ካሊድ አቅሉ
رفتن به کانال در Telegram
8 526
مشترکین
-424 ساعت
-347 روز
-19330 روز
آرشیو پست ها
8 525
*ሱፊዎች የሚነግሩን የእዉቀት እርሀብ የሚሻረዉ በማሰብ ብቻ ነዉ ለዚህም ነዉ ሩሚ ሲናገሩ “ ማሰብ የማይችል ሰዉ በገሀነም ተጥሎ ሳለ ነገር ግን ለዘላለማዊነት አሁንም የሚጨነቅ ሰዉን ይመስላል” የሚሉት
ሰላም ዋሉልኝ !
8 525
ጁመአ
هَلْ جَزَاءُ الْإِحْسَانِ إِلَّا الْإِحْسَانُ
የበጎ ሥራ ዋጋ በጎ እንጅ ሌላ ነውን?
فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
(ሱረቱ አል ረሕማን 60- 61)
8 525
ማራት አልኩኝ
( ካሊድ አቅሉ)
በስግደት ላይ በፀሎት
ዉስጥ እረስቼሽ ዝም
እያልኩኝ
ድንገት ጎኔ ስታስነጥስ
ተሯርጭ ማራት አልኩኝ !
ሰዉም ቅፅበት ፍጡር ነዉሩን
ደብቆ ለሌላ ይማፀናል
ይማርህ ለሚሉት ደስታ ባጀበዉ
ገፅ ያኑራቹ ይላል ።
8 525
Repost from ካሊድ አቅሉ
የደመቁ ገፆች . . . . . .
እንዲህ ስትልም ተጠምደሃል ፦ አንዳንዴ መስኪድ የምሔደው ለማንቀላፋት ነው "
" ከፈጣሪ ጋር በሠላም የሚኖር ብቻ
ነው በስግደት ላይ እያለ እንቅልፍ
የሚወስደው ። "
ቃዲው ቢገርመውም ዑመር ተበርታትቶ ቀጠለ ፦
" ተአምኖን እንደ አንዳንዶች ፣ የፍርድና የፍርሀት ጉዳይ አድርጌ አልቆጥረውም ። እነሆ የኔ ፀሎት ፦ ፅጌሪዳዋን ማድነቅ ፣ ክዋክብትን መቁጠር - ማስላት ፣ የፍጥረት - ዐለሙን ትንግርት መዘከር . . . ስለ ሰብአዊ ፍጡር - ስለዚህ ድንቅ የአምላክ ቁራጭ ፍጡር - መገረም ነው።
አእምሮውን ዕውቀት፣ ልብን ፍቅር የሚጠማው . . . የህዋሳቱስ ንቃትና እርካታ ! . . . ድንቅ ዘድንቅ ፍጡር!"
" አድምጠኝ ወጣቱ ጓዴ ሆይ ፣ ሀያሉ እግዜአብሔር ለሰው ልጅ የሚለግሳቸው ውድ ነገሮች ሁሉ ተለግሰውሃል ። አእምሮ ፣ አንደበት ፣ ጤና ፣ መልክ ፣ የዕውቀት ፣ ጥማትና የሕይወት ጉጉት ። የሰው አድናቆትና እንዲሁም - አይጠረጠርም - የሴቶች አፍቅሮት ። የአርምሞ ክሂሎት እንዳልነፈገህም እተማመናለሁ። ያለ አርምሞ ፣ ያለ ዝምታ ከላይ የዘረዘርኳቸው ሁሉ አይጠቅሙም ። "
" እንዴ! የማስበውን ሁሉ መናገር እንድችል እስከ እርጅና መጠበቅ አለብኝ ?"
" ያሰብከውን ሁሉ መናገር እስክትችል የልጅ ልጆችህ ያረጃሉ ። የምንኖርበት ዘመን የምስጢር መያያዝና የመፈራራት ዘመን ነው። ሁለት ፊት ያሻሃል። አንዱን ለሰፊው ህዝብ የምታሳየው ፣ አንዱን ለራስህና ለፈጣሪ የምትይዘው። ዓይኖችህን ፣ ምላስህንም ጭምር ሳታጣ እንድትኖር ከፈለግህ እንደሌሉህ አርገህ ቁጠራቸው ። "
-----------------------------------
ዑመር ኻህያም እንደፃፈው
ረ/ፕሮፌሰር ተስፋዬ ገሠሠ እንደተረጎሙልን ።
8 525
Jumea
“ Always Be Ready To Say , Good bye To Any Thing “
ጁመዓ
“ሁልጊዜ ዝግጁ ሁን ሁሉንም ነገር ለመሰናበት ። “
8 525
“አሳላፊ ቅጣት መጋቢ ይቅርታ
እኔ ጎድሎ አዳም እኔ ሙሉጌታ!”
ሙሉጌታ ተስፍዬ
(አያ ሙሌ)
መገን አንተ ሩቅ ሰዉ
ሀድራህ የሚካድም
ብዕርህ የሰላ
ከመኖር ሚቀድም !
( ካሊድ አቅሉ)
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
