Murad Tadesse (Official Channel)☪️🇪🇹
ትክክለኛው ኢስላማዊ አስተምህሮ፦ 1) ከቁርኣን፣ 2) ከሐዲሥ፣ [በሰለፎች አረዳድ] 3) ከታማኝ ዑለማዎችና 4) ከትክክለኛ ቂያስ ተጠናቅሮ ይቀርብበታል። √ አዳዲስና ወቅታዊ ኢስላማዊ የሆኑ ጉዳዮችም ይዳሰሳሉ። √ አላማዬ በቻልኩት አቅም ያለውን የመረጃ ክፍተት መሙላት ነው። ማንኛውም አስተያዬት ሲኖራችሁ @MuradTadesseBot ላይ አስፍሩት። ስህተትም ባያችሁ ጊዜ አርሙኝ። ጀዛኩሙል`ሏህ ኸይራ!
نمایش بیشتر📈 تحلیل کانال تلگرام Murad Tadesse (Official Channel)☪️🇪🇹
کانال Murad Tadesse (Official Channel)☪️🇪🇹 (@muradtadesse) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 117 686 مشترک است و جایگاه 278 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 239 را در منطقه أثيوبيا دارد.
📊 شاخصهای مخاطب و پویایی
از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 117 686 مشترک جذب کرده است.
بر اساس آخرین دادهها در تاریخ 24 ژوئیه, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 311 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 33 بوده و همچنان دسترسی گستردهای حفظ شده است.
- وضعیت تأیید: تأیید نشده
- نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 23.60% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 16.83% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب میکند.
- دسترسی پستها: هر پست به طور میانگین 27 770 بازدید دریافت میکند. در اولین روز معمولاً 19 800 بازدید جمعآوری میشود.
- واکنشها و تعامل: مخاطبان بهطور فعال حمایت میکنند؛ میانگین واکنش به هر پست 320 است.
📝 توضیح و سیاست محتوایی
نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاههای شخصی توصیف میکند:
“ትክክለኛው ኢስላማዊ አስተምህሮ፦
1) ከቁርኣን፣
2) ከሐዲሥ፣ [በሰለፎች አረዳድ]
3) ከታማኝ ዑለማዎችና
4) ከትክክለኛ ቂያስ ተጠናቅሮ ይቀርብበታል።
√ አዳዲስና ወቅታዊ ኢስላማዊ የሆኑ ጉዳዮችም ይዳሰሳሉ።
√ አላማዬ በቻልኩት አቅም ያለውን የመረጃ ክፍተት መሙላት ነው።
ማንኛውም አስተያዬት ሲኖራችሁ @MuradTadesseBot ላይ አስፍሩት።
ስህተትም ባያችሁ ጊዜ አርሙኝ።
ጀዛኩሙል`ሏህ...”
به لطف بهروزرسانیهای پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 25 ژوئیه, 2026)، کانال همواره بهروز و دارای دسترسی بالاست. تحلیلها نشان میدهد مخاطبان بهطور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کردهاند.
در حال بارگیری داده...
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 25 ژوئیه | +21 | |||
| 24 ژوئیه | +33 | |||
| 23 ژوئیه | +22 | |||
| 22 ژوئیه | +26 | |||
| 21 ژوئیه | +19 | |||
| 20 ژوئیه | +13 | |||
| 19 ژوئیه | +11 | |||
| 18 ژوئیه | +13 | |||
| 17 ژوئیه | +32 | |||
| 16 ژوئیه | +35 | |||
| 15 ژوئیه | +12 | |||
| 14 ژوئیه | +7 | |||
| 13 ژوئیه | +29 | |||
| 12 ژوئیه | +11 | |||
| 11 ژوئیه | +32 | |||
| 10 ژوئیه | +51 | |||
| 09 ژوئیه | +25 | |||
| 08 ژوئیه | +21 | |||
| 07 ژوئیه | +30 | |||
| 06 ژوئیه | +14 | |||
| 05 ژوئیه | +22 | |||
| 04 ژوئیه | +28 | |||
| 03 ژوئیه | +29 | |||
| 02 ژوئیه | +26 | |||
| 01 ژوئیه | +39 |
| 2 | بدون متن... | 2 195 |
| 3 | በአንድ ወቅት አንዲት ድመት አይጦችን እያደነች ቁም ስቅላቸውን ስታሳያቸው፤ አይጦቹ ይህንን ከባድ መቅሰፍት ለማስወገድ አስቸኳይ ስብሰባ ጠሩ። ሁሉም መፍትሄ ፍለጋ የየራሳቸውን ሃሳብ ያዋጡ ጀመር።
በዚህ መሃል አንዲት ወጣት አይጥ ብቅ ብላ፦ "ድመቷ ወደ እኛ ስትጠጋ አስቀድመን ሰምተን እንድንሸሽ፤ አንገቷ ላይ ቃጭል (ደወል) እንሰርላት!" የሚል ድንቅ ሃሳብ አቀረበች። ሁሉም አይጦች በደስታ እየዘለሉ ሃሳቡን ደገፉት፤ በአዳራሹም ውስጥ የደስታ ጩኸት አስተጋባ።
ነገር ግን... በደስታው ጩኸት መሃል አንዲት በዕድሜ ጠገብ አሮጊት አይጥ ካለችበት ጥግ ረግታ ተነሳችና፦ «ሃሳቡማ የማይጣልና እጅግ ግሩም ነው። ሆኖም ለመሆኑ ሄዶ ቃጭሉን በድመቷ አንገት ላይ የሚያስረው ማን ነው?» ስትል ጠየቀች። በዚያው ቅጽበት መላው ስብሰባ በድንገተኛ ፀጥታ ተዋጠ፤ የደስታው ጩኸትም በአንዴ ጸጥ ረጭ አለ።
ይህ ቀላል ምሳሌያዊ ታሪክ ዛሬም ድረስ በህይወታችን ውስጥ የሚደገም ትልቅ መርህን ያስተምረናል፦ ትልቁ ፈተና የሚያምርና ድንቅ እቅድ ማውጣት ሳይሆን፤ ያንን እቅድ ወደ ተግባር መለወጥ መቻል ነው።
🔗 ብዙ ጊዜ ትርጉም ያለው ለውጥ የሚመጣው በውይይት ብዛት ወይም በምኞት ወረቀት ላይ በሚጻፉ ቃላት ሳይሆን፤ አስፈሪውንና ከባዱን የመጀመሪያ እርምጃ ደፍሮ የሚወስድ 'ባለ ተግባር' ሰው ሲገኝ ብቻ ነው።
ዛሬ በየማህበራችን፣ በየሥራ ቦታችን፣ አልፎ ተርፎም በሀገራችን ደረጃ... የሚያምር ሃሳብና እቅድ የሚያቀርበው ሰው ሞልቷል።
ነገር ግን ዛሬም ድረስ ትልቁ ጥያቄ፦ «ለመሆኑ ቃጭሉን በድመቷ አንገት ላይ የሚያስረው ማን ነው?» የሚለው ነው።
መንቁል
https://t.me/STEMwithMurad | 2 855 |
| 4 | ድመቷ አይጦች እያደነች ቁም ስቅላቸውን ስታሳይ አንጦች ተሰብስበው ይኸንን ችግር ለመቅረፍ መከሩ። ሁሉም ሀሳብ አዋጡ። አንዷ አይጥም መጥታ "ድመቷ ስትመጣ እንድንሰማ አንገቷ ላይ ቃጭል (ደወል) እናስርላት!" የሚል ምርጥ ሃሳብ አቀረበች። ሁሉም አይጦች በደስታ ጨፈሩ፣ ሃሳቡን ደገፉት።
...
ነገር ግን... በመጨረሻ አንዲት አሮጊት አይጥ ተነስታ "ሀሳብ የማይጣል እና ግሩም ነው። ሆኖም ለመሆኑ ቃጭሉን ሄዶ ድመቷ አንገት ላይ ማን ያስራል?" ስትል ስብሰባው በዝምታ ተዋጠ።
...
ትልቅና የሚያምር እቅድ ማውጣት ሳይሆን፤ ዋናው ቁምነገር እቅዱን ወደ ተግባር መለወጥ ነው። ብዙ ጊዜ ለውጥ የሚመጣው ዝም ብሎ በማውራት ሳይሆን፣ አስፈሪውንና ከባዱን የመጀመሪያ እርምጃ ደፍሮ የሚጀምር ሰው ማግኘት ነው።
....
በየማህበራችን፣ በየስራ ቦታችን አልፎ ተርፎም በሃገራችን... ሃሳብ የሚያቀርበው ሞልቷል። ግን ቃጭሉን የሚያስረው ማን ነው?
መንቁል | 3 |
| 5 | ዓለም በአሰቃቂ ትዕይንቶች፣ በአጸያፊ ምግባሮች ስትሞላ ወደአላህ መጠጋትን የመጨረሻ አማራጫችን እናድርግ።
منقول | 12 062 |
| 6 | بدون متن... | 12 193 |
| 7 | በሐራም ግንኙነት ውስጥ ብዙ ነገሮችን ታጣለህ። ገንዘብህን፣ ግዜህን ከዛም ወንጀል ላይ ትወድቃለህ።
አላህ ይጠብቀን🤲 | 18 907 |
| 8 | ዛሬ ይህን ፕሮግራም ታድሜ ነበር፣ ባለፈ ጥሪ ተደርጎልኝ።
ጥሩ ነው፤ በተለይ እንደ ጅማሮ ጥሩ መነቃቃት ነው ከነበርንበት አንፃር። የተሠሩ ሥራዎችንም ዙሬ ጎብኝቻለሁ።
ነገር ግን ያው የሚያወቅን ወይም የተሠራን ነገር ከስተማይዝ ማድረግ ወይም ዳታ ሴት ብቻ ቀይሮ ባሉ ሞደሎችና አልጎሪዝሞች ላይ መሥራት ብቻውን ለኔ የምወደው አይነት ኤአይ አይደለም። አዲስ ማትስ፣ አዲስ አርኪቴክቼር፣ የተሻለ ኦፒቲማይዝድና ኢፊሼንት ነገር ማምጣት፣ ፓራዲግም ሺፍት… ይፈልጋል።
በተረፈ በርቱ። | 18 892 |
| 9 | ቴሌግራም በራሱ ጊዜ የሚጨምረው Ad ነው።
ልክ የዩ ቲዩብ ወይም ፌስቡክ ቪድዮ እያያችሁ ሳለ፤ በመሃል ጣልቃ እንደሚገቡት ማስታወቂያዎች።
ለኔ አይታየኝም፣ የሚታየው ለናንተ ነው፤ ከየመጨረሻው ፖስቴ ቀጥሎ።
የኔ ሪኮመንዴሽን መስሏችሁ፣ ጆይን እንዳትሉ።
ባይሆን ይሄ እንዲጠፋ ከፈለጋችሁ፤ ፕሪሜም አካውንት ያላችሁ ቻነሉን ቡስት አድርጉትና Level 50 ብታደርሱት መልካም ነው።
https://t.me/boost/MuradTadesse | 18 733 |
| 10 | የ'ነባርና መጤ' የታሪክ ስህተት‼
===================
«እምነቶቹ እንግዶች ናቸው፤ እኛ ግን የአገሩ ባለቤቶች ነን!» → አሕመዲን ጀበል
||
✍️ በኢትዮጵያ የፖለቲካና የማህበራዊ መስተጋብር መድረክ ላይ አልፎ አልፎ የሚስተጋባ፣ የሀገሪቱን ታሪክ ካለማወቅ ወይም እውነታውን ሆን ብሎ ከመካድ የሚመነጭ አንድ በጣም አስገራሚ ትረካ አለ። እርሱም፦ "ክርስቲያኑ ነባርና የአገሪቱ ብቸኛ ባለቤት፣ ሙስሊሙ ደግሞ በጊዜ ሂደት የገባ መጤ ነው" የሚለው አደገኛና የተሳሳተ ድምዳሜ ነው።
🔗 ይህንን የታሪክ መዛባት፣ ኡስታዝ አሕመዲን ጀበል ካስቀመጣቸው እውነታዎች እና ከሎጂካዊ የታሪክ ትንተና አንፃር እንደ አንድ ሙስሊም በሚከተለው ሚዛናዊና ጠንካራ መረጃ መሞገት እንችላለን።
1⃣ መሠረታዊው እውነት፦ ሀገር ከእምነቶች በፊት ነበረች!
🎀 ማንኛውም የታሪክ ተማሪ ሊገነዘበው የሚገባው ቀዳሚ እውነት ቢኖር፦ እምነቶች ከመምጣታቸው በፊት በዚች ምድር ላይ ሀገርና ህዝብ ነበሩ።
ኢትዮጵያዊያን ከጥንት ጀምሮ የተለያዩ እምነቶችን በእንግድነት ተቀብለዋል። የአይሁድ እምነት፣ ክርስትና፣ እስልምና፣ ካቶሊክ፣ እንዲሁም ፕሮቴስታንት ሁሉም ከመካከለኛው ምስራቅና ከአውሮፓ የመጡ "እንግዶች" ናቸው። እምነቶቹን ያመጡት መምህራን መጤዎች
ነበሩ፤ እምነቶቹን ተቀብለው የኖሩት ግን እዚሁ ምድር ላይ የነበሩ ነባር ኢትዮጵያውያን ናቸው።
2⃣ የክርስትና "መጤ" ሰባኪያን ታሪክ:
🎀 ክርስትና ወደ አገራችን የገባው በነባር ኢትዮጵያውያን ጥረት ሳይሆን ከመካከለኛው ምስራቅ በመጡ ስደተኞችና መምህራን አማካኝነት
ነው፦
☑ ፍሪምናጦስ (አባ ሰላማ/ከሳቴ ብርሃን)፦
እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር በ330 E.C. በስደት ወደ አክሱም የመጣ የሶሪያ ተወላጅ ወጣት ነበር። እምነቱን የሰበከውና የአክሱሙን ንጉሥ ኢዛናን ያጠመቀው እርሱ ነው።
☑ ዘጠኙ ቅዱሳን፦
በአምስተኛው ክፍለ ዘመን (በ451 E.C. ከተደረገው የቻልኬዶን ጉባዔ በኋላ) ከሮማ ግዛትና ከመካከለኛው ምስራቅ በሃይማኖታዊ ስደት ተሰደው ወደ አክሱም የመጡ የውጭ አገር ዜጎች ነበሩ። እነ አባ አፍጼ፣ አባ ገሪማ፣ አባ ሊቃኖስና አባ ዘሚካኤል አረጋዊ ለአጠቃላዩ የሰሜን ህዝብ ክርስትናን የሰበኩ "መጤ" ስደተኞች ነበሩ [6]. (ምንጭ፦
AAU, Institute of Ethiopian Studies, Dictionary of Ethiopian Biography, 1975, Pp. 209-210) [6].
⬇️እነዚህ ታላላቅ የክርስትና መምህራን ወደ አገራቸው ስለመመለሳቸው ምንም ዓይነት የታሪክ መረጃ የለም። እዚሁ ምድር ላይ ቀርተው ከህዝቡ ጋር ተዋህደዋል።
3⃣ የእስልምና "እንግዶች" እና የታሪክ ምጸት (The Paradox):
🎀 እስልምና ወደ ኢትዮጵያ የገባው ክርስትና ወደ አክሱም በገባ በ285 ዓመታት ልዩነት ውስጥ (በ615 E.C.) በነቢያዊው ሂጅራ አማካኝነት ነው። ከመካ የመጡት የነቢያችን ﷺ ሶሐቦች በሰሜን ኢትዮጵያ በስደት እንዲቀመጡ ተፈቀደላቸው።
እዚህ ላይ ነው ትልቁና ወሳኙ የታሪክ እውነት የሚመጣው፦
☑ ወደ አክሱም የመጡት እነዚያ የነቢያችን ሰሐቦች በሀገሪቱ የኖሩት ለ15 ዓመታት ብቻ ነው። ረሱል ﷺ በመዲና የእስልምናን መንግስት ሲመሰርቱ፣ ሁሉም ሰሐቦች ሙሉ በሙሉ ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል። በዚሁ በሞት ተለይተው በትግራይ (ነጃሺ) ከተቀበሩት ጥቂት ሰሐቦች ውጪ፣ አንዱም የውጭ አገር ስደተኛ እዚህ ሀገር ውስጥ አልቀረም [1, 2]。
✒️ ይህ ምን ማለት ነው? ሰሐቦቹ ሄደዋል፤ እስልምናን ተቀብለው ያስቀጠሉት ግን 100% ነባር የነበሩ፣ ከዚያ በፊት ክርስትናን ወይም የአይሁድ እምነትን ይከተሉ የነበሩ ነባር ኢትዮጵያውያን ናቸው።
ታላቁ የታሪክ ምጸት (Paradox) እዚህ ላይ ነው፦ የእስልምናን እምነት ያመጡት መምህራን (ሰሐቦች) ሙሉ በሙሉ ወደ አገራቸው ተመልሰው፣ እምነቱ የቀጠለው በነባር ኢትዮጵያውያን ደም ሆኖ ሳለ [1, 2]፤ በሌላ በኩል ግን እምነቱን ያመጡት የውጭ አገር መምህራን (ዘጠኙ ቅዱሳንና ፍሪምናጦስ) ሳይመለሱ እዚሁ ምድር ላይ ቀርተው እያለ [6]፣ ዛሬ ላይ ቆሞ ሙስሊሙን "መጤ" ክርስቲያኑን "ነባር" አድርጎ ለመሳል መሞከር ፍፁም የታሪክ ድንቁርና ነው።
4⃣ የጋራ አገራችንን በጋራ እኩልነት እንገንባ!
🎀 እኛ ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች፣ አባቶቻችን በ615 G.C. የመካ ስደተኞችን (ሶሐቦችን) በነፃነት ተቀብለው ጥገኝነት በመስጠታቸው
እንደምንኮራው ሁሉ፤ የአይሁድ እምነት ተከታዮችንና የክርስቲያን ስደተኞችን (ነገስታቱና ህዝቡ) በእንግድነት ተቀብለው እምነታቸውን እንዲሰብኩ በመፍቀዳቸውም እንኮራለን። ይህ የጋራ አገራዊ ክብራችንና እንግዳ ተቀባይነታችን ማሳያ እሴታችን ነው።
ስለዚህ፦
☑ ማንም በዚህ ምድር ላይ "የበለጠ ነባር" ወይም "ባለቤት" የለም።
☑ማንም በዚህ ምድር ላይ "የበታች መጤ" ወይም "እንግዳ" የለም።
ሀገራችን የሁላችንም ናት! ዛሬም ይህችን ሀገር በጋራ መገንባት የምንችለው የጎንዮሽ ንትርክንና ኋላ ቀር የ"ነባርና መጤ" የድንቁርና ጨዋታዎችን ትተን፣ እኩልነት የሰፈነባት፣ ሁላችንንም በምትመስልና በእኩልነት በምትወክል መንገድ በጋራ መገንባት ስንችል ብቻ ነው።
ያሻቸውን የስም ማጥፋት ዘመቻ (አክራሪ፣ አይ ኤስ፣ ወሃቢያ) ቢለጥፉብን፣ እውነቱ ግን አይለወጥም፤ እኛ አገራችንን እኩል ለማድረግ ከመታገል ወደ ኋላ አንልም!
ቸር እንሰንብት!
||
t.me/MuradTadesse | 19 795 |
| 11 | የማለዳ ስንቅ ለቀልብዎ❤️
[Part: ③②②③]👌
#ቁርኣን | 18 477 |
| 12 | የምሽት ስንቅ ለቀልብዎ❤️
[Part: ③②②②]👌
#ቁርኣን | 18 414 |
| 13 | የጁሙዓህ ኹጥባህ ዛሬ ሰምታችሁ የለ‼
ሃዳከ-ል'ሏህ ያ ኢብኑ አሕመድ ዓሊ! | 20 656 |
| 14 | ቀልድ ቢመስልም… ግን ያለንበት የብዙዎች ተጨባጭ ነው‼ | 23 322 |
| 15 | ወንድማችን አንዋርን እናሳክመው‼
=====================
(«ምን አጥፍቼ ነው የጨከናችሁብኝ...» ያለን ንወንድም ዛሬ አብረን እንቁምለት!)
||
✍️ እውነቱን ልንገራችሁ... ይህ ወንድም ስለ ህመሙ በጣም ብዙ ጊዜ ነግሮኝ ነበር። የልጁ ፊት የታመመ ሰው ስለማይመስል እና ቪዲዮዎችን ደጋግሞ ስለሚለቅ፣ አጭበርባሪ ነው ብዬ ተጠራጥሬው፣ አልፎ ተርፎም አጭበርባሪ ነው ብለን ፖስተንበት ነበር።
🔗ነገር ግን ውስጤ አላረፈም፤ አዳማ ከተማ የሚገኝ አንድ የማምነውን ወንድም በአካል ሄዶ ሁኔታውን በዓይኑ አይቶ እንዲያጣራ ነገርኩት። ያ ወንድሜ በአካል አግኝቶት ነባራዊ ሁኔታውን ሲነግረኝ ግን... አንጀቴ ነው የቆሰለው! አዎ፣ ልጁ እውነተኛ ስቃይ ውስጥ ነው፤ እኛ ፊቱን አይተን ፈረድንበት፣ እሱ ግን ውስጥ ውስጡን እየነደደ ነው።
🔗ፎቶው ላይ "ምን አጥፍቼ ነው የጨከናችሁብኝ" ብሎ የጻፋት ጽሑፍ ወዶ አይደለም። የብቸኝነት፣ የህመም፣ እና "ለምን ሰው አላመነኝም?" የሚል መሪር የስብራት ድምፅ ነው!
የአንዋር ታሪክ...
ገና በለጋ ወጣትነቱ ሙሉ ቤተሰቦቹን በሞት አጣ። በዚህች ምድር ላይ ከአላህ ውጭ ምንም አይነት ረዳትና አይዞህ የሚለው አስታማሚ የሌለው ብቸኛ ሰው ሆነ። የቤተሰብ ማጣት ያመጣው ከባድ የሞራልና የስነ-ልቦና ስብራት ሳያንስ፣ በድንገት የጤናው ሁኔታ ከቀን ወደ ቀን መቃወስ ጀመረ።
በአሁኑ ወቅት የዚህ ወጣት ተስፈኛ የጤና ሁኔታ እጅግ አሳሳቢ ደረጃ ላይ የደረሰ ሲሆን፣ በሰውነቱ ላይ በደረሰው አስከፊ የጤና እክል ምክንያት ሁለቱንም እግሮቹን ሙሉ በሙሉ ለማጣት ጫፍ ላይ ይገኛል። የህክምና ባለሙያዎች በሰጡት አስቸኳይ ውሳኔ መሰረት፤
ወጣቱ በአስቸኳይ ወደ ውጭ ሀገር ሄዶ ከፍተኛ ህክምና ካላገኘ በስተቀር፣ የእግሮቹ የመዳን ተስፋ እጅግ የመነመነ መሆኑ ተረጋግጧል።
.. ዛሬ የተከበረው የጁሙዓ ቀን ነው! ዱዓእ እና ሰደቃ አላህ ዘንድ እጅግ ተወዳጅ የሆኑበት፣ ምንዳቸውም በእጥፍ የሚመዘገብበት ቀን። አንዋር ዛሬ ከጎኑ የሚቆም ወላጅ ወይም ዘመድ የለውም፤ አሁን ያለው ብቸኛ ተስፋ አላህ፣ ከዚያም ደግ የሆናችሁት እናንተ ወንድምና እህቶቹ ብቻ ናችሁ!
🖊 ትናንት ተጠራጥረነው ለፈጠርንበት የሞራል ስብራት፣ ዛሬ በሰደቃችን እና በዱዓችን «አላጠፋህም፣ እኛም አልጨከንብህም፣ ከአላህ በታች አለንልህ!» ልንለው ይገባል። የሁላችንም አቅም የፈቀደውን እገዛ እናድርግለት።
አንዋርን ለማሳከም ሰበብ እንሁን!
☑ የባንክ ሒሳብ ቁጥር (የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ)፦
1000 2763 3311 2
☑ ስም፡ Anwar Abdu Seid
📞 ስልክ ቁጥር፦ 0932686410
ገቢ ያደረጋችሁበትን ደረሰኝ በቴሌግራም t.me/MuradTadesseBot ላይ ወይም ኮመንት ላይ ወይም ኢንቦክስ ላኩልኝ። አላህ ከማንኛውም መጥፎ በሽታ ይጠብቃችሁ! ይህን ፖስት ሼር
በማድረግም የኸይር ስራው ተካፋይ እንሁን! 🤲 | 23 963 |
| 16 | ጁሙዓን የት ሃገር፣ የት መስጅድ ሰገዳችሁ? ኹጥባው ስለምን ነበር? ለሌሎችም እንዲጠቅም ከሰማችሁት ውስጥ የኹጥባውን ጭብጥ በአጭር አስፍሩት። | 20 923 |
| 17 | ሁሌም ቢሆን ሰለምቴዎችን ስታገኟቸው በቻላችሁት አቅም በመልካም ኒያ አግዟቸው።
ይህን ወንድም በሰዓቱ የተባበርከው ወንድማችን አላህ ይጨምርልህ፤ አላህ ስለወፈቀህ በሥራህ ልትደሰት ይገባል።
ለሰለምቴው ወንድማችንም አላህ ጽናቱን ይስጠው። | 21 631 |
| 18 | አብሮ መኖር ወይስ የዐቂዳ መደባለቅ⁉️
========================
(በ"ፍቅር" ስም የሚደረግ የእምነት መሸርሸር!)
||
✍️ ከሰሞኑ በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ በሚለቀቁ ፖድካስቶችና ቪዲዮዎች ውስጥ፣ "ሰላማዊ አብሮ መኖርንና ፍቅርን"
ለመስበክ በሚል ሰበብ፣ የእስልምናን መሰረታዊ የዐቂዳ ድንበሮች የሚያፈሱ እና ኃይማኖታዊ መርሆችን የሚያደበዝዙ ንግግሮች በስፋት ሲስተዋሉ ይደመጣል።
በተለይም በእስልምና ስም ሚዲያ ላይ ቀርበው «መዝሙር ለእኔ መደበኛ ዜማ ነው፣ የሰው ልጅ መዋደዱ ብቻ ፈጣሪን ያስደስተዋል፣ እምነት ያለ ሰብአዊ ፍቅር በዜሮ ማባዛት ነው...» እያሉ ኃይማኖታዊ አስተምህሮቶችን ዋጋ የሚያሳጡ ንግግሮች፣ ከእስልምና ይዘትና መርህ ጋር ፍጹም የሚጋጩ ናቸው።
🔗ይህንን የእምነት መሸርሸር አዝማሚያ፣ ከእውነተኛው እስላማዊ አስተምህሮትና ከዐቂዳ አንፃር ስናየው፦
1⃣ በአብሮ መኖር (Coexistence) እና በዐቂዳ መደባለቅ (Syncretism) መካከል ያለው ቀይ መስመር፦
🎀 እስልምና ከክርስቲያኖችም ሆነ ከሌሎች የእምነት ተከታዮች ጋር በፍትህ፣ በደግነት፣ በአክብሮትና በሰላም አብሮ መኖርን በጥብቅ
ያዛል። ጎረቤትን መርዳት፣ በችግር ጊዜ መድረስ እና ሰብአዊ መብትን ማክበር የእስልምና መገለጫዎች ናቸው።
ነገር ግን፣ ሰላማዊ አብሮ መኖር ማለት እምነትን ማደባለቅ ማለት አይደለም!
" መዝሙር ተራ የሙዚቃ ግጥም ሳይሆን፣ በክርስትና እምነት ውስጥ አምልኮት የሚፈጸምበት፣ በእስልምና አስተምህሮት
መሰረት ደግሞ ከተውሒድ ጋር በቀጥታ የሚጋጩ እንደ "ስላሴ፣ መለኮት ሰው መሆን፣ ወይም የቅዱሳን አማላጅነት" ያሉ ፅንሰ-ሃሳቦችን የያዘ መዝሙር ነው።
🔗ይህ ግለሰብ አንድ ሙስሊም «ግጥሙ ስለተመቸኝ መዝሙር እዘምራለሁ» ማለቱ፣ ስለ ዐቂዳው ያለውን ከባድ ድንቁርና የሚያሳይ ነው። እውነተኛ መቻቻል ማለት የሌላውን እምነትና የአምልኮ መብት ማክበር እንጂ፣ የራስን እምነት ጥሎ በሌላው አምልኮት ውስጥ መሳተፍ አይደለም።
2⃣ የልጁ «ትልቁ ታርጌታችን ፍቅር ነው... የሰውን ልጅ በሰውነቱ ብቻ መውደድ ፈጣሪን ፈገግ ያሰኛል» የሚለው ንግግር መሠረተ-ቢስ ስሜታዊነት ነው።
በእስልምና መሠረት፣ ፈጣሪ አላህን የሚያስደስተውና በመጀመሪያ ደረጃ የሚጠየቀው ታላቁ መብት ተውሒድ (አላህን ብቻ በብቸኝነት ማምለክ) ነው። ሰብአዊ ግንኙነቶችና መልካም ስነ-ምግባራት የሚገነቡት ከዚህ ታላቅ መሠረት ላይ ነው።
🖊 አላህን በብቸኝነት ሳያመልኩ፣ ለእርሱ መገዛትን ወደ ጎን ትቶ፣ ሰዎችን ለማስደሰትና የሰዋዊ ፍቅር ለመስበክ በሚል ሰበብ
የዐቂዳ ድንበርን መጣስ አላህን አያስደስትም። ይልቁኑ መለኮታዊውን ትእዛዝ ማቃለል ነው።
✅ ይህንን የመደባለቅ አዝማሚያ ቁርኣንና ታሪካዊው ነቢያዊ መመሪያ በግልጽ ውድቅ ያደርጉታል፦
✅ የዐቂዳ ድንበር አለመደባለቁን በሚመለከት፦
➡️ የቁረይሽ ከሃዲዎች ወደ ነቢያችን ﷺ በመምጣት፣ «እኛ ያንተን አምላክ አንድ ዓመት እናምልክ፣ አንተም የእኛን አማልክት አንድ ዓመት አምልክ፤ በዚህም ሰላማዊ አብሮ መኖርን እንፍጠር» የሚል የድርድር ሃሳብ አቀረቡ። ነቢያችን ﷺ ግን በ"ፍቅርና በአብሮነት" ስም ይህንን ድርድር አልተቀበሉትም። አላህም እንዲህ የሚል ጠንካራ ምላሽ አወረደ፦
{قُلْ يَا أَيُّهَا الْكَافِرُونَ * لَا أَعْبُدُ مَا تَعْبُدُونَ * وَلَا أَنتُمْ عَابِدُونَ مَا أَعْبُدُ ... لَكُمْ دِينُكُمْ وَلِيَ دِينِ}
«በላቸው፦ እናንተ ከሃዲዎች ሆይ!
የምታመልኩትን (አሁን) አላመልክም። የምታመልኩትንም (ለወደፊቱ) አላመልክም... ለእናንተ ኃይማኖታችሁ አላችሁ፤ ለእኔም
ኃይማኖቴ አለኝ።»
[አል-ካፊሩን: 1-6]
▫️ ይህ የዐቂዳ ልዩነትን ሳያደበዝዙ፣ እምነትን ሳይደረድሩ በሰላም አብሮ የመኖሪያ ታላቅ መለኮታዊ ቀመር ነው!
✅ አምልኮት ለአላህ ብቻ ስለመሆኑ፦
➡️ ማንኛውም ውዳሴ፣ ዱዓና አምልኮት ለአላህ ብቻ መሆን እንዳለበት ቁርኣን እንዲህ ያዛል፦
{قُلْ إِنَّ صَلَاتِي وَنُسُكِي وَمَحْيَايَ وَمَمَاتِي لِلَّهِ رَبِّ الْعَالَمِينَ * لَا شَرِيكَ لَهُ ۚ وَبِذَٰلِكَ أُمِرْتُ وَأَنَا أَوَّلُ الْمُسْلِمِينَ}
«በል፦ ስግደቴ፣ እርዴም፣ መኖሬም፣ መሞቴም ለአጽናፈ ዓለም ጌታ ለአላህ ነው፤ ለእርሱ ተጋሪ የለውም፤ በዚህም ታዝዣለሁ፤ እኔም የሙስሊሞች መጀመሪያ ነኝ።»
[አል-አንዓም: 162-163]
▫️ በሰዎች ዘንድ ተቀባይነትን ለማግኘት፣ ላይክና ቪው ለመሰብሰብ፣ ወይም ሰው ሰራሽ የሆነ ማህበራዊ ሰላምን ለመፍጠር ሲባል
ኃይማኖትን ማቅለል ከባድ ውድቀት ነው።
✒️ ኩሩ ሙስሊም ሁኑ፦
ለእምነታችሁ፣ ለተውሒዳችሁና ለዐቂዳችሁ ፍፁም የማይደራደር አቋም ይኑራችሁ።
✒️ ደግና ፍትሃዊ ሁኑ፦
ከሌላ እምነት ተከታዮች ጋር በንግድ፣ በጎረቤትነት፣ በትምህርት ቤትም ሆነ በሥራ ቦታ እጅግ ደግ፣ ታማኝ፣ ፍትሃዊና መልካም ስነ-ምግባር ያለው ሙስሊም ሆናችሁ ተገኙ።
🎁 እውነተኛ ኢስላማዊ መቻቻል ማለት ለሌላው የእምነት ተከታይ ሰብአዊ መብቱን ማክበር እንጂ፣ የራስን እምነት አቅልሎ በሌላው እምነት አምልኮት (መዝሙር) ውስጥ መሳተፍ አይደለም። ኃይማኖታችንን እናውቅ፣ የዐቂዳችንን ድንበር እንጠብቅ!
በዚሁ አጋጣሚ ሙስሊም ያልሆነችን የተገላለጠች አጅነቢ ሴት ዘይረዋታል የተባሉት ሙፍቲ፤ ልጁ ካልቀጠፈባቸው ብይኑ ምንድን ነው? አላህ ይጠብቀን።
||
t.me/MuradTadesse | 20 961 |
| 19 | የማለዳ ስንቅ ለቀልብዎ❤️
[Part: ③②②①]👌
#ቁርኣን | 18 918 |
| 20 | የምሽት ስንቅ ለቀልብዎ❤️
[Part: ③②②∅]👌
#ቁርኣን | 20 248 |
