en
Feedback
Mereja መረጃ

Mereja መረጃ

Open in Telegram

Information Desk +0 000 000 0000

Show more
2 986
Subscribers
-324 hours
-217 days
-6030 days
Posts Archive
በቡልጋ በተደረገ ውጊያ ቡልጋ ክፍለ ጦር፡ በሪፐብሊካን ጋርድ ኃይል ላይ ከፍተኛ ኪሳራ ማድረሱ ተገለፀ! በአፋብን 5ኛ ዕዝ ከሰም ኮር ቡልጋ ክፍለ ጦር ለከበባ በተንቀሳቀሰው የሪፐብሊካን ጋርድ ኃይል
በቡልጋ በተደረገ ውጊያ ቡልጋ ክፍለ ጦር፡ በሪፐብሊካን ጋርድ ኃይል ላይ ከፍተኛ ኪሳራ ማድረሱ ተገለፀ! በአፋብን 5ኛ ዕዝ ከሰም ኮር ቡልጋ ክፍለ ጦር ለከበባ በተንቀሳቀሰው የሪፐብሊካን ጋርድ ኃይል ላይ ከፍተኛ ድል መቀዳጀቱን የኮሩ ሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አስታወቀ።  የአገዛዙ ስልጣን ጠባቂ የተባለው ሪፐብሊክ ኃይል ከምንጃር አረርቲ ከተማ በመነሳት ወደ በረኸት ወረዳ መተህብላ ከተማ የወረዳው አመራሮችንና የስንቅ አቅርቦት (ሬሽን) ለማድረስ እንቅስቃሴ በማድረግ ላይ ሳለ፣ በቡልጋ ክፍለ ጦር አባላት ባልተጠበቀ ጥቃት ከፍተኛ ኪሳራ አስተናግዷል።  ከምንጃር የተነሳው የአገዛዙ ኃይል ሜጢ በተባለው ልዩ ቦታ ላይ ሲደርስ ከባድ ኪሳራ አስተናግዷል። በተመሳሳይ ሰዓት ከመተህብላ ከተማ በመውጣት የመጣውን ኃይል ለመቀበል ተሬ በተባለ ቦታ በተደረገው የጨበጣ ውጊያ፣ ያልጠበቀው ጥቃት ስለደረሰበት ወደ ኋላ ለማፈግፈግ ተገዷል።  ከ10 ሰዓታት በላይ በፈጀው በዚህ ውጊያ በመንግሥት ኃይል በኩል ከተራ ወታደር እስከ መስመራዊ መኮንኖች ድረስ ሙትና ቁስለኛ መሆናቸው ተገልጿል። በዚሕም አንድ (01) ጥርጥር ክላሽንኮቭ ጠመንጃ ከነ ሙሉ ተተኳሹ መማረኩ ታውቋል።  በዚሕ አውደ ውጊያ ፋኖ በከፍተኛ የስነ-ልቦና የበላይነትና በላቀ ብቃት መጠናቀቁ ተጠቅሷል። እንደ ኮሩ ሕዝብ ግንኙነት ገለፃ፡ የተገኘው ድል በቀጣይ ዘመቻዎች ከፍተኛ የሞራል የበላይነት የሚሰጥ መሆኑን አክሎ ገልጾታል። ምንጭ፦በአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው 5ኛ ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ!

በአዚላ ኦፕሬሽን የተደመሰሰው የጠላት ኃይል ብዛት። (መረጃው የተገኘው ከምርኮኛ ፐርሶኔል ኃላፊ ነው።) በዋግኽምራ ሰቆጣ ደሀና ወረዳ አዚላ ከተማ ላይ ነሀሴ 29/2018 ዓ/ም በተካሄደ ኦፕሬሽን የ
+3
በአዚላ ኦፕሬሽን የተደመሰሰው የጠላት ኃይል ብዛት። (መረጃው የተገኘው ከምርኮኛ ፐርሶኔል ኃላፊ ነው።) በዋግኽምራ ሰቆጣ ደሀና ወረዳ አዚላ ከተማ ላይ ነሀሴ 29/2018 ዓ/ም በተካሄደ ኦፕሬሽን የጠላት ብልፅግና ወታደሮች ሙሉ በሙሉ መደምሰሳቸው ይታወቃል። በአፋብን 2ኛ ምኒልክ ዕዝ ስር ከ303ኛ አሳምነው ፅጌ ኮር የተወጣጡ አሃዶች በቅንጅት በአዚላ ከተማ የጠላት ኃይል ሰፍሮበት የነበረውን ወታደራዊ ካምፕ 360° በመክበብ ከባድ እርምጃ ወስደውበት ሙሉ በሙሉ እንደደመሰሱት መረብ ሚዲያ በወቅቱ መዘገቡ አይዘነጋም። ይህ በምስሉ ላይ የምትመለከቱት የሰው ኃይል መዝገብ በካምፑ ውስጥ ሰፍረው የነበሩ ወታደሮች ብዛትና ስም ዝርዝር ሲሆን፡ በውጊያው ወቅት ከተማረኩት 71 ወታደሮች ውጭ ሌላው ሙሉ በሙሉ ተደምስሷል።

አፋብን በላይ ዘለቀ 3ኛ ዕዝ ዳግማዊ ቴዎድሮስ 5ኛ ኮር ጎንደሬ በጋሻው ክፍለ ጦር አጥናፋ ብርጌድ አባላትን ለማፈን በሌሊት የተንቀሳቀሰው የአገዛዙ ሚሊሻ በደረሰበት ድንገተኛ ምት ከፍተኛ ኪሳራ ደረሰበት! ከሌሊቱ 11:00 ሰዓት ጀምሮ በወገራ ወረዳ  ልዩ ቦታው ብራ ታዲወስ የጠላት ኃይል አፋብን በላይ ዘለቀ 3ኛ ዕዝ ዳግማዊ ቴዎድሮስ 5ኛ ኮር ጎንደሬ በጋሻው ክፍለ ጦር አጥናፋ ብርጌድ አባላት ላይ አፈና ለመፈጸም እንቅስቃሴ አድርጎ የነበረውን የጠላት ኃይል የመልሶ ማጥቃት እርምጃ 3 የኃይል አባላትን ሲደመሰሱ 9 ያህሉን ደግሞ  ከቀላል እስከ ከባድ ቁስለኛ ሆነዋል። በዚህ ድንገተኛ ምት የተደናገጠው የጠላት ኃይል በርካታ ንብረቶችን  ጫማዎችን እና ትጥቆችን እያዝረከረከ ከአምባጊወርጊስ ከተማ ተጨማሪ የመከላከያ እና የአድማ ብተና ኃይል በማስገባት በብራ ታዲወስ እና ሰንበትየ ዙርያ  እየተንቀሳቀሰ ይገኛል። በዚህ ድንገተኛ ምት ሽንፈት የደረሰበት ኃይል ​ተመስገን ጌታ የኋሌ የተባለ የ10 ዓመት ህፃን የተገደለ ሲሆን፣ በክረምት የግብርና እና የእንስሳት ጥበቃ ሥራ ላይ የነበሩ ከ28 በላይ ንፁሃን ዜጎች "የፋኖ ቤተሰብ ናችሁ" በሚል ሽፋን ታስረዋል። ከነዚህ መካከል እድሜ ጠገብ አዛውንቶች፣ ሴቶች እና ህፃናት እንደሚገኙበትና የአርሶ አደሩ እንስሳት ጭምር ማለትም ከብት፣ በግ፣ ፍየልና ዶሮዎችን የማረድ እና የመዝረፍ ድርጊት ዘግናኝ ችግሮችን እየተፈጸመ መሆኑን መረጃውን ያደረሰን የክፍለ ጦሩ የህዝብ ግንኙነት ነው። ምንጭ፦በ​አፋብን በላይ ዘለቀ 3ኛ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ!

በውጊያ መኃል የቆሰለው የጠላት ወታደር እጅ እንዲሰጥ ተጠየቀ።  አንድ የፋኖ አባል "እጅ ስጥ፣ አንጎዳህም ወንድሞችህ ነን፡ እጅህን ሰጥተህ ሕይወትህን አትርፍ" በሚል ይናገራል። ይህን ጊዜ ያ የቆሰለው ወታደር አንድ ጊዜ ተኩሶ እጅ ስጥ በሚል ጥሪ ያቀረበለትን የፋኖ አባል እጁ ላይ መታው። ቁስለኛው ወታደር የፋኖ አባሉን ካቆሰለ በኋላ ክላሹን ወርውሮ እጁን ሰጠ። ይህን ጊዜ ፋኖዎቹ በፍጥነት ሄደው ከወደቀበት በማንሳት ቁስሉን በፋሻ ይጠቀልሉለት ጀመሩ። የሚገርመው ነገር የዚህን የጠላት ወታደር ቁስል በፋሻ ከሚጠቀልሉለት ፋኖዎች መካከል አንዱ እጅ ስጥ እያለ እንዳለ ቁስለኛው ወታደር ተኩሶ እጁን የመታው ነው። እጁ ላይ ተመትቶ  የራሱ ደም እየፈሰሰ ግድ አልሰጠውም፡ የማረከውን ቁስለኛ ሕይወት ለማትረፍ ይረባረባል እንጂ። የእርሕራሔና የእዝነት መለኪያው የአማራ ፋኖ! ይሄንን ያደረገው በአፋብን 4ኛ ቢዛሞ አንሻ ሰይድ ዕዝ አባል ነው። ( መረብ ሚዲያ )

ኦህዴዶች የቻሉትን በግሬደርና በቡልዶዘር፣ ያልቻሉትን ደግሞ በእሳት እያወደሙ አዲስ አበባ ላይ የዲሞግራፊ ቅየራውን ተያይዘውታል! ዛሬ ነሀሴ 30/ 2018 ዓ/ም ምሽት ጀምሮ አዲስ አበባ መርካቶ በእ
ኦህዴዶች የቻሉትን በግሬደርና በቡልዶዘር፣ ያልቻሉትን ደግሞ በእሳት እያወደሙ አዲስ አበባ ላይ የዲሞግራፊ ቅየራውን ተያይዘውታል! ዛሬ ነሀሴ 30/ 2018 ዓ/ም ምሽት ጀምሮ አዲስ አበባ መርካቶ በእሳት እየጋየ ነው። የበርካታ ለፍቶ አዳሪ ነጋዴዎች ሀብት ንብረት የእሳት ሲሳይ ሆኖ ቀርቷል። አደጋው ተባብሶ ቀጥሏል፡ እስካሁን የደረሰ የእሳት አደጋ መከላከያ ሠራተኛ የለም። ከበላይ አካላት በመጣ ትዕዛዝ እንዳይንቀሳቀሱ ታግደዋል።

የእነ አብይ ውንብድና .... በአዲስ አበባ የሚሰለጥነው ሰራዊትና የከተማ ውጊያው

photo content

በምዕራብ ሸዋ ዞን እና በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን በሚገኙ የአማራ ተወላጆች ላይ መንግስት መር ጭፍጨፋ ሊካሄድ ነው! ከነሃሴ 12/2018 ዓ/ም ጀምሮ በምስራቅ ወለጋ ዞን አንገር ጉትን ከተማን ጨምሮ በጊዳ አያና ወረዳ እየተፈፀመ ያለው የንፁኋን እልቂት አድማሱን አስፍቶ በምዕራብ ሸዋ ዞን ስር በኖኖ ወረዳና በአከባቢው እንዲሁም በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን አመያ ወረዳና አከባቢው ላይ በቅርቡ መንግስት መር ጭፍጨፋ እንደሚካሄድ ጥቆማዎች እየወጡ ነው። ለዚህም ደግሞ በአቶ ጃዋር መሀመድ የተመሠረተው ኦኤምኤን/omn/ ሚዲያና ሌሎች የኦሮሞ ፅንፈኛ ኃይሎች ከወዲሁ በአከባቢው አማራዎች ላይ ሀሰተኛ ታርጋ የመለጠፍ ስራ እየሰሩ ይገኛሉ። እነዚህ ፅንፈኛ ኃይሎች ከሳምንታት በፊት በወለጋ አማራዎች ላይ የተቀናጀ ሀሰተኛ ታርጋ የመለጠፍ ዘመቻ ሲያካሂዱ የነበረ ሲሆን፡ በቀናት ልዩነት በመከላከያ ሠራዊቱ፣ በክልሉ ልዩ ኃይል፣ በአባ ገዳ ኮማንዶ፣ በረፔ ሎላ፣ በጋቼና ሲርና እንዲሁም በሚኒሻና በእነዚህ ታጣቂዎች ሽፋን የሚሰጣቸው ቆንጨራና ሌሎች ስለታማ መሣሪያዎችን የታጠቁ የቄሮ ቡድን አባላት ጋር በቅንጅት በከፈቱት ዘግናኝ ጭፍጨፋ ከ200 በላይ ንፁኋን ወገኖች ሲገደሉ፡ አሥር የሚደርሱ መንደሮችና ከተማዎች መውደማቸውን መረብ ሚዲያ በተከታታይነት መዘገቡ አይዘነጋም። ይህ መንግስት መር እልቂት ተባብሶ የቀጠለ ሲሆን፡ ቅድመ ጭፍጨፋ የማመቻቸት ስራ ሲሰሩ የነበሩትና በጭፍጨፋው ወቅት የአማራ ተወላጆችን አስከሬን ምስልና ብዛት በመውሰድ "ኦሮሞ ተገደለ" በሚል ለቅሶ በመቀማት እኩይ ሴራ ተሰማርተው የነበሩት እነዚኸው ቆሞ ቀር፣ ወራሪና ጨፍላቂ እንዲሁም ጨፍጫፊ የኦሮሞ ፅንፈኛ ኃይሎች፡ አሁንም በተመሣሣይ በምዕራብ ሸዋ ዞን እና በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን በሚገኙ የአማራ ተወላጆች ላይ ጭፍጨፋ እንዲካሄድ ቅስቀሳ ጀምረዋል። የብሔር ግጭት ቀስቃሽና ሀገር  አፍራሽ መልዕክቶችን በማስተላለፍና ንፁኋን በገፍ በማስጨፍጨፍ የሚታወቀው አቶ ጃዋር መሀመድ ባቋቋመው ኦኤምኤን ሚዲያና ሌሎች ቆሞ ቀርና ወራሪ እንዲሁም ጨፍላቂና ጨፍጫፊ ፅንፈኛ የኦሮሞ ኃይሎች በተጠቀሱት አከባቢዎች "ኦሮሞ ተገደለ" በሚል በቀጣይ በአማራ ተወላጆች ላይ ለሚፈፀመው ጭፍጨፋ  የተቀናጀ ታርጋ የመለጠፍ ዘመቻ መጀመራቸውን መረብ ሚዲያ ተመልክቷል። ስለሆነው በአከባቢው የሚገኙ የአማራ ተወላጆች ከወዲሁ ቅድመ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ እናሳስባለን።

ካለፉት አራት ቀናት ጀምሮ በተከታታይ መነሻውን ከደባርቅ እና ከማይጠብሪ በማድረግ ወደ ዛሪማ ስትራቴጂካዊ ቦታዎች ተንቀሳቅሶ በነበረው የጠላት ብልፅግና ኃይል ላይ በተወሰደ እርምጃ 20 ወታደሮች ሲገደሉ ከ60 በላይ መቁሰላቸው ታወቀ። በውጊያው ከፋኖ አፈሙዝ ለማምለጥ የእውር ድንብራቸውን ሲሸሹ ከነበሩ የጠላት ኃይሎች መካከል ሰባት ወታደሮች አንድ ብሬንን ጨምሮ ከነሙሉ ትጥቃቸው ዛሪማ ወንዝ ሰጥመው ሕይወታቸው ማለፉን መረብ ሚዲያ ከ3ኛ ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ለማረጋገጥ ችሏል። በተጋድሎው 15 ክላሽንኮፍ መሣሪያን ጨምሮ ሌሎች የወታደራዊ ቁሳቁሶችና ገዢ ስፍራዎች በፋኖ ቁጥጥር ስር ውለዋል።

በሸዋ ጠቅላይ ግዛት መነሻውን ከዓለም ከተማ አድርጎ ወደ ኮላሽ ቀበሌ የኃይል ቅያሬ ለማድረግ ሲንቀሳቀስ በነበረ የጠላት አየር ወለድ ኮማንዶ ላይ በተወሰደ የቆረጣ ማጥቃት እርምጃ በርካቶች መደምሰሳቸው ታወቀ። ከደፈጣ ማጥቃት ወደ ሙሉ የጨበጣ ውጊያ ተቀይሮ ግማሽ ቀን በፈጀው በዚህ ተጋድሎ በርካታ የአየር ወለድ ኮማንዶ አባላት ሲገደሉ፡ በርካቶች ቆስለው ለሕክምና ወደ ዓለም ከተማ እናት ሆስፒታል የተወሰዱ ቢሆንም፡ ነገር ግን ሆስፒታል ከደረሱ በኋላ ሕይወታቸው ያለፈ ወታደሮች መኖራቸውም ተሰምቷል።

photo content

የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ዕዞች የ2019 ዓ/ም የትምህርት ዘመን መደበኛ የመማር ማስተማር ሥራ በይፋ እንዲጀመር ጥሪ አቅርበዋል! ​ትምህርት ለአንድ ሀገር ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ እድገት ወሳኝ መሠረት መሆኑ በውል የሚታወቅ ሲሆን፤ ሀገራችን ከገጠማት ውስብስብ ችግር እና የጸጥታ ስጋት አንጻርም ጭምር የትምህርትን አስፈላጊነት ከግምት ውስጥ በማስገባት የ2019 ዓ/ም የትምህርት ዘመን በወቅቱ እና በአግባቡ እንዲጀመር የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ዕዞች ጥሪ አስተላልፈዋል። ​የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ባስቀመጠው አጠቃላይ አቅጣጫ መሠረት፦ ፩. አፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው 5ኛ ዕዝ (በማኅበራዊ ጉዳዮች መምሪያ ኃላፊ አርበኛ አስታወሰኝ ላቀ  በኩል) እንደገለጸው፤ ትምህርት ሰላም እና መረጋጋት ቢፈልግም፣ ከሀገራችን ነባራዊ ሁኔታ አኳያ በስጋት ውስጥ ሆነንም ቢሆን የ2019 ዓ/ም የትምህርት ዘመን የመማር ማስተማር ሥራ በወቅቱ እንዲጀመር አቅጣጫ ተቀምጧል። በመሆኑም በየደረጃው ያሉ የፋኖ አመራሮች፣ ወላጆች፣ መምህራን፣ ርዕሰ መምህራን እና የሚመለከታቸው አካላት ሁሉ የበኩላቸውን ኃላፊነት እንዲወጡ ጥሪ ቀርቧል። ፪. አፋብን ጎጃም ጠቅላይ ግዛት ቴዎድሮስ 2ኛ ዕዝ ለሁሉም ኮሮች ባስተላለፈው ጥሪ፣ ድርጅታችን ባስቀመጠው አቅጣጫ መሠረት መደበኛ ትምህርት እንዲጀመር አሳስቧል። ለዚህም ስኬት አስፈላጊው ቅድመ ዝግጅት እንዲደረግ አሳስቦ፣ ሁሉም ኮሮች ትምህርት እንዲጀምሩ ጥሪ አቅርበዋል። ፫. አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዘለቀ 3ኛ ዕዝ (በማኅበራዊ ጉዳይ መመሪያ ኃላፊ አርበኛ ብዙአየሁ ወንድምነው አማካኝነት) በሰጠው መግለጫ፣ ድርጅቱ ያስቀመጠውን አቅጣጫ መሠረት በማድረግ በዕዙ ሥር የሚገኙ ሁሉም ኮሮች አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት አድርገው ትምህርት እንዲያስጀምሩ አሳስቧል። ሙሉው ሕዝብ፣ መምህራን፣ የተማሪ ወላጆች እና ባለድርሻ አካላት አስፈላጊውን ኃላፊነት እንዲወጡ ጥሪ ተላልፏል። ፬. አፋብን ወሎ ቤተ-አማራ ጠቅላይ ግዛት ምኒልክ 1ኛ ዕዝ በሰጠው ማሳሰቢያ፣ የ2019 ዓ/ም የትምህርት መርሐ ግብር እውን እንዲሆን በቁጥጥራቸው ሥር በሚገኙ አካባቢዎች የሚገኙ ትምህርት ቤቶች ወደ ሥራ እንዲገቡና የምዝገባ ሥራዎች እንዲጀመሩ አሳስቧል፤ ለዚህም አስፈላጊው ትብብር እንዲደረግ ጥሪ አቅርቧል። ​በአጠቃላይ የአፋብን ዕዞች ባስተላለፏቸው መልእክቶች፤ ትውልድን ለማዳን፣ አስተሳሰብን ለመገንባት እና ትናንትን በአዲስ ተስፋ ለመተካት ትምህርት ቤቶች መደበኛ አገልግሎታቸውን እንዲጀምሩና መላው የህብረተሰብ ክፍል አስፈላጊውን እገዛና ትብብር እንዲያደርግ አጽንኦት ተሰጥቷል። ምንጭ፦የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ(አፋብን) ወታደራዊ ቃል አቀባይ

በዞብል እና በተኩለሽ ግንባር በአገዛዙ ሠራዊት ላይ ከባድ ጥቃት ተፈፀመ! የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ምኒልክ 1ኛ ዕዝ የ102ኛ ኮር የ12ኛ ክፍለጦር ቃኝ ትናንት ነሐሴ 26 /2018 ዓ/ም በራያ ቆቦ ወረዳ ከቆቦ ከተማ በምስራቅ እና በምዕራብ በሚገኙ በዞብል እንድሁም በተኩለሽ በተባሉ አካባቢዎች በአገዛዙ ሰራዊት ላይ ያልተጠበቀ የደፈጣ ጥቃት ወሰዱ። አገዛዙ ከቆቦ ከተማ በምዕራብ ግንባር እና በምስራቅ ግንባር ከሌሊቱ 10 ሰዓት ጀምሮ ጥቃት ሊከፍት እንዳሰበ የ102ኛ ኮር ፀረ-መረጃዎች ባገኙት መረጃ መሰረት የ102ኛ ኮር የ12ኛ ክፍለጦር ቃኝ በሌሊት ተስበው ቀድመው ቦታዎችን በመያዝ ጠላት ባልጠበቀው እና ባለአቀድው መንገድ ዋጋ አስከፍለውታል። በመሆኑም አገዛዙ የ102ኛ ኮር የ12ኛ ክፍለጦር ቃኝ ጀግኖችን ክንድ መቋቋም ባለመቻሉ በሁሉም አቅጣጫ ወደ ኋላ እንድያፈገፍግ ተገዷል። በአውደ ውጊያው የተገኘ አጠቃላይ ውጤት 7 ክላሽን ኮፍ መሳሪያ ፣ ስድሰት F1 ቦንብ ፣ አምስት የወገብ ትጥቅ ፣ሁለት ሞርኮ ፣ አስራ ሶስት የተደመሰሰ እንዲሁም ስምንት ቆስሏል። ምንጭ፦ በአፋብን 1ኛ ምኒልክ ዕዝ የ102ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት ክፍል!

photo content

የብልፅግና አገዛዝ 101ኛ አየር ወለድ ኮማንዶ ክፍለ ጦር ክፉኛ መመታቱ ተገለፀ!! የአፋብን አሳምነው 5ኛ ዕዝ አፄ አምደጽዮን ኮር አፄ ዳዊት ክፍለ ጦር መርሐቤቴ ዓለም ከተማ መሽጎ የነበረው 101ኛ አየር ወለድ ኮማንዶ ክፍለ ጦር፣ ለኃይል ቅያሪ እንቅስቃሴ እያደረገ ባለበት ሰዓት በፋኖ የደፈጣ ጥቃት ከፉኛ መመታቱን የኮሩ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ክፍል ኃላፊ አስታወቀ። የአፄ ዳዊት ክፍለ ጦር፣ ጠላት ከዓለም ከተማ ተነስቶ ወደ ኮላሽ ቀበሌ የኃይል ቅያሬ ለማድረግ ሲንቀሳቀስ፣ የወገን ኃይል ልዩ ቦታው ከማጋስ መሳለሚያ እስከ አበርጅት ድረስ ደፈጣ በመያዝ፣ ጠላት አቅዶት የነበረውን የኃይል ቅያሬ እቅድ እዳያሳካ ሲደረግ የሰውና የንብረት ኪሳራ ማስተናገዱን ታውቋል። ከጠዋቱ 2:00 ሰዓት ጀምሮ የተከፈተው ጥቃት እስከ ቀኑ 07:00 ሰዓት ድረስ የዘለቀ ሲሆን፣ መጀመሪያ ከተደረገው የደፈጣ ጥቃት ወደ ተሟላ የግንባር ውጊያ በመቀየር፣ የጠላትን እቅድ ያከሸፈ፣ የንብረትና የኃይል ውድመት ያደረሰ ውጊያ መካሔዱን አክሎ ገልጿል። በዚሕ ኦፕሬሽን በርካታ የጠላት ኃይል የተደመሰሰና የቆሰለ ሲሆን፣የተመታው ኃይል አሁንም ድረስ እዳልተነሳና ቁስለኛዎችን ብቻ ወደ ዓለም ከተማ እናት ሆስፒታል እያመላለሰ እንደሚገኝ ከስፍራው ባለን መረጃ አረጋግጫለሁ ብሏል። በደረሰበት ድንገተኛ ጥቃት የተደናገጠው የጠላት ኃይል፣ የዋርኝና የኮራ ተራሮችን በዶሽቃና በዙ-23 ከባድ መሣሪያዎች እየደበደበ እደሚገኝ ገልጿል። ምንጭ፦ በአፋብን 5ኛ አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ!

photo content

"Fano's Kingdom" የፎቶ ኤግዚቢሽን በርካታ የዓለም ሚዲያዎችና ታዳሚዎች በተገኙበት በፈረንሳይ እየተካሄደ ይገኛል በፈረንሳይ ፐርፒኛን ከተማ በሚገኘው ኩቫን ዴ ሚኒም (Couvent des Minimes) አዳራሽ እየተካሄደ በሚገኘው ታዋቂው Visa pour l'Image ዓለም አቀፍ የፎቶ ጋዜጠኝነት ፌስቲቫል ላይ፣ ፍራንሳዊው የፎቶ ጋዜጠኛ ሮቢን ቱቴንገስ (Robin Tutenges) ያዘጋጀው "Fano's Kingdom" የተሰኘው የፎቶ ኤግዚቢሽን የበርካታ ታዳሚዎችን ትኩረት ስቧል። ኤግዚቢሽኑ የፋኖ ህዝባዊ ትግል፣ የታጣቂዎቹን ተጋድሎና ፅናት፣ እንዲሁም የተቆጣጠሯቸውን ቀጠናዎች ተጨባጭ ሁኔታ ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ በግልፅ የሚያስተዋውቅ ነው። የፎቶ ጋዜጠኛው ሮቢን ቱቴንገስ ከዓለም አቀፍ ሚዲያዎች ትኩረት ተከልለው በነበሩና በፋኖ ቁጥጥር ስር ባሉ የሰሜን ወሎና የላስታ ተራራማ ቀጠናዎች ውስጥ ለበርካታ ቀናት በአካል ተገኝቶ ተንቀሳቅሷል። ጋዜጠኛው በነበረው ቆይታ የፋኖ ታጣቂዎችን ዕለታዊ ህይወት፣ ጥንካሬ፣ ወታደራዊ ስልጠና፣ ከህዝብ የሚደረግላቸውን ሙሉ ደጋፊነትና በየካምፑ ያለውን የወንድማማችነትና የፅናት መንፈስ በጥራት በሚያሳዩ ምስሎች አስደግፎ መረጃዎችን አሰባስቧል። በተጨማሪም የመንግስት ሃይሎች በሰላማዊ ህዝብ ላይ ያደረሱትን እንግልትና የሰብአዊ መብት ጥሰቶች በስፍራው በመገኘት መዝግቧል። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ፣ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ተቋማትና ዋና ዋና የዓለም ሚዲያዎች ለፋኖ እንቅስቃሴና በስፍራው ለሚካሄደው ህዝባዊ ትግል የሚሰጡት ትኩረት እየጨመረ መምጣቱ ይታወቃል። ይህ በፈረንሳይ የቀረበው ኤግዚቢሽንም የዚሁ ማረጋገጫ ሲሆን፣ በዝግጅቱ ላይ መላው ዓለም የተሰባሰቡ የኪነ-ጥበብ አፍቃሪያን፣ የታሪክ ተመራማሪዎችና ዳያስፖራዎች በነቂስ በመውጣት ታድመዋል። የለንደን ፋኖዎችም ከለንደን በመጓዝ በኤግዚቢሽኑ ላይ ቴድመዋል። ከዚህም በተጨማሪ በርካታ ዓለም አቀፍ የቪዲዮና የፎቶ ጋዜጠኞች በስፍራው በመገኘት የኤግዚቢሽኑን ሂደትና የታዳሚዎችን አስተያየት በቪዲዮ ሲቀርፁ ታይተዋል። ይህ ዝግጅት የፋኖን ህዝባዊ እንቢተኝነትና በክልሉ ያለውን ተጨባጭ ሁኔታ ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ በይፋ በማስተዋወቅ ረገድ ትልቅ አህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ሽፋን እንዲያገኝ አድርጓል።

አፋብን በላይ ዘለቀ 3ኛ ዕዝ 208ኛ ራስ አሞራው ውብነህ ኮር  ድብ ጠለምት ተከዜ ክፍለ ጦር በጠላት ኃይል ላይ ከፍተኛ ጀብድ ተቀዳጅቷል። የጠላት ኃይል ለተከታታይ 4 ቀናት መነሻውን ከደባርቅ እና ከማይጠብሪ  በማድረግ ወደ ዛሪማ ስትራቴጂካዊ አቅጣጫ እንቅስቃሴ ያደረገ ሲሆን፣ የክፍለ ጦሩ 1ኛ እና 2ኛ ሬጅመንቶች በቅንጅት በወሰዱት የደፈጣ እና  ማጥቃት እርምጃ ልዩ ስሟ «ፍድቃ» በተባለች ቦታ ላይ ጠላትን በጽኑ በመደምሰስ ከፍተኛ የሰው እና የቁሳቁስ ኪሳራ አድርሰውበታል።​ በዚሁ የአውደ ውጊያ ቀጣና ላይ የነበረውን ወታደራዊ የበላይነት ለማረጋገጥ የአመራሩ እና የውጊያ ውህደቱ ቁልፍ ሚና ተጫውቷል። እድሜ ጠገቡ አርበኛ ሻለቃ ሰፈር መለሰ በተሳተፈበት በዚህ አውደ ውጊያ ፣አርበኛ ይርጋ ክቡሬ እና አርበኛ ጉርባ ይበይን ግንባር ቀደም በመሆን ከፍተኛ ጀብድ ፈጽመዋል። በተመሳሳይ መልኩ አርበኛ አይቸው መብራቱ (ሸሪፎ) እና አርበኛ አራገው ዳኘው የሰራዊቱን የማዋጋትና የውጊያ ስልት የመምራት አቅማቸውን በተግባር በማሳየት፣ ከሁለት አቅጣጫ የተንቀሳቀሰውን የጠላት ኃይል አሰላለፍ በመበተን እና ከፍተኛ ወታደራዊ ጠቀሜታ ያላቸውን ስትራቴጂካዊ ቦታዎች በመቆጣጠር የጠላትን ሰራዊት ሙሉ በሙሉ ከጥቅም ውጭ አድርገውታል። በጠላት ወታደራዊ መዋቅር ላይ የደረሰው ኪሳራ ሰባዊ ቁሳዊ ኪሳራ:- ➛15 ክላሽኮቭ ጠመንጃዎች ተማርከዋል፤ ➛1150 የብሬን እና የክላሽኮቭ ተተኳሾች ተማርከዋል፤​➛4 የመከላከያ (መትረጊስ) እና የአድማ ብተና አባላት  ተማርከዋል፤​ ➛ከ60 በላይ ከከባድ እስከ ቀላል ቁስለኛ፤ ➛20 የጠላት አባላት ሙሉ በሙሉ የተደመሰሰ( ከነዚህም ሁለቱ ቀደም ሲል በፋኖ ስም በቀጣናው ላይ ዘረፋ እና ግድያ ሲፈጽሙ ቆይተው እርምጃ ሊወሰድባቸው ሲባል ወደ ጠላት ሰፈር በመቀላቀል የመንገድ መሪነት ሚና ሲጫወቱ የነበሩ ናቸው።) ➛7 የጠላት አባላት ወደ ዛሪማ ወንዝ ገብተው በስመጥ ህይወታቸው ያለፈ፤ ➛1 ብሬን (መትረጊስ) እና 8 AK-47 ክላሽኮቭ ጠመንጃዎች ይዘው የጠላት አባላት ከዕዝ ሰንሰለት ተበታትነው ጠፍተዋል። ምንጭ፦በ​አፋብን 3ኛ በላይ ዘለቀ ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ!

አፋብን በላይ ዘለቀ 3ኛ ዕዝ 204ኛ አስቻለው ደሴ ኮር ጋፋት ክፍለ ጦር የደፈጣ ጥቃት በመፈጸም  በጠላት ላይ  ከፍተኛ ኪሳራ አደረሰ! ​በደቡባዊ ጎንደር ዞን ከደብረ ታቦር  በቅርብ ርቀት ወደ ጋሳይ ከተማ በመጓዝ ላይ በነበረ የአገዛዙ ሰራዊት ላይ በተጣለ ደፈጣ 204ኛ አስቻለው ደሴ ኮር ጋፋት ክፍለ ጦር ደጀን ብርጌድ ከፍተኛ ሰብአዊ እና ቁሳዊ ጉዳት አድርሰዋል። ​ልዩ ስሟ “ዋዶ” በተባለ  ቦታ ላይ በተካሄደው ከባድ አውደ ውጊያ፣ የአገዛዙ ሚሊሻ አባላት የሆኑ 5 ሰራዊቶቹ ወዲያውኑ ሲደመሰሱ 7 የሚሆኑት ደግሞ ከባድ እና ቀላል የአካል ጉዳት አስተናግደው  ደብረ ታቦር ሆስፒታል ገብተዋል። በአውደ ውጊያው ከተደመሰሱ የአገዛዙ ኃይሎች  3 የነፍስ ወከፍ  ክላሽኮቭ የጦር መሳሪያዎች ገቢ ሆነዋል። ምንጭ፦በ​አፋብን 3ኛ በላይ ዘለቀ ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ!

photo content