ch
Feedback
Wondo Genet Secondary School

Wondo Genet Secondary School

前往频道在 Telegram

Educational purpose

显示更多
2 718
订阅者
+224 小时
+287
+7530
帖子存档
photo content

+3
💡English Model Exam 2026

#የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ለመስጠት 667 የፈተና ማዕከላት ተዘጋጁ #የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የዘንድሮውን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና በ667 የፈተና ማዕከላት ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ ነው አለ። #የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ (ዶ/ር) ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን እንደገለጹት÷ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተናን በ97 ዩኒቨርሲቲዎች እና በ570 የክልል ማዕከላት ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ ይገኛል። ከሰኔ 24 እስከ ሐምሌ 17 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚሰጠው ፈተና መደበኛ ተማሪዎችን ጨምሮ በሁሉም ፕሮግራሞች በተፈጥሮ ሳይንስ 306 ሺህ 964 እንዲሁም በማህበራዊ ሳይንስ 257 ሺህ 255 በድምሩ 564 ሺህ 219 ተማሪዎች መመዝገባቸውን ገልጸዋል፡፡ ፈተናውን በሙሉ አቅም በበይነ መረብ ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ ነው ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ÷ በተለያዩ ምክንያቶች ቁጥራቸው አነስተኛ የሆኑ በወረቀት የሚፈተኑ ተማሪዎች እንደሚኖሩም ጠቁመዋል። በየክልሎች እና የፈተና ማዕከላት ያለው አቅም የተለያየ ቢሆንም በርካታ ኮምፒዩተሮች ለፈተና ዝግጁ እየተደረጉ እንደሚገኙ አመልክተዋል። ከባለፈው አርብ ጀምሮ ለተፈታኞች የበይነ መረብ የሙከራ ፈተና መሰጠት መጀመሩን አንስተዋል። ፈተናው በ6 ዙር እንደሚሰጥና በማህበራዊ ሳይንስ በሶስት ዙር በተመሳሳይ በተፈጥሮ ሳይንስ ደግሞ በሶስት ዙር በመሆኑ አንድ ኮምፒዩተር ስድስት ተማሪን ያስተናግዳል ነው ሉት። ተማሪዎች የፈተና ስርዓቱን እንዲለማመዱና ትምህርት ቤቶች እና ወላጆች ለተፈታኝ ተማሪዎች አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርጉም አስገንዝበዋል። (ኤፍ ኤም ሲ) ለተጨማሪ መረጃዎች 🖥 ●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬ https://t.me/moedu123

+7
SIDAMA G12_English Model Exam ANSWER KEY.pdf2.90 KB

Answer key 👇👇👇

PHYSICS Model GR-12 2018 final.pdf8.12 KB

MATHS model 2018.pdf4.15 KB

HISTORY Model Exam 2018.pdf5.45 KB

Garde_12_Biology_Model exam, 2018.pdf5.83 KB

G12 Geography Model Exam2_2018EC.pdf6.75 KB

English GR-12_Model_Exam 2018.pdf9.84 KB

ECONOMICS_grade12_Model_exam-2018.pdf5.66 KB

Chemistry Model EXAM GR-12 2018.pdf5.46 KB

photo content
+6

photo content
+9

የ2018 ትምህርት ዘመን 12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ተፈጣኞች የሚለማመዱበት አድራሻ ይፋ ሆነ። ደጋግሞ መለማመድ የእውቀትን እና የክህሎትን ጉድለት ይሞላል፤ በራስ መተማመንን ያሳድጋል። የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የ2018 ትምህርት ዘመን 12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተናን በበይነ መረብ (CBT) ለመስጠት ዝግጅት እያደረገ ይገኛል፡፡ በመሆኑም ሁሉም ተፈታኞች በተደለደሉበት ክልል ወይም ከተማ አስተዳደር ትይዩ ባለው ማስፈንጠሪያ በመጠቀም USER Name በሚለው ላይ የፈተና አዳራሽ መግቢያ ካርድ ላይ ያለውን አድሚሽን ቁጥር በማስገባት እና Pass word በሚለው ላይ 1234 በማስገባት በዴስክቶፕ ኮምፕዩተር፣ በላፕቶፕ ኮምፕዩተር፣ በታብሌት፣ በስልክና በመሰል የኤልክትሮኒክስ መሣሪያዎች ማንኛውንም ዓይነት ኢንተርኔት አማራጭ በመጠቀም ከግንቦት 07/2018 ዓ/ም ከጥዋቱ 3፡00 ሰዓት ጀምሮ እስከፈተናው ድረስ መለማመመድ ይችላሉ። ተፈታኞች አዲሚሽን ካርድ ከየትምህርት ቤታቸው ማግኘት ይችላሉ። በየጊዜው የተለያዩ የሚለማመዱባቸውን ፈተናዎች በተከታታይ የምንሰጥ ይሆናል። ድልድሉ የተካሄደው የተፈታኞችን ብዛት መሠረት በማድረግ ነው። ስለሆነም መምህራን ፣ የትምህርት ቤት አመራርና ወላጆች ተፈታኞቹ እንዲለማመዱ አስፈላጊውን ድጋፍ ሁሉ እንዲያደርጉ በአክብሮት ጥሪ እናቀርባለን። ለትክክለኛ መረጃ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ማህበራዊ ሚዲያዎችን ይከታተሉ። የፈተና ስርቆትንና ኩረጃን በጋር እንከላከል የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ግንቦት 2018 ዓ/ም አዲስ አባባ - ኢትዮጵያ