fa
Feedback
ዶ/ር ምህረት ደበበ እና ዶ/ር እዮብ ማሞ

ዶ/ር ምህረት ደበበ እና ዶ/ር እዮብ ማሞ

رفتن به کانال در Telegram

👉የዶ/ር ምህረት ደበበ ፣ የዶ/ር እዮብ ማሞ እና የሌሎችም ፦፦፦፦፦፦፦፦ 📖አነቃቂና አስተማሪ የሆኑ ወጎች 👉ስለ አመራር 👉አመለካከት(እይታ) 👉mindset 👉ስለ እድገት.......በስፋት እንዳስሳለን 📚 መፅሐፍት pdf 🎙የመፅሐፍ ትረካ 📖 አስተማሪ የሆኑ ፅሁፎች 👉👉👉contact us @Ay_ayche

نمایش بیشتر
3 916
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
-47 روز
-3330 روز

در حال بارگیری داده...

ابر برچسب‌ها
هیچ داده‌ای
مشکلی وجود دارد؟ لطفاً صفحه را تازه کنید یا با مدیر پشتیبانی ما تماس بگیرید.
اشارات ورودی و خروجی
---
---
---
---
---
---
جذب مشترکین
سپتامبر '26
سپتامبر '26
+19
در 0 کانال‌ها
اوت '26
+70
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '26
+81
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '26
+44
در 1 کانال‌ها
Get PRO
مه '26
+60
در 0 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '26
+66
در 1 کانال‌ها
Get PRO
مارس '26
+93
در 2 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '26
+50
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '26
+60
در 0 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '25
+66
در 0 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '25
+64
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '25
+80
در 0 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '25
+61
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اوت '25
+78
در 1 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '25
+79
در 1 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '25
+100
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مه '25
+86
در 0 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '25
+66
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مارس '25
+94
در 1 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '25
+71
در 1 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '25
+81
در 0 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '24
+121
در 0 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '24
+118
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '24
+114
در 0 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '24
+99
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اوت '24
+111
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '24
+117
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '24
+68
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مه '24
+95
در 0 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '24
+95
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مارس '24
+118
در 0 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '24
+81
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '24
+85
در 0 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '23
+86
در 0 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '23
+88
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '23
+84
در 0 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '23
+81
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اوت '23
+101
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '23
+102
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '23
+106
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مه '23
+101
در 0 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '23
+89
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مارس '23
+101
در 0 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '23
+95
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '23
+147
در 0 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '22
+121
در 0 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '22
+142
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '22
+115
در 0 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '22
+127
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اوت '22
+124
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '22
+127
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '22
+105
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مه '22
+200
در 0 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '22
+155
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مارس '22
+160
در 0 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '22
+73
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '22
+98
در 0 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '21
+67
در 0 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '21
+73
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '21
+134
در 0 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '21
+101
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اوت '21
+95
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '21
+113
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '21
+101
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مه '21
+67
در 0 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '21
+106
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مارس '21
+121
در 0 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '21
+131
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '21
+114
در 0 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '20
+1 043
در 0 کانال‌ها
تاریخ
رشد مشترکین
اشارات
کانال‌ها
13 سپتامبر+1
12 سپتامبر+2
11 سپتامبر+3
10 سپتامبر0
09 سپتامبر+1
08 سپتامبر0
07 سپتامبر+1
06 سپتامبر+2
05 سپتامبر0
04 سپتامبر+1
03 سپتامبر+4
02 سپتامبر+4
01 سپتامبر0
پست‌های کانال
#ደስታ_ባንተ_ይደሰት! በዚህች ምድር ያለ -የሰው ልጅ ሁሉ ለማግኘት የሚጥረው #ደስታ ነው። ደስታንም ለማግኘት ከፈለግክ፣ እርግጠኛ የምትሆንበት አንድ መንገድ አለ። እሱም ሀሳብህን መቆጣጠር ነው። ደስታ ከውጭ ሁኔታ የሚታይ አይደለም። የሚያምር ልብስ ብትለብስ፣ ያማረ ቤት ቢኖርህ፣ አዲስ መኪና ብትገዛ፣ ቆንጆ ፍቅረኛ ብትኖርህ፣ አቋምህ የተስተካከለ ቢሆን... ውስጥህ ሰላም ያለው ሀሳብ ከሌለ ደስተኛ ልትሆን አትችልም። ስለዚህ ደስታ የውስጥ ስሜት እንጂ ከላይ የሚታይ አይደለም። ደስታህን የምታገኘው ሀሳብህን መቆጣጠር ስትችል ነው። 👉 ለሁሉም ነገር ጊዜ እንዳለው ሲገባህ 👉 ትግስት መራራ፣ ፍሬዋ ግን ጣፋጭ እንደሆነ ስታውቅ 👉 ለምትሰራው ስራ ለቤተሰብህ፣ ለጓደኞችህ፣ በዙሪያህ ላሉ ሰዎች ሁሉ ፍቅር ሲኖርህ 👉 አዎንታዊ እና አርቆ አሳቢ ስትሆን ከውጪህ ይልቅ ውስጥህን በአእምሮ እውቀት፣ በልብ ፍቅር ለማሳመር ስትሻ… አንተ ብቻ ሳትሆን ደስታም ባንተ ይደሰታል! join us...      @Ab_book    @Ab_book    @Ab_book

2
የራሳችን ሩጫ እና ግብ ጉዳይ! የራስን ግብ ከሌላው ሰው ግብ ጋር ማስተያየት ኋላ ቀርነትን ያስከትላል! የሌሎች ሰዎች እይታ፣ ፍላጎት፣ የውስጥ ግለትና ሌሎች ወሳኝ ነገሮች ከእኛ እጅግ ያነሱ ሆነው ከተገኙ በዚያ ሰው ገደብ እኛም ተገደብን ማለት ነው፡፡ የራስን ጤንነት ከሌላው ሰው ጤንነት አንጻር መመዘን እንዴት አደገኛ ነገር ነው! አልጋው ላይ ተኝቶ ሞቱን የሚጠብቀውን ሰው አይተን ቆመን መሄዳችንን እንደ ሙሉ ጤንነት ከቆጠርከው አደገኛ ንጽጽር ውስጥ ነው ያለነው (ስለዚያ ሰው የማዘናችንና እኛም ስላለንበት የተሻለ ሁኔታ ሊኖረን የሚገባ ፈጣሪን አመስጋኝነት እንደተጠበቀ ሆኖ)፡፡ የራስን ደረጃ ሌላው ሰው ከደረሰበት ደረጃ አንጻር ብቻ መመዘን ኋላ ቀርነትን ያስከትላል! ስኬታማና መስመር ውስጥ የገባ ሕይወት የመመዘኛችን ሁኔታ አንጻራዊ ሲሆን እጅግ አደገኛ የሆነ ጉዳይ ነው፡፡ የራሴን ደረጃ ከገባኝ ነገርና ካወጣሁት ግብ አንጻር ሳይሆን ሌላው ሰው ካለበት ሁኔታ ጋር ብቻ ካነጻጸርኩት ያለሁበትንና የምሄድበትን የማላውቅ ግራ የተጋባሁ ሰው ነኝ፡፡ ትኩረቴን የሳበው እኔ ወዳየሁትና “መድረስ አለብኝ” ወዳልኩት ከፍታ የመገስገሴ ጉዳይ መሆኑ ቀርቶ ማን ምን ደረጃ ደረሰ የሚለው ጉዳይ ከሆነ ከወዲሁ የተሸነፍኩ ሰው ነኝ፡፡ የሌላውን ሰው ልህቀት ለእኛ እንደመነሳሳሻ እንጂ የወደፊ እምቅ ብቃታችን መመዘኛ አናድርገው፡፡ የሌላውን ሰው ኋላ ቀርነት ለእኛ መማሪያ እንጂ ባለንበት ደረጃ የመርኪያ ምክንያት አናድርገው፡፡  አቻችን ነው ብለን በምናስበው ሰው ወቅታዊ ሁኔታ ላይ ያለን አመለካከት ስላስቀመጥነው ግብና መድረስ ስለምንችልበት ደረጃ ብዙ እንደሚያወራ አንዘንጋ፡፡ የራሳችንን ራእይ፣ ዓላማ፣ ግብና ደረጃ እናውጣና በዚያ ልክ እንሩጥ!!! join us...      @Ab_book    @Ab_book    @Ab_book
465
3
መስቀለኛው መንገድ “መስቀለኛ መንገድ ላይ ደረስኩ፣ መሄድ የምችለው በአንዱ መንገድ ላይ ብቻ ነው፡፡ ቆም ብዬ አሰብኩና ብዙ ሰዎች ያልሄዱበትን መንገድ መረጥኩ፡፡ የታሪኬ ታላቅ ነገር የጀመረው ያን ጊዜ ነበር” - Robert Frost ሁል ጊዜ መስቀለኛ መንገድ በፊትህ ይመጣል፡፡ በፊትህ ከሚጋረጡት መንገዶች መካከል አንዱ ቀላልና ብዙዎች የሄዱበት እንደሆነ ያስታውቃል፡፡ የተመነጠረና የብዙ ሰዎችን ኮቴ የያዘ መንገድ ነው፡፡ ሁለተኛው መንገድ ግን ከዚህ በፊት ብዘዎች እንዳልሄዱበት የሚያሳብቅ ጭር ያለ፣ ገና ያልተመነጠረና ያልተጠረገ መንገድ ነው፡፡ የምትመርጠው መንገድ ወሳኝ ነው፡፡ ብዙዎች የሄዱበትን መንገድ ስትመርጥ ብዙዎች የደረሱበት ፍጻሜ ላይ ትደርሳለህ፡፡ የዚህ ጎዳና ጥቅሙ ከዚህ በፊት ተሞክሮ ያለቀለት የመሆኑና ከስጋት ውጪ የሚመስል መሆኑ ነው፡፡ የዚህ ጎዳና ጉዳቱ ደግሞ ከአንተ ሁኔታ፣ ብቃት፣ ራእይና ከሰባት ቢልየን ሕዝብ ለየት የማለትህ ማንነት አንጻር ሌሎች ልትሄድባቸው ከምትችላቸው አዳዲስ ጎዳናዎች የመግታቱ ጉዳይ ነው፡፡ ብዙዎች ያልሄዱበትን መንገድ ስትሄድ ደግሞ ብዙዎች ያልደረሱበት አዲስ ፍጻሜ ላይ ትደርሳለህ፡፡ ይህኛው ጎዳና ምንም እንኳን ስጋት የሞላበት፣ ዝነኛ ያልሆነና እርግጠኝነት የማጣት ስሜት የሚሰጥ ጎዳና ቢሆንም፣ ለራስህና ለሕብረተሰብህ አዲስን ነገር የምታስተዋውቅበት፣ ከተርታው መንደር የምትወጣበትና ለሰዎች ጥቅም ቦግ ብለህ የምትታይበት (Shine የምታደርግበት) መንገድ ነው፡፡ •  ሌላ የላቀ መንገድ እየታየህ ሁሉም የሄደበትን ተራ መንገድ አትምረጥ፡፡ •  ሌላ የተሻለ ነገር በውስጥህ እያለ የተለመደውን እቅድ አታውጣ፡፡ •  ሌላ የላቀ መልእክት በውስጥህ እያለህ ሁሉም የሚያወራውን ተራ ወሬ አታውራ፡፡ •  አዳዲስ የግኝት እንቁዎች በውስጥህ አምቀህ ይዘህ ምንም ጥረት የማይጠይቀውንና በየመንገዱ የሚገኘውን ጠጠር ስትለቅም አትዋል፡፡ join us...      @Ab_book    @Ab_book    @Ab_book
862
4
#ይገርማል! 🎆 በአንድ ወቅት፤ አንድ እጅግ ሀብታም የሆነ ሰአሊ በአንዲት ትንሽዬ መንደር ውስጥ ይኖር ነበር። እጅግ ማራኪ ስእሎችን በውድ ዋጋ በመሸጥም ነበር የሚተዳደረው። ታዲያ በመንደሯ የሚኖሩ ድሀ ሰዎች እጅግ ይጠሉት እና ስግብግብ እንደሆነ ያሙታል። 🎆 ወደ ቤቱም በመሄድ ''አንተ ብዙ ገንዘብ ያለህ ሰው ነህ። ነገር ግን በመንደሯ ያሉትን ድሆች አትደግፍም። ስጋ የሚሸጠውን ሰው ብትመለከት ያንተን ያህል ሃብታም አይደለም። ነገር ግን ከሚሸጠው ስጋ ላይ ለድሆች ያካፍላል። የመንደሩ ሰዎችም ይወዱታል። እንዲሁም ዳቦ ሻጩን ተመልከት እሱም ድሀ ሲሆን ብዙ ቤተሰቦች አሉት። ነገር ግን ለድሆች በነጻ ዳቦ ይሰጣል። አንተ ለምን በዚህ ልክ ስግብግብ ትሆናለህ?'' አሉት። ሰአሊውም ለወቀሳቸው መልስ ሳይሰጥ ሁሌም በፈገግታ ይመልሳቸው ነበር። 🎆 የመንደሯ ነዋሪዎችም የሰአሊው ፈገግታ ግራ ያጋባቸው ነበር። በዚህም ራስ ወዳድ እና ሀብት በመሰብሰብ ብቻ የተጠመደ ስግብግብ አድርገው ይቆጥሩት ነበር። አንድ ቀንም ሀብታሙ ሰአሊ በጠና ታመመ ነገር ግን አንድም የመንደሯ ኗሪ ሊጠይቀው ወይም ሊረዳው አልመጣም። ስለዚህ ብቻውን የሚኖረው ሰአሊ ህይወቱ ያልፋል። 🎆 ከዚያም በኋላ ስጋ-ሻጩ እና ዳቦ-ጋጋሪው ለመንደሩ ይሰጡት የነበረውን ስጋ እና ዳቦ መስጠት ያቆማሉ። ስለዚህ የመንደሩ ድሆች ለምን እርዳታቸውን እንዳቆሙ በሀዘን ተሞልተው ይጠይቃሉ። 🎆 ሁለቱም ከዚህ በፊት ወር እስከ ወር ለሚሰጧቸው ስጋ እና ዳቦ ህይወቱ ያለፈው ሰአሊ ሰው ይከፍላቸው እንደነበር እንዲሁም አሁን  ያ ሰው ስለሞተ ለስጋም ሆነ ለዳቦ ዋጋ የሚከፍላቸው እንደሌለ ይነግሯቸዋል። በዚህም የመንደሩ ኗሪዎች ይጠሉት እና ስግብግብ እያሉ ያሙት የነበረው ሰአሊ ይረዳቸው እንደነበር ይገነዘባሉ። ☑️ቁምነገሩ~ ሰዎችን በውጫዊ ገጽታቸው እና ስለ እነሱ በሚወራው አሉባልታ ልንገምታቸው አይገባም። እንዲሁም አንዳንድ ሰዎች የሚያደርጉትን መልካም ነገር በግልጽ ማሳየት አይፈልጉም ማለት ክፉ ናቸው ማለት አይደለም። መልካምነት ራስ ጋር የሚቆይ ሰላም ነውና። join us...      @Ab_book    @Ab_book    @Ab_book
1 034
5
#ደስታ_የሚመጣው_ችግሮችን_በመፍታት_ነው በሕይወት ውስጥ ሁልጊዜም ችግሮች አሉ፡፡ አንድ ነገር ለማድረግ ስትሞክር ሌሎች ችግሮች መፈጠራቸው አይቀርም። ለምሳሌ፣ የጤና ችግርህን ስፖርት በመስራት ልትፈታው ስትወስን ጂም በጊዜ ለመድረስ በጊዜ መነሳት፣ በጣም እንዲያልብህ በርትተህ መስራትና ወደ ስራ ስትገባ በመጥፎ ጠረን ቢሮውን እንዳትበክል የግድ መታጠብ ስለሚያስፈልግህ ሌላ አዳዲስ ችግሮች ትፈጥራለህ፡፡ ከሴት ጓደኛህ ጋር በቂ ጊዜ ያለማሳለፍ ችግርህን ለመቅረፍ ማክሰኞ ምሽትን ሁልጊዜ የምትገናኙበት ጊዜ አድርገህ ስትመርጥ ሁለታችሁም እንዳይሰለቻችሁ ለማድረግና አሪፍ ራት መብላት ስላለባችሁ በዚያ ቀን የግድ በቂ ገንዘብ የመፈለግ ችግር ትፈጥራለህ፡፡ ችግሮች ይለዋወጣሉ ወይም ይሻሻላሉ እንጂ አይቆሙም፡፡ ደስታ የሚመጣው ችግሮችን ከመፍታት ነው፡፡ በእዚህ አረፍተ ነገር ውስጥ ቁልፍ የሆነው ቃል “መፍታት” የሚለው ነው፡፡ ችግሮችንህ ችላ ካልክ ወይም ችግሮች እንደሌሉብህ የሚሰማህ ከሆነ፣ ራስህን በጣም አሳዛኝ እያደረግክ ነው፡፡ መፍታት የማትችለው ችግር እንዳለብህ የሚሰማህ ከሆነም አሁንም ራስህን በጣም አሳዛኝ እያደረግክ ነው፡፡ ምክንያቱም የደስታ ሚስጥራዊ ቅመም ያለው ችግሮችን መፍታት ላይ እንጂ ችግሮች የሌሉብህ መሆን ላይ አይደለም፡፡ join us...      @Ab_book    @Ab_book    @Ab_book
1 141
6
#ህልመኛ_እና_እብድ_ሁን! ዴል ካርኒጌ እንዳለው ''ለሰው ልጅ አስቸጋሪ ወይም መጥፎ ጊዜ የሚባለው፣ አንድ ሰው የተሻለ አቅም እንዳለው አውቆ ነገር ግን አጠቃቀሙን ሳያውቅ ሲቀር ነው። '' ይሄን ከራስህ ህይወት ጋር አያይዘህ አስበው... የህይወትህ የመጨረሻ ቀን ላይ እንዳለህ ሲሰማህ እና ደግሞ ማድረግ የነበረብህን አሁን ልታደርገው እንደማትችል ስታውቅ። ያኔ ልታደርገው ያልቻልክበት ምክንያት ጓደኞችህ ሀሳብህን ሰምተው እንደ #እብድ ስለቆጠሩህ ይሆን? ቤተሰቦችህን ህልምህን አውቀው ''እሺ ህልመኛው ' እያሉ #ስላፌዙብህ ይሆን? የህይወትህ የመጨረሻ ቀን ላይ ይሄ ሁሉ የሰዎች ማጣጣል ምንም ሆኖ ቁጭት ከሚሆንብህ በፊት፣ አሁን #እብድ እና #ህልመኛ ተብለህ ውስጥህ ያለውን ልዩ አቅም እንዴት መጠቀም እንዳለብህ ብታውቅ ስኬታማ ትሆናለህ። አስታውስ የሚወቅሱህ፣ አይሆንም የሚሉህ ሰዎች እንደማይሆንልህ የሚያሳይ ማስረጃ የላቸውም። ማስፈራሪያቸውን ከምትሰማ ተግባራዊ ሆነህ ውጤትህን እንድታይ እመክርሃለሁ። ምንጊዜም የተሻለ የህይወት ደረጃን ስትመለከት እንዲህ አይነቶችን የፈተና መንገዶች ማቋረጥ ግድ ይልሃል። join us...      @Ab_book    @Ab_book    @Ab_book
1 290
7
በጎ አድራጎት የሕይወት ዘይቤ ሲሆን! አንዲት ሴት በመንገድ ላይ ተቀምጦ እንቁላል የሚሸጥን ሰው አገኘችና፣ “ዋጋው ስንት ነው አለችው፡፡ አንዱን በ50 ሳንቲም (የ Dollar ግማሽ) ነው የምሸጠው” ብሎ መለሰላት፡፡ እሷም፣ “ስድስቱን እንቁላል በሁለት Dollar ከሸጥክ ልግዛህ፣ አለዚያ ትቼህ መሄዴ ነው” አለችው፡፡ የመንገድ ላይ ሻጪውም፣ “ከነጋ ምንም ስላልሸጥኩኝና ገንዘቡን ለህልውናዬ ስለምፈልገው በፈለግሺው ዋጋ ግዢኝ” አላት፡፡ ሁለት Dollar ከፍላ ስድስቱን እንቁላል ይዛ በአሸናፊነት ስሜት ሄደች፡፡ ይህች ሴት በዚያው ቀን ከሰዓት በኋላ ከአንድ ጓደኛዋ ጋር አንድ ያማረ ሬስቶራንት ሄዱና ምግብ በማዘዝ የተወሰነውን በልተው ብዙ ተረፋቸው፡፡ በመጨረሻም፣ ሂሳብ ሲመጣ ዋጋው 150 Dollar ነበር፡፡ ሴትዬዋም 200 Dollar ሰጥታው የሬስቶራንቱን ባለቤት መልሱን ለቲፕ እንዲያስቀረው ነገረችው፡፡ የዚህ ታሪክ ጸሃፊ እንዲህ ሲል ይጠይቃል፡ “ከችግረኞችና አቅም ከሌላቸው ስንገዛ የበላይነትን የምናሳየው፣ ጨከን የምንለውና እስከመጨረሻዋ ሳንቲም ድረስ የምንከራከረው፣ የእኛ ልግስና ለማያስፈልጋቸው ደግሞ ካለልክ ልግስናችንን ለማሳየት የምንሞክረውና ብዙ ገንዘብ የምንረጨው ለምንድን ነው?” ጸሃፊው፣ ከዚህች ሴት በተቃራኒ፣ አንድን ነገር ከአንድ ችግረኛ ሻጭ ሲገዛ ከተጠየቀው ዋጋ በላይ የከፈለን ሰው አጭር ታሪክም ያጋራል፡፡ ልጆቹ ያደረገውን አይተው፣ “አባ፣ ለምንድን ከተጠየከው መጠን በላይ የከፈልከው?” ብለው ሲጠይቁት፣ “ይህ አይነቱ በጎ አድራጎት የሕይወት ዘይቤዬ ነው” ብሎ መለሰላቸው፡፡ በጎ አድራጎት የታይታ ሳይሆን የሕይወት ዘይቤ ሲሆን! join us...      @Ab_book    @Ab_book    @Ab_book
1 199
8
“በነጻ የሚባል ነገር የለም”! ምንም እንኳን አንዳንድ ነገሮችን እንዲሁ በነጻ ብታገኙም ወይም ደግሞ ያገኛችሁ ቢመስላችሁም፣ አጠቃላይ የሕይወታችንን ሂደት ስንመለከተው፣ በነጻ የምናገኛቸው ነገሮች እንደሌሉ እንደርስበታለን፡፡ ማንኛውም ጥራት ያለው ነገር የሆነ ነገር ያስከፍላል፡፡ ማግኘት የምንፈልገውን ነገር በነጻ ስንጠብቅ ባዶ እጃችንን የመቅረታችን እድል የሰፋ ነው፡፡ ማግኘት ለፈለግነው የከበረ ነገር ርካሽ ስንከፍል ደግሞ ርካሽ ነገር የማግኘታችን ሁኔታ የጎላ ነው፡፡ ማግኘት ለፈለግነው መልካም ነገር የሚመጥን ነገር ለመክፈል ዘግጁ ስንሆን ግን አስገራሚ አለም ውስጥ እንገባለን፡፡ ማንኛውን ጠቃሚ ነገር በነጻ ካገኛችሁት . . . 1.  የበለጠ ስላልተሰጣችሁ ከመነጫነጭ ራሳችሁን ጠብቁ፡፡ 2.  በነጻ የሰጧችሁን ባለማመስገን ተጠቅሞ ዘወር ከማለት ተጠበቁ፡፡ 3.  በነጻ ስለተሰጣችሁ አመስጋኝ መሆንን ልመዱ፡፡ ማንኛውንም ጠቃሚ ነገር በነጻ ካላገኛችሁት . . .  1.  ለምን በነጻ እንዳልተሰጣችሁ ከመነጫነጭና ሰዎች ራስ-ወዳድ እንደሆኑ በማሰብ ከመውቀስ ተጠበቁ፡፡ 2.  የሚከፈል እንደሌላችሁ በማሰብና እድላችሁን በማማረር ባዶ እጅን ከመቀመጥ ተጠበቁ፡፡ 3.  በተቻላችሁ መጠን መንገድ ፈልጋችሁ የሚከፈለውን ከፍላችሁ ጠቃሚ ነገሮችን በእጃችሁ ማስገባት ላይ ስሩ፡፡ ደግሜ ላስታውሳችሁ! በዚህች ምድር ላይ ነጻ የሚባል ነገር የለም! •  ምንም ነገር ሰዎች በነጻ ሊሰጧችሁ እንደሚገባ አታስቡ፡፡ በዚያ ምትክ፣ ሰርታችሁ ለማግኘት ራሳችሁን አዘጋጁ፡፡ •  እናንተ ጋር ያለውን መልካም ነገር ሰዎች እንዲሁ በነጻ ይቀበሉታል ብላችሁ አታስቡ፡፡ በዚያ ፈንታ፣ ተቀባይነትን ለማግኘት መከፈል የሚገባውን የታማኝነትን ዋጋ ክፈሉ፡፡ •  ሰዎች እንዲሁ ሊያምኑኝ ይገባል ብላችሁ አታስቡ፡፡ ይልቁንስ፣ ሰዎች እንዲያምኗችሁ የሚያስችል የማያቋርጥ ታማኝነትን የማዳበር ነገር ላይ ስሩ፡፡  ማንኛውንም ጠቃሚ ነገር ለማግኘት ዋጋ መክፈል እንዳለባችሁ ስታምኑና ለዚያም ስትዘጋጁ፣ አስገራሚ አለም ውስጥ ትገባላችሁ፡፡ ይህ አለም፣ ብርቱዎች፣ ትጉዎችና የዲሲፕሊን ሰዎች ያሉበት አለም ነው፡፡ join us...      @Ab_book    @Ab_book    @Ab_book
1 259
9
H
398
10
https://t.me/SkillMoney01_bot/earn?startapp=ref_73FDB385
403
11
በዜሮ የተባዛው አገልግሎት! አንድ ንጉስ አስር አመት ሙሉ በታማኝነት ያገለገለው አገልጋዩ እንዲት ስህተት ስለሰራ ብቻ ቅጣትን አስተላለፈበት፡፡ በንጉሱ ሕግ መሰረት ማንኛውም ስህተት የሰራ አገልጋይ በኃይለኛነታቸውና በተናካሽነታቸው የታወቁት የንጉሱ ውሾች ወደሚኖሩበት ግቢ ለቅጣት ታልፎ ይሰጣል፡፡ ይህንን የንጉሱን ውሳኔ የሰማው ታማኝ አገልጋይ በሁኔታው በጣም አዘነ፡፡ እሱን ያሳዘነው የተላለፈው ቅጣት ሳይሆን፣ ለአስር አመታት ካለምንም ስህተት አገልግሎ፣ አንዲት ስህተት ብቻ ስለተገኘችበት የንጉሱ መጨከን ነው፡፡ ይህ አገልጋይ ቁጭ ብሎ፣ “ይህንን ቅጣት አስቀረሁትም፣ አላስቀረሁት ንጉሱ ግን ይህንን ጥሩ ያልሆነ ልምምድ የሚያቆምበትን አንዲት ትምህርት ባስተምረው ደስ ይለኛል” ብሎ አሰበና አንድ ብልሃት መጣለት፡፡ ንጉሱንም፣ “ቅጣቱን እቀበላለሁ፣ ቅጣቱ ተግባራዊ ከመሆኑ በፊት ግን አስር ቀን ይሰጠኝና ከዚያ በኋላ በፈቃዴ ለቅጣቱ እመጣለሁ” ብሎ ጠየቀው፡፡ ንጉሱም ፈቀደለት፡፡ በእነዚህ አስር ቀናት ለውሾቹ የሚሆንን ምግብ አዘጋጅቶ እነሱ ያሉበት ግቢ በመሄድና ቀስ ብሎ በመቅረብ እያበላቸው፣ እየተንከባከባቸውና እያሻሻቸው በሚገባ ካገለገላቸው በኋላ በአስረኛው ቀን ወደ ንጉሱ መጣ፡፡ ፍርዱ አልቀረለትም ነበረና ወደውሾቹ ግቢ እንዲጣል ትዝዛዝ ተላለፈበትና ተጣለ፡፡ ውሾቹ ለአስር ቀን የተንከባከባቸውንና ያገለገላቸውን ይህንን ሰው ምንም ነገር አላደረጉትም ነበር፡፡ ንጉሱም ለመጀመሪያ ጊዜ የተከሰተ ሁኔታ በመሆኑ ተገርሞ አስጠራውና የተፈጠረውን ጠየቀው፡፡ አገልጋዮም፣ “ንጉስ ሆይ፣ እርሶን አስር አመት በታማኝነት አገልግዬ አንዲት ጥፋት ስለተገኘብኝ ብቻ ያ ሁሉ ታማኝነቴና አገልግሎቴ ተረሳና ምህረትም አላገኘሁም፡፡ እነዚህ ውሾች ግን ለአስር ቀናት ብቻ ስላገለገልኳቸው ምንም እንኳን ጥፋተኛ ሆኜ ለእነሱ ታልፌ ብሰጥም ያንን አገልግሎቴን ባለመርሳት ምንም አላደረጉኝም” አለው ይባላል፡፡ ንጉሱ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ይህንን ባህሪውን ለማረም ክፍት ወደመሆን እንደመጣ ይነገራል፡፡ ሰዎች ያሳዩንን የብዙ ዓመታት ታማኝነትና አገልግሎት በአንዲት ስህተት ምክንያት በዜሮ አናባዛው፡፡ ይቅርታን እንልመድ! ለሰዎች ሁለተኛ እድልን መስጠትን እንልመድ! ውለታ ቢሶች አንሁን! join us...      @Ab_book    @Ab_book    @Ab_book
1 624
12
#ፍቅር_ተስፋ_አይቆርጥም "በዓለም ውስጥ ከእውነተኛ የፍቅር ኃይል የበለጠ ኃያል የለም። ፍቅር በስርቅርቅ ዜማ ብዙ ተዚሞለታል። በሚያማልል ድርሰት ብዙ ተፅፎለታል። ጨካኞችን ሳይቀር በኃይሉ አንበርክኳል። ይህ እውነተኛው የፍቅር ኃይል የሚገኘው ደግሞ ከራስ ወዳድነት ነፃ በሆነ አስተሳሰብ ተግባር ውስጥ ነው። ፍቅር የተፈጥሮ ጉዳይ ብቻ አይደለም። ይልቁንም ከፍተኛ ትዕግስትን፣ ትህትናን፣ ትኩረትን፣ እምነትንና እንክብካቤን ይጠይቃል። ፍቅር ስሜት ሳይሆን ተግባር ነው። በሕይወታችን ውስጥ በጣም አስፈላጊው ነገር ፍቅርን በተግባር እንዴት መስጠት እንደሚቻል መማር እና ወደ ውስጣችን እንዲገባ መፍቀድ ነው። ፍቅር ምንም አይነት እንቅፋት ቢፈጠር መሰናክሎችን እየዘለለ ወደ መድረሻው በተስፋ ይዘልቃል እንጂ ተስፋ አይቆርጥም።" #ከስሙር_መጽሐፍ_የተቀነጨበ join us...      @Ab_book    @Ab_book    @Ab_book
1 464
13
#ድረሱልኝ! 📗 አንድ አባት ልጁን እንዲህ ሲል አዘዛት ''ልጄ ዛሬ ደስ ስላለኝ ድግስ አዘጋጂ፤ ወዳጅ ጎረቤቶቻችን ዘመዶቻችንን ሁሉ ጥሪያቸው፤ እኔ ከስራ ስመለስ አብረን እንሆናለን እስከዛ ከእነሱ ጋር ተደሰቺ '' በማለት ወደ ስራው ሄደ። ብልሁዋ ልጅም ከቤት ወጣችና እንዲህ ስትል ጩኸት አሰማች፡፡ ''እባካችሁ እርዱን ቤታችን ውስጥ እሳት ነዷል አባቴን ከእሳቱ አውጡት እባካችሁ።'' ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ዘመድ እና ጎረቤት የሆኑ ሰዎች መጡ። ነገር ግን የድረሱልን ጥሪዋን እንዳልሰሙ ሆነው አለፉ። ነገር ግን የማታውቃቸው አንዳንድ ሰዎች የድረሱልኝ ጥሪዋን ሰምተው አባቷን ለማዳን ወደ ቤቱ ዘለው ገቡ። ያጋጠማቸው ግን ባማረ ሁኔታ የተዘጋጀ መብል እና መጠጥ ነበር። ከዛም እየበሉ፣ እየጠጡ፣ እየተጨዋወቱ አባቷ ደረሰ። ባየው ነገር ግራ በመጋባትም እንዲህ ሲል ጠየቃት ''ልጄ እኒህን ሰዎች ብዙም አላውቃቸውም፤ ዘመዶቻችን እና ጎረቤቶቻችን የታሉ?'' ሲል ጠየቃት... ብልህ የሆነችው ልጅም ያደረገችውን ከነገረችው በኋላ ''ሊደርሱልህ አልመጡም'' አለችው። አባትም በልጁ አድራጎት እየተደነቀ ሰፈሩ ውስጥ ብዙም ከማያውቃቸው ሰዎች ጋር በመቀላቀል ጥሩ ጊዜ አሳለፈ። ☑️ ቁምነገሩ~ አንዳንዴ ዘመዶቼ ናቸው ወዳጆቼ ናቸው የምትላቸው ሰዎች በችግርህ ጊዜ እንደማይደርሱ ማወቅ አለብህ። እንዲሁም እንብዛም የማታውቃቸው ሰዎች ለችግርህ ጊዜ ደራሽ ሆነው ታገኛቸዋለህ። ስለዚህ በዙሪያህ ላሉ ሰዎች ሁሉ ክብር ይኑርህ። እንዲሁም አንድ የመጽሐፍ ቅዱስ ነገርን አስብ ''ትንሽ ቁስል ለራስህ ስጥና ወዳጅ እና ጠላትህን ለይ'' ሁሌ ብሉልኝ ጠጡልኝ የምትል ከሆነ ወዳጅህም፣ ጠላትህ በፈገግታ ወደ አንተ ይቀርባሉ፤ ''ድረሱልኝ!'' ስትል የደረሰልህ እሱ በትክክል ወዳጅህ እንደሆነ እወቅ። join us...      @Ab_book    @Ab_book    @Ab_book
1 402
14
ጽንአት!!! “አንድ ሰው የሚያልቅለት ሲሸነፍ አይደለም፤ የሚያልቅለት በበቃኝ ሲያቆም ነው” - Richard M. Nixon በሕወትህ በአንድ ባመንክበትና ትክክል በሆነ ዓላማ እስከመጨረሻው ከመጽናት ውጪ ምንም ቁም ነገር ልታከናውን አትችልም፡፡ ዛሬ ይህንና ያንን እየጀመርክ እስከጥጉ ሳታደርሳቸው ነገ ደግሞ ወደሌላ ነገር ዘወር የማለት ለማድ ካለህ በተቻለህ ፍጥነት ይህንን ዘይቤ መቀየር እንዳለብህ ትመከራለህ፡፡ አብዛኛውን ጊዜ አንድን የጀመርነውን ነገር እስከጥጉ የማንወስድበት ዋነኛ ምክንያት ስንወድቅ ወይም ያልተሳካልን ሲመስለን ነው፡፡ ሆኖም፣ ውድቀት፣ አለመሳካት፣ እንቅፋትና የመሳሰሉት ሁኔታዎች በማንኛውም አንድን መልካም አላማ ይዞ በሚራመድ ሰው ሕይወት ውስጥ የማይቀሩ ሂደቶች ናቸው፡፡ ስለዚህም፣ አንደኛችንን ውድቀትን አያያዝ ብልሃት ማዳበር አስፈላጊ ነው፡፡ ሲወድቁ መነሳት በጽንአቱ የታወቀ ሰው ለወደቀበት ለእያንዳንዱ ክስተት መነሳትን አስመዝግቦ ወደ ፊት የሚራመድ ሰው ነው፡፡ መሳሳት፣ መውደቅ፣ መክሰር፣ ግብን አለመምታትና የመሳሰሉት ብዙዎችን ኃያላን የጣሉ ሁኔታዎች ለእሱ የእድገት ምክንያቶች እንጂ የተስፋ መቁረጥ ምንጮች አይደሉም፡፡ ውድቀትን እንደ አንድ ብቸኛ ክስተት ማየት ወድቀው የሚቀሩ ሰዎች ሲወድቁ ውዳቂ ነኝ ብለው የሚያስቡ ሰዎች ናቸው፡፡ በተቃራኒው ስኬታማ ሰዎች አንድ ውድቀት የእነሱን ማንነት እንዲወስን አይፈቅዱም፡፡ ውድቀትን እንደ አንድ ብቸኛ ክስተትና እንደ ትምህርት እድል ነው የሚቆጥሩት፡፡ አደራረግን መቀየር ስኬታማ ሰዎች ነገሮችን በአንድ መልኩ ሞክረው አያቆሙም፡፡ ያልተሳካበትን መንገድ በመተው ሁኔታውን በሌላ መልኩ ይቀርቡታል፡፡ ለማከናወን በአይነ-ህሊናቸው ላዩት ነገር አንዱ መንገድ ካልተሳካ ሌላ መንገድ እንዳለው ጽኑ እምነት አላቸው፡፡ ሃላፊነትን መውሰድ ተሸናፊ ሰዎች ለተከሰተው ስህተት የሚወቀስ ሰው ይፈልጋሉ፡፡ በአንጻሩ ስኬታማ ሰዎች ለሰሩት ስህተት ሃላፊነትን የሚወስዱና የተሻለ መንገድን ለመፈለግ የሚነሱ ሰዎች ናቸው፡፡ አንዱ ሌሎችን በመውቀስ ሲረካና ሲያቆም፣ ሌላኛው ሃላፊነትን በመውሰድ መፍትሄ በማግኘት ይረካል፤ ወደ ፊትም ዘልቆ ይሄዳል፡፡ በውስጥ ላይ ማተኮር አሸናፊ ሰዎች ወሳኙ ነገር በዙሪያቸው የተከናወነው ሳይሆን በውስጣቸው የተከናወነው እንደሆነ ጠንቅቀው ያውቃሉ፡፡ በእነርሱ ዙሪያም ሆነ በእነርሱ ላይ የሆነው ነገር ውስጣቸውን እስካልነካው ድረስ ምንም እንደማይሆኑ ያውቃሉ፡፡ የደረሰባቸው ማንኛውም አስከፊ ሁኔታ በውስጣቸው ያለውን ጽኑ እምነት ካልነካውና ትክክለኛውን ምላሽ መስጠትን ከለመዱ ወደግብ የመድረሳቸው አሸናፊነት ዘላቂነት ይኖረዋል፡፡ በርታ !!! በርቺ !!! join us...      @Ab_book    @Ab_book    @Ab_book
1 453
15
#ደስታ_የሚመጣው_ችግሮችን_በመፍታት_ነው በሕይወት ውስጥ ሁልጊዜም ችግሮች አሉ፡፡ አንድ ነገር ለማድረግ ስትሞክር ሌሎች ችግሮች መፈጠራቸው አይቀርም። ለምሳሌ፣ የጤና ችግርህን ስፖርት በመስራት ልትፈታው ስትወስን ጂም በጊዜ ለመድረስ በጊዜ መነሳት፣ በጣም እንዲያልብህ በርትተህ መስራትና ወደ ስራ ስትገባ በመጥፎ ጠረን ቢሮውን እንዳትበክል የግድ መታጠብ ስለሚያስፈልግህ ሌላ አዳዲስ ችግሮች ትፈጥራለህ፡፡ ከሴት ጓደኛህ ጋር በቂ ጊዜ ያለማሳለፍ ችግርህን ለመቅረፍ ማክሰኞ ምሽትን ሁልጊዜ የምትገናኙበት ጊዜ አድርገህ ስትመርጥ ሁለታችሁም እንዳይሰለቻችሁ ለማድረግና አሪፍ ራት መብላት ስላለባችሁ በዚያ ቀን የግድ በቂ ገንዘብ የመፈለግ ችግር ትፈጥራለህ፡፡ ችግሮች ይለዋወጣሉ ወይም ይሻሻላሉ እንጂ አይቆሙም፡፡ ደስታ የሚመጣው ችግሮችን ከመፍታት ነው፡፡ በእዚህ አረፍተ ነገር ውስጥ ቁልፍ የሆነው ቃል “መፍታት” የሚለው ነው፡፡ ችግሮችንህ ችላ ካልክ ወይም ችግሮች እንደሌሉብህ የሚሰማህ ከሆነ፣ ራስህን በጣም አሳዛኝ እያደረግክ ነው፡፡ መፍታት የማትችለው ችግር እንዳለብህ የሚሰማህ ከሆነም አሁንም ራስህን በጣም አሳዛኝ እያደረግክ ነው፡፡ ምክንያቱም የደስታ ሚስጥራዊ ቅመም ያለው ችግሮችን መፍታት ላይ እንጂ ችግሮች የሌሉብህ መሆን ላይ አይደለም፡፡ join us...      @Ab_book    @Ab_book    @Ab_book
1 318
16
የዓላማና የተስፋ ግንኙነት  በአንድ የማጎሪያ እስር ቤት ውስጥ በመቶዎች የሚቆጠሩ ታራሚዎች ነበሩ፡፡ እነዚህ ታራሚዎች በቂ የሆነና የተሟላ የምግብ አቅርቦት ነበራቸው፡፡ ከተወሰነ የማረሚያ ቤት ቆይታቸው በኋላ እርስ በርሳቸው ስለተላመዱ በተለያዩ ጨዋታዎች እየተደሰቱና አንዳንድ ሞያ ነክ ነገሮችንም እየሰሩ መረጋጋት ጀምረዋል፡፡ ብዙም ሳይቆዩ ግን ሁሉንም የተስፋ መቁረጥ ስሜት ተጫጫናቸው፡፡ በማረሚያ ቤቱ ውስጥ ተስፈኛ ሆነው የመቆየት አቅማቸውንም አጡ፡፡ የሆነው ነገር ይህ ነው፡፡ አንድ ቀን ጠዋት ሲነሱ በማረሚያ ቤቱ ግቢ አንድ ጥግ ላይ የተከመሩ አሸዋ የሞላባቸው ጆንያዎች ነበሩና እነዚህን ጆንያዎች ካሉበት በማንሳት ወደሌላው የማረሚያ ቤቱ ግቢ ጥግ እንዲወስዱና እንዲከምሯቸው ተነገራቸው፡፡ ሁሉም ታራሚዎች በመነሳሳት ያንን ሲያደርጉ ዋሉ፡፡ ከዚያም ወደማምሻው ላይ ጠዋት ወስደው የከመሩትን የጆንያ አሸዋ ክምር ወደ ነበረበት እንዲመልሱ ታዘዙና ይህ ስራ በየቀኑ እንደሚቀጥል ተነገራቸው፡፡  እነዚህ ታራሚች በተወካያቸው በኩል አሸዋ የሞላባቸው ጆንያዎች ወዲያና ወዲህ የሚመላለሱበት ዋና ዓላማ ምን እንደሆነ ሲጠይቁ የተሰጣቸው መልስ ምንም ዓላማ የሌለው ተግባር እንደሆነና አርፈው እንዲታዘዙ ተነገራቸው፡፡ በዚህ ጊዜ ነበር ስሜታቸው በጣም የወረደው፡፡ ምንም ዓላማ የሌለውን ተግባር ሲደጋግሙ መኖር ተስፋ ያስቆርጣል፡፡  ምናልባት ሁል ጊዜ ተስፋ መቁረጥ የሚጫጫነን የመኖራችንን ዓላማና ትርጉም እንዲሁም በየቀኑ የምናደርጋቸውን ነገሮች ለምን እንደምናደርጋቸው ዓላማቸውን በሚገባ ስላላወቅነው ይሆን? join us...    @Ab_book    @Ab_book    @Ab_book
1 361
17
#ውድቀትን_አትፍሩ "በፕላኔታችን ውስጥ ሁለቱንም እጆቹን በኪሱ ውስጥ ከትቶ የስኬት መሰላልን የወጣ አንዳች ሰው የለም። ስኬት በአብዛኛው ጊዜ የምትመጣው በሥራ ተወጥረው ትዝ እንኳን ወደማትላቸው ሰዎች ነው።       ፈጣሪ ሕይወትን በስጦታ መልክ ሰጥቶናል፤ የተመቻቸና በስኬት የታጀበ  ሕይወት መኖርን ግን እኛ ለራሳችን የምንሰጠው ልዩ ስጦታ ነው። ምንጊዜም አንድ እርምጃ ወደፊት ለመራመድ ጉዞ ስንጀምር ጉዟችን የሚፈታተን አንድ እንቅፋት ይኖራል። እንቅፋቱን ፈርተን ጉዟችን ከገታን የተለየ ነገር ለማየት ምንም አይነት ዕድል አይኖረንም። ህልማችን እውን ለማድረግ የሚገድበን ትልቁ መሰናክል ቢኖር ዛሬ ላይ የከበበን የስጋት ቆፈን ነው። ውድቀትን አትፍሩ፤ ውድቀትን ለመደበቅ ጊዜን አታባክኑ፤ ከውድቀት መማርና ወደቀጣዩ የሕይወት ምህዋር መሸጋገር ስኬታማነትን ያፋጥናል። ውድቀትን የስኬት ጠላት አድርገን ካሰብን መቼም ቢሆን ስኬታማ አንሆንም።        ብዙ ጊዜ ታላላቅ ስኬቶች በምቾት ታጅበን የምናሳካቸው አይደሉም፤ ራሳችን በብዙ ውጣ ውረድ አሳልፈንና ምቾት አልባ በማድረግ እንጂ።" #ከስሙር_መጽሐፍ የተወሰደ join us...    @Ab_book    @Ab_book    @Ab_book
1 275
18
እረፍት ከሚያሳጡን ነገሮች አንዱ! እረፍት ከሚነሱን ነገሮች አንዱ፣ የእኛ ያልሆነውን ነገር የእኛ ለማድረግ የምናደርገው ከንቱ ትግል ነው፡፡ በአካባቢያችን ቁጥራቸው ጥቂት ያልሆኑ ሰዎች የእነሱ ለመሆን ያልፈለጉ ሰዎችን የእነሱ ለማድረግ ሲታገሉ ራሳቸውን ያገኙታል፡፡ ይህ ደግሞ እረፍት የሚያሳጣ ጉዳይ ነው፡፡ ሰዎች ከእኛ ጋር ሊኖራቸው የሚፈልጉትን የግንኙነት አይነት የመወሰን መብት አላቸው፡፡ ስለሆነም እነዚህ ሰዎች የግድ የእኛ ጓደኞች፣ አጋሮች፣ ፍቅረኞች . . . እንዲሆኑ ስለፈለግን ብቻ እንደዚያ የመሆን ፍላጎቱ ይኖራቸዋል ማለት አይደለም፡፡ ከማሕበራዊ ግንኙነት በተጨማሪ ለጊዜውም ሆነ እስከወዲያኛው በፍጹም የእኛ ሊሆኑ የማይችሉ ሁኔታዎችንም ሆነ ነገሮችን የእኛ ለማድረግ መታገል ትኩረታችንንና አቅማችንን ማድረግ ከምንችለው ላይ በማንሳት በከንቱ እንድንባክን በማድረግ ሰላም ያሳጣናል፡፡ በሰላም ለመኖር መለማመድ የምትችሏቸው ብዙ መልካም ልምምዶች የመኖራቸው እውነታ እንደተጠበቀ ሆኖ፣ ለዛሬው ግን ይህንን ሚዛናዊና አረጋጊ አመለካከት ላቀብላችሁ፡፡ •  የእናንተ በሆነውና የእናንተ ባልሆነ ሰውም ሆነ ሁኔታ መካከል ለመለየት ሞክሩ፡፡ •  ምንም እንኳን አሁን የእናንተ ባይሆንም ወደፊት ግን የእናንተ ሊሆን የሚችለበት ሁኔታ እንደሚፈጠር ያመናችሁበት ሰውም ሆነ ሁኔታ ካለ ሂደቱን በተረጋጋና ጊዜውን በጠበቀ መልኩ ማድረግን ተለማመዱ ፡፡ •  ፈጽሞ የእናንተ ሊሆን ከማይችለው ሰውም ሆነ ሁኔታ ላይ አይናችሁን መለስ፣ ሃሳባችሁን ሰብሰብ፣ ስሜታችሁን ደግሞ ረገብ ማድረግን ተማሩ፡፡ •  የእናንተ በሆነውና እጃችሁ በገባው ሰውም ሆነ ሁኔታ ላይ ሙሉ ትኩረታችሁን በማድረግ እዚያ ላይ መስራትና ደስተኛ መሆንን ልመዱ፡፡ join us...    @Ab_book    @Ab_book    @Ab_book
1 277
19
ሁለቱ የችግር ቀን ስህተቶች! ሁላችንም ቢሆን እንደማንኛውም ሰው በጣም አስቸጋሪ በሆነና እጅግ በሚሞግተን ሁኔታ ውስጥ እናልፋለን፡፡ ምናልባት በእድሜያችሁ ገና ወጣት ከሆናችሁና ይህች አለም ለሁላችንም ጊዜዋን እየጠበቀች የምታቀብለንን የሕይወት ውጣውረድ ብዙም ካልቀመሳችሁ፣ በሰው ጥላ ስር ከመኖር ወጣ ብላችሁ የራሳችሁን ውሳኔ እየወሰናችሁ የራሳችሁን ኑሮ መምራት ስትጀምሩ ትደርሱበታላችሁ፡፡ በአሁን ጊዜ ከባድ በሆነ ሁኔታው ውስጥ በማለፍ ላይ ካላችሁ፣ እነዚህን ሁለት የችግር ቀን ስህተቶች ከመስራት ራሳችሁን እንድትጠብቁ ልምከራችሁ፡፡ የመጀመሪያው ስህተት አሁን ያለንበት አስቸጋሪ ሁኔታ በእኛ ላይ ብቻ እንደደረሰ ወይም የእኛ ሁኔታ ከሌለው ለየት ያለና የከፋ እንደሆነ ማሰብ ነው፡፡ አንድን ነገር አንዘንጋ፣ አሁን እኛ በምናልፍበት አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ በሚልየን የሚቆጠሩ ሰዎች ከዚህ በፊት አልፈውበታ፣ በማለፍ ላይ ናቸው፣ ወደፊትም ያልፋሉ፡፡ አንዳንዶች ከዚህ ችግር ባነሰ ችግር ደክመው ሲወድቁ፣ ሌሎቹ ደግሞ ከዚህ ችግር እጅግ በገዘፈ ሁኔታ ውስጥ አልፈው እንኳን በብርታት አሸንፈው ይሄዳሉ፡፡ ሁለተኛው ስህተት አሁን ያለንበት አስቸጋሪ ሁኔታ በቶሎ የማይበርድ፣ የማያቆምና ረጅም ጊዜ የሚቆይ እንደሆነ የማሰብ ስህተት ነው፡፡ በአንድ አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ስናልፍ ጊዜው ረጅም እንደሆነ ይሰማናል፡፡ ይህ የተፈጥሮ ሕግና የሰው ባህሪ ነው፡፡ በሌላ አገላለጽ የሚጣፍጥ ነገር ቶሎ ያለቀ ይመስላል፡፡ የሚመር ነገር ደግሞ ቶሎ ያለቀ አይመስልም፡፡ ስለሆነም የምታልፉበት አስቸጋሪ ሁኔታ ረጅምና የማያልቅ እንደሆነ ከማሰብ መለስ በሉና፣ “ይህም ሁኔታ ያልፋል” የሚልን ተስፋ በመያዝ ወደፊት ተራመዱ፡፡  የችግሩን ክብደትና የጊዜውን ርዝመት በማሰላሰል መጨናነቁን ቀነስ አድርጉትና “አልፈዋለሁ!”፣ “አሳልፈዋለሁ!” ማለትን ልመዱ፡፡   join us...    @Ab_book    @Ab_book    @Ab_book
1 279
20
#ህልመኛ_እና_እብድ_ሁን! ዴል ካርኒጌ እንዳለው ''ለሰው ልጅ አስቸጋሪ ወይም መጥፎ ጊዜ የሚባለው፣ አንድ ሰው የተሻለ አቅም እንዳለው አውቆ ነገር ግን አጠቃቀሙን ሳያውቅ ሲቀር ነው። '' ይሄን ከራስህ ህይወት ጋር አያይዘህ አስበው... የህይወትህ የመጨረሻ ቀን ላይ እንዳለህ ሲሰማህ እና ደግሞ ማድረግ የነበረብህን አሁን ልታደርገው እንደማትችል ስታውቅ። ያኔ ልታደርገው ያልቻልክበት ምክንያት ጓደኞችህ ሀሳብህን ሰምተው እንደ #እብድ ስለቆጠሩህ ይሆን? ቤተሰቦችህን ህልምህን አውቀው ''እሺ ህልመኛው ' እያሉ #ስላፌዙብህ ይሆን? የህይወትህ የመጨረሻ ቀን ላይ ይሄ ሁሉ የሰዎች ማጣጣል ምንም ሆኖ ቁጭት ከሚሆንብህ በፊት፣ አሁን #እብድ እና #ህልመኛ ተብለህ ውስጥህ ያለውን ልዩ አቅም እንዴት መጠቀም እንዳለብህ ብታውቅ ስኬታማ ትሆናለህ። አስታውስ የሚወቅሱህ፣ አይሆንም የሚሉህ ሰዎች እንደማይሆንልህ የሚያሳይ ማስረጃ የላቸውም። ማስፈራሪያቸውን ከምትሰማ ተግባራዊ ሆነህ ውጤትህን እንድታይ እመክርሃለሁ። ምንጊዜም የተሻለ የህይወት ደረጃን ስትመለከት እንዲህ አይነቶችን የፈተና መንገዶች ማቋረጥ ግድ ይልሃል። join us...    @Ab_book    @Ab_book    @Ab_book
1 209