ar
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

الذهاب إلى القناة على Telegram

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

تُعد قناة ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 13 342 مشتركاً، محتلاً المرتبة 1 756 في فئة النقل والمرتبة 2 537 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 13 342 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 17 يونيو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 95، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 18، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 41.14‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 15.24‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 5 485 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 2 032 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 16.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 18 يونيو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة النقل.

13 342
المشتركون
+1824 ساعات
+417 أيام
+9530 أيام
أرشيف المشاركات
For the fastest 24/7 updates and analysis on the Iran war, join @geopolitics_prime.

የኢትዮጵያ መንገዶች ባለፉት ስምንት ዓመታት • የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (ኢ.መ.አ) ክልሎችን እርስ በርስ የሚያገናኝና ሀገራዊ የንግድ ኮሪደሮችን የሚያጠናክር ጠንካራ የፌዴራል የመንገድ መረብ የመዘርጋት ተልዕኮውን ወደ ተግባር በመለወጥ ረገድ ያስመዘገበው አሀዛዊ መረጃ በርካታ ውጤቶች መመዝገባቸውን ያሳያል። • በ2010 ዓ.ም የነበረው የ126,773 ኪሎ ሜትር አጠቃላይ የመንገድ ሽፋን በ2018 ዓ.ም አጋማሽ ወደ 180,232 ኪሎ ሜትር በማደጉ፣ ከ53 ሺህ ኪሎ ሜትር በላይ አዲስ መንገድ ለሀገሪቱ ተጨምሯል። • የመንገድ ጥግግቱ በየ1000 ስኩዌር ኪሎ ሜትር ከ115.2 ወደ 157 ኪሎ ሜትር አድጓል። • ባለፉት ስምንት ዓመታት ውስጥ ብቻ 182 ፕሮጀክቶች ወደ ግንባታ እንዲገቡ የተደረገ ሲሆን፣ 71 ግዙፍ ፕሮጀክቶች ግንባታቸው ተጠናቆ ለትራፊክ ክፍት ሆነዋል። • ተቋሙ የመንገድ ጥራትን ከመጠበቅ አንጻርም 80,037 ኪሎ ሜትር መደበኛ ጥገና እና 3,035 ኪሎ ሜትር ከባድ ጥገና በማከናወን የሀገሪቱን የመንገድ ሀብት የመንከባከብ ስራ በትኩረት ሰርቷል። • የውጤቱ ሌላኛው ማሳያ ሀገራችንን የንግድና የኢንዱስትሪ ማዕከል የሚያደርጉ ግዙፍ የፍጥነት መንገዶች እውን መሆናቸው ነው። • ከለውጡ በፊት የነበረው 84.7 ኪ.ሜ የሚረዝመው የአዲስ አበባ-አዳማ የፍጥነት መንገድ ብቻ ሲሆን፣ ዛሬ ግን የሞጆ-መቂ-ባቱ-አርሲ ነገሌ (151 ኪ.ሜ) እና የድሬዳዋ-ደዋሌ (220 ኪ.ሜ) የፍጥነት መንገዶች ተጠናቅቀው ለአገልግሎት በቅተዋል። • ከዚህ በተጨማሪ ተቋሙ ከአዲስ አበባ ወደ ደሴ፣ ጅማ፣ ደብረ ማርቆስ እና ነቀምቴ የሚዘልቁ አራት አዳዲስ የፍጥነት መንገዶችን ለመገንባት የአዋጭነት ጥናት እያጠናቀቀ ሲሆን፣ ይህም ኢትዮጵያን በ10 ዓመታት ውስጥ የ1,600 ኪሎ ሜትር የፍጥነት መንገድ ባለቤት ለማድረግ ለተያዘው ግብ ትልቅ እርምጃ ነው። • ሌላኛው ትልቅ ስኬት ኢትዮጵያን ከጎረቤት ሀገራት ጋር የሚያገናኙ ግዙፍ መንገዶች እውን መሆናቸው ነው። • ተቋማዊ አደረጃጀትን በማዘመንና ዘመናዊ አሰራርን በመዘርጋት ረገድም በለውጡ ማግስት ሰፊ ስራዎች ተከናውነዋል። • ቀደም ሲል ተነጥለው የነበሩ የመንገድ ጥገና ዲስትሪክቶችና ሴክሽኖች ወደ ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር እንዲመለሱ ተደርጓል። • በተጨማሪም በሀገሪቱ በተለያዩ ክፍሎች የግንባታ ፕሮጀክቶች ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤቶች ተከፍተው ስራ እንዲጀምሩ በመደረጉ፣ የፕሮጀክቶች ክትትልና ድጋፍ በመንገድ ግንባታው ስፍራ ቅርብ እንዲሆኑ አስችሏል። • የመንገድ ሀብቱን ለመጠበቅና የከባድ ተሽከርካሪዎችን ጫና ለመቆጣጠር የሚረዱ የሚዛን ጣቢያዎች ከለውጡ ማግስት ጀምሮ በማስፋፋት እና ያሉትን ዲጂታላይዝ እንዲሆኑ ተደርገዋል። • ይህ የዲጂታላይዜሽን ስራ የተሽከርካሪዎችን ክብደት ከሰው እጅ ንክኪ ነጻ በሆነ መልኩ በመመዝገብ፣ የአሰራር ግልጽነትን በማስፈንና የመንገድ ብልሽትን በመቀነስ ረገድ የላቀ ሚና እየተጫወተ ይገኛል። • በመንገድ ምርምር ረገድም የተቋሙን የምርምርና ላቦራቶሪ ማዕከል አቅም በማሳደግ የመንገድ ግንባታ ግብአቶችን ጥራት በሳይንሳዊ መንገድ ለመፈተሽ የሚያስችሉ ስራዎች ተሰርተዋል። • የዘርፉን አቅም ለመገንባትም በቢሊዮን የሚቆጠር ብር ወጪ የተደረገባቸው በርካታ ዘመናዊ ለመንገድ ግንባታ የሚውሉ ማሽነሪዎች ግዢ መፈጸሙ እና ሌሎችም በርካታ ተግባራት ተከናውነውል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

NOTICE OF INVITATION FOR BIDS CAPACITY BUILDING ROAD PROJECTS

የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር የተጠሪ ተቋማትን የዘጠኝ ወራት የሥራ አፈጻጸም ገመገመ አዲስ አበባ፣ መጋቢት 25 ቀን 2018 ዓ/ም (ኢመአ)፡ የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር ተጠሪ የሆኑት የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር፣ የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለሥልጣን እና የግንባታ ማኔጅመንት ኢንስቲትዩት የዘጠኝ ወራት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ አካሄዱ። በመድረኩ የተቋማቱ ጥንካሬና ድክመቶች የተፈተሹ ሲሆን፣ በቀጣይ መወሰድ ስላለባቸው ስትራቴጂካዊ አቅጣጫዎች ላይ ሰፊ ውይይት ተደርጓል። በግምገማው አፈጻጸማቸውን ካቀረቡት ተቋማት መካከል የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የዕቅዱን 78 በመቶ ማሳካቱ ገልጿል። አስተዳደሩ በአሁኑ ወቅት ከ1.3 ትሪሊዮን ብር በላይ ዋጋ ያላቸው ፕሮጀክቶችን እየመራ ሲሆን፣ ዓመታዊ የመንገድ ግንባታ የማጠናቀቅ አቅሙን ከ800 ኪሎ ሜትር ወደ 1,600 እና 2,000 ኪሎ ሜትር ማሳደግ እንደሚገባው አጽንኦት ተሰጥቶበታል። መድረኩን የመሩት የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ዶ/ር የትምጌታ አስራት በተለያዩ ምክንያቶች የተቋረጡ ፕሮጀክቶችን በመለየት መፍትሄ እንዲቀመጥላቸውና በመንገድ ጥገና ሥራዎች ላይ ጥብቅ ክትትል እንዲደረግ አቅጣጫ አስቀምጠዋል። የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለሥልጣን (ECA) በበኩሉ፣ የኮንስትራክሽን ግብዓቶች የዋጋ መረጃ ሥርዓት የመዘርጋት እንዲሁም በምዝገባ፣ በፈቃድ አሰጣጥና በቁጥጥር ሥራዎች በኢንዱስትሪው ላይ ተጨባጭ ለውጥ የማምጣት ኃላፊነቱን እንዲወጣ ተጠቁሟል። በተመሳሳይ የግንባታ ማኔጅመንት ኢንስቲትዩት (CMI) ለሚገነባው የልህቀት ማዕከል ግልጽ የሥራ መመሪያ (Roadmap) እንዲያዘጋጅና ከመንግሥት በጀት ጥገኝነት ወጥቶ ገቢ የሚያመነጩ የኢንተርፕርነርሺፕ ሥራዎች ላይ እንዲያተኩር ሚኒስትር ዴኤታው አሳስበዋል። በመድረኩ ማጠቃለያ ላይ የዋጋ ንረት፣ የነዳጅና የአቅርቦት እጥረት በፕሮጀክቶች ላይ ተጨማሪ ወጪና መጓተት እያስከተሉ መሆኑ ተነስቷል። በመድረኩ ማጠቃለያ መልዕክት ያስተላለፉት የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ዶ/ር የትምጌታ አስራት እነዚህን ተግዳሮቶች ለመወጣት በተጠሪ ተቋማቱ መካከል ያለው ቅንጅት መጠናከር እንዳለበትና ሁሉም ተቋማት ከወዲሁ የ2019 ዓ.ም የቅድመ ዝግጅት ዕቅድ ማውጣት እንዲጀምሩ መመሪያ ሰጥተዋል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የሐይቅ - ቢስቲማ - ጭፍራ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት አፈፃፀም 45.35 በመቶ ደረሰ ኮምቦልቻ | መጋቢት 22 ቀን 2018 ዓ.ም (ኢመአ)፡ በአማራ እና በአፋር ክልሎች መካከል ያለውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ትስስር ይበልጥ ያጠናክራል ተብሎ የሚጠበቀው የሐይቅ - ቢስቲማ - ጭፍራ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት አፈፃፀም 45.35 በመቶ መድረሱ ተገለጠ። ይህ 74.3 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው የመንገድ ፕሮጀክት፣ ከአዲስ አበባ በ430 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ከምትገኘው የሐይቅ ከተማ ተነስቶ አፋር ክልል ጭፍራ ከተማ ላይ ያበቃል። መንገዱ ቀደም ሲል የነበረውን የጠጠር መንገድ ወደ አስፋልት ኮንክሪት ደረጃ ከፍ የሚያደርግ ሲሆን፤ በገጠር 10 ሜትር፣ በቀበሌ 15 ሜትር እንዲሁም በወረዳ ከተሞች 19 ሜትር ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ እየተገነባ ይገኛል። የኢትዮጵያ መንግሥት በ2.1 ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ በጀት እያስገነባው የሚገኘውን ይህንን ፕሮጀክት፤ ፓወርኮን እና አሰር ኮንስትራክሽን በጣምራ (Joint Venture) እያከናወኑት ሲሆን፣ የኮር ኮንሰልቲንግ ኃ/የተ/የግ/ማ የማማከርና ቁጥጥር ስራውን እየሰራ ይገኛል። እስካሁን ባለው ሂደት፦ ✔️የጠረጋ፣ የቁፋሮ እና የሙሌት ስራዎች፤ ✔️የውሃ ማፍሰሻ ቱቦዎች እና የተፋሰስ ስራዎች፤ ✔️ሁለት ድልድዮች እንዲሁም አነስተኛና ከፍተኛ የከልቨርት ግንባታዎች ተጠናቀዋል። ✔️በአሁኑ ወቅት የአስፋልት እና የቤዝ ኮርስ ንጣፍ ለመጀመር የሚያስችሉ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች በትኩረት እየተከናወኑ ይገኛሉ። ከመንገድ ወሰን ማስከበር ስራዎች ጋር ተያይዞ የሚስተዋሉ ችግሮች እልባት ካገኙ፣ ግንባታው በተቀመጠለት ጊዜ ተጠናቆ ለአገልግሎት እንደሚበቃ ይጠበቃል። ግንባታው ሲጠናቀቅ በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ ዞን የሚገኙትን ተሁለድሬ እና ወረባቦ ወረዳዎችን ከአፋር ክልል ጭፍራ ወረዳ ጋር በቅርበት ያገናኛል። ይህም ቀደም ሲል ለጉዞ ይፈጅ የነበረውን 5 ሰዓት ወደ 1 ሰዓት ተኩል ዝቅ የሚያደርገው ሲሆን፤ የአካባቢውን የግብርና ምርቶች ወደ ገበያ ለማውጣትና የማህበረሰቡን የንግድ ልውውጥ ለማቀላጠፍ ከፍተኛ ሚና ይጫወታል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads #የመንገዶችአስተዳደር #የመንገድግንባታ #ኢትዮጵያ #InfrastructureEthiopia #HayqBistimaChifra

+4
WhatsApp Image 2026-03-31 at 11.00.02 AM.jpeg1.30 KB

የኮምቦልቻ ከተማ ተለዋጭ መንገድ ግንባታ በጥሩ አፈጻጸም ላይ ይገኛል አዲስ አበባ፦ መጋቢት 22 ቀን 2018 ዓ.ም (ኢ.መ.አ): በአማራ ክልል በኮምቦልቻ ከተማ በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ እየተገነባ የሚገኘው የከተማዋ ተለዋጭ መንገድ ግንባታ በጥሩ ሁኔታ እየተከናወነ ይገኛል። 7.58 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው ይህ መንገድ፣ የመንገድ ትከሻንና የእግረኛ መንገዶችን ጨምሮ 20.6 ሜትር የጎን ስፋት አለው። ለፕሮጀክቱ ማስፈጸሚያ የሚውለው 1 ቢሊዮን 138 ሚሊዮን 807 ሺህ 808 ብር ከ86 ሳንቲም ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያ መንግስት የሚሸፈን ነው። የመንገዱ ግንባታ "ዮንአብ ኮንስትራክሽን" በተባለ ሀገር በቀል ተቋራጭ እየተከናወነ ሲሆን፣ የማማከርና ቁጥጥር ስራውን ደግሞ "ፓራጎን ኢንጂነሪንግ" የተሰኘ ሀገር በቀል ድርጅት በመስራት ላይ ይገኛል። በአሁኑ ወቅት የፕሮጀክቱ አጠቃላይ አፈጻጸም 42.7 በመቶ የደረሰ ሲሆን፣ 3.24 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን የንዑስ መሰረት (Sub-base) ስራ ተጠናቋል። የጠረጋ፣ የአፈር ቁፋሮና ሙሌት፣ የፍሳሽ ማስወገጃ ቱቦዎች ዝርጋታ፣ የድልድይና የደጋፊ ግንብ ስራዎችም በተቀላጠፈ ሁኔታ እየተከናወኑ ነው። በተጨማሪም የቤዝ ኮርስ እና የአስፋልት ንጣፍ ስራ የተጀመረ ሲሆን፣ የነዳጅ አቅርቦት ሁኔታው ሲስተካከል ስራው ይበልጥ እንደሚፋጠን ይጠበቃል። የወሰን ማስከበር፣ የካሳ ክፍያ መዘግየት፣ የድንጋይ ማምረቻ ቦታ ችግር እንዲሁም የነዳጅና የግብዓት እጥረት ለስራው መሳለጥ ፈተና ሆነው የቆዩ ቢሆንም፤ ከከተማው መስተዳድርና ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር በተደረገ የተቀናጀ ጥረት ችግሮቹ እየተቀረፉ ይገኛሉ። ይህ ተለዋጭ መንገድ ተጠናቆ ለአገልግሎት ሲበቃ፦ • ከባድ ተሽከርካሪዎች ወደ ከተማ ሳይገቡ እንዲያልፉ በማድረግ የከተማዋን መንገዶች ዕድሜ ያራዝማል፤ • በከተማ ውስጥ የሚስተዋለውን የትራፊክ መጨናነቅ ይቀንሳል፤ • የመንገድ ተጠቃሚዎችን ደህንነት ከማረጋገጡም በላይ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ትስስርን ያጠናክራል፤ • ለኢንቨስትመንት መስፋፋትም ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል። የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ፕሮጀክቱ በተቀመጠለት የጊዜ ገደብ እንዲጠናቀቅ ሁሉም ባለድርሻ አካላት አስፈላጊውን ድጋፍና ርብርብ እንዲያደርጉ ጥሪውን ያስተላልፋል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የዳዬ - ጭሪ - ናንሴቦ አስፋልት መንገድ ፕሮጀክት በዚህ ዓመት ይጠናቀቃል ዳዬ በንሳ፣ መጋቢት 16፣ 2018 (ኢ መ አ):- በምሥራቅ ሲዳማ እና ምዕራብ አርሲ ዞኖች ውስጥ የሚገኙ 4 ወረዳዎችን የሚያስተሳስረው የዳዬ - ጭሪ - ናንሴቦ አስፋልት መንገድ ፕሮጀክት በዚህ ዓመት ይጠናቀቃል። የመንገድ ፕሮጀክቱ 71 ነጥብ 5 ኪሎሜትር የሚሸፍን ሲኾን፥ በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ በመገንባት ላይ ይገኛል። በፕሮጀክቱ በአሁኑ ወቅት እየተከናወኑ ከሚገኙ በርካታ የግንባታ ሥራዎች መካከል፤ የሰብቤዝ፣ ቤዝኮርስ እና የአስፋልት ሥራዎች ይገኙበታል። ከአጠቃላይ የመንገዱ ክፍል 66 ኪ.ሜ የአስፋልት ንጣፍ ተከናውኖለታል። አሁን ላይ የመንገድ ፕሮጀክቱ አጠቃላይ አፈጻጸም 91 ነጥብ 8 በመቶ የደረሰ ሲኾን፥ የግንባታውን ቀሪ ዋና ዋና ሥራዎች በዚህ ዓመት ለማጠናቀቅ አስፈላጊው ቅድመ-ዝግጅት ተደርጓል። ቻይና ዊይ ኮ ሊሚትድ ከፌደራል መንግሥት በተመደበ 1 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር ወጪ የመንገድ ግንባታውን በማከናወን ላይ ይገኛል። ክላሲክ ኮንሰልቲን ኢንጅነርስ፣ ፕሮጀክቱን የማማከር እና የቁጥጥር ሥራ በመሥራት ላይ ነው። የመንገድ ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ አካባቢው በስፋት የሚታወቅበትን የቡና ምርት ወደ ማዕከላዊ እና ዓለም-አቀፍ ገበያዎች በቀላሉ ለማድረስ ያስችላል። የበንሳ፣ ዳኤላ፣ ጭሪ እና ናንሴቦ ወረዳዎችን ደረጃውን በጠበቀ የመንገድ መሠረተ-ልማት በማስተሳሰር የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነቱን ያጠናክራል። የመንገድ ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ በአሁኑ ወቅት በግንባታ ሂደት ላይ ከሚገኘው የኤዶ - ሴሮፍታ - ወርቃ አስፋልት መንገድ ፕሮጀክት ጋር ይገጥማል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የፊቅ-ሰገግ የአስፋልት መንገድ /DBST/ ፕሮጀክት 75 በመቶ ተጠናቀቀ አዲስ አበባ፣ መጋቢት 15/2018 (ኢመአ):- በሶማሌ ክልል ውስጥ የሚገኘው እና 90 ኪሎ ሜትር ርዝመትን የሚሸፍነው የፊቅ - ሰገግ - ገርቦ - ደናን፡¬- ክፍል 1 የፊቅ-ሰገግ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ፕሮጀክት 75 በመቶ የተጠናቀቀ ሲሆን ግንባታውን በአጠረ ጊዜ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው። የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱ መነሻውን ፊቅ ከተማ ላይ አድርጎ እስከ ሰገግ የሚዘልቅ ነው። ከአጠቃላይ የግንባታ ስራው አሁን ላይ 75.60% በመቶ የተጠናቅቀቀ ሲሆን የ33.24 ኪ.ሜ DBST ፣የ49.28 ኪ.ሜ ቤዝ ኮርስ ፣ የ71.57 ኪ.ሜ ሰብ ቤዝ፣ የ79.49% የአፈር ቆረጣና ሙሌት ፣ 59 የተጠናቀቀ አና 32 በሂደት ላይ ያሉ የማፋሸሻ ቱቦ ፣ 2 የተጠናቀቀ አና 4 በሂደት ላይ ያሉ የድልድይ ግንባታ፣ 67.1% ጠጠር መፍጨት (ቤዝ ኮርስ እና የአስፋልት ጠጠር) እንዲሁም በርካታ የስትራክቸው ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛል። ለግንባታ ማስፈጸሚያ የሚውለውን ገንዘብ 1,488,968,324.58 (አንድ ቢሊዮን አራት መቶ ሰማንያ ስምንት ሚሊዮን ዘጠኝ መቶ ስልሳ ስምንት ሺህ ሶስት መቶ ሀያ አራት ብር ከሃምሳ ስምንት ሳንቲም) ብር የሚሸፈነው የኢትዮጵያ መንግስት ነው ። የግንባታ ፕሮጀክቱን እያካሄደ የሚገኘው ሀገር በቀሉ ድሪባ ደፈርሻ ጠቅላላ ሥራ - ተቋራጭ ሲሆን የማማከር እና የቁጥጥር ስራውን ደግሞ ቫልዩ ኢንጂነሪንግ ኃ/የተ/የግ/ማ እያከናወነው ይገኛል። የዚህ መንገድ መገንባት ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጠቀሜታው የጎላ በመሆኑ በDBST ደረጃ እየተገነባ ይገኛል:: የመንገድ ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ ከአዲስ አበባ በፊቅ በኩል ጎዴ ለመጓዝ ቀድሞ ይፈጅ የነበረውን 1ሺህ 170 ኪሎ ሜትር መንገድ በ150 ኪ.ሜ ያሳጥረዋል፡፡ ከጎዴ-ጅጅጋ-ሐረር ይወስድ የነበረውን የጉዞ ጊዜ እና የትራፊክ መጨናነቅ ይቀንሰዋል፡፡ በአካባቢው ለሚገኙ አርብቶ አደሮችና በቁም እንስሳት ንግድ ላይ ለተሰማሩ የኅብረተሰብ ክፍሎች የመንገዱ መገንባት ፋይዳው የጎላ ነው፡፡ የአካባቢው ማህበረሰብ በአብዛኛው አርብቶ አደር በመሆኑ የቤት እንሰሳቶች በማርባትና በመሸጥ የሚተዳደር በመሆኑ በቀላሉ ወደ ገቢያ አውጥቶ በመሸጥ የተሻለ የገቢ እንዲያገኝ ያደርገዋል፡፡ መንገዱ አቋርጧቸው የሚሄድባቸው ከተሞች እና ቀበሌዎችን ለትራንስፖርት ምቹ ከማድረጉም ባለፈ የህብረተሰቡን አገልግሎት የትምህርት ፣ የጤና ተቋማት እና የኢኮኖሚ እንቅስቃሴን ይደግፋል። ከመነሻው ፊቅ ተነስቶ ሰገግ ለመድረስ ቀደም ሲል ከ4 ሰዓት በላይ ይወስድ የነበረውን የጉዞ ጊዜ ወደ 2 ሰዓት ዝቅ ያደርገዋል። የመንገድ ግንባታው በከተማ 19 ሜትር፣ በገጠር 10 ሜትር የጎን ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ እየተገነባ ይገኛል ። የዚሁ መንገድ ፕሮጀክት ኮሪደር ቀጣይ ክፍል የሆነው ክፍል ሁለት፦ ሰገግ-ገርቦ-ዮአለ አስፋልት መንገድ በግንባታ ሂደት ላይ ይገኛል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads