ch
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

前往频道在 Telegram

EEP Communication

显示更多

📈 Telegram 频道 EEP Communication 的分析概览

频道 EEP Communication (@eepcommuication) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 533 名订阅者,在 技术与应用 类别中位列第 8 368,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 174

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 533 名订阅者。

根据 30 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 10,过去 24 小时变化为 -6,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 24.86%。内容发布后 24 小时内通常能获得 16.87% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 3 862 次浏览,首日通常累积 2 620 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 9

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
EEP Communication

凭借高频更新(最新数据采集于 01 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 技术与应用 类别中的关键影响点。

15 533
订阅者
-624 小时
-207
+1030
帖子存档
photo content
+1

photo content
+9

በማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክቱ ላይ የስርቆት ወንጀል እየተፈፀመ ነው ………///……… 82 በመቶ የደረሰው የአዋሽ- ወልዲያ- ሀራ ገበያ የባቡር መስመር የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ፕሮጀክት ተደጋጋሚ ስርቆት እየተፈፀመበት መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ግንባታ ዘርፍ የፕሮጀክቱ የሳይት ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ። ሥራ አስኪያጁ አቶ ተክለወይኒ ብርሃነ እንዳስታወቁት በፕሮጀክቱ ላይ እስከ አሁን ከተተከሉ 175 የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ ምሶሶዎች መካከል በ37ቱ ላይ ስርቆት ተፈፅሞባቸዋል። ከመስከረም 2 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ በተፈፀመው ስርቆት 6 ሺህ የሚሆኑ የምሰሶ ብረቶች ተፈተው የተወሰዱ ሲሆን ከዚህ ውስጥ 262 የሚሆኑት በፖሊስ በኤግዚቢትነት ተይዘው እንደሚገኙ ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል። በአፋር ክልል አዋሽ ፈንታሌ ወረዳ ዱብዱብ በሚባል ቀበሌ በፕሮጀክቱ ላይ የተፈፀመው ስርቆት የግንባታ ሥራውን በተያዘለት ጊዜና በጀት ለማጠናቀቅ እንቅፋት እንደሚሆንም አመልክተዋል። አቶ ተክለወይኒ እንዳሉት ስርቆቱ ከተፈፀመ ጀምሮ ችግሩ በስፋት በሚስተዋልበት አካባቢ ከፀጥታ አካላት ጋር በመሆን የቁጥጥርና የጥበቃ ሥራ በመጀመሩ የስርቆት ወንጀሉ የመቀነስ አዝማሚያ አሳይቷል፡፡ ስርቆቱን በተቋሙ፣ በሥራ ተቋራጩ እና በፀጥታ አካላት ብቻ ማስቆም ስለማይቻል ህዝቡ በአካባቢው የተተከሉ የመስመር ተሸካሚ ምሶሶዎችን በእኔነትና በኃላፊነት ስሜት እንዲጠብቅ ለማድረግ የተለያዩ ሥራዎች እየተከናወኑ እንደሆነም አስረድተዋል። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ፕሮግራም-2 የፕሮጀክት አስተዳደር-1 ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ዮናስ አባዲ በበኩላቸው በፕሮጀክቱ ላይ እየተፈፀመ ያለውን የስርቆት ወንጀል ለመከላከል ከፀጥታ አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡ በስርቆቱ የተሳተፉ አካላትን በቁጥጥር ስር ለማዋል እና ህዝቡ ንብረቱን በሚጠብቅበት መንገድ ላይ ግንዛቤ ለመፍጠር፤ በየደረጃው ካሉ የዞን፣ የወረዳና የከተማ የፀጥታ አካላት የተውጣጣ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ መገባቱን ተናግረዋል። የኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ የግንባታ ሥራ ተቋራጭ ፒንጋኦ ግሩፕ የሳይት ሥራ አስኪያጅ ሚስተር ዣይ በበኩላቸው በፕሮጀክቱ ላይ በተፈፀመው ስርቆት ምክንያት በአሁኑ ሰዓት የግንባታ ሥራውን በአግባቡ ማከናወን አልተቻለም ብለዋል። ከአንድ ምሶሶ ከ150 እስከ 200 የሚጠጉ ብረቶች ተፈተው እንደተወሰዱ የጠቆሙት ሥራ አስኪያጁ ተሰርቀው የተወሰዱትን ብረቶች ለመተካት 12 ነጥብ 5 ማሊዮን ብር እንደሚጠይቅ ተናግረዋል። በፕሮጀክቱ ላይ እየተፈፀመ ያለው ስርቆት በወቅቱ መፍትሄ ካልተሰጠው ግንባታውን በተያዘለት በጀት እና ጊዜ አጠናቆ ለማስረከብ ፈታኝ እንደሚያደርገው እና የግንባታ እንቅስቃሴውን አደጋ ላይ እንደሚጥለውም የሥራ ኃላፊዎች አስገንዝበዋል። እስከ አሁን ከስርቆት ወንጀሉ ጋር በተገናኘ ሰባት ሰዎች በቁጥጥር ስር እንደዋሉ እና ከዚህ ውስጥ አራቱ ከንብረቱ ጋር እጅ ከፈንጅ የተያዙ መሆናቸውን ከአዋሽ ፈንታሌ ወረዳ ፖሊስ ኮሚሽን የተገኘው መረጃ ያመለክታል። የአዋሽ - ወልዲያ - ሀራ ገበያ የባቡር መስመር የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ፕሮጀክት በመቶ ደርሷል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 06 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+4

የህፃናት ማቆያ ማዕከሉ 34 ህፃናትን ተቀብሎ እስተናገደ ነው ……..///……. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የህፃናት ማቆያ ማዕከል 34 የሰራተኞች ህፃናትን ተቀብሎ በማዋል ሴት ሰራተኞች በተረጋጋ ስሜት ሥራቸውን እንዲያከናዉኑ እያገዘ መሆኑን የሴቶች ህጻናትና ወጣቶች መምሪያ አስታወቀ፡፡ የመምሪያው ዳይሬክተር ወ/ሮ ሌንሲ ኢደኤ እንደተናገሩት ማዕከሉ የተቋሙን ሴት ሰራተኞች ህፃናት ልጆች ተቀብሎ ከሰኞ እስከ አርብ ከጠዋቱ 2፡00 ስዓት እስከ ቀኑ 11፡00 ስዓት ድረስ በመንከባከብ ላይ ይገኛል፡፡ ማዕከሉ በመቋቋሙ ሠራተኞቹ የስራ ጊዜያቸውን ሳያባክኑ እና ለልጆቻቸው ደህንነት ስጋት ሳይሰማቸው ስራቸውን በአግባቡ እንዲያከናውኑ እያገዘ ነው ብለዋል፡፡ የህፃናት ማቆያ ማዕከሉ ከ6 ወር እስከ 4 ኣመት ድረስ ላሉ የተቋሙ ሴት ሰራተኞች ልጆች የመኝታ፣ የመጫወቻ፣ የምግብና ሌሎች ተጨማሪ አገልግሎቶችን የሚሰጥ መሆኑ ደረጃውን የጠበቀ ማቆያ እንደሚያደርገው ወ/ሮ ሌንሴ ተናግረዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የህፃናት ማቆያ ማዕከል 1 ነርስ እና ስድስት ልዩ ልዩ አገልግሎት የሚሰጡ ሠራተኞችን አሉት፡፡ ኮተቤ በሚገኘው አዲሱ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና መስሪያ ቤት ቅጥር ግቢ ውስጥ የተገነባው የህፃናት ማቆያ ማዕከል ሜክሲኮ ከነበረው የማቆያ ማዕከል ጋር ሲነፃፀር በዘመናዊ መልክ ከመገንባቱ ባሻገር ተቋሙ ለሰራተኖቹ የሰጠውን ትኩረት ያሳያል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ ህይወታቸውን በኤች አይ ቪ/ኤድስ ላጡ የተቋሙ ሠራተኞች ልጆች የገንዘብ እገዛ እየተደረገ መሆኑን በመምሪያው የስርዓተ ፆታ ባለሙያ አቶ ተስፋዬ ዮሐንስ ገልፀዋል፡፡ እንደ ባለሙያው ገለፃ ከ 18 ዓመት በታች ለሆኑ የተቋሙ ሰራተኞች ልጆች በየወሩ 500 ብር ገንዘብ ድጋፍ እየተደረገ ነው፡፡ በዋናው መ/ቤትና በተለያዩ የተቋሙ የስራ አካባቢዎች የውይይት መድረኮችን በመፍጠር ሠራተኞች ስለ ቫይረሱ የተሻለ ግንዛቤ እያገኙ መሆናቸውን እና እያንዳንዱ የተቋሙ ሠራተኞች ከደመወዙ ላይ ተቆራጭ በማድረግ ኤች አይ ቪ በደማቸው የሚገኝ ሠራተኞችና ቤተሰቦታቸውን እንደሚደጉም ባለሙያው አስታውቀዋል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 06 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content