3 142
Subscribers
-424 hours
-77 days
-7130 days
Posts Archive
3 141
+3
🔶ተጠናክሮ በቀጠለው ስቦ ማስከዳት ስምንት የመከላከያ ሰራዊት አባላት ከነሙሉ ትጥቃቸው ፋኖን ተቀላቀሉ!
🔶በአፋብን ምኒልክ ዕዝ 303ኛ አሳምነው ኮርን ስምንት የአገዛዙ ብልፅግና ሰራዊት አባላት ሙሉ ትጥቃቸውን ይዘው ተቀላቅለዋል።
🔶መነሻቸውን በሰሜን ወሎ አስተዳደር ዞን ላስታ ወረዳ ብልባላ ከተማ 204ኛ ኮር በኮሎኔል አባቡ የምትመራው 38ኛ ክፍለ ጦር ቃኝዎች ስድስት አባላቱ ምቹ ቦታና ጊዜን ይጠብቁ የነበሩት የአማራን ህዝብ ግፍ ቆሞ ማየትና ተባባሪ መሆን የሰለቻቸው ለስለላ በተላኩበት እርስ በርስ በመተማመንና ቆራጥ ውሳኔ በመወሰን ሰኔ 22 ቀን 2018 ዓ/ም ፋኖን ተቀላቅለዋል።
🔥በሌላ አቅጣጫ ከ38ኛ ክፍለ ጦር ሁለተኛ ሬጅመንት አንድ መቶ መሪና አንድ ብሬን ተኳሽ ከነ ሙሉ ትጥቃቸው 19ኛ ክፍለ ጦር ወደ ፋኖዎች ቤት ጎራ ያሉ ሲሆን ለመጡት ጥቁር እንግዶችም በአማራነት ባህልና እሴትም በእንክብካቤ ተይዘዋል።
🔥አባላቱም አንድ ጥቁር ስናይፐር፣ ሰባት ጥቁር ክላሽ፣ አራት የደረትና የወገብ ትጥቅ፣ 549 የክላሽ ተተኳሽ፣ ስድስት የእጅ ቦምብ በኮሩ ስር ለሚገኙ 19ኛና 30ኛ ክፍለ ጦር ፋኖዎች አበርክተዋል።
ምንጭ፦ በአፋብን ምኒልክ ዕዝ ሚዲያ እና ኮሚዩኒኬሽን መምሪያ!
3 141
በአፋብን ወለጋ (ቢዛሞ) አይሻ ሰይድ ዕዝ ሥር የሚገኙት የይበልጣል መኮነን አዲስ ዓለም ክ/ጦር አርበኞች ዛሬ ሰኔ 23/2018 ዓ/ም በሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን አሙሩ ወረዳ በወሰዱት የተጠና እርምጃ የጠላት ኃይልን ጠንካራ የተባለ ምሽግ ደርምሰው የጠላትን ወታደሮች በማሽመድመድ አኩሪ ድል መቀዳጀታቸው ታወቀ።
አርበኞቹ ዛሬ ማለዳ በአሙሩ ወረዳ በታዳጊዋ አጋምሳ ከተማ እና ዋሊ ሉቁማ ተብሎ በሚጠራው አከባቢ ባደረጉት የተቀናጀ ተጋድሎ፡ የአገዛዙን ሠራዊት፣ የገዳ ኮማንዶን፣ የሚኒሻና የፖሊስ፣ የኦሮሚያ ክልል ሪፐብሊካን ጋርድ እንዲሁም ጋቸና ሲርና (የስርዓቱ ጠባቂዎች) ይሄንን ሁሉ ኃይል በልዩ ወታደራዊ ጥበብና በአንዳች አማራዊ ወኔ አፍረክርከው ነው ድል ያስመዘገቡት።
ለዘመናት የአካባቢውን አማራ ማህበረሰብ ሲዘርፉና ሲገሉ የቆዩት የአገዛዙ ኃይሎች፡ የአይሻ ሰይድ ዕዝ አርበኞች በወሰዱባቸው የማያዳግም እርምጃ ብትንትናቸው ወጥቶ፡ ከአፈሙዝ እሳት የተረፉ ወታደሮች አከባቢውን ለቀው ወደ አሙሩ ወረዳና ጣቦ ሶንቶም አቅጣጫ መሸሻቸው ታውቋል።
በዚህ የአውደ ውጊያ 43 የጠላት ጥምር ጦር አባላት ሲገደሉ፡ 29 ወታደሮች ደግሞ በፁኑ መቁሰላቸ ታውቋል።
በተጋድሎው 14 ክላሽንኮቭ መሣሪያን ጨምሮ 1ሺ 287 የክላሽ ተተኳሽ፣ ሰባት የወገብ ትጥቅና ሌሎች ልዩ ልዩ ወታደራዊ ቁሳቁሶች በአርበኞቹ ቁጥጥር ስር ውለዋል።
በዚህ ኦፕሬሽን አማካኝነት አረብኞቹ፡ በአካባቢው የነበረውን የጠላት ኃይል አከርካሪ በመስበር፣ በአካባቢው ያለውን የፀጥታ የበላይነት ማረጋገጣቸውንና የሕዝቡን ደህንነት የመጠበቅ ተልዕኳቸውን በፅናት መቀጠላቸውን አስታውቀዋል።
ለዘመናት በስርዓታዊ የዘር ማጥፋት ዘመቻ ሲማቅቅ የኖረው የወለጋ-ቢዛሞ አማራ ህዝብ በብልፅግና አገዛዝ የተጋረጠበትን የህልውና አደጋ ለመመከት ተደራጅቶ ጠላቶቹ ላይ የእሳት መዓት እያወረደ ይገኛል።
ከረጅም ዘመናት ስቃይ በኋላ ራሱን በራሱ የመከላከል አቅምን የገነባው የወለጋ አማራ ማህበረሰብ የተጋረጠበትን የሕልውና አደጋ በፅኑ የመከላከል ትግል እየተቀለበሰ እንደሚገኝ ታውቋል።
በአሙሩ ወረዳ አጋምሳ ከተማ በተደረገው ውጊያ፣ የብልፅግና አገዛዝ ኃይሎች መደምሰሳቸውን ተከትሎ፡ ሕዝቡ ራሱን ከእልቂት የመታደግ ታሪካዊ ኃላፊነቱን በአኩሪ የትግል ብቃት እየተወጣ መሆኑን በድል ማረጋገጥ ችሏል።
እራስን ከእልቂት የመታደግ ተፈጥሯዊ መብቱን ተጠቅሞ የተደራጀውና ብሶት የወለደው ጀግናው የአይሻ ሰይድ ዕዝ ሠራዊት ብርቱ የሆነ የፀረ ማጥቃት እርምጃ በመውሰድ የሕዝቡን ሕልውና ለማረጋገጥ የሚያደርገውን ተጋድሎ አጠናክሮ ቀጥሏል።
3 141
በወለጋ (ቢዛሞ) ለዘመናት በስርዓታዊ የዘር ማጥፋት ዘመቻ ሲጨፈጨፍ የኖረው የአማራ ማህበረሰብ፣ ዛሬ ላይ ተደራጅቶ ራሱን በመከላከል አኩሪ ገድል እየፈጸመ ነው።
በሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን አሙሩ ወረዳ አጋምሳ ከተማና አካባቢው ላይ በተደረገው አውደ ውጊያ ሕዝቡን ሲያሳድዱና ለጅምላ እልቂት ሲዳርጉ የነበሩ 72 የአገዛዙ ወታደሮች መደምሰሳቸው ታውቋል።
ከድሮንና ከጦር ሄሊኮፍተር ጀምሮ ሌሎች ከባባድ የጦር መሣሪያዎችን ታጥቆ በውጊያው ከተሰለፈው የብልፅግና መከላከያ ሠራዊት በተጨማሪ የገዳ ኮማንዶ፣ የኦሮሚያ ሚኒሻና ፖሊስ፣ የኦሮሚያ ሪፐብሊካን ጋርድ፣ እንዲሁም የጋቸና ሲርና (የስርዓቱ ጠባቂዎች) ይህ ሁሉ ኃይል በዛሬው ውጊያ የተሳተፈ ቢሆንም፡ ነገር ግን ከፋኖ ልዩ የጦር ጥበብና የማጥቃት ፍጥነት ጋር ተዳምሮ ጥቃቱን መቋቋም አቅቷቸው ያለቀው አልቆ ቀሪው እግሬ አውጭኝ መፈርጠጡን ለማረጋገጥ ተችሏል።
3 141
የብልፅግናው አገዛዝ ለሱዳኑ ፈጥኖ ደራሽ ኃይል(RSF) የጦር መሣሪያ፣ የሎጂስቲክስና የማሰልጠኛ ድጋፍ በማድረግ በሱዳን ህዝብ ላይ በተለይም በዳርፉር እየተፈፀመ ለሚገኘው እልቂት ተባባሪ ነው በሚል ከፍተኛ ውንጀላ ቀረበበት።
የተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማት የኢትዮጵያ፣ የአረብ ኤምሬትስና የቀጠናው ባለስልጣናት በዓለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት እንዲጠየቁ በይፋ ጠይቀዋል።
የአብይ አህመድ አገዛዝ በውስጥ የዘረጋውን የጭቆናና የጭፍጨፋ ስልት ወደ ጎረቤት አገር በማሸጋገር፡ በሱዳን ግጭት ውስጥ እጁን በማስገባት ለጦር ወንጀሎች ተባባሪ መሆኑ በዓለም አቀፍ ደረጃ አጀንዳ ሆኗል።
3 141
ጋዜጠኛ ሣልሳዊት ባይነሳኝ በእስር ላይ ትገኛለች
በአርሲ ዞን የተፈጸመውን የንጹሐን ክርስቲያኖች ግድያ በጽኑ በመቃወም እና «አትግደሉን» የሚል የፍትሕ ድምፅ በማሰማታቸው ምክንያት ከአገዛዙ የጸጥታ ኃይሎች እስርና እንግልት ከደረሰባቸው ወገኖች መካከል ጋዜጠኛ ሣልሳዊት ባይነሳኝ አንዷ መሆኗ ታውቋል። ጋዜጠኛዋ በነመምህር ዘላለም መዝገብ ተካታ ይፋዊ ክስ እንደቀረበባት ከተለያዩ ምንጮች የተገኘው መረጃ አረጋግጧል።
ጋዜጠኛ ሣልሳዊት ባይነሳኝ በጋዜጠኝነት ሙያዋ በቅድሚያ በዋልታ ቴሌቪዥን፣ በመቀጠልም በፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት (ፋና ቲቪ) ውስጥ በተለያዩ የምርመራና አንጋፋ ዘገባዎች በታማኝነት ያገለገለች ባለሙያ ናት። በማኅበራዊ ሚዲያ ገጾቿ ስለ ኢትዮጵያ አንድነት እና ስለ ኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያን መብትና ክብር በድፍረት በመናገርና እውነትን በመናገር ትታወቃለች።
ጋዜጠኛዋ ሰኔ 1 ቀን 2018 ዓ.ም ሰኞ ዕለት በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን (ፒያሳ አካባቢ) በቁጥጥር ሥር የዋለች ሲሆን፣ በታሰረችባቸው በመጀመሪያዎቹ ሁለት ቀናት ቤተሰቦቿም ሆኑ የሕግ አማካሪዎቿ እንዳይጠይቋትና ያሉበትን ሁኔታ እንዳያውቁ ተከልክለው መቆየታቸው ተገልጿል።
ከቤተሰቦቿ የተገኘው የቅርብ መረጃ እንደሚያመለክተው፣ ጋዜጠኛ ሣልሳዊት በመጀመሪያው የእስር ወቅት መብት የሚገፈፍበትና ሰብዓዊነት የጎደለው አሰራር የሚፈጸምበት ጨለማ ክፍል ተብሎ በሚጠራው ይፋዊ ባልሆነ የማቆያ ክፍል ውስጥ ተዘግቶባት ሰንብታለች። በአሁኑ ወቅት ግን ከቀናት እንግልት በኋላ ወደ መደበኛ እስረኞች ማቆያ ክፍል መዛወሯ ታውቋል።
3 141
+3
ፋኖ ከውጊያው ጎንለጎን በሚወስደው የስቦ ማስከዳት እርምጃ ውጤታማ ድል እያገኘ መሆኑ ታውቋል..... ከክላሽ ጀምሮ ትጥቅ ደርበው ያነገቡ ወታደሮች ፋኖን ተቀላቅለዋል።
3 141
በአምሃራ ሳይንት በለጩማ ግንባር በጠላት ከፍተኛ አመራሮች ላይ አስደናቂ የደፈጣ ጥቃት ተፈጸመ!
በመካነ ሰላም ከተማ ለቀናት የሴራ ስብሰባ ሲያካሂዱ የነበሩት የአገዛዙ ከፍተኛ ወታደራዊ አመራሮች፣ ወደ አምሃራ ሳይንት ወረዳ ለመግባት ሲሞክሩ በንሥሮች በተደገሰላቸው ጥብቅ ደፈጣ ክፉኛ ተመትተዋል።
የአገዛዙ የጦር አመራሮች በመካነ ሰላም የነበራቸውን የግምገማ ስብሰባ ጨርሰው፣ የተለመደ የጥፋት ተልዕኮአቸውን ለመፈጸም በከፍተኛ መኪናዎች ታጅበው እየተንቀሳቀሱ በነበረበት ቅፅበት ጀግኖቹ "በለጩማ" በተባለው ስልታዊ ቦታ ላይ መንገዱን ዘግተው በመጠባበቅ፣ ጠላት ጨርሶ ባልገመተው ሁኔታ መብረቃዊ የደፈጣ ጥቃት ዶግ አመድ አድርገዉታል።
ደፈጣዉም በጀብደኛዉ ምኒልክ ዕዝ ስር በ105ኛ ኮር የ71ኛ ክፍለ ጦር አናብስቶች ሲሆን የተሰራዉ በጥቃቱም የጠላት ዋና ዋና ወታደራዊ መሪዎች ጭምር ሙት እና ቁስለኛ ሁነዋል።
በጀግኖቹ ክንድ የደረሰባቸውን ከባድ ጉዳት መቋቋም ያልቻለው የጠላት ጦር፣ አመራሮቹን ለማዳን በከፍተኛ መደናገጥ ውስጥ ሆኖ ሲያነሳ የዋለ ሲሆን ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸው የጦር መኮንኖች በአስቸኳይ ወደ ደሴ ሆስፒታል በሪፈር የተሸኙ ሲሆን ቀሪወቹ በአምሃራ ሳይንት ወረዳ በሚገኘው አጅባር ሆስፒታል ገብተዋል።
በጉዳቱ የተደናገጠዉ ስርዓት ሽንፈቱን ለመደበቅ ከትናንት ምሽት ጀምሮ በአጅባር ሆስፒታል ዙሪያ ጥብቅ ወታደራዊ ከበባ ያደረገ ሲሆን የቆሰሉት አመራሮች ማህበረሰቡ እንዳያያቸዉ በሚል ስጋት፣ ከሕክምና ባለሙያዎች ውጭ ማንም ሲቪል ታካሚ ወደ ሆስፒታሉ ግቢ እንዳይገባ ሙሉ በሙሉ እስካሁን ድረስ አግደው ይገኛሉ። ምንጭ፦ የምኒልክ ዕዝ ሚዲያ እና ኮሚዩኒኬሽን መምሪያ!
3 141
ከደብረ ማርቆስ ወደ ስናን ሬሽን ለማቀበል በተንቀሳቀሰው የጠላት ኃይል ላይ 206ኛ ኮር 24ኛ ክ/ጦር ስናን አባ ጅሜ ሻለቃ ባደረገው ማጥቃት 20 የአረመኔው ሰራዊት ሲደመሰሱ 12 የሚደርሱ ከባድ ቁስለኛ ሁነው 3 ክላሽ ፣ 1050 ጥይት ተማርኳል።
የአረመኔው ሰራዊት የ6ኛ ዕዝ 602ኛ ኮር 75ኛ ክ/ጦር ከደብረ ማርቆስ ተነስቶ ወደ ስናን ረዕቡ ገበያ ሬሽን ለማቀበል እየተንቀሳቀሰ ባለበት 206ኛ ኮር 24ኛ ክ/ጦር ስናን አባ ጅሜ ሻለቃ ባደረገው ማጥቃት 20 የጠላት ወታደሮች ሲደመሰሱ 12 የሚደርሱት ቁስለኛ ሁነዋል።
በተፈፀመው ፈጣን ጥቃት የጠላት መስመራዊ መኮንኖች ህይወታቸውን ያጡ ሲሆን ፻ አለቃ ታሪኩ በቀለ ባቲሳ የሻለቃ አዛዥ ይገኝበታል።
ጠላት በአልጠበቀው ስዓት በተከፈተበት ተኩስ አስክሬን ሳያነሳ ፈርጥጦ 3 ክላሽ፣ 1050 ጥይት ትጥቆችና ወታደራዊ ቦርሳዎች ተማርኳል።
ምንጭ፦ በአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 206ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት ክፍል!
3 141
በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ምንጃርና ከረዩ አውራጃ ነበልባል ክፍለ ጦር ድል ተቀዳጀች
በአፋብን ሸዋ/ጠ/ግ/አሳምነው ዕዝ ከሠም ፪ኛ ኮር ነበልባል ክፍለ ጦር የብልፅግናውን ጥምር ጦር እንደ ቅጠል አረገፉት።
ሁለት የነበልባል ክፍለ ጦር ሻለቆች የተሳተፉበት ውጊያ ማለትም መብረቅ ሻለቃ እና መቶ አለቃ አበባው ሻለቃ ፋኖዎች በጥምረት ባደረጉት ገድል የብልፅግናውን ግብስብስ ሠራዊት በ06/10/2018 ከቀኑ 6:00 እስከ ማታ 9:45 ሰዓት በነበረው ፍልሚያ ፋኖዎቹ መብረቃዊ ክንዳቸውን በመሰንዘር እንደ እሳት ሲለበልቡት አምሽተዋል።
መነሻውን ከባልጪ አድርጎ ወደ ኢራንቡቲ ቀበሌ ያቀናውን የሪፐፕሊካን ጥበቃ 5ኛ ክፍለጦር እና በስሩ በጥቅማጥቅም የሰበሰባቸውን ሆድ አደር ሚሊሾች እንዲሁም አዲስ ተጨማሪ ሰራዊት በመያዝ ኢራንቡቲ ቀበሌን እቆጣጠራለሁ ብሎ በመንጋ ቢመጣም በአይበገሬዎቹ ነበልባል ክፍለ ጦር ሠራዊታችን ወደ መጣበት እዲመለስ አድርገውታል።
የሀይል ብልጫ የተወሰደበት የጠላት ሀይል ከ15 በላይ እንደተገደለበት እና ቁጥሩ በውል ያልታወቀ ቁስለኛ በአንቡላንስ ከአራት ጊዜ በላይ ጭኖ እንዳመላለሰ እና የሞተበትን ሀይል በአካባቢው ማህበረሰብ በማስገደድ ለህክምና የምታመላልሰው አንቡላንስ ደርሳ እስክትደርስ 15ቱን እሬሳ እዲያቀብሉት ማስገደዱን የውስጥ መረጃችን አሳውቆናል።
ይህ በእንዲሕ እንዳለ የአፋብን ሸ/ጠ/ግ/አ/ዕዝ ዓፄ አምደ ጽዮን ኮር 7/70 ክፍለጦር አንድ(1) የአገዛዙ ወታደር
=> አንድ(1) ዘመናዊ ስናይፐር መሳሪያ
=> አንድ(1) የደረት ትጥቅ
=> አራት(4) ካዝና በመያዝ ወደ ፋኖ ተቀላቅሏል።
በሌላ የአውደ ውጊያ ቀጠና
በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ይፋት አውራጃ አስገራሚ ጀብዶች ተሠርተዋል
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው እዝ የዓፄ ዘርዓ ያዕቆብ ፩ኛ ኮር 7/ለ70 ክፍለ ጦር ዛሬም እንደ ትላንቱ በጠላት ይዞታዎች ውስጥ ሰርገው በመግባት አስገራሚ ድሎችን ማስመዝገባቸውን ቀጥለውበታል።
የክፍለ ጦሩ ልዩ የኦፕሬሽን ቃኝዎች የፋሺስት አብይ አህመድ ግብስብስ ሰራዊትን ወደ ሚንቀሳቀስበት ቦታ ሰርገው በመግባት የጠላትን እቅድ በማክሸፍ መብረቃዊ ጥቃቶችን ፈፅመዋል።
የሰርጎ ገብ ውጊያ ስምሪቱ በቀን 05/10/2018 ዓ.ም ከለሊቱ 5:00 ሰዓት ላይ ከአጣዬ ተነስቶ ወደ በርግቢ አቅጣጫ እየገሰገሰ በነበረው የጠላት መከላከያ ሰራዊት ላይ የ7ለ70 ክፍለ ጦር ጀግኖች በ06/10/2018 በበርግቢ ቀበሌ እና በይምልዎ መካከል ላይ አድፍጠው በመጠበቅ ከባድ ድንገተኛ ጥቃት ፈፅመዋል። በዚህ እልህ አስጨራሽ የለሊት ውጊያ የጠላት ኃይል ድባቅ በመመታቱ ወደ መጣበት ተገዶ ለማፈግፈግ ተገዷል። በዚሕም ከጠላት ሀይል አራት(4) የተገደሉ ሲሆን የተቀሩት ደግሞ በጽኑ ቆስለው በሕክምና ላይ እንደሚገኙ የውስጥ መረጃዎቻችን ገልፀዋል።
ይህ የድል ጉዞ ሳይቋረጥ በማግስቱ በ07/09/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 12:00 ሰዓት ላይ ከአጣዬ ከተማ ተነስቶ ወደ አላላ በመጓዝ ላይ በነበረው የሆድ አደር ሚሊሻ ኃይል ላይ ሌላ ስልታዊ ጥቃት ተፈጽሟል። የክፍለ ጦሩ የቁርጥ ቀን ልጆች አራዳ በር ላይ ቀድመው ሰርገው በመግባትና ምሽግ በመያዝ፣ በሚሊሻው ላይ የጀግንነት ክንዳቸውን አሳርፈዋል።በዚህ እልህ አስጨራሽ ውጊያ እንድሪስ የተባለው የጠላት ሚሊሻ መሪ እስከ ግብረ አበሮቹ ሙሉ በሙሉ የተደመሰሰ ሲሆን፣ ካጋጠማቸው ከባድ ሽንፈት የተረፉት 3ቱ (ሦስቱ) ደግሞ በከባድ የመቁሰል አደጋ ምክንያት ሪፈር ተጽፎላቸው በሕይወትና በሞት መካከል ይገኛሉ ሲል መረጃዎቻችን ተናግረዋል።
ምንጭ፦በአፋብን አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ!
3 141
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የቴክሳስ፣ ኦክላሆማ፣ ሉዊዚያና፣ አርካንሳና ሐዋዪ አካባቢ ሀገረ ስብከት በምሥራቅ አርሲ የጅምላ ፍጅት ለደረሰባቸው ወገኖቻችን ጸሎተ ፍትሐት እንዲደረግ መመሪያ አስተላልፏል። እንዲሁም ለእሑድ ሰኔ 8 ቀን 2018 ዓ.ም (June 14, 2026) ደግሞ ልዩ ጉባዔ ጠርቷል። ዝርዝሩ ከደብዳቤው ላይ ይገኛል።
3 141
+1
በአርሲ ሀገረ ስብከት በኦርቶዶክስ ምእመናን እና በአብያተ ክርስቲያናት ላይ በደረሰው አሰቃቂ ጥቃት የሊባኖስ፣ የተባበሩት ዓረብ ኢምሬትስ እና የመካከለኛው ምሥራቅ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ድሜጥሮስ የሐዘን፣ የጸሎተ ፍትሐት እና የጸሎተ ምሕላ መግለጫ
=========
“ቅዱስና እውነተኛ ጌታ ሆይ እስከ መቼ ድረስ አትፈርድም? ስለ ደማችንስ በምድር በሚኖሩት ላይ እስከ መቼ አትበቀልም?”
(ራእይ 6፥10)
3 141
+2
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የዋሽንግተን ዲሲ እና አካባቢው ሀገረ ስብከት በምስራቅ አርሲ ውስጥ በተደጋጋሚ ስለሚከሰተው የክርስቲያኖች ግድያ ስደት እና መከራን አስመልክቶ የወጣ የአቋም መግለጫ
================
«እስመ በእንቲአሁ ይቀትሉነ ኵሎ አሚረ፤ወኮነ ከመ አባግዕ ዘይጠብሑ። ስለ አርሱ ሁልጊዜ ይገድሉናል፥ እንደሚታረዱም በጎች ሆነናል።” (መዝ ፵፫፡፳፪)
3 141
በአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ሽዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ዓፄ ዘርያዕቆብ ፩ኛ ኮር በፍቃዱ በላይ ክፍለ ጦር የበረሀው ጀግኖች ትናንት ከማለዳ አንድ(1:00) ሰዓት ከ30 ደቂቃ ጀምረው እስከ ምሽቱ አንድ(1:00) ሰዓት ድረስ በተደረገ እልሕ አስጨራሽ ውጊያ በሰረርኩላ እና በቱቲ ከተሞች መሽጎ በነበረው የአገዛዙ ኃይል ላይ እንደ እሳት እያቃጠሉ ጠንካራ ምት አድርገውበታል። ሆኖም የሥርዓቱ ጅምላ ተጋላቢ ኃይል በመሬት ላይ ሊቀበለው የሚገባውን ታሪካዊ ቅጣት ከጀግኖቹ ክንድ ተመግቧል።
የበረሀው ትንታግ በፍቃዱ በላይ ክፍለጦር አንዲት እሳት የለበሰች ሻለቃ ወደ ሰረርኩላ ከተማ በረገጠችበት ቅጽበት በአገዛዙ ጥርቅም ኃይል ላይ የወሰደችው ፈጣንና መብረቃዊ የማጥቃት ስልት ጠላትን ሙሉ በሙሉ ግራ አጋብቶታል። ከዚሕም የተነሳ ጭንቅ ውስጥ የገባውና መውጫ ያጣው የአገዛዙ ኃይል ጫካ ውስጥ ያደራጀውን ዘራፊውን የ"ሸኔ" ስብስብ ለአጋዥነትና ለሕይወት ማዳኛ የጋበዘ ሲሆን የአናብስቶቹ ክንድ የማይነካ በመሆኑ ነገሩ እዳሠበው ሳይሳካ ቀርርቶበታል።
በመጨረሻም ጠላት የሚያስማርከውን አስማርኮ የጓዶቹን አስከሬን እንኳን ሳይሰበስብ ከተማዋን ጥሎ ወደ ጫካ ፈርጥጧል። ጀግኖቹ የሰረርኩላን ከተማ እስከ ምሽቱ ሁለት(2:00) ሰዓት ሙሉ በሙሉ በቁጥጥራቸው ስር አውለዋታል።
በሌላ በኩል በቱቲ ከተማ በተደረገው አውደ ውጊያ እጅ በአፍ የሚያስጭን ነበር። የቱቲ ከተማ በተናዳፊዎቹ ሻለቆች የባሩድ ጢስ ስትታጠን፣ ባሩዱም ሲቆላ በዋለበት በዚያ አስፈሪ ሰዓት ጠላት ምሽጉን በመነጠቁ ከተማዋን ጥሎ ለመውጣት ተገዷል። የወገን ኃይል ከተማዋን ሙሉ በሙሉ በመቆጣጠር ድላቸውን አጣጥመዋል።
ይሕ በእንዲሕ እንዳለ ጠላት በእውር ድንብርና በፍርሃት ተውጦ ዙ-23 እና ሞርተሮችን እያጮኸ ቢውልም በጀግኖቹ የቦታ ቁጥጥርና በማይበገረው የስነ-ልቦና የበላይነት ግንባሩን ተመትቶ እንደ ቅጠል ሲረግፍ አምሽቶ ፣ በዚህ ደማቅ አውደ ውጊያ የተረጋገጠውና በጀግኖቹ እጅ የገባው የምርኮ ዝርዝር እንደሚከተለው ይፋ ሆኗል፦
➾3 ከፋኖ ከድተው ወደ አገዛዙ ገብተው የነበሩ ባንዳዎች
➾1 የአገዛዙ ካድሬ
➾3 የሚሊሻ አባላት
➾የተማረከ ንብረት ዝርዝር ፦
➾8 ክላሽንኮቭ ጠመንጃዎች
➾4 የወገብ ትጥቅ
➾1 የደረት ትጥቅ
➾6 የእጅ ቦንቦች እና... በርካታ ተተኳሽ ጥይቶች በጀግኖቹ እጅ ገቢ ተደርገዋል።
ምንጭ፦ በአፋብን አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ!
3 141
ሳውዲ አረቢያ የሞት ቅጣት ከፈረደችባቸው ውስጥ 4 ኢትዮጵያውያንን ገደለች
የሳውዲ ባለስልጣናት ከ2016 ጀምሮ ቢያንስ 64 ኢትዮጵያውያንን በሞት ቅጣት ፍርድ ገድለዋል፤ ከእነዚህም ውስጥ በ2025 እና 2026 .... 44 ሰዎች ይገኙበታል። https://miniliksalsawi.substack.com/p/saudi-arabia-resumes-executions-after
3 141
ከ"ዘመቻ ህፃን አንሻ ሰይድ" ማግስት የብልፅግና ሰራዊት መፍረሱን ቀጥሏል!
ለብልፅግና የዙፋን መንበር በማወቅም ይሁን ባለማወቅ እየታተረና እየተጋ የሚገኘው ብልፅግና መራሹ ጦር በዘመቻ ህፃን አንሻ ሰይድ በከባድ ሚዛን በፋኖ ክንድ የተመታው ሰራዊት ከአሐዱ በመፍረስ ፋኖ ወደሚገኝበት ቦታ ሁሉ እየተቀላቀለ ይገኛል።
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ 303ኛ ኮር አካል የሆነውን 19ኛ ክፍለ ጦርን የተቀላቀሉት አስር አለቃ አማረ ተፈራ እና ጓደኛው ከ34ኛ ክፍለ ጦር አራተኛ ሬጅመንት በመውጣት የፋኖን ቤት የተቀላቀሉ ሲሆን መከላከያ አሁን ባለው ቁመና የመዋጋት አቅም እንደሌለውና ሰራዊቱም በፍፁም መሰላቸትና በከባድ የስነ-ልቦና ውድቀት ላይ እንደሚገኝ ገልጿል።
በሌላ መረጃ 303ኛ ግዙፉ አሳምነው ኮር አካል የሆነውን 30ኛ ክፍለ ጦርን የተቀላቀሉት የ13ኛ ዕዝ ኦፕሬተር የነበሩት:-
1ኛ. መሰረታዊ ወታደር ማርይሁን ጌታ
2ኛ. መሰረታዊ ወታደር ዮሴፍ አዱኛው
3ኛ. መሰረታዊ ወታደር ቴዎድሮስ ጥላሁን
ሁላቸውንም ቤተሰቦቻቸው ልከው ከሚያስተምሯቸው ኮሌጅ ላይ በማፈን ወደ ማሰልጠኛ በማስገባት ተገደው የገቡ እንደሆኑ ገልፀው የአገዛዙን ጓዳ ከፈተሹና ከመረመሩ በኋላ ለቤተሰቦቻችንና ወንድም እህቶቻችን ማጥፊያ ስርዓትና ተቋም አናገለግልም በማለት ፋኖን እንደተቀላቀሉ ተናግረዋል።
ስቦ በማስከዳት ስርዓቱን ከማፍረስ ጋር ተያይዞ ከመስከረም 14/2018 ዓ/ም ዘመቻ አደም አሊ (አባ ናደው)ን ጨምሮ ለተከታታይ ስምንት ወራት ከ850 በላይ የአገዛዙ ሰራዊት መከላከያ፣ አድማ ብተና፣ ፖሊስ፣ ሚሊሻና ስርዓቱን አገልጋይ ካቢኔ አባላት 303ኛ ግዙፉ አሳምነው ኮር ፋኖን የተቀላቀሉ ሲሆን አሁንም አልረፈደምና ቀሪው የአገዛዙ ሰራዊት በፍጥነት ፋኖን በመቀላቀል ህይዎቱን እንዲታደግ ሲል የኮሩ ፖለቲካ መምሪያ ኃላፊ አርበኛ በሪሁን ደምሌ ጥሪ አቅርቧል።
ምንጭ፦ የምኒልክ ዕዝ ሚዲያና ኮሚኒኬሽን መምሪያ!
Available now! Telegram Research 2025 — the year's key insights 
