fa
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

رفتن به کانال در Telegram

EEP Communication

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام EEP Communication

کانال EEP Communication (@eepcommuication) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 15 533 مشترک است و جایگاه 8 368 را در دسته فناوری و برنامه‌ها و رتبه 2 174 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 15 533 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 30 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 10 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -6 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 24.86% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 16.87% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 3 862 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 2 620 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 9 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
EEP Communication

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 01 ژوئیه, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته فناوری و برنامه‌ها تبدیل کرده‌اند.

15 533
مشترکین
-624 ساعت
-207 روز
+1030 روز
آرشیو پست ها
photo content
+1

photo content
+3

የሰንደቅ ዓላማ ቀን ሲከበር ሁሉም የተቋሙ አመራርና ሠራተኛ ለሀገር ሰላም ዘብ በመቆም ሊሆን ይገባል - አቶ አሸብር ባልቻ ..........///........ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራሮችና ሠራተኞች የሰንደቅ ዓላማ ቀንን ሲያከብሩ ለሀገር ሰላም ዘብ በመቆም መሆን እንዳለበት የተቋሙ የዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አሸብር ባልቻ ገለፁ፡፡ የተቋሙ አመራሮችና ሠራተኞች 16ኛውን ብሔራዊ የሰንደቅ ዓላማ ቀን "የሰንደቅ ዓለማችን ከፍታ ለሕብረ ብሔራዊ አንድነታችንና ሉዓላዊነታችን ዋስትና ነው" በሚል መሪ ቃል በተቋሙ ዋና መሥሪያ ቤት አክብረዋል፡፡ በበዓሉ ላይ አቶ አሸብር ባልቻ እንደተናገሩት ሰንደቅ ዓላማ የህዝቦች ሉዓላዊነትና አንድነት መገለጫ ነው። በዓሉ በሀገራችን አስተማማኝና ዘላቂነት ያለው ሰላም ለማስፈን የሁሉም ዜጋ ኃላፊነት መሆኑን ለማስገንዘብ እንደሚረዳም ተናግረዋል። እንደ ዋና ሥራ አስፈፃሚው ገለፃ የሰንደቅ ዓላማ ቀን መከበሩ አንድነታችንን በማጠናከር ሀገራችን ከገባችበት ችግር ተላቃ ወደ ብልፅግናዋ የምትሻገርበትን ሕብረ ብሔራዊ አቅም ለመፍጠር ያግዛል። ሉዓላዊነቷና ሕብረ ብሔራዊ አንድነቷን ያስጠበቀች ሀገር ለልጅ ልጆቻችን ለማውረስ ሌት ተቀን መስራት ይኖርብናል ብለዋል። ተቋሙ እንደ ሀገር የተጣለበትን ኃላፊነት ለመወጣት ሁሉም የተቋሙ አመራርና ሠራተኞች በተባበረ ክንድ መስራት እንደሚጠበቅባቸው አሳስበዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 05 ቀን 2016 ዓ.ም

ለጥገና ሥራ ሲባል የሚቋረጥ የኃይል አቅርቦት እሁድ ጥቅምት 4 ቀን 2016 ዓ.ም. በወልቂጤ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የጥገና ሥራ ይከናወናል፡፡ በመሆኑም ከጠዋቱ 1፡00 ሰዓት እስከ ቀኑ 7፡00 ሰዓት
ለጥገና ሥራ ሲባል የሚቋረጥ የኃይል አቅርቦት እሁድ ጥቅምት 4 ቀን 2016 ዓ.ም. በወልቂጤ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የጥገና ሥራ ይከናወናል፡፡ በመሆኑም ከጠዋቱ 1፡00 ሰዓት እስከ ቀኑ 7፡00 ሰዓት ድረስ በእንድብር፣ በኢንዱስትሪ፣ በወልቂጤ ከተማ፣ በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ፣ በአገና፣ በጉንችሬ፣ በዋዩ ጦላይ፣ በዘቢደር ቢራ ፋብሪካ፣ በወሊሶ ከተማ እና አካባቢው የኤሌክትሪክ ኃይል ተቋርጦ ይቆያል፡፡ ስለሆነም ክቡራን ደንበኞቻችን ይህንኑ በመገንዘብ ከወዲሁ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት እንድታደርጉ በአክብሮት እናሳስባለን፡፡"ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 02 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+4

የተቋሙ ዋና መስሪያ ቤት ህንፃ ዲዛይን በአረንጓዴ ህንፃ የወርቅ ሰርትፊኬት ደረጃ እየተሰራ ነው …..///…... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አዲስ የሚያስገነባውን የዋና መስሪያ ቤት ህንፃ ዲዛይን የአረንጓዴ ህንፃ የወርቅ ደረጃ ሰርትፊኬት እንዲያገኝ በሚያስችል መልኩ የአጠቃላይ ዲዛይን ሥራ እያከናወነ መሆኑን ፕሮጀክት ጽ/ቤቱ አስታወቀ፡፡ የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ አቶ በኃይሉ ታደለ እንደገለፁት የተቋሙ ህንፃ ዲዛይን በአሜሪካ የአረንጓዴ ህንፃዎች ካውንስል በሚመራው የኢነርጂና የአካባቢ ዲዛይን (LEED) ሥርዓት መሰረት የወርቅ ደረጃ መስፈርቶችን የሚያሟላ ነው፡፡ የህንፃው ዲዛይን ኢነርጂ ቆጣቢ፣ በሰውና በአካባቢ ላይ ምንም አይነት ተፅዕኖ የማያሳድር እንዲሁም ለሥነ-ምህዳር ተስማሚ የሆኑ የአረንጓዴ ስፍራዎች የተካተቱበት በመሆኑ የሚሰጥ የዕውቅና ሰርትፊኬት ነው ብለዋል። ሜክሲኮ በሚገኘው በተቋሙ ቅጥር ግቢ የሚገነባው ባለ 62 ወለል ሰማይ ጠቀስ ህንፃ ተቋሙን የሚገልፁ፤ ከፀሐይ እና ከንፋስ ኃይል በማመንጨት ለህንፃው ፍጆታ ኃይል ማቅረብ የሚያስችሉ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎች እንደሚኖሩት ሥራ አስኪያጁ ገልፀዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት የአፈር ምርምር ሥራ ለማከናወን ከተመረጡት 28 ጉድጓዶች ውስጥ የ25ቱ ጉድጓዶች የቁፋሮ ሥራ መጠናቀቁን የገለፁት ሥራ አስኪያጁ የቀሪ 3 ጉድጓዶችን ቁፋሮ በአንድ ሳምንት ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ እንደሚሰራ ጠቁመዋል፡፡ ዋናው የህንፃ ግንባታ የቁፋሮ ሥራ ከመጀመሩ በፊት አሁናዊ የአካባቢ የመልከዓ-ምድር የቅየሳ ጥናት መጠናቀቁንም ነው አቶ በኃይሉ የተናገሩት፡፡ አማካሪ ድርጅቱ የህንፃውን ዲዛይን ሙሉ በሙሉ አጠናቆ ለማስረከብ የስድስት ወር ጊዜ የተሰጠው ሲሆን ሥራውም በተያዘለት ዕቅድ በጥራት እየተከናወነ መሆኑንም ገልፀዋል፡፡ የህንፃውን ዝርዝር የዲዛይን ሥራ በታህሳስ ወር መጨረሻ ላይ በማጠናቀቅ ዋናውን ግንባታ የሚያከናውነውን ሥራ ተቋራጭ የመለየት ሥራ ይሰራል ብለዋል፡፡ እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ የህንፃውን ግንባታ በተመለከተ ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር፣ ከኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለሥልጣን፣ ከኢትዮ-ቴሌኮም፣ ከአዲስ አበባ ውሃና ፍሳሽ እንዲሁም ከግንባታ ፈቃድና ቁጥጥር ባለሥልጣን ተቋማት የተለያዩ ግብዓቶች ተሰብስቧል፡፡ በ20 ሺህ 792 ካሬ ሜትር ላይ የሚያርፈው እና የወለል ስፋት መጠኑ 197 ሺህ 800 ካሬ ሜትር የሚሆነው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የዋና መስሪያ ቤት ህንፃ ግንባታው ሲጠናቀቅ 327 ነጥብ 5 ሜትር ርዝመት ይኖረዋል፡፡ ግንባታው 445 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር የሚፈጅ ሲሆን በ4 ዓመት ውስጥ ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 01 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

ሁለተኛው ምዕራፍ የሳፕ ትግበራ በተያዘው መርሃ ግብር መሰረት እየተከናወነ ይገኛል ........///…….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የአሰራር ሥርዓቶችን ለማዘመን እና ለማቀላጠፍ ሳፕ በተባለ ሶፍትዌር እያከናወነው ያለው ሁለተኛው ምዕራፍ የሲስተም ትግበራ በተያዘው መርሃ ግብር መሰረት እየተከናወነ እንደሚገኝ በተቋሙ የሞደርናይዜሽን መምሪያ አስታወቀ። የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ገነቱ ደሳለኝ እንዳስታወቁት ሁለተኛው ምዕራፍ የሳፕ ሲስተም የትግበራ ሥራ በአራት ምዕራፎች ተከፍሎ እየተከናወነ ይገኛል፡፡ እንደ አቶ ገነቱ ገለፃ በሁለተኛው ምዕራፍ በሚተገበሩ ሞጅሎች ላይ የሚካተቱ ጉዳዮችን ለማስቀመጥ እና ወሰኑን ለመለየት የሚያስችሉ ከ12 በላይ የሚሆኑ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠናዎች እና አውደ ጥናቶች ተከናውነዋል፡፡ አሁን በተግባር ላይ ባለው አሰራር የሚስተዋሉ ክፍተቶች ተለይተው እንዲሻሻሉ እና በአሰራር ሥርዓቱ ውስጥ እንዲካተቱ ለማድረግ የሚያግዝ የሳፕ መተግበሪያ ሰነድ እንደተዘጋጀም ጠቁመዋል፡፡ የተቋሙ የሥራ ሂደቶች ያሰራናል ብለው ባቀረቧቸው የመፍትሔ ሃሳቦች ዙሪያ የጋራ መግባባት ላይ በመድረስ እየተፈራረሙ እንደሚገኙ የተናገሩት አቶ ገነቱ የመፈራረሙ ሂደቱ እንደተጠናቀቀ ወደ ሙሉ ትግበራ ይገባል ብለዋል፡፡ በመጀመሪያው ምዕራፍ የሳፕ ትግበራ ላይ የሥራ ክፍሎች የሞጁሎችን ወሰን ለይቶ በማቅረብ፣ መረጃዎችን በማጠናቀር፣ ሥልጠናዎችን በአግባቡ በመከታተልና ድርሻቸውን በማወቅ በኩል ክፍተቶች እንደነበሩ ያስታወሱት ዳይሬክተሩ በሁለተኛው ምዕራፍ ላይ ችግሮቹ አንዳይደገሙ ከየሥራ ክፍሎች ጋር በቅርበት እየተሰራ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል። በተቋሙ የተዋቀረው የተቋማዊ ለውጥ ቡድን ሠራተኛው በሲስተሙ ፋይዳ ላይ ግልጽ ግንዛቤ እንዲኖረው እና የሥራ ክፍሎች በእኔነት ስሜት እንዲሰሩ ግንዛቤ በመፍጠር ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ እንደሚገኝ አመልክተዋል፡፡ እስከ አሁን ባለው ሁኔታ ትግበራው በተያዘለት በጀትና መርሃ ግብር መሰረት እየተካሔደ ነው ያሉት አቶ ገነቱ ተቋሙ በአዲስ መልክ ለመተግበር ያስጠናው የመዋቅር ሥራ በሳፕ የትግበራ ሂደት ላይ ተጽዕኖ ሳያሳድር እንዲከናወን ለማድረግ ከሚመለከታቸው የሥራ ክፍሎች እና ከተቋሙ የሥራ አመራር ጋር ውይይት እየተካሄደ እንደሆነም አስታውቀዋል፡፡ ሁለተኛውን ምዕራፍ የሳፕ ትግበራ በተያዘለት ጊዜ፣ በጀትና ጥራቱን በጠበቀ መልኩ ለማጠናቀቅ በየደረጃው የሚገኙ አመራሮችና ሠራተኞች በቁርጠኝነትና በኃላፊነት እንዲሠሩም ጥሪ አቅርበዋል፡፡ በሲስተሙ ውስጥ አሪባ፣ ሰክሰስ ፋክተር፣ ፕላንት ሜንቴናንስ፣ ስፒር፣ ጂ.አር.ሲ የተሰኙ ሞጂሎች ተግባራዊ የሚደረጉ ሲሆን ሞጁሎቹ ሙሉ በሙሉ መተግበር ሲጀምሩ የተቋሙን የአሰራር ሥርዓት ለማዘመን፣ ጠንካራ የሀብት ቁጥጥር ሥርዓት ለመዘርጋት፣ ወጭ ለመቀነስና ሥራን ለማቀላጠፍ እንዲሁም መረጃዎችን በአግባቡ አደራጅቶ በጥራት ተደራሽ ለማድረግ ከፍተኛ ፋይዳ ይኖረዋል ተብሏል። ሁለተኛው ምዕራፍ የሳፕ ትግበራ በፋይናንስ፣ በሰው ኃይል አስተዳደር፣ በግዥ፣ ዕቃ ግምጃ ቤት እንዲሁም ከመጀመሪያው ምዕራፍ የቀጠሉ የተለያዩ ሥራዎች ላይ ትኩረት እንደሚያደርግ ከዚህ በፊት መዘገባችን የሚታወስ ነው። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 30 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+1

የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሾፌር 4ኛ የሥራ መደብ ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር ጳጉሜ 01 ቀን 2015 ዓ.ም የውጪ ማስታወቂያ ማውጣቱ ይታወሳል፡፡ በዚሁ መሰረት ከዚህ በታች ስማችሁ የተገለጸው አመልካቾች ጥቅምት 06 ቀን 2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት ማንነታችሁን የሚገልጽ የታደሰ መታወቂያ በመያዝ  ኮተቤ በሚገኘው በዋናው መ/ቤት ማሰልጠኛ አዳራሽ  የጽሁፍ ፈተና የሚሰጥ በመሆኑ ለፈተና እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡

photo content
+5

በሪጅኑ በ186 ሚሊዮን ብር በጀት የማከፋፈያ ጣቢያዎችን የሲቪል ጥገና ይከናወናል …….///……. በተያዘው በጀት ዓመት በ186 ሚሊዮን ብር ወጭ የማከፋፈያ ጣቢያዎችን የሲቪል ጥገና ለማከናወን አቅዶ እየሠራ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማዕከላዊ ሪጅን 3 የማስተላለፊያና ማከፋፈያ ጣቢያዎች መምሪያ አስታወቀ፡፡ መምሪያው በዋቢሸበሌ ሆቴል የበጀት ዓመቱን የመጀመሪያ ሩብ ዓመት አፈጻጸም ሲገመግም መደበኛ የጥገናና የኦፕሬሽን ሥራዎች አፈጻጸም እና በጣቢያዎች ላይ የሚሰሩ የሲቪል ጥገና ሥራዎች አፈፃፀምን በትኩረት ተመልክቷል፡፡ የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ጋሻው እንድሪያስ በግምገማው ላይ እንደገለጹት በሁሉም የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች የሚሰሩ መደበኛ የክትትል፣ የጥገናና የኦፕሬሽን ሥራዎች በተያዘላቸው ጊዜ እየተከናወኑ ይገኛሉ፡፡ ሪጅኑ ከሚያከናውናቸው መደበኛ ሥራዎች በተጨማሪ በ17 የማከፋፈያ ጣቢያዎች ውስጥ 38 የተለያዩ የሲቪል ጥገና ሥራዎችን ለማከናወን አቅዶ ወደ ተግባር መግባቱን ዳይሬክተሩ ገልጸዋል፡፡ በ17ቱ ማከፋፈያ ጣቢያዎች ለሚከናወኑት የአጥር ግንባታ፣የመኖሪያ ቤት እድሳት፣የፍሳሽ ማስወገጃ ግንባታና የመቆጣጠሪያ ክፍል ጥገና ሥራዎች 186 ሚሊዮን ብር በጀት ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል፡፡ በማከፋፈያ ጣቢያዎቹ ዙሪያ የህዝብ አሰፋፈርና የከተሞች መስፋፋት እየጨመረ በመምጣቱ የማከፋፈያ ጣቢያዎችን ደህንነት የበለጠ ለመጠበቅ ደረጃውን የጠበቀ የአጥር ግንባታ አስፈላጊ መሆኑን ዳይሬክተሩ ተናግረዋል፡፡ እንደ ዳይሬክተሩ ገለፃ በመጀመሪያው ሩብ ዓመት የአምስት ማከፋፈያ ጣቢያዎች የሲቪል ጥገና ሥራ ለማከናወን በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጨረታ ወጥቶ አሸናፊዎቹ በተለዩባቸው በቃሊቲ 2፣ በአንፎ እና በሰበታ 1 ጣቢያዎች ተቋራጮቹ ሥራ ጀምረዋል፡፡ ሌሎች የማከፋፈያ ጣቢያዎችም በዕቅዱ መሠረት ጨረታ በማውጣት ግንባታዎቹና ጥገናዎቹ እንደሚከናወኑ ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 29 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+6

ፕሮጀክቶቹን በተያዘላቸው የጊዜ ገደብ ለማጠናቀቅ በትኩረት እየተሰራ ነው ….....///…….. የገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን፣ የበቆጂ እና የደብረ-ታቦር የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ ፕሮጀክቶችን በተቀመጠላቸው በጀትና የጊዜ ገደብ ለማጠናቀቅ እየሰራ እንደሚገኝ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የራስ ኃይል ግንባታ መምሪያ አስታወቀ። የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ሰሎሞን ኃ/ጊዮርጊስ እንደገለፁት የፕሮጀክቶች ግንባታ በተያዘላቸው የጊዜ ገደብ ተጠናቆ ለአገልግሎት ዝግጁ እንዲሆኑ ለማድረግ የሚያስችሉ አሰራሮች ተዘርግተዋል፡፡ የፕሮጀክቶች ግንባታ ከመጀመሩ በፊት ባለሙያዎች በግንባታ ወቅት ሊገጥሟቸው ስለሚችሉ ችግሮች በቂ ግንዛቤና ሥልጠና እንዲያገኙ መደረጉን ተናግረዋል። እንደ አቶ ሰለሞን ገለፃ መምሪያው የራሱ የግዥ አደረጃጀት እንዲኖረው በመደረጉ በግዥ መዘግየት ምክንያት ይገጥሙት የነበሩትን የፕሮጀክት ግንባታ አፈፃፀም ችግሮችን ማስወገድ ችሏል። በግንባታ ብረቶች አቅርቦት እጥረት ምክንያት በየጊዜው የሚፈተነውን የፕሮጀክቶች የግንባታ እንቅስቃሴ በዘላቂነት ለመቅረፍም ዓመታዊ የብረት ግዥ ለመፈፀም መታሰቡን ጠቁመዋል። ዓመታዊ ግዢው ከጊዜ ወደ ጊዜ በሀገሪቱ እየጨመረ የመጣውን የብረት ዋጋ ታሳቢ ያደረገና የአቅርቦት ችግር እንዳይፈጠር ያለመ እንደሆነም ነው ዳይሬክተሩ ያብራሩት። በገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን የኃይል አቅርቦት ፕሮጀክት የግንባታ ሒደት ላይ የታዩ መልካም ተሞክሮዎችን በሌሎች ፕሮጀክቶች ላይ ለመተግበር እንቅስቀሴዎች መጀመራቸውን አቶ ሰለሞን ገልፀዋል። የበቆጂ እና የደብረ-ታቦር የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቶች የኤሌክትሮ ሥራዎች ሜካኒካል ዲዛይን በመጠናቀቁ የትራንስፎርመር የመሠረት ሙሌት ግንባታ እየተከናወነ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡ ፕሮጀክቶችን በዕቅዳቸው መሠረት እንዲጠናቀቁ ማድረግ ለተጠቃሚው ህብረተሰብ እና ኢንዱስትሪዎች በተፈለገው ወቅት ኃይል በማቅረብ ረገድ ጠቀሜታው የጎላ መሆኑንም ነው አቶ ሰለሞን የገለፁት። እንደ ዳይሬክተሩ ገለፃ በተቀመጠላቸው የጊዜ ገደብ የማይጠናቀቁ ፕሮጀክቶችን በመለየት ተቋሙ አፋጣኝ እርምጃ መውሰድ አለበት፡፡ በተያያዘ ዜና የገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን፣ የበቆጂና የደብረታቦር የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታዎችን ሙሉ በሙሉ በተቋሙ የራስ ኃይል ግንባታ መምሪያ በመከናወኑ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ማዳን መቻሉን አቶ ሰለሞን ተናግረዋል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 28 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በተለያዩ የስራ መደቦች መጋቢት 02 ቀን 2015 ዓ.ም በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ባወጣው ማስታወቂያ መሰረት ፈተና የወሰዳችሁ መሆኑ ይታወቃል፡፡ ስለሆነም ከዚህ በታች ስማችሁ የተገለጸው ተወዳዳሪዎች አብላጫ የማለፊያ ነጥብ ያመጣችሁ ስለሆነ ከመስከረም 28 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት 5 /አምስት/ ተከታታይ የስራ ቀናት ኮተቤ በሚገኘው ዋና መ/ቤት የሰው ኃይል ምደባ ቢሮ ዋናውን የትምህርት ማስረጃችሁን እና የስራ ልምዳችሁን ይዛችሁ በመቅረብ ሪፖርት እንድታደርጉ እናሳስባለን፡፡