Mereja መረጃ
رفتن به کانال در Telegram
3 187
مشترکین
-424 ساعت
-277 روز
-10630 روز
آرشیو پست ها
3 187
ሳውዲ አረቢያ የሞት ቅጣት ከፈረደችባቸው ውስጥ 4 ኢትዮጵያውያንን ገደለች
የሳውዲ ባለስልጣናት ከ2016 ጀምሮ ቢያንስ 64 ኢትዮጵያውያንን በሞት ቅጣት ፍርድ ገድለዋል፤ ከእነዚህም ውስጥ በ2025 እና 2026 .... 44 ሰዎች ይገኙበታል። https://miniliksalsawi.substack.com/p/saudi-arabia-resumes-executions-after
3 187
ከ"ዘመቻ ህፃን አንሻ ሰይድ" ማግስት የብልፅግና ሰራዊት መፍረሱን ቀጥሏል!
ለብልፅግና የዙፋን መንበር በማወቅም ይሁን ባለማወቅ እየታተረና እየተጋ የሚገኘው ብልፅግና መራሹ ጦር በዘመቻ ህፃን አንሻ ሰይድ በከባድ ሚዛን በፋኖ ክንድ የተመታው ሰራዊት ከአሐዱ በመፍረስ ፋኖ ወደሚገኝበት ቦታ ሁሉ እየተቀላቀለ ይገኛል።
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ 303ኛ ኮር አካል የሆነውን 19ኛ ክፍለ ጦርን የተቀላቀሉት አስር አለቃ አማረ ተፈራ እና ጓደኛው ከ34ኛ ክፍለ ጦር አራተኛ ሬጅመንት በመውጣት የፋኖን ቤት የተቀላቀሉ ሲሆን መከላከያ አሁን ባለው ቁመና የመዋጋት አቅም እንደሌለውና ሰራዊቱም በፍፁም መሰላቸትና በከባድ የስነ-ልቦና ውድቀት ላይ እንደሚገኝ ገልጿል።
በሌላ መረጃ 303ኛ ግዙፉ አሳምነው ኮር አካል የሆነውን 30ኛ ክፍለ ጦርን የተቀላቀሉት የ13ኛ ዕዝ ኦፕሬተር የነበሩት:-
1ኛ. መሰረታዊ ወታደር ማርይሁን ጌታ
2ኛ. መሰረታዊ ወታደር ዮሴፍ አዱኛው
3ኛ. መሰረታዊ ወታደር ቴዎድሮስ ጥላሁን
ሁላቸውንም ቤተሰቦቻቸው ልከው ከሚያስተምሯቸው ኮሌጅ ላይ በማፈን ወደ ማሰልጠኛ በማስገባት ተገደው የገቡ እንደሆኑ ገልፀው የአገዛዙን ጓዳ ከፈተሹና ከመረመሩ በኋላ ለቤተሰቦቻችንና ወንድም እህቶቻችን ማጥፊያ ስርዓትና ተቋም አናገለግልም በማለት ፋኖን እንደተቀላቀሉ ተናግረዋል።
ስቦ በማስከዳት ስርዓቱን ከማፍረስ ጋር ተያይዞ ከመስከረም 14/2018 ዓ/ም ዘመቻ አደም አሊ (አባ ናደው)ን ጨምሮ ለተከታታይ ስምንት ወራት ከ850 በላይ የአገዛዙ ሰራዊት መከላከያ፣ አድማ ብተና፣ ፖሊስ፣ ሚሊሻና ስርዓቱን አገልጋይ ካቢኔ አባላት 303ኛ ግዙፉ አሳምነው ኮር ፋኖን የተቀላቀሉ ሲሆን አሁንም አልረፈደምና ቀሪው የአገዛዙ ሰራዊት በፍጥነት ፋኖን በመቀላቀል ህይዎቱን እንዲታደግ ሲል የኮሩ ፖለቲካ መምሪያ ኃላፊ አርበኛ በሪሁን ደምሌ ጥሪ አቅርቧል።
ምንጭ፦ የምኒልክ ዕዝ ሚዲያና ኮሚኒኬሽን መምሪያ!
3 187
የአርበኛ ሳሙኤል ባለዕድል ቤተሰቦች በፋሽስቱ አገዛዝ ታገቱ!
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ከፍተኛ አመራር አርበኛ ሳሙኤል ባለዕድል ቤተሰቦች በአገዛዙ ብልፅግና ሰኔ 2/2018 ዓ.ም ታግተዋል::
የአፋብን ስልጠና መምሪያ ሃላፊው ቤተሰቦች ማለትም ባለቤቱ እህቱና የእህቱ ባል ከህፃናት ልጆቻቸው ጋር በጅምላ ታፍነው ታስረው ይገኛሉ:: ባለፈው ጊዜ የከፍተኛ አመራሩ አጎትና የአጎቱ ልጅ በአገዛዙ በግፍ እንደተገደሉበት የሚታወቅ ነው::
ፋሽስቱ የብልፅግና አገዛዝ ህዝባቸው ላይ እየተፈፀመ ያለውን ዘር ማጥፋት ለመቀልበስ እየታገሉ ያሉ አርበኞችን ታግሎ ማሸነፍ ሲያቅተው ቤተሰቦቻቸውን በመግደል በማገትና ከሃገር እንዲሰደዱ በማድረግ ግፍ በመፈፀም ከአላማቸው ለማደናቀፍ ቢሞርም ተግባሩ ግን አርበኞችን በከፍተኛ ፅናትና ቁርጠኝነት እንዲታገሉ ከማድረግ የዘለለ ሚና የለውም::
3 187
በምኒልክ ዕዝ 104ኛ ኮር 23ኛ ክፍለ ጦር አምባሰል ላይ አንፀባራቂ ድል ተቀዳጀ!
መነሻዉን ከኩታበር ወደ ተለያዬንና ዚሃ እንዲሁም ከደላንታ በተሬ አድርጎ ወደ ዚሃ በምድር ሞርተር ፣ዙ23 እና መድፍ ሲጠቀም በሰማይ በሁለት ድሮን ታግዞ ፋኖን አጠፋለሁ በሚል የተለምዶ ቅዠቱ የመጣ ቢሆንም ጀግኖቹ ምንም ነገር ሳይበግራቸዉ እንደቃሪያ ሲያራግፉት ዉለዋል።
ዉጊያዉም ከንጋቱ 11:00 እስከ 6:00 የተደረገ ሲሆን በዚህ እልህ አስጨራሽ ውጊያ የ104ኛ ኮር 23ኛ ክ/ጦር ተናዳፊወች ዚሃ የገባውን ሃይል ሙሉ ለሙሉ የደመሰሱት ሲሆን በዚህ የተበሳጨዉ አገዛዝ በዘፈቀደ ሶስት ጊዜ ድሮን በመጣል ከጦርነቱ ተሳታፊ ያልሆኑ ንፁሀንን የጥቃቱ ሰለባ አድርጓል።
አሁን ላይ በድሮን ሽፋን በመስጠት ሬሳና ቁስለኛ እያነሳ ሲሆን ከግሸን በአባላ ለመቁረጥ ቢቀሳቀስም በንስሮቹ በደፈጣ ተመቶ ሙትና ቁስለኛውን ይዞ ወደ መጣበት ተመልሷል።
ምንጭ፦ በአፋብን ምኒልክ ዕዝ 104ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት ክፍል!
3 187
ከዚህ ቀደም የሰላም ስምምነት ተቀብያለሁ በሚል ለሁለት ዓመታት ያህል ከአገዛዙ ስንቅና ትጥቅ ሲሰፈርለት የቆየው የአገው ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (አዴን) ታጣቂ ኃይል በዋግ ኽምራ ዞን አበርገሌ እና ፃግብጂ ወረዳዎችን ሙሉ በሙሉ መቆጣጠሩን አስታወቀ!
ከሁለት ዓመት በፊት በአገዛዙና በታጣቂ ኃይሉ መካከል ተደርሶ የነበረውን የሰላም ስምምነት እራሱ አገዛዙ በመጣስ ትንኮሳ ፈፅሟል በተባለበት በዚህ ቀጠና፡ ታጣቂዎቹ ከሕወሓት ኃይሎች ጋር በመቀናጀት በወሰዱት እርምጃ ነው በሰቆጣ ዙሪያ የሚገኙ ሁለት ትላልቅ ወረዳዎችን ሙሉ በሙሉ የተቆጣጠሩት።
የዞኑ ፀጥታ ኃይሎች ከነጌታቸው ረዳ የሓራ መሬት ታጣቂዎች ጋር በመቀናጀት በአዴን ቡድን ወታደሮች ላይ አፀፋዊ እርምጃ በመውሰድ ወረዳውን ዳግም ለመቆጣጠር ያደረጉት ሙከራ ከሽፎ ከፍተኛ ኪሣራን አከናንቧቸው በውረደት እንዲሸሹ መደረጋቸው ታውቋል።
(ምስል፦ በታጣቂዎቹ ቁጥጥር ስር የዋሉ የአገዛዙ ተሽከርካሪዎች)
3 187
አፋብን በላይ ዕዝ መይሳው ካሳ ኮር 16ኛ ልባርጋቸው ሙጨ ክ/ር ግዙፍ 2ኛ ዙር ኮማንዶ የፋኖ ሰራዊት አስመረቀ!
ትናንት ሰኔ 02/2018 ጣና ብርጌድ በመባል የሚታዎቀው አደረጃጀት አሁን ላይ ከቀጠናው አቀማመጥ ለግዳጅ በሚያመች መንገድ የመፍትሔ አቅጣጫዎችን በዉል በማጤንና በመምከር ታላቁ አርበኛ ልባርጋቸው ሙጨ ያለመውን ትክክለኛ የመታገያ ሀሳብ ከዳር ለማድረስ ጥልቅ ውይይት በማድረግ የክ/ሩን አደረጃጀት አፋብን በላይ ዕዝ መይሳው ካሳ ኮር 16ኛ ልባርጋቸው ሙጨ በሚል ስያሜና በስሩ አራት ሬጅመንቶችን በማደራጀት ካጠናቀቀ የሰነባበተ ሲሆን ለወራት በአስቸጋሪ ሁኔታ ብዙ መሰናክሎችን በማለፍ በተለይ የታላቁ አርበኛ ልባርጋቸው መስዋትነት ሳይበግራቸው እንደ ታጋይ በቁጭት የተሻለ በመስራት አንድ ልቡ ቢሰዋ እሽ ልቡ ይወለዳል በማለት ስልጠናውን በብቃት ማጠናቀቅ ተችሏል።
ምንጭ፦ አፋብን በላይ ዕዝ መይሳው ካሳ ኮር ሕዝብ ግንኙነት ክፍል!
3 187
በአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነዉ ዕዝ ዓፄ ዘርዓያዕቆብ ኮር ነጎድጓድ ክፍለ ጦር 2ኛ ሻለቃ በሰራችው ድንቅ ና ልዩ የከተማ ውስጥ ኦፕሬሽን ካለምንም የተኩስ ልውውጥ የአገዛዙን የሚሊሻ ሻንበል መሪ ከነ ሙሉ ትጥቁ ጋማውን አንጠልጥላ በድል ተመልሳለች።
የነጎድጓድ ክፍለ ጦር 2ኛ ሻለቃ ሰኔ 1/2018 ዓ/ም ከሌሊቱ 10:00 ሰዓት ገደማ ላይ በደብረ ብርሃን ከተማ ዙሪያ በሚገኘው በሲያደብርናዋዩ ወረዳ ስር ልዩ ስሙ አንጨቆረር ከተማ ድረስ ዘልቃ በመግባት በወሰደችው የተጠና ልዩ ኦፕሬሽን የአገዛዙን ወንበር አስጠባቂ ሚሊሻ ሻምበል መሪ የሆነውን መካሻ አግደው በጋሻው የሚባለውን ባንዳ ሚሊሻ ከነሙሉ ትጥቁ ስታወጣ አቶ መካሻ አግደው በበኩላቸው ይሕንን ብለዋ፡ ፋኖ እደመብረቅ ድንገት ከፊቴ ሲበራብኝ የእምነታቸውና የታማኝነታቸው ልክ ገብቶኛል ስለሆነም በአገዛዙ እንደኔ የተታለላችሁ አድማ ብተና ና ሚሊሻወች አገዛዙ አያዋጣም እኔ አረጋግጫለሁ ስለዚሕ እናተም ተረዱና ወደ ፋኖ ተቀላቀሉ ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
የፋኖ አናብስቶቹም ይሕንን ሲሉ መልዕታቸውን አስተላልፈዋል ፡ ከአገዛዙ ጎን የተሠለፋችሁ ሁሉ እኛ ስራችን ነውና ከዚሕ ብትማሩ ይበጃችኋል ብለዋል ።
ምንጭ፦አፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ!
3 187
204ኛ አስቻለው ደሴ ኮር ለወራት ያሰለጠናቸውን የፋኖ ሠራዊት አባላትን አስመረቀ።
አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ 204ኛ አስቻለው ደሴ ኮር ግዙፉ እቴጌ ጣይቱ ክፍለ ጦር ለወራት ያሰለጠናቸውን የፋኖ ሰራዊት አባላት በዛሬው ዕለት በደማቅ ሥነ-ሥርዓት አስመርቋል።
በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የዕዝ፣ የኮር እና የክፍለ ጦር ከፍተኛ አመራሮች፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች፣ የሀይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ ወጣቶች እና የአካባቢው ማኅበረሰብ አባላት ተገኝተዋል። የኮሩ ዋና አዛዥ አርበኛ ተሾመ አበባውን ጨምሮ ከፍተኛ አመራሮች በመርሃ ግብሩ ላይ ተሳትፈዋል።
በዕለቱ የተገኙት ክቡር እንግዳ ባስተላለፉት መልዕክት፣ “ይህ የኮማንዶ ኃይል የአማራን ህልውና ከማስከበር ባለፈ ለሕዝቡ መከታና ጋሻ በመሆን ትልቅ አቅም የሚፈጥር እና ጠንካራ አሸናፊ ኃይል ነው” ብለዋል።
ተመራቂዎቹ በቆይታቸው ወቅት የወታደራዊ ስልጠና ንድፈ ሐሳብን ከተግባራዊ ልምምድ ጋር በማጣመር በቂ ዝግጅት ማድረጋቸው ተገልጿል። በምረቃው ሥነ-ሥርዓቱም የሰለጠኑበትን ጥበብና ወታደራዊ ዝግጁነታቸውን የሚያሳዩ የማርሽ ትርኢቶችና ሌሎች ልዩ ልዩ ትዕይንቶች ቀርበዋል።
በተጨማሪም በስልጠናቸው ከፍተኛ ውጤትና ዓርአያነት ላሳዩ የኮማንዶ አባላት የዕውቅናና የሽልማት አሰጣጥ ተከናውኗል።
204ኛ አስቻለው ደሴ ኮር የተጣለበትን ታሪካዊ ኃላፊነት ለመወጣትና የሕዝቡን ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ መሰል የሰው ኃይል ግንባታዎችን አጠናክሮ እንደሚቀጥል በዕለቱ ተገልጿል።
ምንጭ፦ በአፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ 204ኛ አስቻለው ደሴ ኮር ሕዝብ ግንኙነት ክፍል!
3 187
ዋለ አባተን ጨምሮ የምስራቅ ጎጃም ካድሪን በእንባ ያራጨው የሻለቃ በርይሁን ውዱ ድምሰሳ በተጨማሪ ደግሞ 6 አድማ ብተናዎችን ወደ ጥቁር አንበሳ ተልከዋል።
ከታች በምስሉ ላይ የሚታየው የ36ኛ ሻለቃ የአድማ ብተና አዛዥ ሻለቃ በርይሁን ውዱ በጀብደኛው 206ኛ ኮር 14ኛ ክ/ጦር በጅበላ ሙተራ ሻለቃ የተደመሰሰ ነው። ጠንካራ የሚባሉ አራት አጃቢዎቹን አስከትሎ ከ23 የሰራዊት አባላት ጋር ከደብረ ማርቆስ ወደ ሊባኖስ እየሔደ ባለበት የቦ ማርያም አካባቢ በተደረገበት የደፈጣ ጥቃት ድባቅ ተመቷል።
ዋለ አባተ የምስራቅ ጎጃም አስተዳደሪ ስቅስቅ ብሎ ያለቀሰበት ትልቅ ድል ተቀናጅተናል። የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ፣ የብልፅግና ሹማምንትና አዛውንት ደረት እየደቁ በሚገኙበት በዚህ ስዓት በደብረ ማርቆስ ሆስፒታል በነፍስ ውጭ ነፍስ ግቢ ማጣጣር ላይ የነበሩት ፦
1. ግዛት ወርቁ
2. ሰጠኝ አላምነህ
3.ጌታሰው ታደሰ
4. ማሙሸ አዳነ
5. ፈለቀ ጌታቼው
6. መሀመድ አህመድ ህይወታቸውን በደብረ ማርቆስ ሆስፒታል መታደግ ባለመቻሉ ወደ ጥቁር አንበሳ ተልከዋል።
1. ሁሴን ያሲን- ደብረ ማርቆስ ሆስፒታል የሚገኝ ከባድ ቁስለኛ
2.ፋሲል ሲሳይ- ቀላል ቁስለኛ።
በዚህ ስዓት የደብረ ማርቆስ ከተማ ነዋሪዎች በጀግኖች ልጆቻቸው ጀብድ በሃሴት እየቦረቁ መሆናቸውን ታውቋል።
ምንጭ፦ በአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 206ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት ክፍል!ዋለ አባተን ጨምሮ የምስራቅ ጎጃም ካድሪን በእንባ ያራጨው የሻለቃ በርይሁን ውዱ ድምሰሳ በተጨማሪ ደግሞ 6 አድማ ብተናዎችን ወደ ጥቁር አንበሳ ተልከዋል።
ከታች በምስሉ ላይ የሚታየው የ36ኛ ሻለቃ የአድማ ብተና አዛዥ ሻለቃ በርይሁን ውዱ በጀብደኛው 206ኛ ኮር 14ኛ ክ/ጦር በጅበላ ሙተራ ሻለቃ የተደመሰሰ ነው። ጠንካራ የሚባሉ አራት አጃቢዎቹን አስከትሎ ከ23 የሰራዊት አባላት ጋር ከደብረ ማርቆስ ወደ ሊባኖስ እየሔደ ባለበት የቦ ማርያም አካባቢ በተደረገበት የደፈጣ ጥቃት ድባቅ ተመቷል።
ዋለ አባተ የምስራቅ ጎጃም አስተዳደሪ ስቅስቅ ብሎ ያለቀሰበት ትልቅ ድል ተቀናጅተናል። የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ፣ የብልፅግና ሹማምንትና አዛውንት ደረት እየደቁ በሚገኙበት በዚህ ስዓት በደብረ ማርቆስ ሆስፒታል በነፍስ ውጭ ነፍስ ግቢ ማጣጣር ላይ የነበሩት ፦
1. ግዛት ወርቁ
2. ሰጠኝ አላምነህ
3.ጌታሰው ታደሰ
4. ማሙሸ አዳነ
5. ፈለቀ ጌታቼው
6. መሀመድ አህመድ ህይወታቸውን በደብረ ማርቆስ ሆስፒታል መታደግ ባለመቻሉ ወደ ጥቁር አንበሳ ተልከዋል።
1. ሁሴን ያሲን- ደብረ ማርቆስ ሆስፒታል የሚገኝ ከባድ ቁስለኛ
2.ፋሲል ሲሳይ- ቀላል ቁስለኛ።
በዚህ ስዓት የደብረ ማርቆስ ከተማ ነዋሪዎች በጀግኖች ልጆቻቸው ጀብድ በሃሴት እየቦረቁ መሆናቸውን ታውቋል።
ምንጭ፦ በአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 206ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት ክፍል!
3 187
ባሕርዳር ዩኒቨርሲቲ ግሽዓባይ ካምፓስ
ወጣቶቹ በጋራ ካሠሙት መፈክር ውስጥ ጥቂቱ፦
# "የአባቶቻችን የእናቶቻች የወንድሞቻችን ደም መሬት ላይ ፈሶ አይቀርም"
# "እነርሱ በእኛ ላይ ያደረጉብንን እኛም ማድረግ አላቃተንም"
# "የአባቶቻችንን ሃይማኖት (አደራ)አንበላም" ...... የቪዲዮ ምንጭ Abreham Ze Tewahido ገጽ
3 187
በጦር ጠበብቶች የሚመራው ጀብደኛው ምኒልክ ዕዝ ታሪክ በደሙ እየፃፈ ይገኛል!!
አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ የ106ኛ ኮር 22ኛ ክፍለጦር ረፋዱን የጠላትን ሰራዊት ሙትና ቁስለኛ በማድረግ አይቀጡ ቅጣት ቀጥተውታል።
ከጋሸና ተነስቶ ወደ ገረገራ ሊሻገር በነበረ የአገዛዙ ሰራዊት ላይ የቀኝአዝማች ተበጀ ወርቁ ትንፋሾች ዶግ አመድ አድርገውታል።
ንስሮቹ የጠላትን እንቅስቃሴ በማፈንፈን ከቋና ሮቢት እንደ አቦ ሸማኔ ተምዘግዝገው ዛሬ ማለትም ግንቦት 29/2018 ከረፋዱ 2:00 ሰዓት ላይ አርቢት ኪዳነ-ምህረት ጋሸና አፍንጫ ስር ላይ የስርዓቱ ወንበር አስጠባቂዎች ከባድ ጥቃት ፈፅመዉበታል።
በዚህ ጥናታዊ ኦፕሬሽን ከ09 በላይ የተደመሰሱ እና ከ17 በላይ ከባድ ቁስለኛ ማድረግ ተችሏል።
የተወሰደበት ጥናታዊ እርምጃ አስከፊ በመሆኑ ወደ መጣበት የፈረጠጠ ሲሆን ባጃጅ በማስገደድ ቁስለኛና ሙቱን ጭኖ ሲፈረጥጥ የአርቢት ኪዳነምህረት ምድር አስከሬናቸው በተገተቱ የጠላት ሰራዊቶች ደም ጨቅይቷል።
በርካታ ቁስለኛውን ወደ ኮን ሆስፒታል እያሳከመ የሲቃ ድምፁን እያሰማ ይገኛል ሲል 106ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት መምሪያ መረጃዉን አድርአድርሷል።
መዳረሻውን ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ሕዝብ የሕልውና ተጋድሎ ይቀጥላል!!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ!!
ግንቦት 29/2018 ዓ/ም
3 187
+2
አፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ለወራት ያሰለጠናቸውን የኮማንዶ አባላት በደማቅ ሁኔታ አስመረቀ!
የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ እየተዋጋን እንሰለጥናለን እየሰለጠንን እንዋጋለን በሚል መርህ፤ ለረጅም ወራት በጽናት፣ በልዩ ሁኔታና በከፍተኛ ዲሲፕሊን ሲያሰለጥናቸው የቆያቸውን የኮማንዶ አባላት በዛሬው ዕለት የዕዙ ዋና መሪ ኢንጅነር ደሳለኝ ሲያስብ ሸዋ ና ሌሎች የዕዝና የኮር ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት በደማቅ ሁኔታ አስመርቋል።
ተመራቂዎቹ በቆይታቸው ወታደራዊ ስልጠናው ንድፈ ሀሳብን በተግባር በማጣመር በበቂ ሁኔታ በብቁ አሰልጣኞች ሁሉንም አይነት ውጣውረድ ተቋቁመው በቂ ስልጠና የወሰዱ ሲሆን፣ የተሰጣቸውን ተልዕኮ በአስተማማኝ ሁኔታ ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን ገልፀዋል።
በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የዕዙ ከፍተኛ አመራሮች፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እና የአካባቢው ማኅበረሰብ አባላት የተገኙ ሲሆን፣ የዕለቱ ክቡር እንግዳ ባስተላለፉት መልዕክት፦
"ይህ የኮማንዶ ኃይል የአማራን ህልውና ከማስከበር ባለፈ፣ ለሕዝባችን መከታና ጋሻ በመሆን ረገድ ትልቅ አቅም የሚፈጥር እና ጠንካራ አሸናፊ ሀይልም ነው" ብለዋል።
በምረቃው ስነ-ስርዓት ላይ ተመራቂዎቹ ወታደራዊ ዝግጁነታቸውን የሚያሳይ ልዩ ልዩ ትዕይንቶችንና የማርሽ ትርኢቶችን ያቀረቡ ሲሆን፣በስልጠናቸው ከፍተኛ ውጤትና አርአያነት ላሳዩ የኮማንዶ አባላትም የዕውቅናና የሽልማት አሰጣጥ ተከናውኗል።
አሳምነው ዕዝ የተጣለበትን ታሪካዊ ኃላፊነት ለመወጣትና የሕዝቡን ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ መሰል የሰው ኃይል ግንባታዎችን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም በዕለቱ ተገልጿል።
ምንጭ፦በአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ!
3 187
+2
አፋብን ግንቦት 24 ተካሂዷል የተባለውን ምርጫ ተከትሎ የምርጫ ታዛቢ ቡድኖች የሰጡትን ግምገማ በተመለከተ ጥልቅ ስጋቱን እንዲሁም ነባራዊ የሀገሪቱን ሁኔታ እና የምርጫውን ሒደት በተመለከተ ሰፊ የግንዛቤ ማስጨበጫ ይዘቶች ያየዘ ደብዳቤ ተፅፏል ፡፡
ደብዳቤው የተፃፈው፦ ለአንቶኒዮ ጉቴሬዝ(ተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሀፊ)፣ ለማህሙድ አሊ የሱፍ (የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር)፣ ለኡሁሩ ኬንያታ (የቀድሞ የኬንያ ፕሬዝዳንት እና የአፍሪካ ህብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን መሪ) ነው።
3 187
የብልፅግና መከላከያ ሠራዊት ንፁኋን ላይ ያነጣጠረ የመድፍ ድብደባ በመፈፀም የሰው ሕይወት ቀጠፈ
የአገዛዙ ኃይል በሐይቅ ከተማ ሸይኽ ሙሳ ተራራ ላይ ባጠመደው ከባድ መሣሪያ ንፁኋን ላይ ያነጣጠረ ድብደባ በመፈፀም አንዲት የሁለት ልጆች እናትን በአሰቃቂ ሁኔታ ሲገድል መኖሪያ ቤቶችን ማውደሙን ተረጋግጧል። ጥቃቱ የተፈፀመው ትናንት ግንቦት 27/2018 ዓ/ም ማርፈጃውን፡ በሐይቅ ከተማ ዙሪያ ልዩ ስሙ ግም ውሃ ክሬቸር ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ላይ ሲሆን፡ ጥቃቱ አገዛዙ ለአማራ ሕዝብ ያለውን ጥላቻና ሃገር አውዳሚነቱን ዳግም ያረገጠ ነው ተብሏል።
የአገዛዙ ወታደሮች ንፁኋንን እና መኖሪያ ቤቶችን ኢላማ አድርገው በፈፀሙት በዚህ የመድፍ ድብደባ፡ የሁለት ታዳጊ ልጆች እናት የነበረችው ወይዘሮ ተምሬ ይማም በአሰቃቂ ሁኔታ መገደሏንም ለማረጋገጥ ተችሏል። ወይዘሮ ተምሬ ይማም የተገደለችው ቤት ውስጥ እንዳለች በላዩዋ ላይ ባረፈ የመድፍ ቅምቡላ ነው።በዚህ ጥቃት ሌሎች ንፁኋኖች ክፉኛ መቁሰላቸው ታውቋል።
3 187
በወሎ ቤተ አማራ ቀጠና በአምባሰልና በኩታበር ግንባሮች የጠላትን አከራካሪ የሰበረ ከባድ አውደ ውጊያ መካሄዱ ታወቀ!
በአምባሰል ግንባር የምኒልክ ዕዝ አርበኞች በከፈቱት ከባድ ውጊያ በርካታ የጠላት ወታደሮች ሲደመሰሱ፡ ቀሪዎቹ ሕይወታቸውን ለማትረፍ ሲሽቀዳደሙ ገደል ገብተው አልቀዋል።
በተመሳሳይ በኩታበር ግንባር፡ በፋኖ ቀለበት ውስጥ የገባው የጠላት ኃይል አከርካሪው ተሰብሮ ሁለት ተሽከርካሪ ሙሉ ሙትና ቁስለኛ ወታደር ጭኖ በውርደት ወደ ደሴ ለመሸሽ መገደዱን ለማረጋገጥ ተችሏል።
3 187
አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒሊክ ዕዝ ልዩ ዘመቻ መምሪያ በተጓደሉ አዳዲስ የስራ ኃላፊዎችን ሾመ!!
በአፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ልዩ ዘመቻ መምሪያ የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት ለ 2 ቀናት የፈጀ ስብሰባና ግምገማ ካደረገ በኋላ ክፍት በነበሩ ቦታወች ላይ አመራር መድቧል።
2ቀን በፈጀዉ በዚህዉ ስብሰባ፣ እየተደረገ ለሚገኘው የህልውና ተጋድሎ ይበልጥ ምቹ ሁኔታን ለመፍጠርና የአደረጃጀት ጥንካሬን ለመጨመር ይረዳ ዘንድ የአዳዲስ የሥራ ኃላፊዎች ሹመትና የሥራ ሽግሽግ አድርጎ ዛሬ ይፋ አድርጓል።
በዚሁ መሠረት በ ልዩ ዘመቻ መምሪያዉ ውስጥ ክፍት የነበሩ የሥራ ቦታዎች ላይ የተመደቡ አዳዲስ የሥራ ኃላፊዎች ዝርዝር እንደሚከተለው ቀርቧል፦
1. ልዩ ዘመቻ መምሪያ ሀላፊ ................አርበኛ ተሾመ ፈንታየ
2. ወታደራዊ አዛዥ.............አርበኛ መ/አለቃ ግርማ አብየ
3. ም/ወታደራዊ አዛዥ.........አርበኛ አሻግሬ ሙሉ
4. ዘመቻ መምሪያ............አርበኛ አሸናፊ ዳኜ
5.ወታደራዊ አስተዳደር ና ፋይናስ ..አርበኛ በላይ ተሾመ
6.ፖለቲካ መምሪያ .........አርበኛ አባተ ካሳ
7.ህ/ግንኙነት ና ሀብት አፈላላጊ .....አርበኛ ሀብታሙ ታደሰ
8.ሎጆስቲክ ክፍል ...................... አርበኛ አማረ ተገኘ
9.ኦርዲናስ ክፍል ......................አርበኛ በቀለ ቢራራ
10.ህግ ክፍል ........................አርበኛ ዘገየ ገሰሰ
11. መረጃ ክፍል*አርበኛ***
12.ንብረት አስተዳደር...........አርበኛ መርጌታ ሀይለማርያምን አድርጎ ሹሟል።
ምንጭ፦በአፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ሚዲያ እና ኮምኒኬሽን መምሪያ!
3 187
በተደረገ የደፈጣ ውጊያ ራሱን ጥምር ጦር ነኝ ብሎ የሚጠራው የአብይ ወንበር ጠባቂ ኃይል እንደቅጠል ሲረግፍ፣ የራሳቸውን ከፍተኛ አመራር የገደሉ የመከላከያ የኮማንዶ አባላት የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው እዝን በይፋ ተቀላቀሉ::
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ መሐመድ ቢሆነኝ ኮር የአስቻለው ደሴ ክፍለጦር ሶስተኛ ሻለቃ ቃኝዎች ከመንዝ ሞላሌ ወደ መሃል ሜዳ ሲንቀሳቀስ በነበረው የ104ኛ ኮማንዶ ክፍለጦር ላይ ልዩ ስሙ መለያ በተባለ ቦታ ፋኖዎች ደፈጣ በመጣል የጠላት ኃይል ላይ ከፍተኛ ሰብዓዊ እና ቁሳዊ ኪሳራ አድርሰውበታል:: የሸዋ መሬት ረመጥ እሳት የሆነበት እራሱን ጥምር ጦር ነኝ ብሎ የሚጠራው የጠላት ኃይል መለያ ላይ በደረአሰበት ከፍተኛ የደፈጣ ጥቃት ሙት እና ቁስለኛውን ሳያነሳ ወደ መሃል ሜዳ ከተማ እንዳያልፍ በመደረጉ ወደ መጣበት ሞላሌ ከተማ ተመልሷል::
በሌላ ዜና የኮማንዶ የመከላከያዎቹ የሻለቃ አመራሮች የመከላከያውን ከፍተኛ አመራር የሆነውን ባለ ቀይ ቦኔቱን የመቶ አለቃ ማዕረግ ያለውን እስከወዲያኛው አሰናብተው የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አጼ ዘርዓያዕቆብ ፩ኛ ኮር ብሩኬ ደምሴ ክፍለጦርን በይፋ ተቀላቀሉ። በወረኢሉ ወረዳ መሽጎ የነበረዉ የአገዛዙ የ84ኛ ክፍለ ጦር 4ኛ ሻለቃ አመራሮች እና በፋኖ በኩል የብሩኬ ደምሴ ክፍለጦር የሻለቃ አመራሮች ሚስጥራዊ ግንኙነት ሲያደርጉ ቆይተው በስተመጨረሻ የአገዛዙ ኃይሎች በራሳቸው አመራር ላይ ኦፕሬሺን ሰርተዉ እንዲመጡ ተነጋግረው መግባባት ላይ ከደረሱ በኋላ በትላንትናዉ ዕለት ከምሺቱ 12:00 ሰአት አካባቢ በወኢሉ ወረዳ 01 ቀበሌ ማርያም ደብረ-ንግስት አካባቢ መቶ አለቃ ታደሰ እምቢአለ የተባለዉን የራሳቸውን ከፍተኛ የጦር መሪ ገድለዉ በእጁ ላይ ያለዉን መገናኛ እና ሙሉ ትጥቁን ይዘው እንዲሁም የራሳቸውን በእጃቸው ያለውን ሙሉ ትጥቅ ከነ መሳሪያቸው ይዘው ወደ ብሩኬ ደምሴ ክፍለጦር በክብር ተቀላቅለዋል:: በክብር የተቀላቀሉትም:-
1. የሻለቃ ዘመቻ መሪ
2. የሻለቃ ሎጄስቲ ኃላፊ
3. የሻለቃ ኦርዲናንስ ኃላፊ
4. የሻለቃ አልባሳት ኃላፊ
በአካባቢው የምትንቀሳቀሰው የብሩኬ ደምሴ ክፍከጦር የፋኖ የሻለቃ አመራራሮች አገዛዙን ከድተው የመጡትን የመከላከያ የኮማንዶ አባላትን በክብር ተቀብለዋቸልዋል።
ክብር ለትግሉ ሰማዕታት!!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!!
የአ.ፋ ብ.ን ሽዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግኑኝነት መምሪያ!!
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
