fa
Feedback
Wondo Genet Secondary School

Wondo Genet Secondary School

رفتن به کانال در Telegram

Educational purpose

نمایش بیشتر
2 804
مشترکین
-124 ساعت
-67 روز
+1730 روز
آرشیو پست ها
ማስታወቂያ ለ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ለተማሪዎች በሙሉ ዛሬ 24/10/2018 ዓም ከሰዓት 8:00 ሰዐት ላይ ኦረንቴሽን ስለሚኖር ሀላችሁም ተፈታኞች ት/ቤታችን ግቢ ውስጥ እንድትገኙ አሳስባለሁ። ማሳሰቢያ:- አለባበስ እና ወንዶች ፀጉራችሁን አሳጥራችሁ እንድትቀርቡ እናሳስባለን።

https://exp10.ethernet.edu.et/ በዚህ link እየገባችሁ ለmock exam የተለቀቀውን ፈተና ስሩ Username: Admission number Password: 1234

2018 ትምህርት ዘመን 12ኛ ክፍል ሀገራዊ ፈተና ዝግጅት የአፈፃፀምና ቀሪ ስራዎችን በሚመለከት የክልሉ ግብረ ሀይሉ ግምገማ ተካሄደ ። ሰኔ 18/2018 ዓ.ም የኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት የዘንድሮ ሀገራዊ ፈተና የሚፈተኑ በክልሉ ውስጥ የሚገኙ የ12ኛ ክፍል ፈተና ቅድመ ዝግጅት በተመለከተ የሲዳማ ክልል ትምህርት ቢሮ ከግብረ ሀይል ጋር ግምገማ አድርገዋል። ከሰኔ 23/2018 ዓ.ም እስከ ሀምሌ 17/2018 ዓ.ም ለሚሰጠው የ12ኛ ክፍል ፈተና በስድስት ዙር የሚሰጥ ሲሆን በመጀመሪያ ሶስት ዙር የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች የሚፈተኑና ቀጣይ ሶስት ዙር የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች የሚፈተኑ ይሆናል ። የ12ኛ ክፍል ፈተና የሚሰጠው በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ የሚገኙ ሁሉም ካምፓሶች፣ከኮሌጆችና ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቋማት እንዲሁም በተመረጡ በመንግስትና ግል ትምህርት ቤቶች መሆኑንም ተገልጿል። በፈተና ላይ የመብራት፣የኔትወርክ የመሳሰሉት ችግር እንዳይፈጠር የቅንጅት ስራ መስራት እንደሚገባና የክትትልና ድጋፍ ስራ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት በግምገማ ወቅት ተነስተዋል ። ክቡር አቶ በየነ ባራሳ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳደርና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ የግብረ-ሀይል ሰብሳቢ እንደገለጹት ተማሪዎች በሁለቱም መንገድ ፈተናውን ያለ ምንም መስተጓጎል የጉዞ ቀናትን ጨምሮ በፈተና ቀናት ሰላማዊ ሆኖ እንድጠናቀቅ የሁሉም ባለድርሻ ቅንጅት መጠናከር እንደሚገባ አሳስበዋል።

👍

round 6(six).xlsx0.11 KB

Round 6.pdf4.27 KB

Round 5.pdf6.39 KB

round 5(five).xlsx0.26 KB

round 4(four).xlsx0.17 KB

Round 4.pdf5.05 KB

round 3(three).xlsx0.24 KB

Round 3.pdf6.04 KB

round 2.pdf4.75 KB

round 2(two).xlsx0.16 KB

Dear All, For tomorrow’s mock exam and the final examination, pls find below the exam website URLs. We kindly request that your team use the appropriate URL assigned to your region. Central Ethiopia, Somali, and Afar https://exp11.ethernet.edu.et/ Sidama, South West Ethiopia Peoples’ Region (SWEP), Dire Dawa, Tigray, Benishangul-Gumuz, Harari, and Gambella https://exp10.ethernet.edu.et/ Amhara Region https://exp8.ethernet.edu.et/ South Ethiopia https://exp9.ethernet.edu.et/ Pls note that the URLs for Addis Ababa and Oromia have been shared separately. Thank you

በጥንቃቄ እያታችሁ የምትፈተኑበትን ዙር ከተሳሳታችሁ አስቸጋሪ ነው። በስማችሁ ቀጥታ ስትሄዱ R1 ከሆነ Round 1 ሰኔ 23 የሚጀምሩ የተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች ናቸው። Round 2 ሰኔ 26 የሚጀምሩ የተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች ናቸው። Round 3 ሐምሌ 1 የሚጀምሩ የተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች ናቸው። ከRound 4-6 የማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች ናቸው። Round 4 ሐምሌ 6 የሚጀምሩ የማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች ናቸው። Round 5 ሐምሌ 9 የሚጀምሩ የማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች ናቸው። Round 6 ሐምሌ 14 የሚጀምሩ የማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች ናቸው። የምትፈተኑበትን ዙር እና መፈተኛ ቦታችሁን በጣም በጥንቃቄ ለይታችሁ እወቁ። መልካም የፈተና ጊዜ ይሁንላችሁ።

HawassaUniversityWonoGenetList.xlsx0.94 KB

ማስታወቂያ ለወንዶ ገነት 2ኛ ደረጃ ት/ቤት የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በሙሉ የፈተና ቦታችሁሐዋሳ ዩኒቨርስቲ መሆኑ ታውቋል። ስለሆነም የምትፈተኑበት ዙር እና የምትፈተኑበት ዩኒቨርስቲ ስለተለቀቀ ስማችሁን እና የምተፈተኑበትን የፈተና ዙር በጥንቃቄ በማየት ከወዲሁ ዝግጅት እንድታደርጉ እናሳስባለን።

ማስታወቂያ ለ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በልምምድ ወቅት ወደ system ለመግባት password rest ያላስደረጋችሁ ተማሪዎች ነገ ትምህርት ቤት በመምጣት ማስተካከል የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን ። ማሳሰቢያ፦ ባለማስተካከላችሁ ለሚፈጠረው ችግር ኃላፊነት አንወስድም ።