሩን በዉሃ ሊያረጥበዉ ሻተ ፤ መንገድ ያዛለዉን ጉልበቱን አርፍ ሊልበት ፈለገ። እንዲህ ሲሆን ነዉ ፎዚን በአዲስ መንፈስ የማገኛት ብሎ በማሰብ። "ሙቤ እስኪ ዉሃ ካለህ አጠጣኝ" ሲል ሱቅ ጠባቂዉን ሙባረክን ጠየቀዉ። ሰዉነቱ በመንገድ ከመዛሉም በላይ በሀሳብ ዝሏል ፤ ከጸሐዩ በላይ የሀሳቡ ሙቀት ረቶታል። "አ..ን..ተ ..." አለ ሙቤ። አማረኛን በግድ ተናገር ያሉት ይመስል ቃላቶቹን በጠረባ አያለ ይዘርራቸዋል። ሁለተኛ ቋንቋዉ እንደሆነ ያስታዉቅበታል። "ና በዚ ተቅመጥ" አለዉና ትንሽዬ ኩርሲ አቀበለዉ። ዉሃን ከመስጠቱ በፊት ሀቢብን ሲያገኘዉ ሊነግረዉ የሚፈልገዉ ጉዳይ እንዳለዉ አሳብቆበታል። "ዛሬ ...ያቺ..." ብሎ ስሟ ጠፋዉና እንደማሰብ አደረገ። ነገር ግን አላገኘዉም። ስሟ ተሰወረበት። "ማን ነበር ስሟ" ብሎ ሀቢብን ጠየቀዉ። ሀቢብም ነገሩ ስላልገባዉ መልሶ እርሱኑ "የቷ ሙቤ!?" በማለት ጠየቀዉ። "ያቺ ናታ ያንተ ሚስት" ሀቢብ ድንጋጤ ዉስጡን ስንጥቅ አድርጎት ከተቀመጠበት ተነስቶ "እ... ምን ሆነች!!?" ብሎ ሙቤ ላይ አፈጠጠበት። "ዛሬ መጣችና ኩልና ሊፒስቲክ ገዝታኝ....." ብሎ ንግግሩን ሳይጨርስ "ኦህህ...." አለና በረጅሙ ትንፋሹን ካወጣ ቡኃላ ፊቱ ላይ በሰከንዶች ችፍ ብሎ የነበረዉን ላብ እየሟዠቀ ተቀመጠ። "ቆይ እሷም ትቀባባለች እንዴ!?" ብሎ ሲጠይቀዉ። ለጥያቄዉ ሳይመልስለት የጠየቀዉንም ዉሃ ሳይጎነጭ እየበረረ ወደ ቤቱ ከነፈ። ╔═══❖•🌺🌺•❖═══╗ ከ100like👍 በኋላ ይቀጥላል ‼️ ╚═══❖•🌺🌺•❖═══╝ ❥............🍃💐💐🍃..............❥ https://t.me/Melkam_liboch1
2 223
11
​​💞​​ጤዛዉ ፍቅሬ"💞 💝በመልካም ልቦች የቴሌግራም ቻናል ተዘጋጅቶ የቀረበ💝 💐💐ክፍል ስምንት💐 ✍✍(በኑዕማን ኢድሪስ)✍✍❥............🍃💐💐🍃..............❥ ...... ፎዚያ የሀምዛን ሚስት (መኪያን) ሀምዛ ትንሽ እንዳመመዉና ሆስፒታል እንደተኛ ቀለል አድርጋ ነገረቻት፡፡ የሀምዛ ሚስት ግን 'የህመም ትንሽ የለዉም፡፡" ብላ የምትይዘዉ የምትጥለዉ ተደናግሯት በፍጥነት ወደ ሆስፒታል አመራች፡፡ . ..... ሀቢብ ጉዳዩን ሁሉ ለሀምዛ ነግሮታል፡፡ ሀምዛ ግን ለነግሩ ክብደትና ቦታ ሳይሰጠዉ ቀለል አድርጎ የራሱን ሀሳብ ይነግረዋል፡፡ . "የብዙዎቻችን ችግር ምን እንደሆነ ታዉቃለህ?..." ብሎ የሀቢብን አይኖች በአትኩሮት እየተመለከተ ጠየቀዉ፡፡ ሀቢብም ጥያቄዉን ከመመለሱ ይልቅ ሀምዛን በፅሞና ማዳመጡን መርጧል፡፡ ..."ሀቢቢ እኔ የቅርብ ጓደኛህ ነኝ፡፡ አንተ ስለኔ እንደምታዉቀዉ ሁሉ እኔም ስላንተ ብዙ ነገር አዉቃለሁ፡፡ ... የሰርጋችሁ ቀን በማግስቱ ስለ አዳራችሁ ስጠይቅህ ሙሉ እንደሆነችና እስከ ክብረ ንጽህናዋ እንዳገኘሃት ነግረኸኝ ነበር፡፡..." ..."አዎ ምን መሰለህ ..." ብሎ የዚያ ቀን ለምን እንደዋሸዉ ሊያስረዳዉ ሲል ሀምዛ የሀቢብን ወሬ አቋረጠዉና፡፡ ..."ይገባኛል ጓደኛዬ የዚያን ቀን ለኔም ሆነ ለቤተሰቦችህ የዋሸህዉ የሷን ክብር ለመጠበቅና እሷን ዝቅ አድርገን እንዳናስባት በማሰብህ ነዉ፡፡... (ሀቢብ የዋሸበትን ምክንያት ሀምዛ ስለተረዳለት አንገቱን ወደ ላይና ወደ ታች ከፍ ዝቅ እያደረገ ነቀነቀ፡፡)... አየህ ሀቢብ ትወዳታለህኮ! - ምክንያቱም ለሷ ክብር የምትጨነቅ አሳቢዋ ነህ፡፡..." እያለ ጥሩነቱን ከነገረዉ በኃላ ... " ግን ሀቢብ የተወሰኑ ወራቶችን ችለህና በፍቅር አብረህ ኑረህ ስታበቃ እንዴት አሁን ያ ነገር ትዝ አለህ? ለምን በዚህ ምክንያት ነገር ትቀሰቅሳለህ?፡፡ ያ ያለፈ ጉዳይ አይደለ እንዴ" ብሎ ጠየቀዉ፡፡ ሀቢብ በረጅሙ ትንፋሹን "እህህህህህ...." ብሎ ካወጣ በኃላ፡፡ . ..."ልክ ነህ ሀምዛ...! በወቅቱ ለነገሩ ትኩረት አልሰጠሁትም ነበር፡፡ ምክንያቱም በጣም ስለማፈቅራት፡፡ እያደር ግን ዉስጤን ይከነክነኝ ጀምር፡፡ ከመጀመሪዉ በጣም እተማመንባት ስለነበር ክብረ ንፅህናዋን ሳይሆን እሷነቷን ነበር የፈለግኳት፡፡ አሁን ግን እሷነቷን ብቻ ሳይሆን እሷነቷን ሙሉ ሁና እስከ ክብረ ንፅህናዋ ማግኘት ፈለግኩ፡፡ በዚህ ምክንያት ለሷ ያለኝ ቦታ ወረደ፣ በፊት የማፈቅራትን ያክል ላፈቅራት አልቻልኩም፡፡ ምክንያቱም ሁሌ ሳስባት ርካሽ መስላ ትታየኛለች፡፡...." ወሬዉን ቀጥሏል በስተመጨረሻም ሀምዛ የሀቢብን የጥላቻ መነሻ ከሰማ በኃላ... "ሀቢብ አንተ ሙሉ ነበርክ እንዴ? ...ማለቴ አንተ ፎዚያን ስታገባት ክብረ ንፅህና ነበረህ?" ብሎ ጠየቀዉ፡፡ ሀቢብ ጓደኛዉን ለማስረዳት ሲዳዳ ሀምዛ የጥያቄዉን መልስ ራሱ መለሰለት፡፡ ..."ሁለታችንም እንተዋወቃለንኮ፡፡ አንተ ለስንት ሴቶች መበላሸት ምክንያት ሆነሃል? ... ስንት እህቶችን እስከ ክብራቸዉ ትዳር እንዳይመሰርቱ አድርገሃል? እና አንተ ስለ ክብረ ንፅህና መጠየቅ ነበረብህን?... ይሄዉልህ ሀቢቢ ክብር የሚገባዉ ክብር ላለዉ ሰዉኮ ነዉ፡፡...." ብሎ ወሬዉን ቀጠለ፡፡ ሀቢብን ብዙ ጠየቀዉ፤ መከረዉ፣ ገሰጸዉ ነገር ግን ሀቢብ ሊዋጥለት አልቻለም፡፡ እንደገና የፎዚያን ክብረ ንጽህና ሊያመጣለት ስለማይችል ሊቀበለዉ አልቻለም፡፡ . ..."ተዉ እንጂ ሀምዛ ...(አለዉ ቆጣ ብሎ)... እኔንና እሷን በምን ስሌት ነዉ የምታወዳድረን? እ?... እሷኮ ሴት ናት፡፡" አለዉ፡፡  ሀምዛ ክብረ ንፅህና የሚባለዉ ነገር ወንድም እንዲኖረዉ፤ ከትዳር በፊት ከማንም ሴት ጋር ግንኙነት ይኑረዉ የሚል እምነት የለዉም፡፡ ..."ወንድ ይንዘላዘል ያለዉ ማን ነዉ ሀቢብ? ወንድ ሲበላሽ አብሮ የሚያበላሸዉ ሴትን አይደል?... ወንድም ጥሩ ፤ ሴትም ጥሩ መሆን አለባቸዉ፡፡ መልካም የሆነ ሰዉ መልካምን እንጂ አያገኘም፡፡ ደግሞ ሀቢብ ሁለታችንም የምንስማማበት ነገር አንተ ከትዳር በፊት የነበረህ ህይወት ጥሩ እንዳልሆነ ነዉ፡፡ እርግጠኛ ሁኜ የምነግርህ ግን ፎዚያ ችግሯን ስላልተረዳሃት፤ እንደ ባል ጠጋ ብለህ ስላልጠየቅካት እንጂ ንፁህና ሙሉ ናት የሚል ግምት አለኝ፡፡" ብሎ ፎዚንም በተጠራጠረ አንደበት ነገረዉ፡፡ . ......ዉይይታቸዉ ወደ ክርክር እየተለወጠ ነዉ፡፡ ሁለቱም ሞቅ ብሏቸዋል፡፡ በዚህ መካከል መኪያ .. ሀምዛ ወዳለበት ክፍል ገባች፡፡ የሀምዛን አልጋ ላይ መተኛት ያየች ጊዜ በድንጋጤ እየጮኸች ተጠመጠመችበት፡፡ ......" ሀምዛ...." እያለች፡፡ ╔═══❖•🌺🌺•❖═══╗ ክፍል ዘጠኝ ከ like👍 በኋላ ይቀጥላል‼️ https://t.me/Melkam_liboch1
2 200
12
​​​​💞"ጤዛዉ ፍቅሬ"💞 💝ከመልካም ልቦች የቴሌግራም ቻናል የቀረቀ💝 💐💐ክፍል ሰባት (➐)💐💐 ✍✍( በኑዕማን ኢድሪስ )✍✍ - ..... አንዳንድ ጊዜ ተጨማሪ ፈተና ለሌላዉ ችግር መልስ ወይም መፍትሄ ሆኖ ይገኛል፡፡ ምናልባትም የሀምዛ የመኪና አደጋ መድረስ ለሀቢብና ለፎዚያ ትዳር መስተካከልና መስመር ጥሩ አጋጣሚ ይሆናል፡፡ ማን ያዉቃል.... ፎዚያ ሆስፒታል ስትደርስ በፍጥነትና በሶምሶማ ከመራመዷ የተነሳ እያለከለከችና እጅግ በጣም ደክማ ነበር፡፡ ሀምዛ ከድንገተኛ ክፍል አልጋ ላይ ተንጋሎ ተኝቷል፡፡ እግሩ ክፉኛ ተጎድቷል፡፡ ቶሎ ሆስፒታል በመድረሱ ከሰዉነቱ የሚፈሰዉ ደም በህክምና እርዳታ ሊቆም ችሏል፡፡ ሀቢብ ደግሞ ከጎኑ ተቀምጦ እያወሩ ነበር፡፡ የሚያወሩት ስለ ሀቢብ ትዳር መበጣበጥ ነበር፡፡ "ከሞትኩም እንኳ የጓደኛዬን ህይወት ደስተኛ አድርጌ፤ ትዳሩን አስምሬለት መሆን አለበት፡፡" ብሎ ለራሱ ቃል ገብቷል፡፡ የጓደኛ ልኩ እንደ ሀምዛ ነዉ፡፡ እራሱን እያጣ ለጓደኛዉ ያስባለል፣ በአደጋ የተጎዳዉን እግሩን እያመመዉ ረስቶት የጓደኛዉን የልብ ህመም ያስታምማል፡፡ ሀቢብ ደግሞ ከዚህ ርዕስ ለመዉጣት የማያደርገዉ ጥረት አልነበረም፡፡ በወሬያቸዉ መካከል "ቆይ ግን መኪያ ሰምታለች?" እያለ ወሬ ያሰናክላል፡፡ (መኪያ የሀምዛ ሚስት ነች)  'እግርህን እንዳያምህ አትገላበጥበት!' እያለ መኝታዉን እንደማስተካከል ያደርጋል፡፡ ሀምዛ ግን ወይ ፍንክች የፎዚያን እንባ ማበስ ሽቷል፡፡ ...... ፎዚያ ሆስፒታል ስትደርስ ይገጥመኛል ብላ ያሰበችዉ ነገር መጥፎ ነበር፡፡ ነገር ግን ያ ያሰበችዉ ነገር ደርሶና ሆኖ ባለማገኘቷ ጌታዋን አመሰገነች፡፡ ሆኖም  የደረሰበት ነገር አስከፊ በመሆኑ በጣም እያዘነች ባሏንና የባሏን ጓደኛ 'አሰላሙዓለይኩም' ብላ ተቀላቀለች፡፡ ..."አልሐምዱሊላህ ሀምዛ ... መኪና አደጋ ሲሉኝ ክፉኛ የተጎዳህ ነበር የመሰለኝ... እንዴት ነህ ግን በአላህ?' ብላ ጠየቀችዉ፡፡ ሀምዛ ስለደረሰበት አደጋና ስለገጠመዉ ሁኔታ ቀለል አድርጎ ለፎዚ ካስረዳት በኃላ... "አንቺ እንዴት ነሽ?" ብሎ ጠየቃት፡፡ ስለ ደህንነቷ ሲጠይቃት ቤቷ ሰላም እንደሌላት ያዉቋል፡፡ የሀቢብን ባህሪ ጠንቅቆ ስለሚያዉቀዉ ይሄን ለመረዳት አያዳገተዉም፡፡ .... ሀምዛ ቀስበቀስ ወደ ነገሩ እየገባ ሁለቱንም ጥንዶች መከራቸዉ፡፡ 'ትዳርን መተሳሰብ ካልተጨመረበት ህይወታችሁ ሰቆቃ፤ ትዳራችሁ እንደ ህፃን እቃቃ ያደርግባችኃል፡፡ (ሁለቱም ተመስጠዉ ያዳምጡታል፡፡ በተለይ ሀቢብ የጓደኛዉ ምክር ኑዛዜ እስኪመስለዉ ድረስ ልብ ሰጥቶት እየሰማዉ ነበር፡፡) ... ነጋ ጠባ የምትጣሉት ነገር ፍቅራችሁን እያደፈረሰ መቃቃርን ያመጣል፡፡ መናናቅን በስተመጨረሻም የከፋ ደረጃ ያደርሳችኃል፡፡ በተለይ ሀቢብ ዉድ ጓደኛዬ ለትዳርህ ቦታ ስጠዉ፤ ለሚስትህም እንክብካቤ አትንፈጋት፡፡ (ይሄንን ቃል በፎዚ ፊት በመናገሩ ዉስጧን ሀሴት ተሰማት፡፡ ሀምዛ ... ሀቢብን ተቆጥቶና ገስጾ፤ ለፎዚያ ደግሞ ትዕግስት ማደረግ አለብሽ ብሎ ንግግሩን ቋጨ፡፡)..." ..... በመካከላቸዉ ለተወሰነ ደቂቃ ዝምታ ከሰፈነ ቡኃላ ሀምዛ ወደ ፎዚያ ዞረና... "የመኪያ ስልክ ስለማይሰራ ቤት ሂጂና አረጋግተሽ ንገሪያት፡፡ በዚያም ወደ ቤትሽ ሂደሽ አረፍ በይ" አላትና ፎዚ ተነስታ ተሰነባብታ ለመዉጣት ስትሰናዳ ..."ባይሆን ወዱን ባልሽን ተዉበሽ ጠብቂዉ...እ..." ብሎ ሀቢንም ፎዚንም ፈገግ አደረጋቸዉ፡፡ ..... ሀቢብ ..ሀምዛ ላይ የነበረዉን ጥርጣሬ አስወግዶ ሁሉንም ሚስጥር ለመንገር ከዉስጡ ጋር ሙግት ያዘ፡፡ በስተመጨረሻም የሀምዛ የዋህነትና ቅን አሳቢነት አሸንፎት ፎዚን ለምን ሊጠላት እንደቻለ? ለምን የቤታቸዉ ሰላም እንደደፈረሰ? ለምን የበፊት ፍቅሩ እንደተወገደና ለፎዚ ያለዉ ክብር እንደቀነሰ ሊነግረዉ ፈለገ፡፡ ..... "ሀምዛ..." አለዉ አንገቱን ጎንበስ፤ አይኑን ቀለስ፤ አንደበቱን ለስለስ አድርጎ፡፡ ሀምዛም ሲጎነጭ የነበረዉን ጁስ ትቶ ..... "ወይዬ ሀቢብ..." ብሎ መለሰለት፡፡ ..... "ሀምዛ በጣም ይቅርታ" አለዉ፡፡ ..... "ለምኑ?" ..... "ጓደኛዬ ... ባልሆነ ነገር ጠርጥሬህ ነበር፡፡ የምትመክረኝን ነገር አልሰማ ብዬ በሌለህበት ባንተ ጉዳይ መጥፎን ሳስብ ነበር፡፡ አሁን ግን በጣም ይቅርታ ተፀፀቻለሁ ሀምዛ..." አለዉና የሀምዛን ይቅርታ ሽቶ ጠየቀዉ፡፡ ..... "ኧረ ጓደኛዬ ... እኔና አንተ ስንት ነገር ያሳለፍን ሰዎች በዚች ትንሽ ነገር ይቀየመኛል ብለህ ፈራህ?? አብሽር ሀቢቢ ... ይቅርታም አያስፈልገዉም፡፡ አንተን ደስስስስ የሚልህ ከሆነ ግን... ልባዊ ይቅርታ አድርጌላሃለሁ፡፡" ብሎ የሀቢብን ልብ አስፈነደቃት፡፡ ዉስጡንም ረሃ ሰጣት፡፡ ይበልጥ በሀቢብ ልብ ዉስጥ ተወዳጅና ምርጥ ጓደኛዉ እንዲሆን አደረገ፡፡ ..... "በጣም አመሰግናለሁ ጓደኛዬ..." ..... "ምንም አይደል ሀቢቢ... (ጁሱን እንደ መጎንጨት ሊያደርግ እያለ)  ... ለመሆኑ ፎዚን እንዲህ የምታደርጋት ለምንድን ነዉ ሀቢቢ?" ብሎ ጠየቀዉ፡፡ ሀቢብም ከዚህ በኃላ ሀምዛን የቤቱ ጠበቃ አድርጎ ስለሳለዉ ምንም ነገር ላይደብቀዉ ለራሱ ቃል ገባ፡፡ ..... "ሀምዛ ... እ ብዙ ነዉ ሚስጥሩ አሁን ግን ከአንተ የምደብቀዉ ምንም ነገር የለም" አለዉና ፎዚን የጠላባትንና የራቀባትን ምክንያት ሊነግረዉ ከተቀመጠበት ቦታ እንደ መደላደል  አለ.... ╔═══❖•🌺🌺•❖═══╗        ክፍል 8 ከlike 👍    በኋላ    ይ  ቀ  ጥ  ላ  ል‼️ https://t.me/Melkam_liboch1
2 259
13
​​​​💞"ጤዛዉ ፍቅሬ"💞 💝በመልካም ልቦች የቴሌግራም ቻናል የቀረበ💝   ክፍል ስድስት (➏)   ✍✍(በኑዕማን ኢድሪስ)✍✍ ፎዚያ ዉስጧን እየጨነቃት፤ ምጥ እንደያዛት ድመት እየተቁነጠነጠች 'ዛሬ ደግሞ ምን ሊለኝ ይሆን' ብላ ራሷን በሀሳብ መወጠኑን ተያያዘችዉ፡፡ ጀመረ አልጀመረ እያለች አይን አይኑን ስታየዉ፡፡ ሀቢብ ደግሞ አንገቱን ወደ መሬት ቀብሮ በተረጋጋ መንፈስ ነገሩን እንዴትና ከየት መጀመረበት እንዳለበት እያሰበ ጣቶቹን ያፋትጋል፡፡ ያለወትሮዉ ያ መኮሳተርና መቆጣቱን አስወግዶታል፡፡ በዚህ መሃል አንገቱን ቀና አደረገና የፎዚያን አይን እያየ."ፎዚ..." አላት፡፡ እሷም ከስንት ጊዜ በኃላ ባሏ ስሟን አቆላምጦ ሲጠራላት በደስታ ብዛት መልሱ ጠፍቷት ልቧ ልትወጣ ደረሰች፡፡ ..."ወይዬ ሀቢቢ! ... ምን ነዉ ችግር አለ እንዴ ሁቢ?" አለችዉ፡፡ በዚህ መካከል ግን ዉስጧን ሚረብሽ ስሜት ዉል አለባት፡፡ 'ሀቢብ ዛሬ ያለወትሮዉ እንዲህ የተረጋጋዉ እንለያይ ሊለኝ ነዉ? ወይንስ ያሳለፍነዉ ከፍቅር የራቀ ህይወት ቆጭቶት በፍቅር ልቤንም ቤቴንም ሊሞላዉ ነዉ?' እያለች የዚህን ጥያቄ መልሷን ከሀቢብ ፊት ላይ ታገኘዉ ይመስል አይኗቿን አይኖቹ ላይ ተክላ ታስተዉለዋለች፡፡ ..."ፎዚዬ ብዙ እየበደልኩሽ እንደሆነ ይገባኛል...፡፡ (ንገግግሩን ቀጠለ ፎዚም ደስታ እየተሰማት ነዉ)  በርግጥ አንቺ ከእኔ የተሻልሽ ነሽ ማለቱ ይከብዳል፡፡ ምክንያቱም የሰርጋችን ...." ንግግሩን ሳይጨርስ ወዲያዉ ስልኩ አቃጨለ "ጢርርር ጢርርር...." ስልኩን ከኪሱ አዉጥቶ ደዋዬን ሲያይ 'Hamza' ይላል፡፡ 'አሁን ተለያይተን አሁን ምን አስደወለዉ' እያለ ስልኩን አነሳዉ፡፡ "ሄሎ..." አለችዉ፡፡ በሀምዛ ስልክ የደወለችዉ ሴት ነበረች፡፡ ሀቢብ ግራ በተጋባ መንፈስ .."ሄሎ..." አላት፡፡."ሀቢብ ነህ?" ብላ ጠየቀችዉ፡፡ ድምጿ መርዶ ልተትናገር እንደሆነ ያስብቃል፡፡ ሀቢብም ከምታወጣዉ ድምፅ የሆነ ችግር እንዳለ ስለተረዳ..."አዎ ሀቢብ ነኝ! ሀምዛ ምን ሆነ?" ብሎ ጠየቃት፡፡ የደወለችዉም ሴት ሀምዛ የመኪና አደጋ ደርሶበት ሆስፒታል እንዳለና ከተደወሉ ስልኮች መጀመሪያ ላይ የሱን ስልክ አግኝታ እንደደወለች ነገረችዉ፡፡ በዚህ ጊዜ ሀቢብ እምጥ ይግባ ስምጥ አልታወቀዉም፡፡ ብቻ "ምን?" ብሎ ከተቀመጠበት ፈትለክ ብሎ ተነሳ፡፡ ፎዚ የሀቢብ ድንጋጤ ግራ ስለገባት እሷም ደንግጣ "ሀቢቢ ማን ናት? ሀምዛ ምን ሆነ? ምንድን ነዉ?" እያለች በጥያቄ ስታጣድፈዉ ለፎዚ ምንም አልመለሰላትም፡፡ ፎዚም ተከትላዉ እስከ ግቢዉ በር ከሮጠች ቡኃላ ... እንደማትደርስበት ስታዉቅ ወደ ቤቷ ተመለሰች፡፡ አሁንም ቢሆን "ሀቢብ ምን ሊነግረኝ ነበር?" እያለች በሀሳብ ራሷን መወጠሩን ተያያዘችዉ፡፡ 'እንደጎዳኝና እንደበደለኝ ያዉቃል፡፡ ነገር ግን ለምን...." ብላ ራሷን ጠየቀች፡፡ አሁንም ሀቢብ ከነገራት ዉስን ቃላቶች ዉስጥ የጥላቻዉን ምክንያት ታገኘዉ ይመስል መፈለግ ያዘች፡፡  "ለምንስ ነዉ ከኔ የተሻልሽ አይደለሽም ያለኝ?.... የሰርጋችን ቀን ምን አጠፋሁኝ? ምን አይነት ችግር አገኘብኝ...?" ጥያቄ በጥያቄ ብቻ፡፡ እንደገና መለስ ብላ  የሀምዛ ሁኔታምና ምን ችግር እንደገጠመዉ አሳስቧታል፡፡ ምክንያቱም ለሀቢብ ምርጥ ጓደኛዉ ነዉ፡፡ ከዚህም በላይ ደግሞ ለትዳሯ የሚያስብላትና በሀቢብና በርሷ መካከል ስምምነት እንዲፈጠር፤ ፍቅራቸዉ እንዲጠነክር የሚተጋ ብቸኛ የልብ ጓደኛና ወዳጃቸዉ ነዉ፡፡ ... ስልኳ ካለበት አነሳችና ወደ ሀቢብ ደወለች፡፡ ስልኩ እየጠራ ነዉ ነገር ግን ስልኩን አያነሳም፡፡ "የደወሉላቸዉ ደንበኛ ጥሪ እያስተላለፉ ነዉ፡፡ እባክዎ ቆየት ብለዉ ይደዉሉ..." የምትለዉ የኮሚኒታተሯ ድምፅ ተሰማት፡፡ ስልኩን ከዘጋች በኃላ ወደ ወደ ሀቢብ መደወሉን ትታ ወደ ሀምዛ ደወለች፡፡ ..."ሄሎ አሰላሙዓለይኩም..." አለች ..."ጤና ይስጥልኝ..." የሚል ምላሽ ተሰጣት፡፡ ሴት ነበረች፡፡ ..."ይቅርታ ሀምዛ የለም እንዴ? የሀቢብ ባለቤት ነኝ" ብላ ማንነቷንም ጭምር ነገረቻትወደ.."ሀምዛ የመኪና አደጋ ደርሶበት ሆስፒታለል ነዉ፡፡" ብላ አረዳቻት፡፡ በሀሳብ ላይ ሀሳብ የሚደራረብባት ፎዚ ድነንጋጤ ተጨምሮባት ..."ምንንን?" ብላ አንባረቀች፡፡ ነርሷም ያለበትን ሆስፒታል ከነገረቻት በኃላ ሆስፒታል ለመሄድ ልብሷን ለመቀየር ወደ መኝታ ክፍሏ ገባች፡፡ ╔═══❖•🍄🍄•❖═══╗        ክፍል 7 ከlike👍 በኋላ   ይ ቀ ጥ ላ ል‼️ https://t.me/Melkam_liboch1
2 229
14
​​​​❣"ጤዛዉ ፍቅሬ"❣ 💝በመልካም ልቦች የቴሌግራም ቻናል የቀረበ💝 🍂ክፍል-➎- አምስት ❥............🍃💐💐🍃..............❥ .... ብዙ የፍቅር አይነቶች ቢኖሩም የሀቢብ አይነት ፍቅር ግን መጀመሪያዉኑም ፍቅር ሊያስብለዉ የሚችል አልነበረም፡፡ ሀምዛ በሀቢብ ንግግር ወደ መናደዱ እየሄደ ነዉ፡፡ ሀምዛ   ሀቢብና ፎዚን ሊያስማማ፤ በሁለት ባለትዳሮች መካከል የነበረን ጥላቻ አስወግዶ እርቅ ለማስፈን ነበር አካሔዱ፡፡ ነገር ግን የሀቢብ ንግግር ወደ ድርድር የሚያስገባ ሳይሆን መቃቃርን የሚፈጥር እንደ ስድቡ 'ርካሽ ቃላትን የሚመርጥ 'ርካሽነቱን የሚያንፀባርቅ ባህሪ አወጣ፡፡ ..."ጓደኛዬ (አለዉ ሀምዛ... ለዘብ ባለ ንግግር) ... እየዉልህ ሀቢብ በርግጥ አንተ ከፎዚ በፊት ብዙ ሴቶችን ታዉቃለህ፤ ከብዙ ሴቶችም ጋር ነበርክ፡፡ እነዚያ ጋር የነበርከዉ ብዙ አመታት ግን ፎዚ ጋር እንዳለህ የትዳር ዘመን የተባረከ ሳይሆን የረከሰ ጊዜ ነበር፡፡ ፎዚ ጋር አዲስ ህይወት ከጀመርክ ሰነባበትክ የመጀመሪያ ሰሞን ደስተኛ ነበርክ፡፡ አሁን ምን ተፈጥሮ ነዉ የተቀየርከዉ ሀቢብ...!?" ብሎ ጠየቀዉ፡፡ ሀምዛ በሚያወራበት ጊዜ ግን የሀቢብ ሀሳቡ በሙሉ በጥላቻ የመረዘዉ ልቡን ተጠቅሞ ጥላቻን እየሰነቀ ነበር፡፡ ....."ሀቢብ!!? ሄይ... ወደ የት ነጎድክ?" አለዉ ከተጓዘበት አለም እየመለሰዉ፡፡ ....."ሀምዛ እየሰማሃኝ ነዉ፡፡ አንተ ፎዚን ልትወዳት ትችላለህ እኔ ግን... እጠላታለሁ?" ሀምዛ የሀቢብ ነገር አዝማሚያ የገባዉ ይመስላል፡፡ ሀቢብ ወሬዉን ቀጠል አደረገና፡፡ ..."ለመሆኑ ከፎዚ ጋር ከመቼ ጀምሮ ነዉ መገናኘት የጀመራችሁት?" ..." ያዉም እኔ ባለቤቷ ሳላዉቅ?? ... እ??" ብሎ ዉስጡ ያለዉን ስሜት ቀስ እያለ ያወጣዉ ጀመር፡፡ "ሀቢብ.." አለዉ ሀምዛ በተምስጦ አይኑን እየተመለከተ ..."የኔና ያንተ ጓደኝነት ዛሬ አልተጀመረም፡፡ ፎዚያን ከማግባትህ በፊት ብዙ ችግሮችንና ፈተናዎችን አሳልፈናል፡፡ አያሌ የደስታ ቀኖችን አብረን ቦርቀናል፡፡ እኔም እነዚያን መልካም ጊዜዎች በማስታወስ የተለመደዉን የጓደኝነቴን ከጎንህ ልሆን ስለፈለኩኝ፣ ትዳርህ የሰመረና በባለቤትህ ደስተኛ እንድትሆን እንጂ ሌላን ነገር አስቤ አልነበረም፡፡" ብሎ መለሰለት በተረጋጋ መንፈስ፡፡ ሀቢብ ግን ለትዳሩ መስመር፣ ለህይወቱ መቃናት የሚጥርለትን ጓደኛዉን ዛቻም ጭምር እየተናገረዉ ነዉ፡፡ ..."ሰማሃኝ ሀምዛ... ምንም እሰብ ምን ከዚያች ሴት ሴት ጋር ያለህ ግንኙነት ጤነኛ አይደለም፡፡" አለዉ፡፡ መደዋወላቸዉንና ግንኙነታቸዉን እንዲያቋርጥ በማስጠንቀቅ፡፡ ..."እሺ ይቅርታ ጓደኛዬ...." ብሎ ከሀቢብ ጋር የያዘዉ ሙግት መፍትሄ እንደሌለዉና እንደማይበገርለት አወቀ፡፡ . . . ..... ፎዚ የቤቱ ስራ አድክሟት  ምንም ሳትተጣጠብ በስራ ልብሷ ቤቷ ቁጭ የማትመለስበት በሚመስል ያለፈ ትዝታዋ ላይ ተተክላ በሀሳብ ባህር ሰምጣለች፡፡ የትዝታን ቅኔ እያዜመች፤ እጆቸቿን አገጯ ላይ እንዳስደገፈች አይኖቿ ላይርገበገቡ ምለዉ የልጅነት ምኟቷን፤ የኮረዳነት ደስታዋን ማስታወስ ይዛለች፡፡ አሁን የተማረረችበትን ህይወት በትዝታ እንኳ ትደሰትበት እንጂ...፡፡ በዚህ መካከል ሀቢብ ከጓደኛዉ ሀምዛ ጋር የነበራቸዉን እሰጥ አገባ ጨርሰዉ ባለመስማማት ተለያይተዉ ወደ ቤቱ መጣ፡፡ ቤቱ እንደደረሰ በሩን ሳያንኳኳ ከፍቶ ገባ፡፡ ፎዚያ ከበሩ ፊት ለፊት ሶፋዉ ላይ ተቀምጣ ሀቢብ በሩን ከፍቶ ሲገባ አላስተዋለችዉም፡፡ ደትዝታን ባህር እየቀዘፈች ነበርና አዮታዉ ሳታየዉ ቀረች፡፡ አይኖቿ ሀቢብን በር ከፍቶ ሲገባ ቢያዩትም ልቧ ከትዝታዋ ጋር ነበርና ሳታስተዉለዉ ቀረች፡፡ 'ልብ ካላዬ አይን አያይም' አይደል ተረቱስ፡፡ ሀቢብ የበሩን እጄታ ይዞ መልሶ ከዘጋ በኃላ እየተንጎራደደ ወደ ፎዚያ ተጠጋ፡፡ እሷ ግን አሁንም አላየችዉም፡፡ ወደ እሷ የሚጠጋዉ ሰዉ ይሁን ሌላ ነገር አላስተዋለችዉም፡፡ ወደ እሷ ተጠግቶ ከተቀመጠችበት ሶፋ ፊት ለፊቷ ካለዉ ሶፋ ተቀምጦ ..."ፎዚ አላት" እሷ ግን አልሰማችዉም፡፡ አዉቃ ዝም እንዳላለችዉና በሀሳብ  እንደተዋጠች በአቀማመጧና ከሁኔታዋ አስተዉላሏል፡፡ እጁን በፊቷ ላይ እየወዘወዘ "ሄይይ ኧረ ፎዚ..." ሲላት ፎዚያ ከእንቅልፏ እንደሚነቃ አይነት ሰዉ ብትት ብላ ..."  እ ሀቢቢ መጥተሃል እንዴ? ልብስ ሳጥብኮ ቆይቼ ድክም ብሎኝ ነዉ፡፡" እያለች ክስም ብሎ የነበረ ፊቷን በፈገግታ አደመቀችዉ፡፡ ሀቢብም ለጠጥ ብሎ ሶፋዉን እንደ መደገፍ እያለ ..."እ ... ነዉ?" ብሎ ወሬዉን አሳጠረዉ፡፡ ..."አዎ! ሁቢ ደግሞ ሶፊ ጋር ደዉዬ ስናወራ ቆዬን" ብላ ስትነግረዉ .."ለምን እሷ ጋር ደወልሽ?" ብሎ ጮኸባት፡፡ (ሶፊያ የሀቢብ እህት፤ የፎዚያ ደግሞ የግቢ ጓደኛዋ ናት!)፡፡ በዚህ ጊዜ ፎዚያ ደንገጥ ብላ ደህና ሆኖ የነበረዉን ለምን አሁን እንዲህ ብዬ ለምን አስከፋሁት ብላ ለራሷ አሰበች፡፡ 'ግን ሶፊ ጋር እንድደዉል ለምን አልፈለገም፡፡' ብላም ራሷን ጠየቀች እንደገና መለስ ብላ 'አይይ እንደፈለገ!' አለች፡፡ ..."ሀቢቢ የስራ ልብሴን ሳልቀይር እንኳ መጣህ... ቆይ ልብስ ቀይሬ ልምጣ" ብላ ከተቀመጠችበት ስተትነሳ ..."ተቀመጭ..." አላት፡፡ ደንገጥ ብላ ..."እ..." አለችዉ፡፡ ..."ተቀመጭ" ብሎ ቃሉን ደገመዉ፡፡ ..."እ...እ እሺ " ብላ ተቀመጠች፡፡ ፊቱ ሳይፈታ እንደተኮሳተረ ቆጣ ብሎ... ..."እንድናወራ የምፈልገዉ ጉዳይ አለ" አላት፡፡ ╔═══❖•🌺🌺•❖═══╗       ክፍል 6 ከ like በኋላ     ይ  ቀ  ጥ  ላ  ል https://t.me/Melkam_liboch1
2 608
15
​​​​❣"ጤዛዉ ፍቅሬ"❣ 💝በመልካም ልቦች የቴሌግራም ቻናል የቀረበ💝 🌿ክፍል አራት (➍)🌿 ጢርርር ... ጢርርርር..." ጥሪዉ (ደዋዩ) ማን እንደሆነ ለማየት ስልኩን ከሱሪዉ ኪስ አወጣና አየ፡፡ "Hamza" ይላል፡፡ ስልኩን ሳያነሳዉ ድምፁን ቀነሰና ጥሪዉን ድምፅ አልባ አደረገዉ፡፡ ንዴቱ ዉስጡን እያላወሰ ነበርና አይኑን ማጉረጥረጡን ቀጠለ፡፡... ..."ማን ነዉ የደወለዉ?" አላት፡፡ እጆቹን ጨብጦ ለቡጢ እያዘጋጃቸዉ፤ ሁኔታዉ ከሚስቱ ፊት ሳይሆን ከደመኛዉ ሊበቀለዉ ከሚፈልገዉ ሰዉ ፊት የቆመ ይመስላል፡፡ ፎዚያ ፈራችዉ፡፡ በዚህ ንዴቱ መምታት ከጀመራት እንደማያቆም ታዉቋት ትርበተበት ገባች፡፡ ወደ'ሷ ጠጋ እያላት ጥያቄዉን ደገመዉ፡፡ ..."ማን ነዉ የደወለዉ?... እ...?..." ፡፡ ምን ብላ ትመልስ?፡፡ ተደዉሎላት ሳይሆን ደዉላ ነዉ፡፡ 'ሀምዛ ነዉ ብለዉስ?.. ከ'ሱ ጋር ይጠረጥረኝ ይሆን?... የሚዋደዱ ጓደኛሞች በ'ኔ ምክንያት ቢጣሉስ?" እያለች ዉስጧን በስጋት ሞላችዉ፡፡ በዚሁ መካከል ሀምዛ ቅድም ደዉሎ ስላልተነሳለት በድጋሚ ለሀቢብ ደወለ ... "ጢርርርር... ጢርርርር...." የፎዚን ንዴት ስልኩ ላይ ሊወጣዉ ይመስል እጆቹን በሃይል ወደ ኪሱ ልኮ ስልኩን አወጣና  አረንጓዴዉን ተጭኖ..." ሄሎ ..." አለ፡፡ ..."ሄሎ ... ሃቢብ ብደዉልልህኮ አታነሳም" የሀምዛ ድምፅ ነበር፡፡ ከመበሳጨቱ የተነሳ ያሁኑ ደዋይ ማን እንደሆነ አላወቀዉም ነበር፡፡ ..."እ... አንተ ነህ እንዴ ሃምዛ..." ..."ስልክ ቁጥሬ ቢጠፋህ መቼም ድምፄ አይጠፋህም!" እሱ ራሱ ሃምዛ መሆኑን እያረጋገጠለት ነበር፡፡ ..."እ...ለማንሳት አልተመቸኝም ነበር" አለዉ፡፡ ..."ከፎዚ ጋር በምን ተጋጭታችሁ ነዉ?" ..."ማን ነገረህ?" ብሎ በቤቱ ዉስጥ አንገቱን አዟዙሮ ተመለከተ፡፡ 'ይሄ ሰዉዬ ተደብቆ እያየኝ ነዉ እንዴ?' ብሎ አሰበ፡፡  መጥፎ የሚሰራ ሰዉ እንኳን ሌላ ሰዉ ራሱንም ይጠራጠራል፡፡ ስራዉ እንደ ቂል አደረገዉ፡፡ ..."ፎዚ አሁን ደዉላልኝ ነበር፡፡"  ስልኩን ከጆሮዉ ስር 'ራቅ እያደረገ ወደ ኃላ እንደማፈግፈግ ብሎ ፎዚን በቆመችበት ትቷት ወደ መኝታ ክፍሉ ተመለሰ፡፡ ..."እና... ምን አባቷ ወደ አንተ አስደወላት..." አለዉ፡፡ የተጠራጠረ ይመስላል፡፡ 'ግንኙነት አላቸዉ ማለት ነዉ' ሲል አሰበ፡፡ 'በዚህ አይነትማ እስከዛሬ የምነግረዉን ለሷ ይነግራት ነበር ማለት ነዉ!' ... 'ቆይ ግን... ምንድን ነዉ ግንኙነታቸዉ?'፡፡ ሀምዛ ማሜን እየመከረዉ ነዉ፡፡ 'አትጣሉ...' እያለ የጓደኝነቱን ይነግረዋል፡፡ ሀቢብ ግን አልሰማዉም፡፡ እንደዉም ይባስ ብሎ ሀምዛን ከፎዚ ጋር መጠርጠር ይዟል፡፡ ካፉ አላወጣዉም እንጂ 'እሰራለሃላችኃለሁ' እያለ ከንፈሩን በቁጭት ይነክሳል፡፡ ..."እሺ በቃ አንጣላም ... ስንገናኝ እናወራለን!" ብሎት ስልኩ ተዘጋ፡፡ ሀቢብ ፎዚን ጠልቷታል እንዳይባል ይቀናባታል፤ ይወዳታል እንዳይባል ደግሞ ያሰቃያታል፡፡ ነገረ ስራዉ ሁሉ 'እሱ እንዲህ ነዉ!' ብሎ ለመወሰን ይከብዳል፡፡ .... ፎዚያ እራሷን ማስጨነቁን ተያያዘችዉ ..'ቆይ ሀቢብ ሊጠላኝ የቻለበት ምክንያት ምን ይሆን?' ብላ እርግጠኛ ሁና መመለስ በማትችለዉ ጥያቄ ራሷን ታፋጣለች፡፡ 'ያ የበፊቱ ፍቅርስ የት ገባ?' ...'ሶፊ ስለ ሀቢብ ጥሩነት እንጂ አንድም ቀን መጥፎነቱን አዉርታኝ አታዉቅም ነበር፡፡ ፍቅር መስጠት እንደሚችል እንጂ ልቡ በጥላቻ የጠቆረ መሆኑን አልነገረችኝም ነበር፡፡' ነበር... ነበር ... ነበር... እያለች እራሷን ወደ ኃላ እየጎተተች ሀቢብን የተዋወቀችበትን የምርቃን ጊዜዋን አማረረች፡፡ ያን በደስታ የተፍነከነከችበትን ቀን ረገመችዉ፡፡ 'ቆይ ግን ምን አጉድየበት ተቀየረ?'.... ጥያቄ በጥያቄ ላይ ብቻ መልሱን አታዉቀዉም፡፡ ብታዉቀዉ ግን ደስ ይላታል፡፡ ምክንያቱም ራሷን በራሷ ያፋጠጠችበትን ጥያቄ መልስ ከተመለሰላት ትዳሯ ይሰምራል፤ ፍቅሯ ያብባል ስለዚህ ለራሷ ለህይወቷ ስትል መሆን ያለባትን ሁና፤ መክፈል ያለባትን መስዋእትነት ከፍላ ደስታዋ እንደገና መለምለም አለበት፡፡ . ... ሀቢብና ሀምዛ ሁሌም ከሚገናኙበት ዘቢብ ካፌ ተገናኝተዉ እየተጨዋወቱ ነዉ፡፡ ሀቢብ ዉስጡ ልቡ በጥላቻ ከመጥቆሩም በላይ ከርፍቷል፡፡ የገዛ ጓደኛዉን ሀምዛን በፊት በሚወዳት ዛሬ ምክንያቱ ባልታወቀ ምክንያት ከሚጠላት ሚስቱ ጋር ጠርጥሮታል፡፡ በጨዋታቸዉ መካከል እየተሳሳቁ ቢያወሩም የሃቢብ ሳቅ የማስመሰል ግልፈጣ፤ የሀምዛ ግን ከልቡ የሚመጣ ነበር፡፡ ሀምዛ ቀስ እያለ ወደ ቁምነገሩ እየተንደረደረ ነዉ፡፡ ..."ታዉቃለህ ግን ሀቢብ?" ..."ምኑን ነዉ የማዉቀዉ?" አለዉ፡፡ ግንባሩን አጨማዶ፡፡ ሀምዛም ቀጥታ ስለ ፀቡ አንስቶ ይበልጥ ከሚያበሳጨዉ ምናልባት ያንን ጣፋጭ የፍቅር ጊዜዉን አስታዉሸዉ ልቡ ቢለዝብ ብሎ አሰበ፡፡ ..."ያንን የፍቅር ጊዜህን፡፡ በፍቅር ክንፍ ብለህ ከፎዚ ዉጭ ማሰብም ሆነ ማለም ያቆምክበት..." እያለ ስለ መልካም የፍቅር ጊዜዉ ሊያስታዉሰዉ ሲሞክር ሀቢብ የሃምዛን ወሬ አቋረጠና... ..."እ... አዎ ትዝ አለኝ!" ብሎ ወሬዉን ከመቀጠሉ በፊት ተንፈስ ሲል ሀምዛ ወደ በፊት አቋሙ ሊመለስልኝ ነዉ በማለት ልቡን ደስታ ተሰምቶት ጥርሶቹ ታዩ፡፡ ፈገግ አለ፡፡ ሀቢብም ያዘዉን ማኪያቱ ፉት ብሎ አፉን በማኪያቶዉ ቃና ካጣጣመ በኃላ ወሬዉን ቀጠለ... ..."እርካሽ መሆኗን ባዉቅ ኑሮ በፍቅር ቅልጥ ባላልኩላት ነበር፡፡" ብሎ ፈግጎ የነበረዉን የሀምዛን ፊት ወዲያዉ አከሰመዉ ╔═══❖•🌺🌺•❖═══╗        ክፍል 5 ከlike👍 በኋላ       ይ  ቀ  ጥ  ላ  ል https://t.me/Melkam_liboch1
2 855
16
​​​​​​❣ጤዛዉ ፍቅሬ"❣ 💝በመልካም ልቦች የቴሌግራም ቻናል የቀረበ💝   💐ክፍል ሶስት 💐   ....ፎዚ 'አሁን ደግሞ ምን አጠፋሁ?' ብላ የሀቢብ ሁኔታ አስጨነቃት፡፡ ከእለት ወደ እለት ለሷ ያለዉ ጥላቻ እየጨመረ መሄዱ ሃሳብ ገባት፡፡ እንዲህ አምራና ተዉባ ስጠብቀዉ 'የኔ ቆንጆ ዛሬ ደግሞ ይበልጥ አምሮብሻል' እንዲላት ነበር የፈለገችዉ፡፡ እሱ ግን ማሞገስ፤ ዉበት ማድነቅ የሚባለዉ ሃሳብ ሊመጣለት ቀርቶ እሷን መሸሽና እንደ ቆሻሻ ይርቃታል፤ ይፀየፋታል፡፡ ለዚህ ነገር መፍትሄ ማበጀት እንዳለባት አምና የሀቢብን የልብ ጓደኛ ሀምዛን ማማከር እንዳለባት ወሰነች፡፡ ምክንያቱም ሀቢብን ወደ ቀድሞዉ ፍቅሩ መመለስ ካልቻለች ትዳራቸዉ ገደል ስር እንደበቀለ ዛፍ በጊዜ ቆይታ ብዛት ተመንጉሎ እንደሚወድቅ ታዉቋታል፡፡ በፀብ የጠነከረ ትዳር፤ በንትርክ የተገነባ ፍቅር፤ በመቃቃር የተዋቀረ መዋደድ እንደሌለ ታዉቃለችና፡ . ... ሀምዛ የሀቢብ የልብ ጓደኛዉ ነዉ፡፡ ሁለቱ ጓደኛሞች (ሀቢብና ሀምዛ) መካከል ሚስጥር የሚባል ነገር የለም፡፡ እናም የሀቢብን የባህሪ መቀየር ሀምዛ ሊያዉቀዉ ይችላል በሚል ስልኳን አነሳችና የሃምዛን ቁጥር ጽፋ ደወለች፡፡ ስልኩ እየጠራ ነዉ፡፡ ሀምዛ ስልኩን አነሳና የፎዚ ጥሪ እንደሆነ በቁጥሩ ስላወቀ... ..." ሄሎ ፎዚ..." አላት፡፡ ..."አሰላሙዓለይኩም ሀምዛ... እንዴት ነህ?" ድምፅዋ ለቅሶዋን አቋርጣ የደወለች ሀዘንተኛ አስመስሏታል፡፡ ..."ወአለይኩም ሰላም ፎዚ ...ምን ሁነሻል?" ብሎ ጠየቃት፡፡ ልትደብቅዉ ያልቻለችዉ የዉስጥ ሀዘን እንዳለባት ያስታዉቅባታል፡፡ ፎዚም እየሆነች ያለችዉንና የሀቢብን የባህሪ መቀየር ለመንገር ስለደወለች ልትደብቀዉ ወይም በዝምታ ልታልፈዉ አልፈለገችም፡፡ ለሃምዛ ከመንገሯ በፊት ግን ዉስጧ ያለዉን ስሜቷን ትንፋሿ ቀድመዉ ነገሩት፡፡ "እህህህህ..." አለች፡፡ ሳታስበዉ ነበር በረጅሙ የተነፈሰችዉ፡፡ ..."ምነዉ ፎዚ?... ከሀቢብ ጋር ተጣላችሁ እንዴ?" ብሎ ከምትቀዝፈዉ የሀሳብ ባህር ዉስጥ አናጠባት፡፡ ..."ሀምዛ... (ብላ ጠራችዉና ለማዳመጥ ዝግጁ እንደሆነ ስታዉቅ ተንፈስ ብላ ንግግሯን ቀጠለች... ) ... ከሀቢብ ጋር እንደምንጣላ ታዉቃለህ እንዴ?" ብላ ጠየቀችዉ፡፡ ሀምዛ ያላሰበዉን ጥያቄ ስትጠይቀዉ ደንገጥ አለና... ..." ፎዚ ... ሀቢብ ጓደኛዬ እንደሆነ ታዉቂ የለ? ሁሌም ቤቱ ዉስጥ ስለተፈጠረዉ ነገር አይደብቀኝም" አላት፡፡ ..." ለምን ተገናኝተን አናወራም?" ብላ የትዳሯን አሳሳቢነትና አስጊ ሁኔታ ላይ እንዳለ ልትነግረዉ ፈለገች፡፡ በዚሁ ቅፅበት ግን ሀቢብ ሌላዉን ሁሉ የስልክ ንግግር ሳይሰማ "ለምን ተገናኝተን አናወራም?" የምትለዋን ቃል ሰይጣን ለጆሮዉ አቀበለዉ፡፡ ..."ምን? ... ከማን ጋር ነዉ የምትገናኘዉ?" ብሎ ጋደም ካለበት አልጋ ዘሎ ተነሳና ፎዚያ ወዳለችበት ክፍል ተጣደፈ፡፡ ልክ እሷ ጋር እንደደረሰ ከሀምዛ ጋር የሚገናኙበትን ቦታና ሰአት ተነጋግረዉ ስልኩን እየዘጋችዉ ነበር፡፡ እሷ ጋር እንደደረሰ አይኖቹ ሊወጡ ምንም አልቀራቸዉም፡፡ አፈጠጠባት፡፡ ፎዚ ፈራችዉ፡፡ ምን ትበለዉ? ምታወራዉ አጣች፡፡ ፊቷ የቆመዉ የምትወደዉና ዛሬ ቢቀየርም ድሮ የሚወዳት ባልሽ አልመስልሽ አላት፡፡ እሷን ለመደብደብ፤ ህይወቷን ለማበሳቆል፤ ትዳሯን ለማተራመስ፤ ኑሮዋን ለማዘባረቅ የተላከ 'ሰይጣን' ተመሰለባት፡፡ ሀቢብም ንዴቱ ምንም ሊያነጋግረዉ አልቻለም፡፡ አይኖቹ የሆነ ኢንች ያክል ቦታቸዉን ለቀዉ ወደ ፊት ወጣ ያሉ ይመስላሉ፡፡ ጉንጮቹ ተለጠጡ፤ ግባሩ ላይ የተጋደሙት መስመሮች የዘጠና አመት አዛዉንት አስመሰሉት፡፡ ኩስትርትር ብሏል፡፡ ሊመታትም ይቃጠዋል፡፡ በዚህ መሃል ጓደኛዉ ሀምዛ ደወለለት ... "ጢርርር ጢርርር..... ❥..........🍃💐💐🍃............❥ ክፍል 4  ከ100like👍 በኋላ   ይ  ቀ  ጥ  ላ  ል https://t.me/Melkam_liboch1
2 751
17
​​​​​​❣" ጤዛው ፍቅሬ"❣ 💝በመልካም ልቦች የቴሌግራም ቻናል የቀረበ💝 🍄ክፍል ሁለት (➋)🍄 ....... የሃቢብ ስድብ በየቀኑ ቢብስም ፎዚ ግን ቁብ ሳሰጠዉ እሱን ከማፍቀር አላስቆማትም ነበር፡፡ እየሰደባት ትወደዋለች፡፡ ከምንም በላይ የማትረሳዉ ነገር ቢኖር... አንድ ቀን ከስራ መመለሻዋ ሰአት ደርሶ ወደ ቤት እየሄደች ስልኳ ከቦርሳዋ ዉስጥ ሆኖ ይጠራ ነበር፡፡ ፎዚ አልሰማችዉም፡፡ በምትሄድበት መንገድ ዳር የነበረዉ ጫጫታና ሁካታ የስልኩን ድምፅ ሊያወጣዉ ስላልቻለ ፎዚ ስልኩን አንስታ ጥሪዉን ሳታስተናግድ ቀረች፡፡ ቤቷ እንደደረሰች ሃገር አማን - ቤቴ ሰላም ብላ የቤቷን የበር ቁልፍ ከፖርሳዋ አዉጥታ ስትሞክር እንዳጋጣሚ ሆኖ በሩ ክፍት ነበር፡፡ ሀቢብ ቀድሞ እንደገባ ስለተረዳች ሀሳቧን ሁሉ በሩ ላይ ጥላ ባሏን በአንዲስ መንፈስ ለመገናኘት በሙሉ ፈገግታና በሚያስቀና ደስታ እየተፍነከነከች የበሩን እጄታ ይዛ ከፈት ስታደርገዉ ያላሰበችዉ ነገር ገጠማት፡፡ ... ጣቶቹ ከብረት የጠነከሩ የሚመስሉ ሸካራ መዳፍ የፎዚ ፊት ላይ አረፈ "ጯ........." አይኗ እስኪሸፈን፤ የጉንጯ ቆዳ እስኪገፈፍ በጥፊ መታት፡፡ በድጋሜ 'ጯ...........'፡፡ ሀቢብ ነበር፡፡ "ለምንድን ነዉ ስልክ ያላነሳሽዉ?" በሚል ጥያቄ አንባረቀባት፡፡ ፎዚ አይኖቿን በግድ ከገለጠቻቸዉ በኃላ በፍርክርክ መዳፎች ጥፊ የቆሰለዉን ጉንጯን በእጆቿ እያሻሸች፤ ለማልቀስ እየዳዳት አይኖቿ በመቅፅብት እምባ አዝለዉ በለሆሳስ ድምፅ ... " ደዉለህ ነበር እንዴ?" አለችዉ፡፡ ሁሌም በመጥፎ ይጠረጥራት ኑሯልና... "አሃ... አንቺ ከማንም ወንድ ጋር እየዘለልሽ አዉቀሽ ያላነሳሽዉን ልትዋሺ ነዉ??" ብሎ ደም ማንባት በቀራቸዉን አይኖቹ አፈጠጠባት፡፡ አይኖቹ ቀልተዉ ነበር አይገልፃቸዉም፡፡ ደም የለበሱ፤ በርበሬ የጎረሱ መስለዋል፡፡ ሞባይሏን ለማዉጣት እጇን ወደ ፖርሳዋ እየሰደደች "ወላሂ አልዋሸሁህም" አለችዉ፡፡ "ዝምም በይ .. ቀጣፊ!" ብሎ ጥፊዉን ሊደግመዉ ቃጣዉ፡፡ . ... ፎዚያ በሃቢብ ከቦክስ ያላነሰ ጥፊ ጉንጯ ላይ ጠባሳ የቀረ ይመስል ይሄን ክስተት አረሳችዉም ነበር፡፡ ይሁን እንጂ ፍቅሩ በልጦ፤ መዉደዷ ገጦ ይበልጥ ነበርና ሁሉንም ይሁን ብላ በተቀበለችበት፤ ፀቡንም ነገሩንም ወደ ፍቅር ለዉጣ ትዳሯን አቆይታለች፡፡ . ...የሀቢብን መጥፎ ጥርጣሬ ለማስወገድ ስትል የድሮዉ ፍቅሩን ቢመልሰዉ ብላ ከምትሰራበት መስሪያ ቤት የመልቀቂያ ደብዳቤ እንኳ ሳታስገባ ለቀቀች፡፡ ምክንያቷ ደግሞ በተደጋጋሚ ከመስሪያ ቤት ወንዶች ጋር ትቀብጫለሽ 'እኔን ቀይረሽኛል' እያለ መዉጫ መግቢያ ሲያሳጣት፤ በቤቷ ዉስጥ ሰላም ሲነሳት 'ወጥቼ እንድሰራ ካልፈለክና ካላስደሰተህ ቤቴ እዉላለሁ' ብላዉ ባሏን ለመንከባከብ ለሀቢብ ካላት ሙሃባ የተነሳ ስራዋን እርግፍ አድርጋ ትታ ቤት ዉላለች፡፡ . ....... ይሄን ዱላና ተዳጋጋሚ የሆነዉ ስድቡ (ቀጣፊ...ዉሸታም...) ሳይከብዳት ዛሬ የተነፈሳት "እርካሽ" ያላት 'ርካሽ' ቃል ፎዚን እያነፋረቀ ያስለቅሳታል፡፡ 'እኔ ነኝ?... እኮ እኔ?... እኔ ነኝ እርካሿ?" እያለች ታላዝናለች፡፡ የኔ ዉድ የሚለዉ ጥሪዉ ባንዴ ተወግዶ፤ የፍቅር ቃላቶች እንደ ስደተኛ ርቆ ተሰዶ ቤታቸዉ የፀብ አዉድማ ሁኗል፡፡ ሰሞኑን ያመጣዉ አዲስ ፀባይ ደግሞ ፎዚን እየተፈታተናትና ትዳር እንዲያንገሻግሻት ሊያደርጋት ምነንም አልቀሯትም፡፡ ለሱ ብላ ስራ እንዳቆመች፤ በፀብ የጠለሸዉን ትዳር ወደ ፍቅር ለመቀየር እየተጋች ባለበት ወቅት......"እኔ ማመጣዉን ተቀምጦ መብላት አይከብድሽም?" ይላት ጀምሯል፡፡ ምንም አትመልስለትም ይልቁንስ በሱ መጥፎ ንግግርና ፀያፍ ተግባሩ ብትማረርም ሀቢብን መንከባከቧ ከእለት ወደ እለት ጨምሯል፡፡ ከስራ መመለሻዉ ሰአት ሲደርስ በሚያማምሩ ልብሶች ተሽቀርቅራ፤ እሱን በሚያማልሉ ነገሮች ተዉባ፤ እሱዉ በመረጠዉ ሽቶ ጠረኗን አዉዳ ትጠብቀዋለች፡፡ ..."... ሀቢቢ እንኳን ደህና መጣህልኝ!" ብላ እቅፏ ዉስጥ ልታስገባዉ እጇን ስትዘረጋ፤ የዘረጋችዉን እጇቿን በእጆቹ ገፍትሮና አመናቅሮ ... ..."አንቺማ በደህና እንድመለስ አትፈልጊም ነበር... ያዉ ተመለስኩ" ብሎ ነገሩን ይጀምረዋል፡፡ አሁንም ግን... ነገሩን ወደ ነገር ቀይራ ቤቱን በፀብ ቦንብ ማጋይት ስለማትፈልግ በሙሉ ፈገግታ ፈግጋ ወደ'ሱ ጠጋ እያለች... ..." ሀቢቢ ንፍቅ ብለኸኛል!" ትለዋለች፡፡እንደምታፈቅረዉ ያዉቃል፡፡ ነገር ግን እሱ ጸቡን ስለሚፈልገዉ የሷ የፍቅር ቃል አይረታዉም፡፡ "ሀቢቢ...፤ የኔ ማር...፤ የኔ ፍቅር...፤ ዉዴ..." እያለች የምትጠራዉ ነገር አይዋጥለትም፡፡ አጠገቡ ከተቀመጠች በኃላ ፀጉሩን እያሻሸች "ምን ሁነህብኝ ነዉ ዉዴ?" አለችዉ፡፡ እጆቿን ከፀጉሩ ላይ እያነሳ "ለምን ትነኪኛለሽ?" ብሎ አይኑን ጎለጎለባት፡፡ ፎዚ ይብስ እንዳይናደድ ብላ ዝም አለችዉ፡፡ ብቻ በስስት እያየችዉ አይኖቿን አይኖቹ ላይ ታንከባልላቸዋል፡፡ ግንባሩ ተጨማዶ ተኮሳትሮና ተቆጥቶ ከተቀመጠበት ምንጥቅ ብሎ ተመናጭቆ ተነሳና ወደ መኝታ ክፍሉ ገባ፡፡ በአስተያየቷ ተናዷል፡፡ የፍቅሯ ሃያልነት አፉን ዘጋዉ እንጂ በስስት የምታዬዉን ሚስቱን "ምን ታፈጫለሽ?" ማለትም አስቦ ነበር ። ❥..........🍃💐💐🍃............❥ ክፍል 3 ከ150 like በኋላ ይ  ቀ  ጥ  ላ  ል‼️ https://t.me/Melkam_liboch1
0
18
​​​​​​❣" ጤዛው ፍቅሬ"❣ 💝በመልካም ልቦች የቴሌግራም ቻናል የቀረበ💝 🍄ክፍል ሁለት (➋)🍄 ....... የሃቢብ ስድብ በየቀኑ ቢብስም ፎዚ ግን ቁብ ሳሰጠዉ እሱን ከማፍቀር አላስቆማትም ነበር፡፡ እየሰደባት ትወደዋለች፡፡ ከምንም በላይ የማትረሳዉ ነገር ቢኖር... አንድ ቀን ከስራ መመለሻዋ ሰአት ደርሶ ወደ ቤት እየሄደች ስልኳ ከቦርሳዋ ዉስጥ ሆኖ ይጠራ ነበር፡፡ ፎዚ አልሰማችዉም፡፡ በምትሄድበት መንገድ ዳር የነበረዉ ጫጫታና ሁካታ የስልኩን ድምፅ ሊያወጣዉ ስላልቻለ ፎዚ ስልኩን አንስታ ጥሪዉን ሳታስተናግድ ቀረች፡፡ ቤቷ እንደደረሰች ሃገር አማን - ቤቴ ሰላም ብላ የቤቷን የበር ቁልፍ ከፖርሳዋ አዉጥታ ስትሞክር እንዳጋጣሚ ሆኖ በሩ ክፍት ነበር፡፡ ሀቢብ ቀድሞ እንደገባ ስለተረዳች ሀሳቧን ሁሉ በሩ ላይ ጥላ ባሏን በአንዲስ መንፈስ ለመገናኘት በሙሉ ፈገግታና በሚያስቀና ደስታ እየተፍነከነከች የበሩን እጄታ ይዛ ከፈት ስታደርገዉ ያላሰበችዉ ነገር ገጠማት፡፡ ... ጣቶቹ ከብረት የጠነከሩ የሚመስሉ ሸካራ መዳፍ የፎዚ ፊት ላይ አረፈ "ጯ........." አይኗ እስኪሸፈን፤ የጉንጯ ቆዳ እስኪገፈፍ በጥፊ መታት፡፡ በድጋሜ 'ጯ...........'፡፡ ሀቢብ ነበር፡፡ "ለምንድን ነዉ ስልክ ያላነሳሽዉ?" በሚል ጥያቄ አንባረቀባት፡፡ ፎዚ አይኖቿን በግድ ከገለጠቻቸዉ በኃላ በፍርክርክ መዳፎች ጥፊ የቆሰለዉን ጉንጯን በእጆቿ እያሻሸች፤ ለማልቀስ እየዳዳት አይኖቿ በመቅፅብት እምባ አዝለዉ በለሆሳስ ድምፅ ... " ደዉለህ ነበር እንዴ?" አለችዉ፡፡ ሁሌም በመጥፎ ይጠረጥራት ኑሯልና... "አሃ... አንቺ ከማንም ወንድ ጋር እየዘለልሽ አዉቀሽ ያላነሳሽዉን ልትዋሺ ነዉ??" ብሎ ደም ማንባት በቀራቸዉን አይኖቹ አፈጠጠባት፡፡ አይኖቹ ቀልተዉ ነበር አይገልፃቸዉም፡፡ ደም የለበሱ፤ በርበሬ የጎረሱ መስለዋል፡፡ ሞባይሏን ለማዉጣት እጇን ወደ ፖርሳዋ እየሰደደች "ወላሂ አልዋሸሁህም" አለችዉ፡፡ "ዝምም በይ .. ቀጣፊ!" ብሎ ጥፊዉን ሊደግመዉ ቃጣዉ፡፡ . ... ፎዚያ በሃቢብ ከቦክስ ያላነሰ ጥፊ ጉንጯ ላይ ጠባሳ የቀረ ይመስል ይሄን ክስተት አረሳችዉም ነበር፡፡ ይሁን እንጂ ፍቅሩ በልጦ፤ መዉደዷ ገጦ ይበልጥ ነበርና ሁሉንም ይሁን ብላ በተቀበለችበት፤ ፀቡንም ነገሩንም ወደ ፍቅር ለዉጣ ትዳሯን አቆይታለች፡፡ . ...የሀቢብን መጥፎ ጥርጣሬ ለማስወገድ ስትል የድሮዉ ፍቅሩን ቢመልሰዉ ብላ ከምትሰራበት መስሪያ ቤት የመልቀቂያ ደብዳቤ እንኳ ሳታስገባ ለቀቀች፡፡ ምክንያቷ ደግሞ በተደጋጋሚ ከመስሪያ ቤት ወንዶች ጋር ትቀብጫለሽ 'እኔን ቀይረሽኛል' እያለ መዉጫ መግቢያ ሲያሳጣት፤ በቤቷ ዉስጥ ሰላም ሲነሳት 'ወጥቼ እንድሰራ ካልፈለክና ካላስደሰተህ ቤቴ እዉላለሁ' ብላዉ ባሏን ለመንከባከብ ለሀቢብ ካላት ሙሃባ የተነሳ ስራዋን እርግፍ አድርጋ ትታ ቤት ዉላለች፡፡ . ....... ይሄን ዱላና ተዳጋጋሚ የሆነዉ ስድቡ (ቀጣፊ...ዉሸታም...) ሳይከብዳት ዛሬ የተነፈሳት "እርካሽ" ያላት 'ርካሽ' ቃል ፎዚን እያነፋረቀ ያስለቅሳታል፡፡ 'እኔ ነኝ?... እኮ እኔ?... እኔ ነኝ እርካሿ?" እያለች ታላዝናለች፡፡ የኔ ዉድ የሚለዉ ጥሪዉ ባንዴ ተወግዶ፤ የፍቅር ቃላቶች እንደ ስደተኛ ርቆ ተሰዶ ቤታቸዉ የፀብ አዉድማ ሁኗል፡፡ ሰሞኑን ያመጣዉ አዲስ ፀባይ ደግሞ ፎዚን እየተፈታተናትና ትዳር እንዲያንገሻግሻት ሊያደርጋት ምነንም አልቀሯትም፡፡ ለሱ ብላ ስራ እንዳቆመች፤ በፀብ የጠለሸዉን ትዳር ወደ ፍቅር ለመቀየር እየተጋች ባለበት ወቅት......"እኔ ማመጣዉን ተቀምጦ መብላት አይከብድሽም?" ይላት ጀምሯል፡፡ ምንም አትመልስለትም ይልቁንስ በሱ መጥፎ ንግግርና ፀያፍ ተግባሩ ብትማረርም ሀቢብን መንከባከቧ ከእለት ወደ እለት ጨምሯል፡፡ ከስራ መመለሻዉ ሰአት ሲደርስ በሚያማምሩ ልብሶች ተሽቀርቅራ፤ እሱን በሚያማልሉ ነገሮች ተዉባ፤ እሱዉ በመረጠዉ ሽቶ ጠረኗን አዉዳ ትጠብቀዋለች፡፡ ..."... ሀቢቢ እንኳን ደህና መጣህልኝ!" ብላ እቅፏ ዉስጥ ልታስገባዉ እጇን ስትዘረጋ፤ የዘረጋችዉን እጇቿን በእጆቹ ገፍትሮና አመናቅሮ ... ..."አንቺማ በደህና እንድመለስ አትፈልጊም ነበር... ያዉ ተመለስኩ" ብሎ ነገሩን ይጀምረዋል፡፡ አሁንም ግን... ነገሩን ወደ ነገር ቀይራ ቤቱን በፀብ ቦንብ ማጋይት ስለማትፈልግ በሙሉ ፈገግታ ፈግጋ ወደ'ሱ ጠጋ እያለች... ..." ሀቢቢ ንፍቅ ብለኸኛል!" ትለዋለች፡፡እንደምታፈቅረዉ ያዉቃል፡፡ ነገር ግን እሱ ጸቡን ስለሚፈልገዉ የሷ የፍቅር ቃል አይረታዉም፡፡ "ሀቢቢ...፤ የኔ ማር...፤ የኔ ፍቅር...፤ ዉዴ..." እያለች የምትጠራዉ ነገር አይዋጥለትም፡፡ አጠገቡ ከተቀመጠች በኃላ ፀጉሩን እያሻሸች "ምን ሁነህብኝ ነዉ ዉዴ?" አለችዉ፡፡ እጆቿን ከፀጉሩ ላይ እያነሳ "ለምን ትነኪኛለሽ?" ብሎ አይኑን ጎለጎለባት፡፡ ፎዚ ይብስ እንዳይናደድ ብላ ዝም አለችዉ፡፡ ብቻ በስስት እያየችዉ አይኖቿን አይኖቹ ላይ ታንከባልላቸዋል፡፡ ግንባሩ ተጨማዶ ተኮሳትሮና ተቆጥቶ ከተቀመጠበት ምንጥቅ ብሎ ተመናጭቆ ተነሳና ወደ መኝታ ክፍሉ ገባ፡፡ በአስተያየቷ ተናዷል፡፡ የፍቅሯ ሃያልነት አፉን ዘጋዉ እንጂ በስስት የምታዬዉን ሚስቱን "ምን ታፈጫለሽ?" ማለትም አስቦ ነበር ። ❥..........🍃💐💐🍃............❥ ክፍል 3 ከ150 like በኋላ ይ  ቀ  ጥ  ላ  ል‼️ https://t.me/Melkam_liboch1
0
19
​​​​​ ❣ጤዛዉ ፍቅሬ🌿❣ 💝በመልካም ልቦች የቴሌግራም ቻናል የቀረበ💝      💘💘ክፍል አንድ💘💘 ❥..........🍃💐💐🍃...... .....የመቀሌ ዩኒቨርሲቲ የአራቱም ካምፓስ ተማሪዎች የምርቃን ፕሮግራም ለመታደም ተማሪዎች ቤተሰቦቻቸዉን ይዘዉ ከታሪካዊዉ ቦታ ተገኝተዋል፡፡ ይህ ቦታ ብዙ ሰዎች ይቺን ሃገር ለመታደግና ለመጠበቅ  ተሰግስጎባት የነበረዉን መዥገር ለመንቀል ለትግል የወጡ ጀግኖች የተቀበሩበት ቦታ 'ሀወልቲ-ሰማእታት' ነዉ፡፡ ተማሪዉቹ ደስታ ዉጧቸዉ ይፍነከነካሉ፡፡ እዚህም እዚያም ከወላጆቻቸዉ ጋር ተቃቅፈዉ ፎቶ የሚነሱ ይስተዋላሉ፤ እቅፍ አበባዎችና ሌሎች ዉድ ዉድ  ስጦታዎች ከወላጅና ከወዳጆቻቸዉ ይነጉዳሉ፡፡ በደስታ ብዛት ጥርሳቸዉ መከደን ያቃታቸዉ ተማሪዎች በዝተዋል፡፡ ከእነዚህ ተመራቂ ተማሪዎች መካከል ደግሞ ፎዚ አንደኛዋ ናት፡፡ ፌሽታ በፌሽታ ሆናለች፡፡ እንኳን ስቃ አኩርፋም እጅግ በጣም ዉብ ናት!፡፡ በዚያ ላይ ደስታዋ ሰዉነቷን፤ ፈገግታዋ ፊቷን አስዉቦት ከቤተሰቦቿ ጋር የሰማእታቱን ሀዉልት እየተጠጉ ፎቶ ይነሳሉ፡፡ ... ትንሽ እህቱን ለማስመረቅ ከአዲስ አበባ ተነስቶ የሰሜኗን ኮከብ መቀሌን የረገጣት ሀቢብ በእህቱ ጓደኛ ዉበት ፈዞ፤ ፍቅሯን አርግዞ ወደ አዲስ አበባ ተመልሷል፡፡ ፎዚ የሀቢብ እህት ጓደኛ በመሆኗ መቀሌ በቆየባቸዉ የአምስት ቀን እድሜ በደንብ ተግባብተዉና ስልክ ተለዋዉጠዉ ነዉ የተመለሰዉ፡፡ ትዉዉቃቸዉ በዚሁ ጀመረ.... ፡ ፡ ....... ሀቢብና ፎዚያ ከተጋቡ ሳምንታቶች ነጉደዉ ወራቶች ተቆጥረዋል፡፡ ፎዚን ከማግባቱ በፊት ለሁለት አመት ያክል ፍቅሩን በዉስጡ አምቆ ይዞት ለአንድ አመት ያክል ደግሞ የፍቅር ጥያቄ እያቀረበላት በመጨረሻም በጌታ ፍቃድ ተጋቡ፡፡ በጣም ይወዳታል፡፡ ሲወዳት ይወዳታል የሚለዉ ቃል ያንሰዋል፡፡ ሲያፈቅራት ያፈቅራታል የሚለዉ የፍቅር ትልቁ ቃል ሀቢብ ለፎዚያ ያለዉን ፍቅር አይገልፀዉም፡፡ ዘመኑን ሙሉ ከርሷ ጋር ሊኖር ምሎ፤ ዘላለም ላይለያት፤ በማንም ላይቀይራት ተገዝቶ ለምኗት አስለምኗት ብዙ መስዋእትነትን ከፍሎ ፎዚን የራሱ የግሉ ሊያደርጋት ችሏል፡፡ አግብቷታል፡፡  ህይወቷን በህይወቱ አቆራኝቱ የሰዉነቱ አምሳል፤ የአካሉ ክፋይ አድርጓታል፡፡ . ....... ፎዚያ የልጅነት ህልሟ ለትዳር ስትደርስ ማግባት የምትፈልገዉ ወንድ በዲኑ የላቀ፤ በትምህርቱ የረቀቀ፤ ጥላቻን አድክሞ፤ ፍቅርን አጣጥሞ መስጠት የሚችል ሰዉ እንዲያገባት ትፈልግ ነበር፡፡  የአካሉ ፍላጭ፤ የችግሩ ተጋፋጭ እንዲያደርጋት መሆን ምኞቷ ነበር፡፡ የፀባዬ ሸጋ፤ የቁመተ ሎጋ ወንዳ ወንድነትን ተላብሶ በሱና የደመቀ፤ በዒባዳ ለጌታዉ የወደቀ ሰዉ እንዲዘዉጃት- የዚያ ሰዉ ሚስት መሆን አቅዷ ነበር፡፡ . ....... ሁሌም ቢሆን አላህ የፈለገዉና የወሰነዉ ተግባር ላይ  ይዉላል እንጂ ሰዉ የፈለገዉን አያገባም፡፡ ሰዉ ያቀደዉን አይኖርም፡፡ ለህይወቱ ስኬት የቀየሰዉን መንገድ አይጓዝበትም፡፡ ሁሉም የአላህ ዉሳኔና የጌታ መሻት ናቸዉ፡፡ በዚህም ፎዚያ የልጅነትን ህልሟን በሚያኮላሽ መልኩ ስትመኘዉን የነበረ ነገር ሁሉ ሳይሳካላት በተቃራኒዉ የሆነዉን ሀቢብን አገባች፡፡ . ...... በርግጥ ሀቢብ የዲን እዉቀትም የለዉም፤ እንዲኖረዉም ጥረት አድርጎ አያዉቅም፡፡ ሶላት ሊሰግድ ቀርቶ የሶላት ጥሪ /አዛን/ ሲሰማ ያንገሸግሸዋል፡፡ ፎዚያ ይሄንን ሁሉ ተግባር ሳታገባዉ በፊት ቀድማ አዉቃ ነበር፡፡ ነገር ግን ... ፎዚን ለማግባትና ላለማጣት የራሱ ማድረግ ስለነበረበት፤ እንቡጥ ፅጌረዳ አይቶ ማለፍ ተስኖት ... 'የዲን እዉቀት የሌለኝ የቤተሰቦቼ አስተዳደግ ነዉ' እያለ ዋሻት፡፡ 'አንቺን የማገባ ከሆነ ግን ፀባዬ ይስተካከላል፤ ሶላት እጀምራለሁ፤ ቁርዓንም እቀራለሁ' ብሎ አሳምኗት የዋኀ ፎዚም ይሁን ብላ አምና ተቀብላዉ 'ባሌ ይስተካከላል፡፡ ቃል የገባልኝን ይፈፅማል' እያለች በባዶ የህልም ሩጫ ትሮጣለች፡፡ ....... በተጋቡ ከጥቂት ሳምንታት ቆይታ በኃላ ነገሩን ጀምሮት እያመሸ መግባት አዘወተረ፡፡ ከእሷ ጋር ላለማደር አልጋ እየለየ መተኛት ከጀመረ ሰነባበተ፡፡ የሚገባትን ክብርና እንክብካቤ ነፍጓት ሳያገባት በፊት ለፎዚ የነበረዉ ፍቅር በሚገርም ፍጥነት አሽቆልቁሎ በገባ በወጣ ቁጥር ባ'ፉ እያከላፈታት፤ አይኑና ፊቱ እየገለመጧት ኑሮን ከሃቢብ ጋር እየኖረች ነዉ፡፡ የሚገርመዉ ግን... ትወደዋለች፡፡ በጣም አፍቀረዋለች፡፡ ባሏን (ሀቢብ) በልቧ ዉስጥ እንደ ንጉስ አንግሳ፤ የፍቅር ካባን አልብሳ እየተንከባከበች ይዘዋለች፡፡ . .......ከእለታት ባንዱ ቀን ፎዚ መኝታ ቤቷ ዉስጥ አልጋዋ ላይ እጥፍጥፍ ብላ ተኝታ የተንተራሰችዉ ትራስ በእንባዋ ርሶ ታጥቦ እንደተጠመዘዘ ጨርቅ ረጥቧል፡፡  ... "እኔ ነኝ እርካሿ?" እያለች በመነፋረቅ አይኖቿን ቀይስር ያገመጠቻቸዉ እስኪመስል ድረስ ታነባለች፡፡ ታለቅሳለች፡፡ 'እርካሽ..." የሚለዉ የሀቢብ ስድብ በአይነ-ህሊናዋ እየተመላለሰ እንደ ገደል-ማሚት ያስተጋባባታል፡፡  "እርካሽ.... እኮ እኔ...እርካሽ....!" ❥..........🍃💐💐🍃............❥ ክፍል 2 ከ200like👍 በኋላ  ይ  ቀ  ጥ  ላ  ል‼️ https://t.me/Melkam_liboch1 ሼር🙏
0
20
ምርጥ ባህሪ🧡✅ --------- ★. ጥቂት አዉራ፡፡ ስታወራ ቀስ ብትል መልካም ነዉ ★. አንድ ቦታ ላይ ብዙ አትታይ፡፡ ስራህ ላይ አተኩር ተግባቢና የተረጋጋ ሰዉ ሁን ★. ማንም ትክክል ነህ እንዲልህ #አትጠብቅ፡፡ ማንም ደጋፊህ እንዲሆን አትጎትጉት ★. ስላለህ ነገር ደጋግመህ እየተናገርክ የመጎረር ስሜትን አስወግድ ★. ምርጥ #አዳማጭና መፍትሄ አምጪ ሁን ★. አደርገዋለሁ ያልከዉን ነገር አድርገዉ ★. በጣም ደስ ሲልህ ወይም በጣም ስታዝን ዉሳኔ #አትወስን! ★. የግል ጉዳይህን ላገኘኸዉ ሰዉ አትናገር ★. ሰዉ ስላንተ የፈለገዉን ቢያስብ ከማንነትህ ጋር አታገናኘዉ ★. ማንንም ለመጉዳት ብለህ ጉድጓድ ከመቆፈርም ይሁን ከማስቆፈር ራስህን አሽሽ ★. የጎዱህንና ‘ምንም የለዉም!’ ብለዉ የራቁህን ሰዎች ስኬታማ በመሆን አሳያቸዉ ★. ሃሳብህን ለማሳመን የሰዎችን ማንነት አትጉዳ፡፡ ትክክክል ብትሆን እንኳን ካመኑ ይመኑህ ካላመኑህ ጊዜዉ ያሳምናቸዋል መልካም ምሽት ምርጦቼ💛 https://t.me/Melkam_liboch1 ሼር አደራ
0