uz
Feedback
ካሊድ አቅሉ

ካሊድ አቅሉ

Kanalga Telegram’da o‘tish

"ከባባድ ጥያቄዎች በቀላል መልሶች ይረታሉ" ሀሳብ ለማስፈንጠር.... @kalu30

Ko'proq ko'rsatish
8 647
Obunachilar
-924 soatlar
-567 kunlar
-20730 kunlar
Postlar arxiv
Story

Jumea “ Always Be Ready To Say , Good bye To Any Thing “ ጁመዓ “ሁልጊዜ ዝግጁ ሁን ሁሉንም ነገር ለመሰናበት ። “
Jumea “ Always Be Ready To Say , Good bye To Any Thing “ ጁመዓ “ሁልጊዜ ዝግጁ ሁን ሁሉንም ነገር ለመሰናበት ። “

“አሳላፊ ቅጣት መጋቢ ይቅርታ እኔ ጎድሎ አዳም እኔ ሙሉጌታ!” ሙሉጌታ ተስፍዬ (አያ ሙሌ) መገን አንተ ሩቅ ሰዉ ሀድራህ የሚካድም ብዕርህ የሰላ ከመኖር ሚቀድም ! ( ካሊድ አቅሉ)
“አሳላፊ ቅጣት መጋቢ ይቅርታ እኔ ጎድሎ አዳም እኔ ሙሉጌታ!” ሙሉጌታ ተስፍዬ (አያ ሙሌ) መገን አንተ ሩቅ ሰዉ ሀድራህ የሚካድም ብዕርህ የሰላ ከመኖር ሚቀድም ! ( ካሊድ አቅሉ)

Story

አልኩሽ ጨረቃ ( ካሊድ አቅሉ) “ቀትር አይደለ እንምሰል ፀሀይ ጊዜን ይመስላል የሁሉም ፀባይ “ ብለሽ ነግረሺኝ . . . ማምሻ ጠብቄ ካደለኝ አምላክ ልሆን የበቃ ለካ ሙሉነት ደርሶ መጉደልም አንቺጋ አበቃ እኔም አጅቦኝ ፀሀይ ባልኩሽ አፍ አልኩሽ ጨረቃ !

ዋንጫዉን ለ ፒኤስጂ ባላንዶሩን ላንተ ትለያለህ 😊🙏
ዋንጫዉን ለ ፒኤስጂ ባላንዶሩን ላንተ ትለያለህ 😊🙏

"የምስጢር ፍቅር" °°°°°°°°°°°°°°° (ነብይ መኮንን) ከጀማው መካከል ፥ በዐይኔ ሳምኩሽና፤ ከአደባባይ መሀል ፥ በዐይንሽ ሳምሽኝና፤ እንደቆረበ ሰው ፥ አፋችንን ይዘን፤ "ዋ! ትናገርና!...
"የምስጢር ፍቅር" °°°°°°°°°°°°°°° (ነብይ መኮንን) ከጀማው መካከል ፥ በዐይኔ ሳምኩሽና፤ ከአደባባይ መሀል ፥ በዐይንሽ ሳምሽኝና፤ እንደቆረበ ሰው ፥ አፋችንን ይዘን፤ "ዋ! ትናገርና!..." "ዋ! ትናገሪና!..." አልን በሆዳችን። ===========||==========

- ካመናቸዉ ይልቅ የጠረጠርናቸዉ በብዙ ቃል ጠብቀዋል ። ( ካሊድ አቅሉ)

መራር ሀቅ!
መራር ሀቅ!

“ ወዳጆቼና ተከታዮቼ ሆይ - በርካታ እምነቶች ባዶ ሃይማኖት ላለዉ ሕዝብ እዘኑለት። ያልሸመነዉን ጨርቅ ለሚለብስ ፤ ያልጋገረዉን ዳቦ ለሚመገብና ያልጠመቀዉን ወይን ለሚጠጣ ሰዉ እዘኑለት : “ አቅመ
“ ወዳጆቼና ተከታዮቼ ሆይ - በርካታ እምነቶች ባዶ ሃይማኖት ላለዉ ሕዝብ እዘኑለት። ያልሸመነዉን ጨርቅ ለሚለብስ ፤ ያልጋገረዉን ዳቦ ለሚመገብና ያልጠመቀዉን ወይን ለሚጠጣ ሰዉ እዘኑለት : “ አቅመ - ደካሞችን የሚያጠቃን በጀግንነት ለሚያወድስና ወራሪን ለጋስ ብለዉ ለሚመርቁ እዘኑላቸዉ። ህልሙን በመናቅ በንቃቱ ወቅት ራሱን ለሚያስገዛ ሕዝብ እዘኑለት ። “ ቀብር ላይ እንጂ ሌላ ቦታ ድምፁን ለማያሰማ ሕዝብ እዘኑለት ። አንገቱ ላይ ሰይፍ ካላረፈበት በቀር ልቡ ለማይነሳ ሕዝብ እዘኑለት ። “ መሪዉ እንደ ቀበሮ ለሆነ ፤ ሊቃዉንቱ አጭበርባሪ ለሆኑበት ፤ የሃገሬዉ ጥበብ የተጣፈና የተኮረጀ ለሆነበት ለዚያ ህዝብ እዘኑለት ። “ አዲስ መሪዉን መለከት እየነፋ ተቀብሎ ሲሞት በጩኸት ለሚሸኝ ፤ መልሶ ደግ ተተኪውን ለመቀበል መለከት ለሚነፋ ለዚያ ህዝብ እዘኑለት። “ ጠቢባኑ ለዓመታት ለደነቆሩበት ፤ ጠንካራ ሰዎች ከሕፃናት አልጋ ላልተነሱ ለዚያ ህዝብ እዘኑለት። “ ብዙ ቦታ ለተበጣጠሰ እና እያንዳንዱ ብጣሽ ራሱን እንደ ምሉዕ ሕዝባዊ መንግስት ለሚመለከት ሕዝብ እዘኑለት።” ——————————- The prophet ( ነብዩ) ካህሊል ጂብራን እንደፃፈዉ ሙሉቀን ታሪኩ እንደተረጎመዉ።

Story

Story

መልስ አለሽ ግን ልጠይቅሽ? ( ካሊድ አቅሉ) ያኔ ገና አፍላ ሳለን እንቡጥ ሆነሽ ምትፈነጂ ማማር ሲሉን የምንገልፅሽ ስንቱን ፀደይ የምትፈጂ ከቃላቶች ከፍ ያልሽ ቃል የምትከርሚ ነፍስ መንደር ሀገሩ በእጁ የቀለለዉ አንቺን አይቶ ሲግደረደር ስንቱን አየን በዛች እድሜ በትኩስ ሀይል ወኔን አዝለን ጉርምስናን አሳለፍነዉ ሴት ልጅ ሲባል አንቺን ስለን ጠበቅሽን ከአጉል ሩጫ ከመብከን በከንቱ ትግል ዉበትን በጥለት አየን ማማርን ከአንቺ ስንፈትል የልጅነት ፅጌሬዳ መስታወቴ የአስራዎቹ ባንቺ ምስል ተደግፌ አለም አየዉ ሆና ምቹ የዘመናት ሂደት ነበር መኖር ድርሳን የከተበዉ አሁን ግን ደብዝዞ አየዉ ማነዉ አዝኖ ነዉ የረገመዉ ? ህይወት ወንፌት ጉምን መሳይ ያዝኳት ስትል ደርሳ ምንም ድጋሜ አይኔ አቃጨለሽ መጠዉለጌን ላለመልም ግና ሳቅሽ መለሰኝ ዉሉ ሆንዋል የግራጫ ከመንገዱ ህፃን አቅፋ አይኔ ገባች ስትንጫጫ ልብስዋ ጊዜዉን መስልዋል የራቀ ነዉ ከመታጠብ እራሴን ከመንገድ አየዉ እንባ ያሉትን ሳንጠባጥብ . . . . ብቻ ሄደች ሳላገኛት ካያችሁዋት ጠይቁልኝ ካሳለፋዋት ብዙ እዉነት አንዱን እዉነት ጠይቁልኝ ቢሆንልኝማ ……. ዓይን ዓይንዋን ደፍሬ እያየዉ እላት ነበር ልጠይቅሽ ? መኖርን መኖር ያረገን ማን ነጠቀሽ ያንን ሳቅሽ? ( መልስ አለሽ ግን ልጠይቅሽ?)

አለኝ ያሉት በምድር ቀድሞ ለሚያሳፍር ! አብነት አጎናፍር (ለማን ብዬ)

ያሻኝ ቦታ ሄጄ ያሻኝን ከመምረጥ እኔን ሚያስደስተኝ መንገድ ለመሻገር እናቴን መጨበጥ ! ( ካሊድ አቅሉ) ልጅ እያለው ነፍስ በቅጡ ሳላውቅ እናቴ ነበረች ትምህርት ቤት ምታደርሰኝም ምትመልሰኝም ፣ ጠዋት ከቤት ስንወጣ ነፃነት እንዲሰማኝ ስለምትሻ የተወሰነ መንገድ አስባልቱ አቅራቢያ እስክንደርስ ትለቀኝና ዋና መንገዱን ልንደርስ አንድ ቅያስ ሲቀረን "ያዘኝ አለሜ" ብላ እጇን ወደኔ አቅጣጫ ሰዳ አጥብቃ ትይዘኝና ወደ ዜብራው አቅጣጫ ሄደን ሁለት ሶስት ግዜ ግራ ቀኝ ከቃኘች ብሃላ ይዛኝ ታልፋለች ። ነፍስ ካወኩ ብሃላ ሳሰላስለው እጅጉን ይገርመኛል እናቴ እንዳሻገረችኝ አስባልት መንገድ እጄኑ ይዛ ብዙ የህይወት ፈተናዎችን አልፋለች ፣ ማሻገር ማለት ማሳለፍ ብቻ አይደለም ማድረስም እንጂ መንገዱን አሳልፋኝ አትመለስም ትምህርት ቤት ግቢ አስገብታኝ ነው ወደ ቤት ምታቀናው ። እንደዚህ የህይወት ቅጥልጥሎቼን እየሰፋች በዘመን ሂደት ድርብ ኩታ አልብሳኛለች ፣ አሁንም ጭንቅ ሲለኝ እና በኔ ጥበብ ብቻ ማላልፈው ችግር ሲጠናብኝ የእናቴን ልብ እጆች በልቦቼ እጆች ዳብሼ ፈልጋለው አጥብቀው ይዘው እንዲያሳልፉኝ ብዙ ሰዎች እኔ አሻግርሀለው እጅህን ስጠን ይላሉ ችግሩ ግን አጥብቀው አይዙኝም መሀል ላይ ልሩጥ ስል አጉል ቦታ ይለቁኛል እናት አጥብቃ መያዝዋ ልጄ መሀል መንገድ ለቆኝ ቢሮጥስ ሚል ፍርሃት ነው ፍርሃቱ ከምን መነጨ ተዝቆ ከማያልቅ ለልጅዋ ካላት ፍቅር ..

Story

ጁመአ “ከቅን ሰዎች ጋር ምታረጉት ቆይታ ልብ ያላላቹት ምቾታቹ ነዉ.” ( ቼኩቪራ) “Deep conversation with open - minded people is such an underrated luxur
ጁመአ “ከቅን ሰዎች ጋር ምታረጉት ቆይታ ልብ ያላላቹት ምቾታቹ ነዉ.” ( ቼኩቪራ) “Deep conversation with open - minded people is such an underrated luxury.” (Che Guevara) @kalidakelu

ዐይን የሚሰማው ንግግር (ካሊድ አቅሉ) " ካላየነው በቀር የማንረዳው ብዙ ንግግር አለ ። " ---------------------------- ከአለቃዬ ጋር በመስሪያ ቤት Cafe ውስጥ ሻይ ቡና እያልን ነው በጫወታ መሀል ስላለፈው የአፍላ ወጣትነት ዘመንዋ በቁጭት አነሳች ፣ " እኔ እኮ ቃሊ ሚቆጨኝ ያኔ መንገድ ስስት ተመለሺ ብሎ ሚይዘኝ አንድ የቤተሰብ እንዴት አይኖርም ? ሁሉም እንደፈቀድሽ ብለው እሳት ውስጥ ስገባ ዳር ይዘው አዩኝ እናት ,አባት, ወንድም,እህት ጎረቤት .... አንድም አንቺ ልጅ ተመለሽ አይልም ? " " እነሱን ወቀስሽ እንጂ ያኔ ቢመክሩሽስ ከጥፋት መንገድ እንደምትመለሺ እርግጠኛ አትሁኚ በወጣትነት ያውም ደሞ አፍላው ሰዓት ከምክር በላይ ዱላ ይቀለናል" አልኳት መብሰልሰልዋን ለመቀነስ በሚጥር ድምፅ . . . . " ልክ ነህ ደግሞም ካላየነው በቀር የማንረዳው ብዙ ንግግር አለ ፤ ወጣትነቴን ተጠቅሞ አንድ ልጅ አስታቅፎኝ ጥሎኝ ሄደ ፈጣሪዬን አመሰግነዋለው ጥርሴን ነክሼ ልጄን አሳደግኩ በማታ ፕሮግራም ማስተርሴን ተማርኩ ግን አሁንም ከሱ ጋር ያባከንኩት የመሸነጋገል ዘመን እንደ እግር እሳት ያንገበግበኛል !" ጥርስዋን አሁንም በቁጭት ስትነክስ "አይ አሁንም እኮ አረፈደም አንቺ እንደው ገና ነሽ " አልኳት ስላሳዎቹን ወደ መጨረስ ያለችዋን ሰብሊን በሙሉ አይኔ እያየው . . . . . . " እሱስ አዎ ግን ቀትር ላይ ያለው ፀሐይና አመሻሽ ላይ ምትጠልቀው ፀሐይ እኩል ብርሃን አይሰጡም " አለችኝ ለዘብ ብላ " ያንቺ ግዴታ በነቃሽ ሰዓት ያገኘሻትን ብርሃን በአግባብ መጠቀም ነው ። " ብዬ ከአፎችዋ መልስ ጠበኩ ሁለታችንም አቀርቅረን በትዝታ በየፈርጃችን ነጎድን . . . . . @kalidakelu

Jumea تَجْمَعُونَ مَا لَا تَأْكُلُونَ، وَتَأْكُلُونَ مَا لَا تَكْنِزُونَ" “ የማትበሉትን ታግበሰብሳላቹ የማትኖሩበትን ትገነባላቹ “ ነብያችን (ሰ.ዐ.ወ)

ዝርዝር ይበተናል ልጠይቅሽ በድፍን ቃል ከራሱ ጋር የተጣላ እንዴት ሰዉን ያስታርቃል ? ( ካሊድ አቅሉ)