uz
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

Kanalga Telegram’da o‘tish

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር analitikasi

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 13 602 obunachidan iborat bo'lib, Transport toifasida 1 731-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 493-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 13 602 obunachiga ega bo‘ldi.

13 Iyul, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 305 ga, so‘nggi 24 soatda esa 1 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 33.83% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 15.05% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 4 603 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 2 048 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 10 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 14 Iyul, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Transport toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

13 602
Obunachilar
+124 soatlar
+517 kunlar
+30530 kunlar
Postlar arxiv
የዩኒሳ - ቢሾፍቱ የመንገድ ግንባታ ሥራን ለማፋጠን እየተሰራ ነው አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 13፣ 2018 (ኢመአ) በአዲስ አበባ እና በተለያዩ የክልል ከተሞች መካከል ያለውን ትስስር ለማጠናከር ከሚከናወኑ ዋና ዋና የመግቢያና መውጫ ፕሮጀክቶች መካከል አንዱ የሆነው የ 16 ነጥብ 8 ኪሎ ሜትር የዩኒሳ - ቢሾፍቱ መንገድ ግንባታና ማስፋፊያ ሥራን ለማፋጠን እየተሰራ ይገኛል። ይህ ግንባታ የዩኒሳ - ገላን - ቢሾፍቱ - በዩ የመንገድ ፕሮጀክት አካል ሲሆን፤ በአሁኑ ወቅት የዚሁ ፕሮጀክት ክፍል የሆነው የዩኒሳ - ቢሾፍቱ ሎት 3 የመንገድ ግንባታ በይፋ ተጀምሮ ሥራው እየተካሄደ ነው። ፕሮጀክቱ በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የራስ ሀይል ኮንስትራክሽን አማካኝነት እየተገነባ የሚገኝ ሲሆን የመከላከያ ዲዛይን ድርጅት ደግሞ የማማከሩንና የቁጥጥሩን ሥራ እያከናወነ ይገኛል። በኢትዮጵያ መንግሥት በተመደበ 8 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር የሚከናወነው ይህ ፕሮጀክት በአሁኑ ወቅት በጅማሬ ላይ በመሆኑ በአብዛኛው የአፈር ቁፋሮ እና የሙሌት ሥራዎች እየተሰሩ ናቸው። የመንገዱን መጨናነቅ በዘላቂነት ለመቅረፍ ታስቦ የሚገነባው ይህ መንገድ ቀደም ሲል ከከተማ ውጭ 7 ሜትር፣ በከተማ ውስጥ ደግሞ 14 ሜትር ብቻ የነበረው ስፋቱ ወደ 30 ነጥብ 5 ሜትር ከፍ እንዲል ተደርጎ የሚገነባ በመሆኑ የትራፊክ ፍሰቱን በከፍተኛ ደረጃ ያቀላጥፋል። ግንባታው አዲስ አበባን እንደ ዱከም፣ ገላንና ቢሾፍቱ ካሉ የኢንዱስትሪ ማዕከላት ጋር በቀጥታ በማገናኘት፣ በመሃል አገርና በክልል ከተሞች መካከል ያለውን ሁለንተናዊ እንቅስቃሴ ያሻሽላል ። በተለይም እስከ ጅቡቲ ወደብ በሚዘልቀው ዋና መስመር ላይ የሚታየውን የትራፊክ መጨናነቅ በመቀነስ የትራንስፖርት ፍሰቱን ያቀላጥፋል። ከዚህ በተጨማሪ በከተማዋ የሚገነባው ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ መግቢያና መውጫ መስመር በመሆን የሚያገለግል ይሆናል። በተመሳሳይ መልኩ ለቢሾፍቱ የቱሪዝም ዘርፍ መነቃቃትና ለአካባቢው መሠረተ ልማት መዘመን ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያለው መሆኑ ለአካባቢው ህብረተሰብ ደህንነቱ የተጠበቀ፣ ዘመናዊና ፈጣን የትራንስፖርት አገልግሎት ተደራሽ ያደርጋል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የጊንጪ-ሽኩቴ ሎት 1፡ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክትን በዚህ አመት ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው አዲስ አበባ፣ ግንቦት11/2018 (ኢ መ አ):- 62 ነጥብ 2 ኪሎሜትር የሚረዝመው የጊንጪ - ሽኩቴ ሎት 1 አስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በዚህ አመት ለማጠናቀቅ እየተሰራ ይገኛል ። አሁን ላይ 88 በመቶ የሚሆነው የግንባታ ሥራው የተጠናቀቀ ሲሆን 59 ኪሎ ሜትር  የአፈር ቆረጣና ሙሌት ፣ የዉሃ ማፍሰሻና የፉካ ስራዎች  ፣ የሰብቤዝ ፣ የቤዝኮርስ ስራ እንዲሁም 58 ኪሎ ሜትር የአስፋልት ንጣፍ ሥራ ተከናውኗል፡፡ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱን በማከናወን ላይ የሚገኘው ሀገር በቀሉ ገምሹ በየነ ጠቅላላ የሥራ ተቋራጭ ነው። የማማከርና  የቁጥጥር ሥራውን ፎርትረስ ኢንጂነሪንግ ከኮንሰልታንትስ ከአሶሼትስ ማህበር  ጋር በጥምረት እየሰሩት ናቸው። የግንባታው 1,150,000,000 (አንድ ቢሊየን አንድመቶ ሀምሳ ሚሊዮን )ብር ወጪ በኢትዮጵያ መንግስት የተሸፈነ ነው። መንገዱ በወረዳ 18 ፣ በቀበሌ 14.2 ፣ በገጠር ደግሞ 10 ሜትር ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ እየተገነባ የሚገኝ በመሆኑ ቀድሞ ይወስድ የነበረውን የጉዞ ጊዜን የሚያሳጥር ይሆናል። የጊንጪ - ሽኩቴ የመንገድ ግንባታ ሲጠናቀቅ በምዕራብ ሸዋ ዞን ውስጥ የሚገኙትን ደንዲ እና ጀልዱ ወረዳዎችን እንዲሁም ሶስት ቀበሌዎችን ጨምሮ የጎጆ እና የሽኩቴ ከተሞችን በቀላሉ ለማስተሳሰር ያስችላል። በተጨማሪም በአካባቢው የሚገኙትን የስንዴ ፣ የጤፍ ፣ የገብስ እና የቅባት እህል ምርቶች በቀላሉ ወደ ማዕከላዊ ገበያ ለማውጣት ያግዛል ፡፡ እንዲሁም በዚሁ በአከባቢ የሚገኘው የጭልሞ ደን ለጎብኚዎች ተደራሽ እንዲሆን በማድረግ ለሀገራችን የቱሪዝም እድገት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያደርጋል፡፡ የዚሁ መንገድ አካል የሆነውን 63 ነጥብ 2 ኪሎ ሜትር የሚሸፍነው የሽኩቴ - ጩሉጤ ቀጣይ ክፍል ወደስራ ለማስገባት  የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች እየተሰሩ ይገኛሉ። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የቦኖሻ - አጫሞ አስፋልት መንገድ ፕሮጀክት ዋና ዋና ሥራዎች በዚህ ዓመት ይጠናቀቃሉ አዲስ አበባ፣ ግንቦት 07/2018 (ኢ መ አ):- የሃዲያ እና ስልጤ ዞኖችን የሚያገናኘው የቦኖሻ - አጫሞ አስፋልት መንገድ ፕሮጀክት ዋና ዋና ሥራዎች በዚህ ዓመት ይጠናቀቃሉ ። የመንገድ ፕሮጀክቱ 22 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ሲኾን፥ በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ በመገንባት ላይ ይገኛል። አሁን ላይ የ21 ኪ. ሜ የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት፣ የ19 ኪ. ሜ ሰብቤዝ፣ የ7 ኪ. ሜ ቤዝኮርስ፣ የ4 ኪ.ሜ የአስፋልት ንጣፍ እንደዚሁም የውኃ መፋሰሻ ቱቦ እና የከልቨርት ሥራዎች ተሠርተዋል። ከዚህ በተጨማሪም የ1 ድልድይ ግንባታ ተጠናቅቋል። የመንገድ ፕሮጀክቱ በአሁኑ ወቅት አጠቃላይ አፈጻጸሙ 81 ነጥብ 72 በመቶ ደርሷል። የግንባታውን ዋና ዋና ሥራዎች በቀጣይ ጥቂት ወራት ውስጥ ለማጠናቀቅ የሚያስችሉ አስፈላጊ የቅድመ-ዝግጅት ሥራዎች ተጠናቅቀዋል። የመንገድ ግንባታውን ሀገር-በቀሉ ይርጋለም ኮንስትራክሽን ከፌደራል መንግሥት በተመደበ 682 ሚሊዮን ብር ወጪ በማከናወን ላይ ይገኛል። ጎንዱዋና ኢንጅነሪንግ የፕሮጀክቱን የማማከር እና የቁጥጥር ሥራ ያከናውናል። የመንገድ ግንባታ ሥራው ሲጠናቀቅ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ መቀመጫ የኾነችው ሆሳዕና ከተማ ተነስቶ ወደ ሃላባ እና ሐዋሳ እንዲሁም በዙሪያው የሚገኙ ከተሞች በቀላሉ ለመንቀሳቀስ ያስችላል። በአካባቢው በስፋት የሚገኙትን የበርበሬ፣ በቆሎ እንዲሁም መሰል የግብርና ምርቶች በቀላሉ ወደ ማዕከላዊ ገበያ ለማድረስ ያስችላል። ከዚህ ቀደም ከሆሳዕና ወደ ሃላባ ለመጓዝ በውልባራግ በኩል ይደረግ የነበረውን ረጅም እና አድካሚ ጉዞ በማስቀረት በአቋራጭ ለመጓዝ ያስችላል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የባህርዳር - ጢስ እሳት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት አፈፃፀምን ለማሻሻል እየተሰራ ነው አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 28 2018 ዓ.ም (ኢመአ):- 21 ነጥብ 2 ኪሎ ሜትር የሚረዝመውን የባህርዳር - ጢስ እሳት የአስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት አፈፃፀምን ለማሻሻል እየተሰራ ይገኛል፡፡ እስካሁን ባለው የመንገዱ ግንባታ የዲዛይንና የቅየሳ ስራዎች ተጠናቀው 16.44 ኪሎ ሜትር የአፈር ቆረጣና ሙሌት፣ 5.02 ኪሎ ሜትር የሰብቤዝ፣ 4.8 ኪሎ ሜትር የቤዝ ኮርስ ንጣፍ እንዲሁም 4.5 ኪሎ ሜትር የሚሆን የአስፋልት ንጣፍ ሥራ ተከናውኗል። ግንባታው በሀገር በቀሉ መልኮን ኮንስትራክሽን እየተከናወነ የሚገኝ ሲሆን ጎንድዋና ኢንጅነሪንግ ከዋይ.ኤል.ኤስ ኢንጅነሪንግ ጋር በጥምረት የማማከር ሥራውን እየሰሩት ይገኛሉ። ለግንባታው የሚውለው 957,930,208.44 (ዘጠኝ መቶ ሃምሳ ሰባት ሚሊዮን ዘጠኝ መቶ ሰላሳ ሺህ ሁለት መቶ ስምንት ብር በኢትዮጵያ መንግስት የተሸፈነ ነው። በመንገዱ ክልል ውስጥ የሚገኙ ንብረቶች በወቅቱ አለመነሳት፣ የካሳ ክፍያ መዘግየት ፣የአካባቢው የፀጥታ ችግሮች እና የሥራ ተቋራጩ አፈፃፀም ማነስ በሥራው ላይ ጫና ፈጥሮ ቆይቷል። የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ችግሮቹን ለመፍታት ከአካባቢው መስተዳደር ጋር በመሆን ተገቢውን ክትትልና ድጋፍ እያደረገ ይገኛል። ይህ የመንገድ ፕሮጀክት የአካባቢውን የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ትስስር ለማጠናከር ከፍተኛ ፋይዳ ያለው ከመሆኑ ባሻገር የአካባቢውን ማህበረሰብ ከባህር ዳር ከተማ ጋር በማገናኘት የመጓጓዣ ጊዜንና እንግልትን በመቀነስ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ነው፡፡ በተጨማሪም እንደ ጤፍ፣ ሸንኮራ፣ ሽንኩርት እና ጫት ያሉ የግብርና ምርቶችን በፍጥነት ለገበያ ለማቅረብ ከማስቻሉም በላይ የጢስ አባይ ፏፏቴን ለጎብኚዎች ይበልጥ ተደራሽ በማድረግ የአካባቢውን የቱሪዝም እንቅስቃሴ እንደሚያሳድግ ይታመናል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የድሬዳዋ- ሸነሌ የመንገድ ፕሮጀክት የምረቃ ሥነ-ሥርዓት ተካሄደ ሱማሌ፣ ሸነሌ፣ ሚያዚያ 28 2018 ዓ.ም (ኢመአ):- ድሬዳዋ ከሸነሌ ከተማ ጋር የሚያገናኘው የድሬዳዋ- ሸነሌ የመንገድ ፕሮጀክት የምረቃ ሥነ-ሥርዓት ተካሄደ በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ እና የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አደም ፋራ፣ የሱማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር  አቶ ሙስጠፌ መሃመድ ፣ የከተማ እና መሠረተ-ልማት ሚንስትር ደኤታ የትምጌታ አሥራት (ዶ/ር)፣ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር መሃመድ አብዱራህማን (ኢንጅነር) ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ የፌደራል እና የክልል የመንግሥት የሥራ ኅላፊዎች ተገኝተዋል። በሸነሌ ከተማ በተካሄደው የምረቃ መርሃ ግብር ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት ክቡር አቶ አደም ፋራህ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ እና የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት እንደተናገሩት፤ ዛሬ የድሬዳዋ – ሸነሌ መንገድ መጠናቀቅ በክልሉ ልማት ታሪካዊ ምዕራፍ እንደተከፈተ ግልጽ ማሳያ ያሉ ሲሆን መንገዶች አንድ ላይ ሲገናኙ የኢኮኖሚን እና የማህበራዊ  እንቅስቃሴን በስፋት እንደሚያጠናክሩ ገልፀዋል። አያይዘውም ከመንገድ ባሻገር  በክልሉ ውስጥ ሌሎች የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች እየተሰሩ መሆኑን ገልፀው ኢትዮጵያ በተግባር የተገነባ የትስስር እና የኢኮኖሚ ኮሪደር ስርዓት በመዘርጋት ወደፊት እየተጓዘች መሆኑን ተናግረዋል። የሱማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ ዛሬ በሱማሌ ክልል የምናየው ልማት የተለየ ነው።  ይህ የድሬዳዋ – ሸነሌ መንገድ ምርቃት በቃል ሳይሆን በተግባር የተፈጠረ ለውጥ ምስክር ነው ያሉ ሲሆን ይህ መንገድ ከተሞችን ብቻ አያገናኝም፤ ህዝብን ከህዝብ ጋር ያገናኛል፣ ንግድን ያበረታታል፣ እንዲሁም የኢኮኖሚ እድገትን ያፋጥናል። አርብቶ አደሩም ሆነ ገበሬው ምርታቸውን ወደ ገበያ ማድረስ ያስችላል፣ ለወጣቶቻችን ዕድል ይፈጥራል፣ ለሕዝባችን አገልግሎትን ያቀርባል ብለዋል። መንገዱ የድሬዳዋ እና የሸነሌን ህዝቦች በኢኮኖሚ እና በማህበራዊ ግንኙነት ይበልጥ በማስተሳሰር በሁለቱ ከተማዎች መካከል ያለውን ወንድማማችነትና አብሮነት ከማጠናከሩም ባለፈ አንዱ አካባቢ ከሌላው ሳይነጠል በጋራ የማደግ ፍልስፍናችንን በተግባር የሚያሳይ ስኬታማ የመንገድ ልማት ነው  ያሉት የከተማ እና መሠረተ-ልማት ሚንስትር ዲኤታ ዶ/ር የትምጌታ  አስራት  አክለውም የሃገራችን ከተሞች ለነዋሪዎቻቸው ምቹ ለኢንቨስትመንት ሳቢ እና ለንግድ እንቅስቃሴ ቀልጣፋ እንዲሆኑ በከፍተኛ ቁርጠኝነት እየሰራ ይገኛል ብለዋል። የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር መሀመድ አብዱራህማን በበኩላቸው ይህ ስኬት መንግስታችን ለመሠረተ-ልማት ግንባታ የሰጠውን ልዩ ትኩረትና የማይለወጥ ቁርጠኝነት በተግባር የሚያረጋግጥ እንደሆነ ተናግረዋል። ይህ ከፍተኛ የመንግስት መዋዕለ-ነዋይ ወጪ የሆነበት መንገድ ተገቢውን አገልግሎት ለመስጠት ይችል ዘንድ ሁሉም ባለድርሻ አካል ተገቢውን እንክብካቤ እንዲያደርግለት መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። የመንገድ ፕሮጀክቱ የድሬዳዋ–ሽነሌ እና የድሬዳዋ ባይፓስ የመንገድ ፕሮጀክቶችን ያካተተ ሲሆን፣   ከ1 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር በላይ በፌደራል መንግሥት ወጪ ተደርጎበታል።  የድሬዳዋ አስተዳደርን ከሽነሌ ከተማ ጋር የሚያገናኘው ይኸው መንገድ  10.5 ኪ.ሜ ርዝመት ያለው መንገዱ 7.5 ኪ.ሜ በሶማሌ ክልል ሲቲ ዞን ውስጥ ሲገኝ፣ ቀሪው ክፍል በድሬዳዋ አስተዳደር ስር ይገኛል ዓለም - አቀፉ ቻይና ሲቪል ኢንጂነሪንግ ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን የመንገዱን ግንባታ ያካሄደው ሲሆን የማማከር እና የቁጥጥር ሥራው በቤዛ ኢንጂነሪንግ ኬንያ ሊሚትድ ተከናውኗል። መንገዱ ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ፋይዳ ያለው ሲሆን ከድሬዳዋ ተነስቶ ሽንሌን በማቋረጥ ሰፊውን የሶማሌ ክልል ከሀገራዊ የንግድ መረብ ጋር የሚያስተሳሰር ወሳኝ የልማት ድልድይ ነው። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የጣፎ አደባባይ - ለገዳዲ - ኩራ ጅዳ መንገድ ግንባታ እየተፋጠነ ይገኛል አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 21/ 2018 ዓ.ም (ኢመአ)፦ የአዲስ አበባ ከተማን ከክልል ከተሞች ጋር ከሚያገናኙ አምስት ዋና ዋና መግቢያና መውጫዎች መካከል አንዱ የሆነው የጣፎ አደባባይ - ለገዳዲ - ኩራ ጅዳ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት  ግንባታ እየተፋጠነ ይገኛል። 15 ኪሎ ሜትር የሚረዝመው ይህ የመንገድ  ሥራ በኢመአ የራስ ኃይል (ዓለም ገና መንገድ ጥገና ዲስትሪክት) ፣በአሰር ኮንስትራክሽን እንዲሁም በዋይብ ትሬዲንግ ኃ/የተ/የግል ማህበር ጥምረት ነው እየተከናወነ የሚገኘው። የማማከርና የቁጥጥሩን ሥራ  የኢትዮጵያ ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን የትራንስፖርት ሴክተር እየሰራው ሲሆን ለመንገዱ ግንባታ የሚውለውን 19 ቢሊየን ብር በላይ ወጪ በፌዴራል መንግሥት የተሸፈነ ነው። መንገዱ  በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ እና በሸገር  ከተማ አስተዳደር ውስጥ  የሚገኙትን  ኤካ ጣፎ እና ኩራ ጅዳ ወረዳዎችን አቋርጦ ያልፋል። ቀደም ሲል የነበረው  7 ሜትር  የጎን ስፋት የነበረው መንገድ አሁን ላይ  በግራና በቀኝ 4 ተሽከርካሪዎችን ማስተናገድ በሚችል መልኩ ወደ 28 ሜትር ስፋት እንዲያድግ ተደርጓል። የፕሮጀክቱ ግንባታ የትራፊክ ፍሰቱን ከማሳለጥ ባለፈ 4 ሜትር የአረንጓዴ ስፍራ እንዲሁም 14 ሜትር የእግረኛና የሳይክል መንገዶችን ያካተተ ነው። መስመሩ ከአዲስ አበባ ወደ ሰሜኑ የሀገሪቱ ክፍል ደብረ ብርሃን፣ ደብረ ሲና፣ ኮምቦልቻ እና ደሴ ለሚደረግ ጉዞ ዋነኛ መተላለፊያ በመሆኑ የትራፊክ መጨናነቅ በከፍተኛ ደረጃ ይቀንሳል። ከዚህም በተጨማሪ በአካባቢው ከሚገኙ የኢንዱስትሪ ዞኖች የሚወጡ የኤክስፖርት ምርቶችን እንቅስቃሴ ከማሳለጡም በላይ የግብርና እና የወተት ውጤቶች ያለምንም መጓተት ወደ ማዕከላዊ ገበያ እንዲቀርቡ በማድረግ ረገድ የላቀ ፋይዳ ይኖረዋል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር 75ኛ ዓመት የአልማዝ ኢዮቤልዩ በዓል የመክፈቻ ዝግጅት ተካሄደ አዲስ አበባ፣ሚያዝያ 12/2018(ኢመአ):- የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በሀገሪቱ የመንገድ መሠረተ ልማት ግንባታ የ75 ዓመታት ጉዞ የሚዘክርበትን የአልማዝ ኢዮቤልዩ በዓል በአዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ማዕከል በተሰናዳ የመክፈቻ ሥነ-ስርዓት ተካሄዷል። ይህንን በማስመልከት የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር መሐመድ አብዱራህማን፤ ኢመአ ባለፉት ሰባት አስርት ዓመታት ውስጥ ያለፈባቸውን አስቸጋሪና ስኬታማ የሥራ እንቅስቃሴዎች በዝርዝር አብራርተዋል። ዋና ዳይሬክተሩ "ይህ በዓል ያለፈውን ታሪካዊ ስኬት የምናደንቅበት ብቻ ሳይሆን፣ የወደፊቱን የልማት ግቦች የምንቃኝበትና አዳዲስ የቴክኖሎጂ አሰራሮችን ለማስተግበር ቃል የምንገባበት ጭምር ነው" በማለት ሁሉም በጋራ በመቆም የተጀመረውን የብልጽግና ጉዞ በስኬት እንደሚያስቀጥሉ ያላቸውን ጽኑ እምነት ገልጸዋል። የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ዶ/ር የትምጌታ አሥራት በበኩላቸው ተቋሙ የሀገሪቱን የኢኮኖሚና ማህበራዊ ትስስር በማጠናከር ረገድ እየተወጣ ያለውን ሚና አድንቀዋል። የመንገድ ልማት ሥራዎችን በጥራትና በፍጥነት ከማከናወን ጎን ለጎን፣ የመንገድ ግንባታ ሥራ እንቅስቃሴዎችን በቅርበት በመከታተልና የአሠራር ውጤታማነትን በማረጋገጥ የዜጎችን ተጠቃሚነት ማሳደግ እንደሚገባም በአፅንኦት አሳስበዋል። የክብረ በዓሉ አንዱ አካል ሆኖ በልዩ ሁኔታ በቀረበው አውደ-ርዕይ፤ ተቋሙ በኢትዮጵያ ተራራማና አስቸጋሪ መልክዓ-ምድር ውስጥ መንገዶችን ለመገንባት የከፈለውን መሥዋዕትነት የሚያሳዩ ሥራዎችን አካቶ ለታዳሚው ቀርቧል። ዘመናዊ መሣሪያዎች ባልነበሩበት ወቅት የነበረውን አድካሚ የሥራ ሂደት ህያው አድርገው የሚያሳዩት እነዚህ የታሪክ አሻራዎች፤ ተቋሙ ያለፈበትን ጥንካሬና ለዛሬው የዕድገት መሠረት መሆናቸውን ማሳየት ተችሏል ። በመርሀ ግብሩ ላይ የተገኙት አንጋፋ አመራሮችም፣ ተቋሙ በየዘመኑ የነበሩበትን ተግዳሮቶች እንዴት በፅናት እንደተወጣና አሁን ላለው ደረጃ እንደደረሰ የሚያሳይ ዘመን ተሻጋሪ የሥራ ተሞክሮአቸውን ለታዳሚው አካፍለዋል። በዕለቱ የኢመአ የ75 ዓመታት ጉዞ ውስጥ የተከናወኑ ታላላቅ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶችንና የወደፊት ዕቅዶችን የሚያሳይ ዘጋቢ ፊልም ለተሳታፊዎች ቀርቧል። በዛሬው እለት የተካሄደው የአልማዝ ኢዮቤልዩ የመክፈቻ ሥነ -ሥርዓት ሲሆን በቀጣይም በዋናው መስሪያቤት እንዲሁም በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች በሚገኙ ዲስትሪክቶች እና የፕሮጀክት ፅ/ቤቶች በተለያዩ ዝግጅቶች የሚከበር ይሆናል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

“ኢትዮጵያ ትገነባለች!”፦ የመጀመሪያው ሀገራዊ የኮንስትራክሽንና መሰረተ ልማት ሳምንት በታላቅ ድምቀት ተከፈተ አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 9/2018 ዓ.ም (ኢመአ): በሀገር አቀፍ ደረጃ ለመጀመሪያ ጊዜ የተዘጋጀው የኢትዮጵያ የመሰረተ ልማትና የኮንስትራክሽን ሳምንት፤ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ እና በከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት ዛሬ ሚያዝያ 9 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ሴንተር በይፋ ተጀመረ። “ኢትዮጵያ ትገነባለች!” በሚል መሪ ቃል በከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር የተዘጋጀውና እስከ ሚያዝያ 12 ቀን የሚቆየው ይህ ታላቅ መድረክ፤ የዘርፉ ተዋናዮችና ባለድርሻ አካላት ልምድ የሚለዋወጡበትና ለሀገር ግንባታ የጋራ ራዕይ የሚሰንቁበት መድረክ እንደሚሆን ይጠበቃል። የዕለቱ ክብር እንግዳ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በዘርፉ የታዩ ሀገራዊ ስኬቶችንና የቴክኖሎጂ አማራጮችን የሚያሳየውን አውደ-ርዕይ መርቀው የከፈቱ ሲሆን፣ ከመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ጋር በመሆን ጉብኝት አድርገዋል። አቶ ተመስገን በመክፈቻው ባስተላለፉት መልእክት፤ መሰረተ ልማት ለሀገር እድገት ያለውን ወሳኝ ሚና አብራርተዋል። ኩነቱ አዳዲስ የግንባታ ቴክኖሎጂዎችን ለማስተዋወቅ፣ የሀገር በቀል አቅምን ለማሳደግና የሀገር ውስጥ ኩባንያዎች አገልግሎታቸውን ለዓለም አቀፍ ገበያ እንዲያስተዋውቁ ምቹ ሁኔታ እንደሚፈጥር ተመልክቷል። በቀጣዮቹ ቀናትም በዘርፉ ስኬቶችና የወደፊት አቅጣጫዎች ላይ ያተኮሩ የፓናል ውይይቶች እንደሚካሄዱና ልዩ ልዩ ሰነዶች እንደሚቀርቡ ታውቋል። በኤግዚቢሽኑ ላይ የተለያዩ የግንባታ ግብዓቶች፣ ግዙፍ ማሽነሪዎች እና ዲጂታል የግንባታ ቴክኖሎጂዎች ለዕይታ ቀርበዋል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

"ኢትዮጵያ ትገነባለች!" በሚል መሪ ቃል የሚካሄደው ሀገራዊ የኮንስትራክሽንና መሰረተ ልማት ሳምንት ነገ ይጀምራል የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የመጀመሪያው የኢትዮጵያ የመሰረተ ልማትና የኮንስትራክሽን ሳምንት ነገ ሚያዝያ 9 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ሴንተር (CMC) በይፋ ይጀምራል። እስከ ሚያዝያ 12 ቀን 2018 ዓ.ም ለአራት ተከታታይ ቀናት የሚቆየው ይህ መድረክ፣ በዘርፉ የተመዘገቡ ስኬቶችን ለማሳየትና የቀጣይ የልማት አቅጣጫዎችን ለመጠቆም ያለመ መሆኑ ተገልጿል። መርሐ ግብሩ "ኢትዮጵያ ትገነባለች! ፈጠራ፣ ፍጥነት እና ጥራት ለመሠረተ ልማት እምርታ" በሚል መሪ ቃል የሚካሄድ ሲሆን፣ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የዘርፉ መሪዎች፣ ዓለም አቀፍ የልማት አጋሮች እና የግሉ ዘርፍ ተዋናዮች የሚሳተፉበት ይሆናል። የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ ቀደም ብለው በሰጡት መግለጫ እንዳመለከቱት፣ ይህ ሳምንት በኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪው ውስጥ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን ለማስተዋወቅና የሀገር በቀል አቅምን ለማሳደግ ትልቅ ዕድል ይፈጥራል። በተለይም ባለፉት አምስት ዓመታት የተገነቡ 40 ሺህ ኪሎ ሜትር የሚጠጉ አዳዲስ መንገዶችና የአዲስ አበባን ገጽታ የቀየሩ የኮሪደር ልማት ውጤቶች በመድረኩ በዝርዝር እንደሚቀርቡ ይጠበቃል። በኤግዚቢሽኑ ላይ፦ የግንባታ ግብዓቶች፣ ግዙፍ ማሽነሪዎች እና ዲጂታል የግንባታ ቴክኖሎጂዎች ለዕይታ ይቀርባሉ። የ10 ዓመቱ የልማት ዕቅድ አፈጻጸም ለሕዝብ ይፋ ይደረጋል። በዘርፉ ከፍተኛ አፈጻጸም ላሳዩ ተቋራጮች፣ አማካሪዎችና ባለሙያዎች ዕውቅና ይሰጣል። ይህ ሳምንት የኢትዮጵያን የ67 ቢሊዮን ዶላር የኮንስትራክሽን ገበያ ለዓለም አቀፍ ኩባንያዎች በማስተዋወቅ ረገድም ቁልፍ ሚና እንደሚኖረው ተመልክቷል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads