fa
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

رفتن به کانال در Telegram

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

کانال ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 13 810 مشترک است و جایگاه 1 693 را در دسته حمل و نقل و رتبه 2 461 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 13 810 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 28 اوت, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 140 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 13 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 36.14% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 15.65% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 4 989 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 2 160 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 8 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 29 اوت, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته حمل و نقل تبدیل کرده‌اند.

13 810
مشترکین
+1324 ساعت
+267 روز
+14030 روز
آرشیو پست ها
የ75 ዓመታት የፅናት ጉዞ በምስል መነፅር የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የ75ኛ ዓመት የአልማዝ ኢዮቤልዩ በዓሉን አስመልክቶ በዋናው መሥሪያ ቤት ልዩ ታሪካዊ የፎቶ አውደርዕይ በይፋ ተከፈተ። ​ይህ አውደርዕይ ተቋሙ "የአውራ ጎዳና ባለሥልጣን" ከተባለበት ጊዜ ጀምሮ ላለፉት 75 ዓመታት በመንገድ ልማት ያለፈባቸውን ውጣ ውረዶች በምስል የሚያሳይ ነው። ተቋሙ ሥራውን በጀመረበት ወቅት ሀገሪቱ ከነበራት አነስተኛ የመንገድ ርዝማኔ ተነስቶ ዛሬ ላይ የደረሰበትን የዘመናዊ ፈጣን መንገዶች፣ የድልድዮችና የሜጋ ፕሮጀክቶች የምህንድስናን ከፍታ የሚያሳዩ በርካታ  ታሪካዊ ፎቶግራፎችን በማቅረብ ያለፈበትን የዕድገት ጎዳና ለታዳሚዎቹ ያሳያል። በዝግጅቱ ላይ የአስተዳደሩ ቁልፍ የሥራ ዘርፎች የሆኑት የማሠልጠኛ ተቋማት፣ የምርምር ማዕከል፣ የፕላኒንግ፣ የዲዛይ እና ግንባታ ፣ የመንገድ ሀብት እና የድልድዮች ግንባታ ክፍሎች የየራሳቸውን ተቋማዊ የሥራ ክንዋኔዎችና ውጤቶች እንዲሁም ያለፉበትን ዓመታት ለጎብኚዎች በስፋት አቅርበዋል። ​መርሐ-ግብሩን በይፋ የከፈቱት የከተማ እና መሠረተ-ልማት ሚኒስትር ወ/ሮ ጫልቱ ሳኒ ሲሆኑ፣ የኢመአ የቦርድ አባላት፣ የከተማ፣ መሠረተ ልማትና ትራንስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት፣ ጥሪ የተደረገላቸው ተቋማት ኃላፊዎች፣ የቀድሞ የኢመአ ዋና ዳይሬክተሮች  የቀረቡትን ታሪካዊ ሁነቶች ተዘዋውረው ጎብኝተዋል። ​በዕለቱም ለረጅም ዘመን ተቋሙን በታማኝነትና በፅናት ያገለገሉ፣ በጡረታ ላይ የሚገኙ አንጋፋ ሠራተኞች ተሳትፈዋል። በሀገሪቱ ወጣ ገባ መልከዓ-ምድሮች ውስጥ በታላቅ ሀገራዊ ፍቅርና መስዋዕትነት መንገድ ለመክፈት ይከፈል የነበረውን ታላቅ ዋጋ ያሳየ መሆኑንም አረጋግጠዋል። ከዚህም ባለፈ ይህ የፎቶ አውደርእይ  የታሪክ ማስታወሻ ብቻ ሳይሆን፣ ለአዲሱ ትውልድ  የአገልግሎት ፅናትንና ሙያዊ ሥነ-ምግባርን የሚማርበት፣ የትውልድ ቅብብሎሽ በተግባር የታየበት ድልድይ ሆኗል። ​አስተዳደር መ/ቤቱ የመንገድ መሠረተ ልማቱን በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ለማዘመንና ተደራሽነቱን ለማስፋት ያለውን ቁርጠኝነት ያሳየበት ይህ አውደርዕይ በቀጣይም ለሁለት ቀናት ክፍት ሆኖ ይቆያል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የኢትዮጵያ መንገዶች አሥተዳደር 75ኛ ዓመት የምሥረታ በዓሉን በደማቅ ሁኔታ እያከበረ ይገኛል አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 16/2018 (ኢመአ) የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ባለፉት 75 ዓመታት የተጓዘበትን ታሪካዊ የመንገድ ልማት አሻራዎች በማስታወስ፣ የተቋሙን ስኬቶች በመዘከር እና ለነገው አዲስ የልማት ምዕራፍ ቃል ኪዳን በመግባት የአልማዝ ኢዮቤልዩ በዓሉን በደማቅ ሥነ-ሥርዓት እያከበረ ይገኛል። በዝግጅቱ ላይ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የቀድሞ የተቋሙ አመራሮችና ሠራተኞች፣ የልማት አጋር ተቋማት፣ የሥራ ተቋራጮች፣ አማካሪዎች፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እና የመስሪያ ቤቱ የሥራ ኃላፊዎችና ሰራተኞች ተገኝተዋል። በክብረ በዓሉ ላይ የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ እንደገለጹት፤ ይህ የ75ኛው ዓመት የአልማዝ ኢዮቤልዩ በዓል ተቋሙ ባለፉት ሰባት አሥርተ ዓመታት ያከናወናቸውን ታላላቅ ሥራዎች የሚዘክርበት ብቻ ሳይሆን ወደፊት የሚጠብቁትን ሀገራዊ ግቦች ለማሳካትም አዲስ ቃል የሚገባበት ታሪካዊ ምዕራፍ መሆኑን ገልጸዋል። ሚኒስትሯ አክለውም ተቋሙ በምስረታው ወቅት ከነበረው ውስን አቅም ተነስቶ ዛሬ የሀገሪቱን ገጽታ የሚቀይሩና ትውልድ ተሻጋሪ የሆኑ ታላላቅ የመንገድ ፕሮጀክቶችን የማከናወን ብቃት ላይ መድረሱ የሚያኮራ ስኬት መሆኑን አብራርተዋል። ከዚህም በተጨማሪ የመንገድ መሠረተ ልማት ለኢንዱስትሪ ዕድገት፣ ለግብርና ምርታማነትና ለቱሪዝም መስፋፋት ዋነኛ አንቀሳቃሽ ኃይል በመሆኑ የተቋሙ የወደፊት ጉዞ በዘመናዊ ቴክኖሎጂና በዲጂታል አሠራር የታገዘ እንዲሆን የሚደረጉ የሪፎርም ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል። የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የቦርድ ሰብሳቢ ዶ/ር እዮብ ተካልኝ በበኩላቸው፣ በዓሉ ተቋሙ ባለፉት 75 ዓመታት ከአንደኛው የሀገሪቱ ጫፍ እስከ ሌላኛው ጫፍ ሕዝቦችን በማገናኘት ያከናወናቸውን ሥራዎች የሚያደንቅበት ብቻ ሳይሆን፣ ሀገራዊ ራዕይን ዕውን ለማድረግና የተጀመሩ የልማት ምዕራፎችን ለማጠናከር አዲስ ጉልበት እንደሚሰጥ ተናግረዋል። የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር መሐመድ አብዱራሕማን የኢመአ የ75 ዓመታት ጉዞ ባለፉት ዓመታት ብዛት ብቻ የሚለካ ሳይሆን በራዕይ፣ በቁርጠኝነት፣ በሙያዊ ብቃትና በትውልዶች ትጋት የተገነባ ታሪክ መሆኑን ገልጸዋል። በተቋሙ ምስረታ ወቅት የነበረው የሀገሪቱ የመንገድ አውታር 6, ሺህ 400 ኪሎ ሜትር ብቻ እንደነበር ጠቅሰው፣ ዛሬ ግን 182 ሺህ 232 ኪሎ ሜትር የደረሰ ሰፊ የመንገድ አውታር መገንባቱን ጠቁመዋል። እንደ ዋና ዳይሬክተሩ ገለጻ፣ ቀድሞ ከነበሩት የአውራ ጎዳና ፕሮግራሞች ተነስቶ እስከ መንገድ ሴክተር፣ እንዲሁም ከ1989 ዓ.ም ወዲህ በተተገበሩ ተከታታይ የመንገድ ዘርፍ ልማት ፕሮግራሞች አማካኝነት የተከናወኑ የመንገድ ግንባታና ጥገና፣ የድልድይ ልማት፣ የመንገድ ንብረት አስተዳደር፣ የመንገድ ደኅንነትና የተቋማዊ አቅም ግንባታ ላይ ከፍተኛ እመርታ ተመዝግቧል። በቀጣይም ተቋሙ በጥራት፣ በዘላቂነት፣ በደኅንነት፣ በአካባቢ ጥበቃና በዘመናዊ የንብረት አስተዳደር መርሆዎች ላይ በመመሥረት የመንገድ ልማቱን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል። ለሦስት ቀናት በሚቆየው በዚህ የበዓል መርሃ-ግብር ፣ የተቋሙን የ75 ዓመታት የመንገድ ልማት ጉዞ የሚያሳዩ የፎቶና የሰነድ ኤግዚቢሽኖች፣ የዘመናዊ ቴክኖሎጂ ማሳያዎች እንዲሁም የውይይት መድረኮች ይከናወናሉ። ከዚህም በተጨማሪ የእውቅና አሰጣጥ ሥነ-ሥርዓቶችና የባሕል ዝግጅቶችን ጨምሮ የተለያዩ ይዘት ያላቸው ፕሮግራሞች የዚሁ ሁነት አካል ናቸው። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የ75ኛ ዓመት የአልማዝ ኢዮቤልዩ በዓሉን በይፋ ማክበር ጀመረ   አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 16/2018 (ኢ መ አ):- የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የተመሰረተበትን 75ኛ ዓመት የአልማዝ ኢዮቤልዩ  በዓሉን በተለያዩ መርሃ ግብሮች ማክበር ጀምሯል።   በመክፈቻ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች፣ የተቋሙ አመራሮችና ሠራተኞች ተገኝተዋል።   ተቋሙ በ1943 ዓ.ም ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ ሀገሪቱን በማገናኘት በነበረው የሰባት አስርት ዓመታት ጉዞ  ከጠጠር  መንገድ  ግንባታ ተነስቶ አሁን ላይ ፈጣንና ዘመናዊ የአስፋልት ኮንክሪት መንገዶችን፣ የክፍያ መንገዶችን እና ድልድዮችን  እስከ  መገንባት የደረሰ የቴክኖሎጂና የክህሎት ሽግግር አድርጓል።   ኢመአ ሲመሰረት የነበረው የመንገድ ሽፋን 6 ሺህ 400 ኪሎ ሜትር ብቻ የነበረ ቢሆንም፤ ባለፉት ዓመታት ባደረገው ያልተቋረጠ ጥረቶች አሁን ላይ የሀገሪቱን የመንገድ ኔትወርክ 180 ሺህ 232 ኪሎ ሜትር ማድረስ ተችሏል።   ተቋሙ "መንገዳችን ኃላፊነታችን" በሚል መርህ የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ግንኙነቶችን እንዲሁም የንግድ እንቅስቃሴዎችን በማፋጠን ረገድ ከፍተኛ ሚና ሲጫወት ቆይቷል።   "ምርጥ መንገዶች ለኢትዮጵያ ብልፅግና" የሚለውን ራዕዩን ለማሳካት የግብርናና የኢንዱስትሪ ምርቶች ወደ ገበያና ወደብ እንዲደርሱ በማድረግ፤ የጤናና የትምህርት አገልግሎቶችን በማስፋፋት እንዲሁም የሀገሪቱን ሁለንተናዊ ትስስር በማጠናከር በኩል ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክቷል።   የተቋሙን የ75 ዓመታት ታሪክ የሚያሳዩ ልዩ ልዩ ዝግጅቶች የተካተቱበት ይህ ክብረ በዓል፤ በቀጣይ ቀናትም በተለያዩ መርሃ ግብሮች መከበሩን ይቀጥላል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

75 ዓመታት – ከፓንች ካርድ ወደ ዘመናዊ ዲጂታል መሠረተ ልማት የኢትዮጵያ መንገዶች አሥተዳደር የዲጂታል ለውጥ ጉዞ ለ75 ዓመታት የኢትዮጵያ መንገዶች አሥተዳደር ሀገራችንን በመንገዶች አገናኝቷል። ከዚህ ታላቅ ጉዞ ጀርባ ግን መረጃን፣ ቴክኖሎጂን እና ፈጠራን በማስተሳሰር የተቋሙን ዲጂታል ለውጥ የመራው የICT ዘርፍ ይገኛል። የICT የለውጥ ጉዞ ከቀላል የመረጃ ማቀናበሪያ እስከ ዘመናዊ ዲጂታል መሠረተ ልማት ይዘልቃል። ይህ ጉዞ ከግማሽ ምዕተ ዓመታት በፊት ተጀምሯል። በ1964 ዓ.ም. የመረጃ ማቀናበሪያ ክፍል ሲቋቋም፣ መረጃን በዘመናዊ መንገድ የማሥተዳደር አዲስ ምዕራፍ ተከፈተ። በወቅቱ የፓንች ካርድ ቴክኖሎጂ በመጠቀም የደመወዝ፣ የሠራተኞች እና ሌሎች አሥተዳደራዊ መረጃዎች በሥርዓት መደራጀትና መቀናበር ተጀመረ። ይህም ለተቋሙ የዲጂታል ለውጥ የመጀመሪያውን ጠንካራ መሠረት ጣለ። በዚያን ዘመን የቴክኖሎጂ ዋና ዓላማ የቁጥር ሥራዎችን ማቀላጠፍ ነበር። ጉዞው ግን በዚያ አላበቃም። ከፓንች ካርድ... ወደ ዘመናዊ ኮምፒውተሮች። ከአንድ የመረጃ ሥርዓት... ወደ የተቀናጁ ዲጂታል ሲስተሞች። ከተናጠል መረጃ... ወደ የተሳሰረ ዲጂታል መረብ። ICT የተቋሙን የአሠራር መንገድ በቀስታ ነገር ግን በጥልቀት ቀይሮታል። የደመወዝ አሥተዳደር፣ የፋይናንስ ሥርዓት፣ የመንገድ ንድፍ፣ የጥገና አሥተዳደርና ሌሎች የመረጃ ሥርዓቶች በቴክኖሎጂ ተደግፈው ቀልጣፋና የተቀናጁ ሆነዋል። ዛሬ ላይ ICT የመረጃ ማዕከል ብቻ አይደለም፤ የሥራ ፍሰትን የሚያፋጥን፣ ውሳኔን በመረጃ የሚደግፍ እና መላውን ተቋም በአንድ ዲጂታል መረብ የሚያስተሳስር የቴክኖሎጂ መሠረት ሆኗል። ዋናውን መሥሪያ ቤት፣ ዲስትሪክቶችን እና የሥራ ክፍሎችን በአንድ ዲጂታል መረብ በማገናኘት የመረጃ ልውውጥን አፋጥኗል፤ የሰነድ አሥተዳደርን አዘምኗል፤ የሥራ ሂደቶችን ቀልጣፋ፣ የተቀናጀ እና ውጤታማ አድርጓል። ከዚህም በላይ በመረጃ ላይ የተመሠረተ ውሳኔን አጠናክሮ፣ የፕሮጀክት ክትትልንና የመንገድ አሥተዳደርን በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ደግፏል። በ75 ዓመታት ሀገርን የማገናኘት ጉዞ ውስጥ መንገዶች ሀገርን ሲያገናኙ፣ ICT ደግሞ መረጃን፣ ሰዎችን እና የሥራ ሂደቶችን አስተሳስሯል። ዛሬ የተገነባው የዲጂታል አቅም የነገውን የመንገድ ልማት በቴክኖሎጂ የሚደግፍ ጠንካራ መሠረት ሆኗል። ኢትዮጵያን የማገናኘት 75 ዓመታት መንገዳችን፤ ኃላፊነታችን! በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

ከዬት ወዴት? 75 ዓመታት የመንገድ ልማት፤ ትናንት እና ዛሬ:- የኢትዮጵያ መንገዶች አሥተዳደር 75ኛ ዓመትን ስናከብር፣ የተገነቡ መንገዶችን ብቻ ሳይኾን በእነዚህ መንገዶች የተፈጠረውን የሀገር ለውጥ እናስታውሳለን። ከ75 ዓመታት በፊት ከአንድ አካባቢ ወደ ዋና የአስፋልት መንገድ ለመድረስ ሰዓታት አልፎ ተርፎም ቀናት ይወስድ ነበር። ዛሬ ላይ ግን በመንገድ አውታሩ መስፋፋት ምክንያት ዜጎች በአማካኝ 1 ሰዓት ከ25 ደቂቃ ወደ ዋና መንገዶች መድረስ ችለዋል። ይህ የጊዜ ለውጥ ብቻ አይደለም፤ የኢኮኖሚ ዕድገት፣ የማኅበራዊ ትስስር እና የአገልግሎት ተደራሽነት መሠረት ነው። መንገዶች የገበያ በሮችን ከፍተዋል፤ የግብርና ምርቶችን በፍጥነት ወደ ገበያ እንዲደርሱ፣ ኢንዱስትሪዎች ከጥሬ ዕቃና ከወደብ ጋር እንዲገናኙ፣ ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታቸው፣ ሕሙማን ወደ ጤና ተቋማት እንዲደርሱ አስችለዋል። በጥራትም እንዲሁ ከፍተኛ ለውጥ ታይቷል። ትናንት የመንገድ ግንባታ በውስን ቴክኖሎጂና አቅም ይከናወን ነበር፤ ዛሬ ግን የዘመናዊ ምህንድስና መርሆዎች፣ የጥራት ቁጥጥር ሥርዓቶች፣ የላብራቶሪ ምርመራዎችና የብቁ የሀገር ውስጥ ባለሙያዎች አቅም የዘላቂነትና የጥራት አዲስ ምዕራፍ ፈጥረዋል። ወደፊትም ግባችን የበለጠ ጥራት ያላቸው፣ ዘላቂ፣ አካባቢን የሚጠብቁ፣ በዲጂታል ቴክኖሎጂ የተደገፉ እና ለቀጣዩ ትውልድ የሚመጥኑ መንገዶችን መገንባት ነው። በመንገድ ዘርፉ የተገኘው ሌላው ታላቅ ለውጥ የሰው ኃይል አቅም ነው። በአንድ ዘመን በውጭ ባለሙያዎች ይመራ የነበረው ዘርፍ፣ ዛሬ በኢትዮጵያውያን መሐንዲሶች፣ ዲዛይነሮች፣ ተቆጣጣሪዎች እና ባለሙያዎች እየተመራ ነው። ይህ የ75 ዓመታት ጉዞ ስኬቶች መካከል አንዱ ነው።   የ75 ዓመታት ቁጥራዊ ዕውነታዎች:-   👉ጠቅላላ የመንገድ አውታር       1943 ዓ.ም - 6 ሺህ 400 ኪ.ሜ (ጠጠር እና አፈር)       2018 ዓ.ም - 180 ሺህ 232 ኪ.ሜ 👉 የአስፋልት መንገድ ርዝመት        1943 ዓ.ም - ውስን       2018 ዓ.ም - 16 ሺህ 760 ኪ.ሜ 👉 ወደ ዋና የአስፋልት መንገድ ለመድረስ የሚፈጀው ጊዜ       1943 ዓ.ም - የቀናት ጉዞ (ክረምት ከበጋ የሚያስኬድ)       2018 ዓ.ም - 1 ሰዓት ከ25 ደቂቃ 👉 የመንገድ ጥግግት      1943 ዓ.ም - 0.46 ኪ.ሜ      2018 ዓ.ም - 1.46 ኪሜ 👉 በጥሩ ሁኔታ ላይ የሚገኝ መንገድ      1943 ዓ.ም - 22 በመቶ      2018 ዓ.ም - 62 ነጥብ 7 በመቶ 👉 ኢትዮጵያዊያን መሀንዲሶች      1943 ዓ.ም - ደጃዝማች ዒሳ ሸሪፍ      2018 ዓ.ም - በሺዎች የሚቆጠሩ   ኢትዮጵያን የማገናኘት 75 ዓመታት መንገዳችን፣ ኃላፊነታችን! በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

75 ዓመታት፤ ከውስን የመንገድ አውታር ወደ ሀገርን የሚያስተሳስር ዘመናዊ መሠረተ ልማት! ሀገራችን ከዝቅተኛ የመንገድ መሠረተ-ልማት ወደ ሰፊ፣ ዘመናዊና የኢኮኖሚ ኮሪደሮችን የሚያገናኝ መንገድ ጉዞ አድርጋለች። በተለያዩ ምዕራፎች የተተገበሩ የመንገድ ዘርፍ የልማት ፕሮግራሞች ይህን ጉዞ በተቀናጀ አቅጣጫ የመሩ ሲኾን፤ የመንገድ ግንባታ ከቁጥር ባለፈ፣ ዘላቂነትና ተደራሽነትን ያረጋገጠ ተጨባጭ ለውጥ እንዲያስመዘግብ ቁልፍ ሚና ተጫውተዋል። የመንገድ ዘርፍ የልማት ፕሮግራም በ1989 ዓ.ም የተጀመረው የመንገድ ዘርፍ የልማት ፕሮግራም በኢትዮጵያ የመንገድ ልማት ታሪክ አዲስ ምዕራፍ ከፍቷል። የፕሮግራሙ ዋና ዓላማ የመንገድ አውታሩን ማስፋት፣ ጥራትን ማሻሻል፣ የጥገና ሥርዓትን ማጠናከርና ተቋማዊ አቅምን መገንባት ነበር። የመጀመሪያው የመንገድ ዘርፍ ልማት ፕሮግራም (1989–1994 ዓ.ም)፡- ዋና ትኩረቱ አዲስ አበባን ከክልል ዋና ከተሞች፣ ከንግድ ማዕከላትና ከወደብ መስመሮች ጋር የሚያገናኙ አውራ ጎዳናዎችን ማሻሻል ነበር። በዚህ ወቅት 8 ሺህ 709 ኪ.ሜ መንገድ ተገንብቶና ታድሶ ለአገልግሎት በቅቷል። ሁለተኛው የመንገድ ዘርፍ ልማት ፕሮግራም (1995–1999 ዓ.ም)፡- የመንገድ አውታርን ማስፋት፣ የገጠር ተደራሽነትን ማሻሻልና አዳዲስ መንገዶችን መገንባት ተቀዳሚ ትኩረቶች ነበሩ። በዚህ ወቅት 11 ሺህ 589 ኪ.ሜ መንገድ ተገንብቷል። ሦስተኛው የመንገድ ዘርፍ ልማት ፕሮግራም (2000–2002 ዓ.ም)፡- ነባር የጠጠር መንገዶችን ወደ አስፋልት ማሳደግ፣ አዳዲስ አገናኝና ዋና መዳረሻ መንገዶችን መዘርጋት ላይ ተተኮረ። በዚህ ወቅት 12 ሺህ 395 ኪ.ሜ መንገድ ተገንብቷል። አራተኛው የመንገድ ዘርፍ ልማት ፕሮግራም (2003–2007 ዓ.ም)፡- የገጠር አካባቢዎችን ከመንገድ አውታር ጋር ማገናኘትና ተደራሽነትን ማስፋት ትኩረት አግኝቷል። በዚህ ወቅት 85 ሺህ 860 ኪ.ሜ የሚሸፍኑ የተለያዩ መንገዶች ተገንብተዋል። አምስተኛው የመንገድ ዘርፍ የልማት ፕሮግራም (2008–2012 ዓ.ም)፡- ይህ ዘመን የመንገድ ልማትን ከጥራት፣ ከዘላቂነትና ከቴክኖሎጂ ጋር ያስተሳሰረ ምዕራፍ ነበር። በፕሮግራሙ የመጀመሪያ ሦስት ዓመታት ውስጥ በአጠቃላይ 27 ሺህ 210 ኪሎ ሜትር የሚሸፍኑ መንገዶች ግንባታ ተካሄዷል፡፡ ስድስተኛው የመንገድ ዘርፍ የልማት ፕሮግራም (2012–2017 ዓ.ም)፡- በዚህ ዘመን 28 ሺህ 949 ኪ.ሜ የፌዴራል እንዲሁም የክልልና የወረዳ መንገዶች ተገንብተው ለአገልግሎት በቅተዋል። በዚህም የሀገሪቱ አጠቃላይ የመንገድ አውታር በ1989 ዓ.ም ከነበረበት 26 ሺህ 550 ኪ.ሜ ወደ 180 ሺህ 232 ኪ.ሜ አድጓል። ባለፉት 28 ዓመታት በተተገበሩ ስድስቱ ፕሮግራሞች በአጠቃላይ 805 ነጥብ 76 ቢሊዮን ብር የሚጠጋ መዋለ-ንዋይ ፈሰስ ተደርጓል። በአጠቃላይ እነዚህ ፕሮግራሞች የመንገድ አውታርን በማስፋት ብቻ ሳይወሰኑ፤ የጥራት ደረጃን ከፍ ማድረግ፣ የገጠርና የከተማ ትስስርን ማጠናከር፣ የኢኮኖሚ ኮሪደሮችን ማሳደግና የሀገር አቀፍ ልማትን ማፋጠን የቻሉ የለውጥ ምዕራፎች በመኾን ወደ ተሻለ የዕድገት ጎዳና የምትጓዝ ኢትዮጵያን ገንብተዋል። ኢትዮጵያን የማገናኘት 75 ዓመታት  መንገዳችን፣ ኃላፊነታችን! በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads