Wondo Genet Secondary School
الذهاب إلى القناة على Telegram
2 923
المشتركون
+324 ساعات
+127 أيام
+11330 أيام
أرشيف المشاركات
#ዜና
ነሐሴ 16 2018
የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ውጤት ዛሬ ይፋ ይደረጋል።
ትምህርት ሚኒስቴር በላከልን መረጃ የዘንድሮ የ12ኛ ክፍል የሀገር አቀፍ ፈተና ውጤትን በተመለከተ ከሰዓት በኋላ መግለጫ እንደሚሰጥ ጠቅሷል።
በዓመቱ ፈተናውን ከወሰዱ ተማሪዎች መካከል 62 በመቶ የሚሆኑት በኦንላይን ፈተናውን ወስደዋል።
በ2018 የትምህርት ዘመን አጠቃላይ 563 ሺህ 501 ተማሪዎች በ607 የፈተና ማዕከላት ውስጥ የተፈተኑ ሲሆን ፈተናው በ6 ዙሮች ተሰጥቷል።
ከዘንድሮ ጠቅላላ ተፈታኞች መካከል 306 ሺህ 456 የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ሲሆኑ፣ 257 ሺህ 45 ደግሞ የማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ነበሩ፡፡
ውጤቱን በተመለከትም ትምህርት ሚኒስቴር በ9 ሰዓት መግለጫ እሰጣለሁ ብሏል፡፡
በረከት አካሉ
ሸገር ሬዲዮ
Repost from SIDAAMU QOQQOWI ROSU BIIRO/የሲዳማ ክልል ትም/ ቢሮ/
የ2019 ትምህርት ዘመን የተማሪዎች ምዝገባ ከነሐሴ 18/2018 ዓ.ም እንደሚጀመር ተገለፀ ።
ነሐሴ 15/2018 ዓ.ም የቢሮ ኮሙኒኬሽን
በሲዳማ ክልል የ2019 ትምህርት ዘመን የተማሪዎች ምዝገባ አስመልክተው የሲዳማ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና ትምህርት ቢሮ ሀላፊ አቶ በየነ ባራሳ
ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥተዋል።
አቶ በየነ በመግለጫቸውም በትምህርት ሰክተር የሚታዩ ክፍተቶችን ለመሙላት ዘርፈ ብዙ ስራዎች መሰራቱን የገለጹት አቶ በየነ የ2019 ዓ.ም ትምህርት ለመጀመር በክረምት ወቅት አስፈላጊውን ዝግጅት መደረጉን ገልጸዋል ።
በዚህም ስራ ለትምህርት ምቹ የሆኑ አካባቢዎች ለመፍጠር እንደ ክልል 90 በመቶ የሚሆኑ ትምህርት ቤቶች ለመማርና ማስተማር ዝግጁ መሆኑን አስረድተዋል ።
በክልል ደረጃ የ2019 ትምህርት ዘመን 1 ነጥብ 3 ሚሊዮን ተማሪዎች ለማስመዝገብ ዕቅድ መያዙን የገለጹት ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና ትምህርት ቢሮ ሀላፊ የተማሪዎች ምዝገባ ከነሐሴ 18/2018 ዓ.ም እንደሚጀመርና የተማሪዎች ምዝገባ ለሁለት ሳምንት ብቻ እንደሚቆይ ተናግረዋል ።
አቶ በየነ አክለውም ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህፃናት በሙሉ በትምህርት ገበታ ላይ በመገኘት ያለመንጠባጠብ እንዲመዘገቡ ወላጆችና ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል ሀላፊነታቸውን እንዲወጡ ጥሪውን በማቅረብ መላው የክልላችን ማህበረሰብ እንኳን ለ2019 ትምህርት ዘመን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል ።
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
ትምህርት ሚኒስቴር ከ2019 የትምህርት ዘመን ጀምሮ ተግባራዊ የሚደረጉ የ11 የሥራና ተግባር ትምህርት የሙያ አይነቶችን ዝርዝር አሳውቋል።
የኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር እና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እና በክልል ትምህርት ቢሮዎች፣ ከ2019 የትምህርት ዘመን ጀምሮ በሁለተኛው ዙር ተግባራዊ የሚደረጉ 11 የሥራና ተግባር ትምህርት የሙያ ዓይነቶችን ለመተግበር እየተደረገ ያለውን ዝግጅት የተመለከተ መመሪያ አስተላልፏል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የተመለከተው የትምህርት ሚኒስቴር መመሪያ በአዲሱ የትምህርትና ሥልጠና ፓሊሲ ላይ "የሙያና ቴክኖሎጅ ትምህርት ከቅድመ አንደኛ ደረጃ ጀምሮ ከእድሜያቸው ጋር የተመጣጠነ ሆኖ እንዲሰጥ ይደረጋል" በሚል አቅጣጫ መቀመጡን ያመለክታል።
በዚህ መሰረት በየደረጃው የሥራና ተግባር ትምህርት ከሌሎች ትምህርቶች ጋር ተቀናጅቶ እንዲሁም 7ኛ እና 8ኛ ክፍል ራሱን ችሎ ተማሪዎች በቀጣይ የሚፈልጉትን ሙያ እንዲመርጡ በሚያስችል መልኩ እየተሰጠ ይገኛል ብሏል፡፡
ከዚህ በተጨማሪ በ11ኛ እና 12ኛ ክፍል በተለያዩ የሙያ አይነቶች ከቀለም ትምህርታቸው ጎን ለጎን ከ2017 የትምህርት ዘመን ጀምሮ በ12 የሙያ አይነቶች እየተሰጠ እንደሚገኝም ሰርኩላሩ ያትታል።
ትምህርት ሚኒስቴር ከ2019 የትምህርት ዘመን ጀምሮ ደግሞ በሁለተኛው ዙር እንዲተገበሩ ለተለዩት 11 የሙያ አይነቶች ለ11ኛ እና 12ኛ ክፍል መርሐ ትምህርቶች እንዲሁም ለ11ኛ ክፍል የተማሪ ሞጁሎችና የመምህር መምሪያዎች ዝግጅት ማጠናቀቁን ገልጿል።
በመሆኑም እነዚህን ተጨማሪ የሙያ አይነቶች ከ2019 የትምህርት ዘመን ጀምሮ በ11ኛ ክፍል ለማስጀመር :-
• የክልሉ/የከተማ አስተዳደሩ ትምህርት ቢሮ ዝርዝር እቅድ በማዘጋጀት እና እቅዱን ለማከናወን በጀት በመያዝ የሙያ አይነቶችን በትምህርት ቤት እና በተማሪዎች ደረጃ በማስመረጥ፣
• የየሙያ አይነቱ መምህራንን በመቅጠር፣
• የመማሪያ ማስተማሪያ ግብዓት በሂደት በማሟላት፣
• መምህራንን እና የትምህርት አመራሮችን በማሰልጠን እና የህዝብ ንቅናቄ ስራዎችን በማከናወን ትምህርቱን ለማስጀመር ከወዲሁ ቅድመ ዝግጅት እንዲያደርጉ አሳስቧል።
ትምህርት ሚኒስቴር ከ2019 የትምህርት ዘመን ጀምሮ ተግባራዊ የሚደረጉ የ11 የሙያ አይነቶችን ዝርዝር አሳውቋል።
የሙያ አይነቶቹ ፦
- ብረታ ብረት ሥራ ቴክኖሎጂ፣
- አውቶሞቲቭ ቴክኖሎጂ፣
- አልባሳት ቴክኖሎጂ፣
- ህንፃ ኤሌክትሪክ መስመር ዝርጋት፣
- ቧንቧ ስራ፣
- ሶፍትዌር ማበልጸግ፣
- ሰብል አመራረት፣
- ጤና ክብካቤ አገልግሎት፣
- ሆቴል አገልግሎት፣
- ፀጉር ሥራና ውበት አገልግሎት እንዲሁም ምግብ ዝግጅት ናቸው።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
ነሐሴ 4 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
ተለዋጨ ማስታወቂያ
የዘው የ8:00 ሰዓት የነበረን የ12ኛ ክፍሎች ስብሰባ ድንገተኛ ስብሰባ ሰለተጠራን ላልተወሰነ ጊዜ የዛሬው ስብሰባ ተላልፏል። በሌላ ማስታወቂያ እስከሚገለጽ ተጠባበቁ። ላልሰሙት እንዳይሀፉ እና አላሰፈላጊ ወጪ እንዳያወጡ ሼር አድርጉ ተደዋወሉ።
ማስታወቂያ ለ2019 ዓም 12ኛ ክፍል የተዛወራችሁ ተማሪዎች በሙሉ
ሐምሌ 28/11/2018 ዓም ማክሰኞ ዕለት ከሰዓት 8:00 ሰዓት ላይ በ2019 12ኛ ክፍል የተዛወራችሁ ብቻ ትምህርት ቤት ጊቢ እንድትገኙ በጥብቅ አስታውቃለሁ።
ማሳሰቢያ:- በዚህ ቀን ያልተገኘ ተማሪ በ2019 የማይመዘገብ መሆኑ ታውቆ በዕለቱ ሙሉ ዩኒፎርም ለብሳችሁ እንድትገኙ እና ዪኒፎርም ያለበሰ ተማሪ የማናስተናግድ መሆኑን አሰታውቃለሁ ሌሎችም በማጋራት/share/ በማድረግ አስታወቂ።
Repost from Wondo Genet Secondary School
ማስታወቂያ ለ4ኛ ዙር ተፈታኝ ተማሪዎች በሙሉ ሰላም ለእናንተ ይሁን እያልኩኝ መኪናዎችሁ 1:00 መጥተው ሁሉም ተማሪዎች ይሳፈራሉ ተብሎ ተገልጾልናል። ስለዚህ ከ12:50 እስከ 1:00 ብቻ እንድትገኙ አሳስባለሁ።
መረጃውን ለሌሎችም አዳርሱ
መልካም አዳር ይሁንላችሁ ።
ማስታወቂያ ለ5ኛ ዙር ተፈታኝ ተማሪዎች በሙሉ ሰላም ለእናንተ ይሁን እያልኩኝ መኪናዎችሁ 1:00 መጥተው ሁሉም ተማሪዎች ይሳፈራሉ ተብሎ ተገልጾልናል። ስለዚህ ከ12:30 እስከ 1:00 ብቻ ትምህርት ቤት በርላይ እንድትገኙ አሳስባለሁ።
ከኬላ የምትመጡ ግሪኑ ጋር በአንድነት ተሰብስባችሁ እንድትጠብቁ ይሁን።
መረጃውን ለሌሎችም አዳርሱ
መልካም አዳር ይሁንላችሁ ።
ማስታወቂያ ለ4ኛ ዙር ተፈታኝ ተማሪዎች በሙሉ ሰላም ለእናንተ ይሁን እያልኩኝ መኪናዎችሁ 1:00 መጥተው ሁሉም ተማሪዎች ይሳፈራሉ ተብሎ ተገልጾልናል። ስለዚህ ከ12:50 እስከ 1:00 ብቻ እንድትገኙ አሳስባለሁ።
መረጃውን ለሌሎችም አዳርሱ
መልካም አዳር ይሁንላችሁ ።
ማስታወቂያ ለ3ኛ ዙር ተፈታኞች መኪናዎችሁ 1:15 መጥተው 1:30 ሁሉም ተማሪዎች ይሳፈራሉ ተብሎ ተገልጾልናል። ስለዚህ ከ1:15 እስከ 1:30 ብቻ እንድትገኙ አሳስባለሁ።
ማስታወቂያ ለ3ኛ ዙር ተፈታኝ ተማሪዎች በሙሉ እንኳን ለ12ኛ ክፍል የመልቀቂያ ፈተና ቀን በሰላም አደረሳችሁ እያልኩኝ ነገ ረዕቡ ሐምሌ 01/11/2018 መኪና የሚመጣው ከጠዋቱ 12:00 ሰዓት ሲሆን ትምህርት ቤታችን በር ላይ ከ12:00-12:30 ብቻ መገኘት የቻለ ተማሪ ይዘን የምንሄድ ሲሆን አረፍዳችሁ ለሚፈጠረው ችግር ሀላፊነት የማንወስድ መሆኑን በጥብቅ አሳስባለሁ። ከ12:30 በኋላ መኪና የማይቆይ መሆኑ ስለተነገረን በተባለው ሰዓት እንድትገኙ በድጋሜ አሳስባለሁ።
