Murad Tadesse (Official Channel)☪️🇪🇹
ትክክለኛው ኢስላማዊ አስተምህሮ፦ 1) ከቁርኣን፣ 2) ከሐዲሥ፣ [በሰለፎች አረዳድ] 3) ከታማኝ ዑለማዎችና 4) ከትክክለኛ ቂያስ ተጠናቅሮ ይቀርብበታል። √ አዳዲስና ወቅታዊ ኢስላማዊ የሆኑ ጉዳዮችም ይዳሰሳሉ። √ አላማዬ በቻልኩት አቅም ያለውን የመረጃ ክፍተት መሙላት ነው። ማንኛውም አስተያዬት ሲኖራችሁ @MuradTadesseBot ላይ አስፍሩት። ስህተትም ባያችሁ ጊዜ አርሙኝ። ጀዛኩሙል`ሏህ ኸይራ!
نمایش بیشتر📈 تحلیل کانال تلگرام Murad Tadesse (Official Channel)☪️🇪🇹
کانال Murad Tadesse (Official Channel)☪️🇪🇹 (@muradtadesse) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 117 635 مشترک است و جایگاه 274 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 237 را در منطقه أثيوبيا دارد.
📊 شاخصهای مخاطب و پویایی
از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 117 635 مشترک جذب کرده است.
بر اساس آخرین دادهها در تاریخ 20 ژوئیه, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 445 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -24 بوده و همچنان دسترسی گستردهای حفظ شده است.
- وضعیت تأیید: تأیید نشده
- نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 23.78% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 17.18% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب میکند.
- دسترسی پستها: هر پست به طور میانگین 27 969 بازدید دریافت میکند. در اولین روز معمولاً 20 208 بازدید جمعآوری میشود.
- واکنشها و تعامل: مخاطبان بهطور فعال حمایت میکنند؛ میانگین واکنش به هر پست 318 است.
📝 توضیح و سیاست محتوایی
نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاههای شخصی توصیف میکند:
“ትክክለኛው ኢስላማዊ አስተምህሮ፦
1) ከቁርኣን፣
2) ከሐዲሥ፣ [በሰለፎች አረዳድ]
3) ከታማኝ ዑለማዎችና
4) ከትክክለኛ ቂያስ ተጠናቅሮ ይቀርብበታል።
√ አዳዲስና ወቅታዊ ኢስላማዊ የሆኑ ጉዳዮችም ይዳሰሳሉ።
√ አላማዬ በቻልኩት አቅም ያለውን የመረጃ ክፍተት መሙላት ነው።
ማንኛውም አስተያዬት ሲኖራችሁ @MuradTadesseBot ላይ አስፍሩት።
ስህተትም ባያችሁ ጊዜ አርሙኝ።
ጀዛኩሙል`ሏህ...”
به لطف بهروزرسانیهای پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 21 ژوئیه, 2026)، کانال همواره بهروز و دارای دسترسی بالاست. تحلیلها نشان میدهد مخاطبان بهطور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کردهاند.
در حال بارگیری داده...
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 21 ژوئیه | +18 | |||
| 20 ژوئیه | +13 | |||
| 19 ژوئیه | +11 | |||
| 18 ژوئیه | +13 | |||
| 17 ژوئیه | +32 | |||
| 16 ژوئیه | +35 | |||
| 15 ژوئیه | +12 | |||
| 14 ژوئیه | +7 | |||
| 13 ژوئیه | +29 | |||
| 12 ژوئیه | +11 | |||
| 11 ژوئیه | +32 | |||
| 10 ژوئیه | +51 | |||
| 09 ژوئیه | +25 | |||
| 08 ژوئیه | +21 | |||
| 07 ژوئیه | +30 | |||
| 06 ژوئیه | +14 | |||
| 05 ژوئیه | +22 | |||
| 04 ژوئیه | +28 | |||
| 03 ژوئیه | +29 | |||
| 02 ژوئیه | +26 | |||
| 01 ژوئیه | +39 |
| 2 | አሕመዲን ጀበል ከሃገራዊ የምክክር ኮሚሽን መድረክ ለኢቢሲ የሰጠው ቃለ መጠይቅ‼ | 10 761 |
| 3 | ማዳመጫ ጆሮና አስተዋይ ልብ ያላችሁ ብቻ፤ ይህቺን አዳምጧት!
ባንክ ይቆጥቡ¡
ጭራሽ 7–8% ወለድ የሌለበት ከወለድ ነፃ ያስቀመጠው ሙስሊም ግን፤ ሌላውን እየጠቀመ ነው። | 15 424 |
| 4 | አሕመዲን ጀበል… እንዳውም ገና በደንብ አልጠየቀም!
ገና ምን ተጠየቀና⁉️
መጨፍለቅና መርገጥ ለምደህ ስለኖርክ፤ እኩል ሁን ስትባል ሊያጠፉኝ ነው የሚል ስሜት ከተሰማህ፣ ችግሩ ያንተ ነው።
አይ ካልክ ደግሞ… በኃይማኖታዊ መንግስትህ በኩል ላሳለፍከው እያንዳንዷ ወንጀል ካሳ ትከፍላለህ። | 16 147 |
| 5 | የጽንፈኞች ምናባዊ ሙግት‼
=================
(የታሪክ ሽብርተኝነት እና የፍርሃት ፖለቲካ)
||
✍️ ሰሞኑን ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽኑ ወደ ሥራ መግባቱን ተከትሎ፣ ለዘመናት በፈላጭ ቆራጭነት የገነቡት የአንድ ወገን የታሪክ ትርክትና የባለቤትነት ማረጋገጫ አደጋ ላይ ይወድቅብናል ብለው የሰጉ ጽንፈኛ ኃይሎች የጠዋት ማታ ቅዳሴያቸው አሕመዲን ጀበል ሆኗል። በዚህ አስመሳይ ጽንፈኛ ልጅ የተጻፈውና ሌሎች ተመሳሳይ ጽንፈኛ አመለካከት ያላቸው ግለሰቦች የሚያራምዱት ትርክት፣ መሠረታዊ የታሪክ ዕውቀት የጎደለው፣ በምክንያት የከሰረ እና በወቅታዊ የፖለቲካ ፍርሃት (Paranoia) የተሞላ ነው። ለዚህም ነው አሕመዲን ጀበልን እንደ ማሳበቢያ
(Scapegoat) በመጠቀም፤ የሙስሊሙን እውነተኛ የማንነት፣ የታሪክና የእኩልነት ጥያቄ ለማጠልሸት የሚሞክሩት።
አሕመዲን ጀበል የኢትዮጵያ ሙስሊሞችን የታሪክ በደል በመረጃና በሰነድ ያቀረበ ግለሰብ እንጂ፣ ራሱን የቻለ አዲስ የውሃቢያ ወይም የአል-ባግዳዲ ቡድን አይደለም። ይህ ዓይነቱ የስም ማጥፋት ዘመቻ (Ad Hominem Attack) ሐሳብን በሐሳብ መሞገት ያቃተው የደካሞች ስትራቴጂካዊ ኪሳራ ማሳያ ነው።
🔗አንዳንድ አስመሳይ ጽንፈኞች «ኢትዮጵያ ውስጥ የነበረው ኢስላማዊ መንግስት ቢሆን ዛሬ አንድ ክርስቲያን፣ አንድ ቤተክርስቲያን ይኖር ነበር?» ብለው መጠየቃቸው፣ የጽንፈኞቹን የታሪክ ድንቁርና እና የአመክንዮ ዝቅጠት ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ነው።
ይህን ባዶ ሙግት በሚከተሉት አራት ታሪካዊ መነጽሮች እንፈትሸዋለን፡-
1⃣) ምናባዊ ሙግታቸው (Hypothetical Fallacy):
🎀 ይህን የጻፈው ጽንፈኛ "ክሱን (የሙስሊሙን መበደል) እንዳለ ተቀብለን..." በማለት በኢትዮጵያ ሙስሊሞች ላይ የደረሰውን ታሪካዊ፣ መዋቅራዊና ስነ-ልቦናዊ ጭቆና እንደ ቀላል ነገር ካለፈ በኋላ፤ በምትኩ "ኢስላማዊ መንግስት ቢሆን ኖሮ..." ወደሚል ምናባዊ (Hypothetical) ማምለጫ ውስጥ ገብቷል።
✒️ በሕግም፣ በታሪክም፣ በፖለቲካ ሳይንስም አኳያ አንድን ተጨባጭ የሆነ ታሪካዊ ወንጀል (ጭቆናን) "እናንተ ብትሆኑ ኖሮ የባሰ ታደርጉ ነበር" በሚል ምናባዊ ትንበያ ማስተባበል (Whataboutism) አይቻልም። ጥያቄው "ምን ሊፈጠር ይችል ነበር?"
ሳይሆን "በገሃድ ምን ተፈጠረ?" የሚለው ነው። የኢትዮጵያ ሙስሊም ዛሬ እየጠየቀ ያለው በገሃድ ስለተፈጸመበት ማግለል፣ የታሪክ ስረዛ እና የመብት ጥሰት እንጂ ስለ ምናባዊ ዓለም አይደለም። ጭቆናን በምናብ ለማጽደቅ መሞከር የሞራል ዝቅጠት ነው።
2⃣ የታሪክ ተጨባጭ፡- ክርስትና በእስልምና ጥላ ስር እንዴት ኖረ?
🎀 ጸሐፊው "በእስልምና ውስጥ የኃይማኖት እኩልነት የለም፤ ክርስቲያን በኢስላም መንግስት ውስጥ መኖር አይችልም" የሚል እጅግ አሳፋሪ የታሪክ ድንቁርናን አንጸባርቋል። ታሪክን ለሚመረምር ሰው ግን እውነታው ተቃራኒው ነው፡-
☑ የግብፅ ኮፕቲክ ክርስቲያኖች፡-
➡️ ግብፅ ከ1,400 ዓመታት በላይ በኢስላማዊ መንግስታት (ከዑመር ኢብኑል ኸጧብ እስከ ኡመያ፣ አባሲያ፣ ፋጢሚያ፣ መማሊክ እና ዑሥማኒያ (ኦቶማን) ኸሊፋዎች) ስር ኖራለች። እስልምና ክርስቲያኖችን የሚያጠፋ ቢሆን ኖሮ፣ ዛሬ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ የኮፕቲክ ኦርቶዶክስ ክርስቲያኖች፣ ጥንታውያን ገዳማት እና አብያተ ክርስቲያናት በግብፅ በኖሩ ነበርን?
☑ የመካከለኛው ምስራቅ ክርስቲያኖች፡-
➡️ በሶሪያ፣ በሊባኖስ፣ በፍልስጤም እና በኢራቅ ዛሬም ድረስ ጥንታዊያን ክርስቲያኖች አሉ። እነዚህ ክርስቲያኖች ለ14 ክፍለ ዘመናት ሙሉ የተረፉት "ክርስቲያናዊ መንግስት" ስለነበራቸው ሳይሆን፣ ኢስላማዊው ሸሪዓህ የሰጣቸው "የአህሉል ዚማ" (የመብት ጥበቃ ቃል ኪዳን) ስላስጠበቃቸው ነው። የዑመር ኢብኑል ኸጧብ የኢየሩሳሌም ቃል ኪዳን (Pact of Umar) አብያተ ክርስቲያናት እንዳይፈርሱ፣ መስቀላቸው እንዳይሰበር ዋስትና የሰጠ ታላቅ ታሪካዊ ሰነድ ነው።
☑ የኦቶማን ኢምፓየር (ዑስማኒያ)፡-
➡️ለ600 ዓመታት ዓለምን የገዛው የኦቶማን ኢምፓየር ስር በነበሩት እንደ ግሪክ፣ ቡልጋሪያ፣ ሰርቢያ እና ሮማንያ ባሉ ሀገራት ኦርቶዶክስ ክርስትና ዛሬም የዋናው ሕዝብ እምነት ነው። ኦቶማኖች ክርስትናን አጥፍተው ቢሆን ኖሮ ዛሬ ምስራቅ አውሮፓ የኦርቶዶክስ ማዕከል መሆን አትችልም ነበር።
3⃣ Psychological Projection:
🎀 ይህ ተራ ጽንፈኛ ልጅ በእስልምና ላይ የለጠፈው "ሌላውን የማጥፋት" ባህሪ፣ የጥንታዊው ክርስቲያናዊ መንግስታት ታሪክ መገለጫ ነው። በስነ-ልቦና ሳይንስ ይህ የራሳቸውን ታሪካዊ ጉድፍ በሌላው ላይ የመለጠፍ (Psychological Projection) አባዜ ይባላል።
☑ የስፔን ኢንክዊዚሽን (Spanish Inquisition)፡-
➡️ ኢስላማዊቷ አንዳሉስያ (ስፔን) በክርስቲያን ነገስታት እጅ ስትወድቅ (በ1492)፣ አንድም ሙስሊም ወይም አይሁድ በስፔን ምድር በሕይወት መኖር አልቻለም። ወይ በግዴታ ክርስትናን መቀበል፣ ወይ መሰደድ፣ አለበለዚያም በእሳት መቃጠል ነበር እጣ ፈንታቸው። ሙስሊሞች አይሁዶችን አቅፈው 800 ዓመት የኖሩባትን አንዳሉስያን፣ የክርስቲያን ነገስታት በአንድ ጀንበር አጸዷት።
☑ የቦሩ ሜዳው አዋጅ፡-
➡️ ወደ ኢትዮጵያ ስንመጣ በ1870ዎቹ አፄ ዮሐንስ አራተኛ በቦሩ ሜዳ ያወጁት አዋጅ ታሪክ አይረሳውም። "ወይ ክርስትናን ተቀበሉ፣ ወይ ሀገሪቱን ልቀቁ" ተብሎ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ የኢትዮጵያ ሙስሊሞች (በተለይም በወሎ) ተፈጅተዋል፣ ምላሳቸው ተቆርጧል፣ ሀብት ንብረታቸው ተዘርፏል።
🌍 ታዲያ ታሪክ እውነታው ይህ ሆኖ ሳለ፣ ይህ ተራ ግለሰብ በምን የሞራል ልዕልና ነው "እስላማዊ መንግስት ቢሆን ክርስቲያን አይኖርም ነበር" ብሎ የሚሟገተው?
4⃣ የኢትዮጵያ ሙስሊም የአሕመዲን ጀበልን መጽሐፍት የሚያነበውና ታሪኩን የሚመረምረው፣ በዘመነ-መሣፍንት ወይም በአፄዎች ዘመን የነበረውን የታሪክ ሒሳብ ዛሬ በበቀል ለማወራረድ አይደለም። ታሪክን ማወቅ ለዛሬው ማንነት፣ ለእኩልነት እና ለነገው
የሀገር ግንባታ መሰረት ስለሆነ ብቻ ነው።
🖊️ የምክክር ኮሚሽኑ አጀንዳ የኢትዮጵያን ታሪክ በሚዛናዊነት ማየት ነው። ጽንፈኛው ኃይል የተደናገጠው፣ "የኔ ብቻ ነው" ይለው የነበረው የሀገር ባለቤትነት፣ ጀግንነት፣ ባንዲራ እና አርማ፤ አሁን ላይ በሙስሊሙም ሆነ በሌሎች የተገለሉ ማህበረሰቦች እኩልነት ሲመዘን ሐሰትነቱ ስለሚጋለጥ ነው።
🎁 የዘመናችንን መብት ጠያቂ ሙስሊም "አል-ባግዳዲ" ወይም "ዋሃቢያ" እያሉ መፈረጅ፣ ያረጀና ያፈጀ፣ ማንም የማይገዛው የፖለቲካ ቁማር ነው። የኢትዮጵያ ሙስሊም ዛሬ እየጠየቀ ያለው ፍጹም ሴኩላር የሆነ፣ ኃይማኖትና መንግስት በህግና በተግባር የተለዩበት፣
በመንግስት መዋቅር እና ታሪክ ላይ እኩል ውክልና ያለው ዘመናዊ ፍትሐዊ ስርዓት እንዲረጋገጥ ነው።
▶️ ያለፈውን ታሪካዊ በደል በ"ምናባዊ ፍርሃት" ልታሸፋፍኑት አትችሉም። ሀገራዊ ምክክሩ እውነታውን አፍረጥርጦ፣ የእኩልነት መሰረት
የሚጣልበት እንጂ፣ በአንዳንዶች ፈላጭ ቆራጭነት የተጻፈው ጥቁር አሻራ የሚቀጥልበት አይሆንም!
||
t.me/MuradTadesse | 16 653 |
| 6 | የሰዎችን ወሬና ሐሜት ይዘው ለሚመጡባችሁ ሰዎች በራችሁን ዝጉባቸው፤ ምክንያቱም አድማጭን መከልከል የተናጋሪውን ምላስ ይቆርጣልና። 🌱
ሐሜተኞች እና ወሬ አምጪዎች ሰሚ ካጡ ወሬያቸው በዚያው ይከስማል።
أغلقوا أبوابكم في وجه من يأتيكم بأخبار الناس، فبتر السامع.. يقطع لسان المتحدث."🌱 | 15 608 |
| 7 | بدون متن... | 17 429 |
| 8 | ትብብራችሁን አድርጉለት። የቀበሌያችን እስልምና ጉዳይ ኃላፊ ነው። ባለቤቱ ላለፉት ተከታታይ አመታት ታማበት ሐኪም ቤት እያመላለሰ ነበር። አሁን ደግሞ ትንሽ አዕመሮዋ ስለተበረዘ በተለይ ማታ ማታ አንዳንደዜ ራሷን ወደማጥፋት ሙከራ ነው የሚጋብዛት ብሎኛል።
የግድ ወደ አማኑዔል አምጥቶ ማሳከም ስላለበት ከትራንስፖርት ጀምሮ ስለሚቸገር የተወሰነ ተባበሩት።
🖊 የንግድ ባንክ አካውንቱ፦
1000643586626
🖊 ስም፦ ዑመር ደጉ
🖊 ኔትወርክ አለበት ቦታ ላይ ስላለ አሁን ስልኩ: 0914573015
የላካችሁበትን ደረሰኝ በውስጥ ላኩልኝ። ከመጠን በላይ እንዳይገባ ፖስቱ ስለሚጠፋ፣ እስከዛው ግን ተሽቀዳደሙ። | 17 246 |
| 9 | አወቅሽ አወቅሽ ቢሏት… መጽሐፍ አጠበች! | 16 824 |
| 10 | أين بُعث الأنبياء والرسل؟ ولماذا كانت أغلب الرسالات في الشرق الأوسط؟
تُظهر الخريطة أماكن بعثات عدد من الأنبياء والرسل وفق ما ورد في القرآن الكريم والسنة النبوية الصحيحة، مع الاستئناس بالمصادر التاريخية الإسلامية.
من المهم التأكيد أن أماكن بعثة عدد من الأنبياء ليست محددة بدقة أو محل اتفاق بين العلماء والمؤرخين، بينما ثبتت أماكن بعضهم بنصوص شرعية أو بأقوال راجحة.
ذكر القرآن الكريم 25 نبيًا ورسولًا بالاسم، وهم: آدم، إدريس، نوح، هود، صالح، إبراهيم، لوط، إسماعيل، إسحاق، يعقوب، يوسف، شعيب، أيوب، ذو الكفل، موسى، هارون، داود، سليمان، إلياس، اليسع، يونس، زكريا، يحيى، عيسى، ومحمد ﷺ.
📍 أبرز أماكن بعثات الأنبياء (وفق الرأي الراجح)
ـ🇸🇦 شبه الجزيرة العربية: محمد ﷺ، صالح، شعيب، إسماعيل، ويُرجح أن آدم عليه السلام عاش فيها بعد هبوطه إلى الأرض وفق بعض الروايات، لكن لا يوجد نص قطعي يحدد مكان هبوطه.
ـ🇪🇬 مصر: موسى، هارون، يوسف عليهم السلام، وكانت مسرحًا لأحداث رسالاتهم.
ـ🇵🇸 فلسطين: إبراهيم، يعقوب، يوسف (عاد إليها لاحقًا)، داود، سليمان، زكريا، يحيى، عيسى عليهم السلام، إضافة إلى ارتباطها بعدد كبير من الأنبياء.
ـ🇮🇶 العراق (بلاد الرافدين) إبراهيم، نوح، إدريس، ويونس عليهم السلام، وترتبط أيضًا بقصة أيوب وفق بعض الأقوال.
ـ🇸🇾 بلاد الشام (سوريا، لبنان) أيوب، إلياس، اليسع، وذو الكفل وفق أشهر الروايات.
ـ🇾🇪 اليمن: هود عليه السلام، حيث يُنسب إلى قوم عاد في منطقة الأحقاف جنوب الجزيرة العربية.
لماذا بُعث معظم الأنبياء في هذه المنطقة؟
تُعد منطقة الشرق الأوسط والهلال الخصيب وشبه الجزيرة العربية ووادي النيل من أقدم مراكز الحضارة البشرية، حيث نشأت أولى المدن والدول الكبرى، وتركزت فيها الكثافة السكانية وطرق التجارة، ولذلك كانت بيئة مناسبة لبعث الرسل ودعوة الناس إلى عبادة الله.
كما أن القرآن الكريم يذكر أن الله أرسل رسلًا إلى مختلف الأمم، وليس فقط إلى المنطقة العربية، قال تعالى:
> ﴿وَلَقَدْ بَعَثْنَا فِي كُلِّ أُمَّةٍ رَسُولًا﴾
(سورة النحل: 36)
وقال أيضًا:
> ﴿وَرُسُلًا قَدْ قَصَصْنَاهُمْ عَلَيْكَ مِن قَبْلُ وَرُسُلًا لَّمْ نَقْصُصْهُمْ عَلَيْكَ﴾
(سورة النساء: 164)
وهذا يعني أن القرآن لم يذكر جميع الأنبياء، بل ذكر عددًا منهم فقط.
💬 سؤال للنقاش: برأيك، ما السبب في أن معظم الأنبياء الذين ذُكرت قصصهم في القرآن ارتبطوا بمنطقة الشرق الأوسط، رغم أن القرآن يؤكد أن الله أرسل رسلًا إلى كل أمة؟ | 16 289 |
| 11 | የማለዳ ስንቅ ለቀልብዎ❤️
[Part: ③②①⑤]👌
#ቁርኣን | 15 832 |
| 12 | የምሽት ስንቅ ለቀልብዎ❤️
[Part: ③②①④]👌
#ቁርኣን | 16 783 |
| 13 | የታሪክ ግብዝነት ሲጋለጥ‼
================
(ለ1,600 ዓመታት በግብፅ (ዐረብ) ጳጳስ ሲመራ የኖረ ተቋም፣ ሙስሊሙን "ዐረብ" ብሎ ሲከስ!)
||
✍️ በሀገራችን የፖለቲካ እና የኃይማኖት ዲስኩር ውስጥ፣ አንዳንዶች የኢትዮጵያን ሙስሊም የዐረብ ተላላኪ ወይም የባዕድ ባህል አራማጅ እና መጤ አድርገው ለመሳል ሲሞክሩ መስማት፣ ለታሪክ ምሁራን ፈገግታን የሚፈጥር የድንቁርና ትርክት ነው።
🖊 እስኪ ስሜትን ወደ ጎን ትተን፣ የታሪክ ማህደሮችን ገልጠን፣ እውነተኛው የዐረብ እና የባዕድ ተጽዕኖ ማን ላይ እንደነበረ በመረጃ እንየው፦
1⃣ ከ4ኛው እስከ 20ኛው ክፍለ ዘመን፡ የባዕዳን (የግብፃውያን) የአመራር የበላይነት!
🎀 በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ከ4ኛው ክፍለ ዘመን (ከአባ ሰላማ ከሳቴ ብርሃን) ጀምሮ እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ (እስከ 20ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ)፣ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ-ክርስቲያን የበላይ መንፈሳዊ መሪ (አቡነ/ጳጳስ) ኢትዮጵያዊ ሆኖ አያውቅም!
🔗ለ1,600 ተከታታይ ዓመታት፣ ቤተ-ክርስቲያኗን በበላይነት ይመሩ የነበሩት ከእስክንድርያ (ግብፅ) ኮፕቲክ ቤተ-ክርስቲያን በውክልና የሚላኩ ግብፃውያን (ዐረብ) ጳጳሳት ነበሩ። ግብፅ ደግሞ ከ7ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ ሙሉ በሙሉ የዐረብ ባህልና ቋንቋ ተጽዕኖ ስር የወደቀች ሀገር ናት። እነዚህ ከግብፅ የሚላኩ ጳጳሳት አብዛኛዎቹ ግዕዝም ሆነ አማርኛ የማይችሉ፣ ከአስተዳዳሪዎቻቸው
ጋር በአስተርጓሚ (በዐረብኛ) የሚግባቡ ነበሩ። የኢትዮጵያ ነገሥታትም ሆኑ ካህናት ለነዚህ ባዕዳን ጳጳሳት ያጎበድዱ፣ ይገብሩ እና ይገዙ ነበር።
🖊 ይህ የግብፃውያን (የዐረቦች) የበላይነት ያበቃው፣ አፄ ኃይለሥላሴ ከእስክንድርያ መንበር ጋር ረጅም የዲፕሎማሲ ትግል አድርገው፣ በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ኢትዮጵያዊው አቡነ ባስልዮስ የመጀመሪያው ፓትርያርክ ሆነው በተሾሙበት በ1951 E.C. (1959 እ.ኤ.አ) ብቻ ነው!
2⃣ «ሙስሊሙ ዐረብኛ ቋንቋ ይጠቀማል» እያሉ ለሚተቹ ወገኖች፣ የገዛ ራሳቸው የኃይማኖትና የሥርዓት መጻሕፍት ከየት እንደመጡ ማወቁ
ያስደነግጣቸዋል።
🤩 የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ-ክርስቲያን አብዛኛዎቹ መሠረታዊ መጻሕፍት ከዐረብኛ ቋንቋ ወደ ግዕዝ የተተረጎሙ ናቸው! ለምሳሌ
ያህል፡-
✅ ፍትሐ ነገሥት፡
➡️ ለዘመናት የኢትዮጵያ ኃይማኖታዊ፣ ፍትሐዊ እና አስተዳደራዊ ሕግ ሆኖ ያገለገለው ይህ መጽሐፍ፣ የተጻፈው "አስ-ሳፊ ኢብኑ አል-አሳል" በተባለ ግብጻዊ (ዐረብ) ኮፕቲክ ክርስቲያን በዐረብኛ ቋንቋ (ክርስቲያናዊ ምሁር) ሲሆን፣ በ15ኛው ክፍለ ዘመን በአፄ ዘርአ ያዕቆብ ዘመን ወደ ግዕዝ የተተረጎመ ነው።
✅ ስንክሳር (Synaxarium)፡
➡️ የቅዱሳን ታሪክ የሚነበብበት ይህ ትልቅ መጽሐፍ የተተረጎመው ከኮፕቲክ ዐረብኛ ጽሑፎች ነው።
✅ ኃይማኖተ አበው (Faith of the Fathers)፡
➡️ ይህ መሠረታዊ የነገረ-መለኮት (ቴዎሎጂ) መጽሐፍ ከዐረብኛ ወደ ግዕዝ የተተረጎመ ነው።
✅ ተአምረ ማርያም (Miracles of Mary)፡
➡️ ይህ በቤተ-ክርስቲያኗ እጅግ የተከበረው መጽሐፍ ጭምር፣ በ14ኛው እና 15ኛው ክፍለ ዘመን ከዐረብኛ ቋንቋ የተተረጎመ ነው!
3⃣ የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ነባራዊ እውነታ!
🎀 አሁን እውነታውን ወደ ኢትዮጵያ ሙስሊሞች እናዙርና፤ እስልምና ወደ ኢትዮጵያ ከገባበት ከ1ኛው ክፍለ ዘመን (ከነጃሺ ዘመን) ጀምሮ፣ የኢትዮጵያ ሙስሊም አንድም ቀን ዐረብ ኢማም፣ ዐረብ ሙፍቲ ወይም ዐረብ ቃዲ ከውጭ ሃገር ተልኮለት አአልተዳደረም!
➡️ የኢትዮጵያ ሙስሊም ሸይኾች፣ ዑለማዎች፣ ኢማሞች እና መሪዎች ከጥንት እስከ ዛሬ 100% ኢትዮጵያውያን (የወሎ፣ የሐረር፣ የባሌ፣
የጅማ፣ የጉራጌ፣ የትግራይ ወዘተ ተወላጆች) ናቸው። የኢትዮጵያ ሙስሊም ዲኑን የጠበቀው፣ መስጂዱን የመራው በገዛ ሀገር በቀል ሊቃውንቱ (Indigenous Scholars) እንጂ፣ እንደ ቤተ-ክህነቱ "ከውጭ ጳጳስ ላኩልን" ብሎ ዐረብ ሀገር በመለመን
አልነበረም። ሙስሊሙ ዐረብኛን የሚማረው ቋንቋው የቅዱስ ቁርኣን መገለጫ ስለሆነ ብቻ እንጂ፣ በአስተዳደር እና በማንነት የዐረብ ተጽዕኖ ስር ስለወደቀ አይደለም!
✅ እንግዲህ እውነታው ይህ ሆኖ ሳለ፣ ለ1,600 ተከታታይ ዓመታት በግብፅ ዐረብ ጳጳሳት ሲመራ የኖረ፣ ኃይማኖታዊ እና ሕጋዊ መጻሕፍቱን ከዐረብኛ ወደ ግዕዝ የተረጎመ፣ እና እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ ቄስ እያስመጣ ያስጠምቅ የነበረ ተቋም፤ በታሪኩ በሙሉ በገዛ ሀገር-በቀል ሊቃውንቱ ሲመራ የኖረውን እና አንድም የውጭ አገር መሪ ተሹሞበት የማያውቀውን ኢትዮጵያዊ ሙስሊም "የዐረብ ተላላኪ" ብሎ መክሰስ ከታሪክ ድንቁርናም ያለፈ የሞራል ክስረት ነው!
በመስታወት ቤት ውስጥ የሚኖር ሰው፣ በሰው ቤት ላይ ድንጋይ መወርወር የለበትም!
እውነተኛው የውጭ (የዐረብ) አስተዳደራዊ ተጽዕኖ የትኛው ተቋም ላይ እንደነበረ ታሪክ ፍንትው አድርጎ አስቀምጦታል። ይህንን ሐቅ
መካድ አይቻልም!
ደህና እደሩ‼
||
t.me/MuradTadesse | 17 191 |
| 14 | 📌 ጥቆማ | ክረምቱን ለልጆቻችሁና እና ለራሳችሁ ምን ስኪል በመማር ለማሳለፍ አቅዳችኋል⁉️
======
(ቤተሰብ ከሆናችሁ 1 ሰው በተመዘገበበት ሌላኛው በነፃ መማር ይችላል – AI Powerd Full Stack Web Dev't መማር ለምትፈልጉ!)
||
✍️ ባለፈው ክረምቱን በአግባቡ እና በቁምነገር እንድታሳልፉበት ከጠቆምኳችሁ በርካታ የመንግስትና የግል ተቋማት መካከል አንዱ የሆነው ሚዛን የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት፤ አሁን ላይ ተቋሙ መደበኛ ምዝገባውን አጠናቋል፤ ነገር ግን ሁለት
ወሳኝ እድሎችን አመቻችቶላችኋል።
1⃣ ለወላጆች (የልጆች የክረምት ጊዜ)፦
ክረምት ላይ ልጆቻችን በዋናነት በቂርኣት እና በዲን ትምህርት መታነፅ እንዳለባቸው ሁላችንም እናምናለን። በጋውንም ከትምህርታቸው በማይጋጭ መልኩ መቀጠል አለበት። ከዚህ የተረፈውን ጊዜ ግን ዝም ብለው ከጓደኛ ጋር እንዲያሳልፉ ክፍተት ከሰጠናቸው፣
ላልተፈለገ ልማድ እና አልባሌ ነገር ሊጋለጡ ይችላሉ። ስለዚህ ትርፍ ጊዜያቸውን ለወደፊቱ ህይወታቸው እጅግ ጠቃሚ በሆነው የቴክኖሎጂ ክህሎት (Tech skills) እንዲያሳልፉ ብታደርጉ መልካም ነው።
☑ በሚዛን መደበኛው የልጆች መማሪያ ስኬጁል በሁሉም ፈረቃ ሞልቷል ብለዋል፤ ነገር ግን አሁን ላይ ለልጆች ክፍት የሆነውና 3ኛ ፈረቃ ማክሰኞ እና ሐሙስ በጠዋቱ ፈረቃ ብቻ ነው። ዛሬ ስለሆነ የሰጡት ቀን የሚጠናቀቀው፣ ሰዓቱ ከማለቁ በፊት ዛሬውኑ በኦንላይን አስመዝግቧቸው።
2⃣ በኦንላይን መማር ለምትፈልጉ፦
ሌላው ያመቻቹት እድል በኦንላይን ለሚማሩ ነው። በሚዛን MiT
ኦንላይን መማር ልዩ የሚያደርገው፤ ትምህርቱ በቀጥታ (Live session) ከመሰጠቱም ባለፈ፣ ቪዲዮው ሪከርድ ተደርጎ በዌብሳይታቸው (LMS) ላይ ስለሚቀመጥ፣ ያልገባችሁን ነገር ደጋግማችሁ እንድትለማመዱበት እና እንድታዩት መደረጉና እዛው ላይ በኤአይ የታገዘ ያልገባችሁን የምትጠይቁበት አሲስታንት መኖሩ ነው።
በነገራችን ላይ ሚዛን የሚያስተምረው ለልጆች እና ለተማሪዎች ብቻ ሳይሆን፤ ከጀማሪ እስከ አድቫንስድ (Beginner to Advanced) በማንኛውም የዕድሜ ክልልና የትምህርት ደረጃ ለሚገኙ እና የቴክኖሎጂ ክህሎት መቅሰም ለሚፈልጉ ሁሉ ነው።
⚠️ የኦንላይኑም ሆነ የልጆቹ ምዝገባ የሚያልቀው ዛሬ ነው!
እድሉ ሳያመልጣችሁ መመዝገብ የምትፈልጉ በዚህ ሊንክ ተመዝገቡ።
http://www.mizantechinstitute.com/admissions
📞 ለበለጠ መረጃ በቴሌግራም አናግሯቸው።
t.me/MizanInstituteOfTechnologyEthio
የተለያዩ የቅናሽ ፓኬጆችንም ዘርዝረዋል፣ አንብቡና በሚመቻችሁ ተመዝገቡ።
እዚህ ላይ ጽፈውታል። https://t.me/MizanInstituteOfTechnology/665 | 16 720 |
| 15 | የሃገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ ከሚያስተካክላቸው ነገሮች አንዱ፤ የጁሙዓን ቀን የእረፍት ቀን ማድረግ መሆን አለበት። ቅዳሜ የሥራ ቀን ይሁን። ጁሙዓና እሁድ ሳምንታዊ የእረፍት ቀን። | 18 194 |
| 16 | بدون متن... | 3 496 |
| 17 | እኔ አላልኩም¡ | 20 423 |
| 18 | «የአሁኗ ሚስቱ እንዳይከፋት በማሰብ ሌላ ሚስት መጨመርን የተወ ባል እሱ ከአላህ ዘንድ ተሸላሚ (ባለምንዳ) ነው።»
[በሕሩ ራኢቅ – ሸርሑ ከንዚ ደቃኢቅ: 3/112] | 20 587 |
| 19 | አንደሉስ → የዛሬዋ ስፔን‼
================
(በአውሮፓ እምብርት ያበራችው የኢስላም ፀሐይ እና የጠፋችው ውብ ገፅታ!)
||
✍️ «የአይቤሪያን ልሳነ ምድር ታሪክና ባህል ለመረዳት የሚሞክር ማንም ሰው፣ ያንን 'አስደናቂ የሆነውን ኢስላማዊ ትሩፋት' ከግምት ውስጥ ሳያስገባ ማለፍ አይችልም!» - (ሪቻርድ ፍሌቸር፣ 'ኢስላማዊቷ ስፔን' በተሰኘው መጽሐፉ)
🖊 ዛሬ ስፔን እና ፖርቱጋል ብለን የምንጠራቸው ሀገራት፣ ከአንድ ሺህ ዓመታት በፊት በአውሮፓ የጨለማ ዘመን (Dark Ages) ውስጥ ብቸኛዋ የበራች የብርሃን ደሴት ነበሩ። ስሟ "አንደሉስ" (Al-Andalus) ይባላል። ይህች ምድር ከ711 እ.ኤ.አ
እስከ 1492 እ.ኤ.አ ለስምንት መቶ ዓመታት በእስልምና አስተዳደር ስር የነበረች፣ ዓለም ያየቻት እጅግ
ስልጡን፣ የሳይንስ፣ የፍትሕ እና የመቻቻል ማማ ነበረች።
እስኪ የዚችን የጠፋችና የተረሳች ታሪከኛ ምድር የተወሰኑ ገጽታዎች እንቃኝ፦
1⃣ ታሪካዊው መግቢያ፡ የጧሪቅ ኢብኑ ዚያድ ድል! ⚔️፦
🎀 በ711 እ.ኤ.አ ታላቁ የኡመውያ ኸሊፋ አል-ወሊድ ኢብኑ ዐብዱልመሊክ ባዘዘው መሠረት፣ ጀግናው የጦር አዛዥ ጧሪቅ ኢብኑ ዚያድ 7,000 የሚጠጉ ወታደሮቹን ይዞ ወደ አይቤሪያ ልሳነ-ምድር ተሻገረ። ያ ተሻግሮ ያረፈበት ትልቅ ተራራ እስከ ዛሬ ድረስ በስሙ "ጀበለ-ጥ'ጧሪቅ" (Gibraltar) ተብሎ ይጠራል።
🖊 በዚያን ጊዜ ስፔንን ይገዛ የነበረው ጨቋኙ የቪዚጎዝ (Visigothic) ንጉስ ሮደሪክ (Roderic) ነበር። ጧሪቅ ኢብኑ
ዚያድ በጓዳሌት ጦርነት (Battle of Guadalete) የሮደሪክን ግዙፍ ጦር ድል በማድረግ፣ አብዛኛውን የስፔን እና
የፖርቱጋል ክፍል፣ አልፎም እስከ ደቡብ ፈረንሳይ ድረስ በ7 ዓመታት ውስጥ በኢስላም ጥላ ስር አስገባ። ይህች ምድርም አንደሉስ ተብላ ተሰየመች።
2⃣ ቆርዶባ (Córdoba)፡ የዓለም የዕውቀት ማዕከል! 😀
🎀 አንደሉስ በተለይም በዐብዱ-ር'ረሕማን አድ-ዳኺል (Abd al-Rahman I) እና በኡመውያ ኸሊፋዎች ዘመን፣ የዓለም የዕውቀት፣
የሥልጣኔ እና የንግድ ማዕከል ሆነች። ዋና ከተማዋ ቆርዶባ (قرطبة) በዚያ የጨለማ ዘመን የአውሮፓ ትልቋ ከተማ ነበረች።
✅ ከ100,000 በላይ ነዋሪዎች ነበሯት።
✅ መንገዶቿ በሌሊት በመብራት (Oil lanterns) ያበሩ ነበር (በዚያን ጊዜ ለንደን እና ፓሪስ በጭቃ እና በጨለማ የተዋጡ ነበሩ)።
✅ በከተማዋ 70 ግዙፍ ቤተ-መጻሕፍት፣ 700 መስጂዶች፣ እና 3,000 የሕዝብ መታጠቢያዎች ነበሩ።
✅ ዛሬም ድረስ በአርክቴክቸር ድንቅነቱ የሚነገርለት የቆርዶባ ታላቁ መስጂድ (Mosque-Cathedral of Córdoba) የዚህ ዘመን ትሩፋት ነው።
3⃣ የሳይንስ እና የሕክምና ወርቃማ ዘመን 🔬
🎀 ዛሬ አውሮፓውያን ለደረሱበት የሳይንስ እና የሕዳሴ (Renaissance) ከፍታ፣ መሠረቱን የጣሉት የአንደሉስ ሙስሊም ምሁራን ናቸው።
✅ ሕክምና፡
➡️ አቡ አል-ቃሲም አል-ዘህራዊ የተባለው ሙስሊም ሊቅ፣ ዘመናዊ የቀዶ ጥገና (Surgery) አባት ይባላል። ዛሬ የምንጠቀምባቸውን 200 የሰርጀሪ እቃዎች የፈጠረው እርሱ ነው።
✅ አስትሮኖሚና ሒሳብ፡
➡️ አል-ዘርቃሊ (Al-Zarqali)፣ የኮፐርኒከስን ሥራዎች ያስቀደመ ታላቅ የአስትሮኖሚ ሊቅ ነበር። ከ0-9 ያሉት ቁጥሮች (Arabic numerals) ወደ አውሮፓ የገቡት በዚችው በአንደሉስ በኩል ነው።
✅ ግብርና (Agronomy)፡
➡️ ሙስሊሞች ዘመናዊ የመስኖ ስርአት (Irrigation)፣ ሸንኮራ አገዳ፣ ሎሚ፣ ሩዝ፣ እና ሮማን (Pomegranate) የመሳሰሉትን ፍራፍሬዎች ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ አውሮፓ ያስተዋወቁት በአንደሉስ ነበር።
4⃣ ፍትህ፣ አብሮነት እና መቻቻል (La Convivencia) 🕊️
🎀 በአንደሉስ ዘመን ሙስሊሞች፣ አይሁዶች እና ክርስቲያኖች በአንድነት በሰላም የኖሩበት "ወርቃማው የአብሮነት ዘመን" ነበር። ክርስቲያኖችና አይሁዶች የራሳቸውን ኃይማኖት በነፃነት መተግበር ብቻ ሳይሆን፣ በመንግስት ውስጥ ትልልቅ የሥልጣን ቦታዎች
(አምባሳደር፣ ሐኪም፣ ሚኒስትር) ነበሯቸው። በተለይም አይሁዶች በአውሮፓ ይደርስባቸው ከነበረው ጭፍጨፋ ሸሽተው ሰላም ያገኙት
በኢስላማዊቷ ስፔን (አንደሉስ) ውስጥ ነበር። ይህ ዘመን በታሪክ "Golden age of Jewish culture" ተብሎ
ይጠራል። ዛሬ ግን እነርሱ ታሪካቸውን ረስተው ፍልስጤምን ወረዋል።
5⃣ የአንደሉስ ብርሃን መጥፋት፡ የውድቀት መጀመሪያ (Reconquista) 💔፦
🎀 ከጥንካሬዋ በኋላ አንደሉስ መዳከም ጀመረች። ምክንያቱ ደግሞ የውጭ ጠላት ሳይሆን፣ የሙስሊሙ የውስጥ ሽኩቻ እና መከፋፈል
(Taifas/የአናሳ መንግስታት ዘመን) መምጣቱ ነበር። በ1031 እ.ኤ.አ የቆርዶባ ኸሊፋነት ሲፈርስ፣ አንደሉስ ወደ ትናንሽ እና እርስበርስ ወደሚዋጉ የሙስሊም ግዛቶች ተከፋፈለች።
✒️ ይህንን የሙስሊሙን መከፋፈል የተጠቀሙት የሰሜን ክርስቲያን መንግስታት (ካስቲል፣ አራጎን፣ ሊዮን) በጋራ በመሆን የሪኮንኪስታ
(Reconquista - ዳግም የማስመለስ) ጦርነት ጀመሩ። መጀመሪያ ቶሌዶን (1085)፣ ከዚያም ቆርዶባን (1236) እና ሲቪልን (1248) ተቆጣጠሩ።
✒️ የመጨረሻዋ ምሽግ መውደቅ፡ ግራናዳ (1492)
💾 የመጨረሻዋ የሙስሊሞች ምሽግ የነበረችው ግራናዳ (Granada)፣ ለ250 ዓመታት ታግላ፣ በመጨረሻ ጃንዋሪ 1 ቀን 1492 እ.ኤ.አ በንጉስ ፈርዲናንድ እና ንግስት ኢዛቤላ ጦር ተከበበች። የአንደሉስ የመጨረሻው ሙስሊም መሪ (አቡ ዐብደልሏህ)፣ ያንን ድንቅ የሆነውን የአልሐምብራ ቤተመንግስት (Alhambra Palace) ቁልፍ አስረክቦ፣ ከከተማዋ ሲወጣ፣ ስቅስቅ ብሎ አለቀሰ። ያኔ እናቱ «እንደ ወንድ ተዋግተህ ማቆየት ያቃተህን ሀገር፣ እንደ ሴት አታልቅስላት» ብላዋለች ይባላል።
✒️ ከዚያ በኋላ ስፔንን የተቆጣጠሩት ካቶሊኮች፣ በሙስሊሞች እና አይሁዶች ላይ ታይቶ የማይታወቅ የዘር ማጥፋት (Inquisition) አወጁ። «ወይ ወደ ክርስትና ግቡ፣ ወይ ሀገር ለቃችሁ ውጡ፣ አለበለዚያ ትገደላላችሁ» የሚል አዋጅ ወጣ። በሚሊዮን የሚቆጠሩ
የሙስሊም መጽሐፍት በአደባባይ ተቃጠሉ፤ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ሙስሊሞች (ሞሪስኮስ በመባል የሚታወቁት) ተገድለዋል፤ ከፊሎችም ወደ ሞሮኮ እና አልጄሪያ ተሰደዋል።
⏰ አንደሉስ ዛሬ በካርታ ላይ የለችም። ነገር ግን የተዋበው አርክቴክቸሯ፣ ያስተማረችው የሳይንስ ብርሃን እና የፍትህ ታሪኳ መቼም አይረሳም። የሙስሊሙን ኡማ ትልቅነትም ሆነ መከፋፈል፣ ምን አይነት ውርደትና ውድቀት እንደሚያመጣ የምታስተምር
ሕያው የታሪክ መጽሐፍ ናት!
ታሪክን እንማር፤ ከስህተታችንም እንንቃ!
#HistoryOfIslam #AlAndalus #IslamicSpain #GoldenAge #Cordoba #MuslimHistory
#EthiopianMuslims
(ይህን ማራኪ ታሪካዊ ጽሑፍ ሼር በማድረግ፣ እኛ ሙስሊሞች ምን አይነት የከፍታ ታሪክ እንደነበረን ለትውልዱ እናስታውስ!)
||
t.me/MuradTadesse | 22 569 |
| 20 | ባለፈ ልጆቻችሁን አስመዝግቡ ብያችሁ ነበር። ከነዚህ 500ዎቹ ውስጥ ስንቶቹ የናንተ ልጆች ናቸው⁉️ | 19 223 |
