fa
Feedback
ዶ/ር ምህረት ደበበ እና ዶ/ር እዮብ ማሞ

ዶ/ር ምህረት ደበበ እና ዶ/ር እዮብ ማሞ

رفتن به کانال در Telegram

👉የዶ/ር ምህረት ደበበ ፣ የዶ/ር እዮብ ማሞ እና የሌሎችም ፦፦፦፦፦፦፦፦ 📖አነቃቂና አስተማሪ የሆኑ ወጎች 👉ስለ አመራር 👉አመለካከት(እይታ) 👉mindset 👉ስለ እድገት.......በስፋት እንዳስሳለን 📚 መፅሐፍት pdf 🎙የመፅሐፍ ትረካ 📖 አስተማሪ የሆኑ ፅሁፎች 👉👉👉contact us @Ay_ayche

نمایش بیشتر
3 970
مشترکین
-224 ساعت
-137 روز
-3130 روز
آرشیو پست ها
#ህልመኛ_እና_እብድ_ሁን! ዴል ካርኒጌ እንዳለው ''ለሰው ልጅ አስቸጋሪ ወይም መጥፎ ጊዜ የሚባለው፣ አንድ ሰው የተሻለ አቅም እንዳለው አውቆ ነገር ግን አጠቃቀሙን ሳያውቅ ሲቀር ነው። '' ይሄን ከራስህ ህይወት ጋር አያይዘህ አስበው... የህይወትህ የመጨረሻ ቀን ላይ እንዳለህ ሲሰማህ እና ደግሞ ማድረግ የነበረብህን አሁን ልታደርገው እንደማትችል ስታውቅ። ያኔ ልታደርገው ያልቻልክበት ምክንያት ጓደኞችህ ሀሳብህን ሰምተው እንደ #እብድ ስለቆጠሩህ ይሆን? ቤተሰቦችህን ህልምህን አውቀው ''እሺ ህልመኛው ' እያሉ #ስላፌዙብህ ይሆን? የህይወትህ የመጨረሻ ቀን ላይ ይሄ ሁሉ የሰዎች ማጣጣል ምንም ሆኖ ቁጭት ከሚሆንብህ በፊት፣ አሁን #እብድ እና #ህልመኛ ተብለህ ውስጥህ ያለውን ልዩ አቅም እንዴት መጠቀም እንዳለብህ ብታውቅ ስኬታማ ትሆናለህ። አስታውስ የሚወቅሱህ፣ አይሆንም የሚሉህ ሰዎች እንደማይሆንልህ የሚያሳይ ማስረጃ የላቸውም። ማስፈራሪያቸውን ከምትሰማ ተግባራዊ ሆነህ ውጤትህን እንድታይ እመክርሃለሁ። ምንጊዜም የተሻለ የህይወት ደረጃን ስትመለከት እንዲህ አይነቶችን የፈተና መንገዶች ማቋረጥ ግድ ይልሃል። join us...    @Ab_book    @Ab_book    @Ab_book

#ማር_ከፈለግክ_የንብ_ቀፎውን_አትምታ! 🏌️‍♂️ስኬት ማለት የምትፈልገውን ማግኘት ሲሆን ደስታ ደግሞ፣ ባለህ ነገር ላይ ፍላጎት ወይም ምስጋና ሲኖርህ የሚሰማህ ሰላም ነው። 🧗‍♂️ ፍርሃትህን ማሸነፍ የምትፈልግ ከሆነ፣ ቤት ተቀምጠህ አታብሰልስለው! ይልቁንም ከቤትህ ውጣና ራስህን በስራ ጥመድ! 🎭 ሊያጠቁህ የሚፈልጉ ጠላቶችህን መፍራት የለብህም። ይልቁንስ እጅግ የሚያወድሱህ፣ ያልተገባ ሙገሳ የሚቸሩህ ጓደኞች ካሉህ እነሱን ፍራ። 🚴‍♂️ ስኬታማ ሰው ከስህተቶቹ ትርፍ ያገኛል። ማለትም ቀድሞ የሞከረበት መንገድ ትክክል አለመሆኑን በመረዳት በአዲስ መልክ ይሞክረዋል። 🎲 ማር የምትፈልግ ከሆነ የንብ ቀፎውን መምታት አይኖርብህም። እንዲሁም አንዳንድ የህይወት ገጠመኞች ትግስት እና ብልሃት የሚጠይቁ ናቸው። አስተሳሰባችን የማንነታችን ነጸብራቅ ነው። 🧘‍♂️ አንድ ነገር አስታውስ #ዛሬ ማለት #ትላንትና #ነገ ብለህ ትፈራው የነበረው ቀን ነው። 🏄 መጀመሪያ ከባድ ስራዎችን አከናውን። ከዚም ቀላል የሆኑ ስራዎችን በራሳቸው ተከናውነው ታገኛቸዋለህ። join us...    @Ab_book    @Ab_book    @Ab_book

የተለያዩ ➠ አስገራሚ አስተማሪ እንዲሁም አዝናኝ ታሪኮችን ➠ የፍልስፍና ፅሁፎችን ➠ Motivation Quotes ➠ መፅሀፍትን በPDF ➠ ግጥም የሚያገኙባቸው ቻናሎች
የተለያዩ ➠ አስገራሚ አስተማሪ እንዲሁም አዝናኝ ታሪኮችን ➠ የፍልስፍና ፅሁፎችን ➠ Motivation Quotes ➠ መፅሀፍትን በPDF ➠ ግጥም የሚያገኙባቸው ቻናሎች

ሳትገደዱ ለውጡ! (“የትራንስፎርሜሽን አመራር” ከተሰኘው የዶ/ር ኢዮብ ማሞ መጽሐፍ የተወሰደ) “ልክ ሕይወትን እንዴት መኖር እንዳለብኝ ያወቅሁ ሲመስለኝ ህይወት ትለወጣለች” - Hugh Prather በሕይወታቸው ባሉበት ከመርገጥና ወደኋላ ከመቅረት ራሳቸውን ነጻ ያወጡ ሰዎች የለውጥን እውነታ የተገነዘቡ ሰዎች ናቸው፡፡ እነዚህ ሰዎች ዛሬ አወኩት፣ ተገነዘብኩት፣ ለመድኩት ያሉት ሁኔታ ነገ ካለምንም ማስጠንቀቂያ ተለወጦ እንደሚያገኙት በሚገባ ገብቷቸዋል፡፡ ስለሆነም ካለማቋረጥ አመለካከታቸውን፣ አደራረጋቸውንና ሕይወታቸውን እያሻሻሉና እየለወጡ ይኖራሉ፡፡ የሃርቫርድ ዩኒቨርስቲ ትንቢቶች ሃርቫርድ የተሰኘው ታዋቂ ዩኒቨርስቲ ለውጥን አስመልክቶ ሶስት እውነታዎችን እንደተነበየ ብራያንና ፒተር ያስታውሱናል፡፡ 1.  አሁን በተሰማራህበት የስራ ወይም የንግድ ዘርፍ ውስጥ በመጪው ጥቂት አመታት ውስጥ ከመቸውም ጊዜ በበለጠ ሁኔታ በርካታ ለውጦች ይከሰታሉ፡፡ 2.  አሁን በተሰማራህበት የስራ ወይም የንግድ ዘርፍ ውስጥ በመጪው ጥቂት አመታት ውስጥ ከመቸውም ጊዜ በበለጠ ሁኔታ የጋለ ውድድርና ፉክክር ይከሰታል፡፡ 3.  አሁን በተሰማራህበት የስራ ወይም የንግድ ዘርፍ ውስጥ በመጪው ጥቂት አመታት ውስጥ ከመቸውም ጊዜ በበለጠ ሁኔታ በርካታ የእድል በሮች ይከፈታሉ፤ ሆኖም እነዚህ እድሎች አሁን ከምታደርጋቸው ነገሮች እጅግ የተለዩ ናቸው፡፡ ከቻላችሁ የለውጥ መልእክተኛ ሁኑ፡፡ ያንን ማድረግ ካልቻላችሁ ግን ቢያንስ ከለውጥ ጋር የምትራመዱ ሁኑ! join us...    @Ab_book    @Ab_book    @Ab_book

የእንደገና መርሆች! እንደገና ሊታረም፣ ሊታደስና በአዲስ መልክ ሊጀመር የማይችል ምንም አይነት ስህተት እንደሌለ በማስታወስ ሳምንታችሁን ጀምሩ፡፡ የማይንቀሳቀስን ነገር ሁሉ ሕይወት የሌለው ግዑዝ ፍጥረት እንለዋለን፡፡ የሚንቀሳቀሰውን ደግሞ ሕይወት ያለው ሕያው ፍጡር እንለዋለን፡፡ ሕይወት ካለ መንቀሳቀስ አለ፡፡ መንቀሳቀስ ካለ ደግሞ ስህተት የማይቀር ነው፡፡ ለስህተት ሊሰጥ የሚገባው ትክክለኛው ምላሽ - እንደገና መነሳት! እንደገና መጀመር! እንደገና መገስገስ! እንደገና!!! ሆኖም፣ ይህንን የእንደገና አመለካከት ተግባራዊ፣ ሚዛናዊና ጤናማ የሚያደርጉልንን መርሆች አንዘንጋ፡፡  1.  ይቅርታ መጠየቅ - እንደገና መነሳት ከፈለጋችሁ፣ ስህተቱ የጎዳው ሰው ካለ ይቅርታን መጠየቅ የግድ ነው፡፡ 2.  ይቅርታ ማድረግ - እንደገና መነሳት ከፈለጋችሁ፣ ስህተቱ የተከሰተው በሰዎች ሰበብ ከሆነ ሰዎቹን ይቅር ማለት የግድ ነው፡፡ 3.  በራስ ላይ አለመጨከን - እንደገና መነሳት ከፈለጋችሁ፣ በሰራችሁት ስህተት ምክንያት ራሳችሁን ከመደብደብና ከመኮነን መቆጠብ የግድ ነው፡፡ 4.  ከስህተቱ ትምህርት ማግኘት - እንደገና መነሳት ከፈለጋችሁ፣ ከተሰራው ስህተት ያላችሁ ብቸኛ ትርፍ፣ ያገኛችሁት ትምህርት መሆኑን በማወቅ ትምህርታችሁን መውሰድና ስህተቱ እንዳይደገም ማቀድ የግድ ነው፡፡ 5.  እንደገና መጀመር - እንደገና መነሳት ከፈለጋችሁ፣ የተሰራውን ስህተት በማስተካከል እንደገና መጀመር የግድ ነው፡፡ 6.  በአዲስ መቀየር - እንደገና መነሳት ከፈለጋችሁ፣ ሊታደስ የማይችሉ ሁኔታዎች ካሉ እነዚህን ሁኔታዎች ስታብሰለስሉ መዋል ማደሩን ትታችሁ በአዲስ በመቀየር ወደፊት መራመድ የግድ ነው፡፡ 7.  ከ“ግን” መጠበቅ - እንደገና መነሳት ከፈለጋችሁ፣ ከላይ የተጠቀሱትንና ሌሎች የእንደገና መነሳት መርሆችን እንዳትተገብሩ ከሚያደርጋችሁ፣ “አዎ፣ ግን . .  .” ከሚል ምክንያት ፈላጊነት መጠበቅ የግድ ነው፡፡ join us...    @Ab_book    @Ab_book    @Ab_book

#የማያስጨንቀው_አያስጨንቅህ በህይወታችን ውስጥ ብዙ የሚያስጨንቁን ነገሮች ይኖሩ ይሆናል። ለምሳሌ፡- የቀድሞ የወንድ ጓደኛሽ የፌስ ቡክ ፎቶ የሚያበሳጭሽ፣ የቲቪ ሪሞት ባትሪ ቶሎ ቶሎ ማለቅ የሚያናድድህ፣ በአንዱ ዋጋ ሁለት የእጅ ማጽጃ የምትገዛበት እድል ስላመለጠህ የሚያበሽቅህ ከሆነ፣ እውነተኛው ችግርህ የቲቪው ሪሞት ወይም የእጅ ማጽጃው ሳይሆን በሕይወትህ የምትሰራው ዋጋ ልትሰጠው የሚገባ ሌላ ነገር የሌለህ መሆኑ ነው፡፡ አንድ ጊዜ አንድ አርቲስት “አንድ ሰው ምንም ችግር ከሌለበት አእምሯችን የሆነ ችግር ለመፍጠር መንገድ ያገኛል” ሲል ሰምቼ ነበር፡፡ አብዛኞቹ ሰዎች በተለይ የተማሩና መካከለኛ ኑሮ ላይ ያሉ ሰዎች ‘የሕይወት ችግሮች’ን የሚመለከቱት ሊጨነቁባቸው የሚገባ በጣም አስፈላጊ ነገሮች ያለመኖር የጎንዮሽ ውጤቶች እንደሆኑ አድርገው እንደሆነ አስባለሁ፡፡  ከዚያ በሕይወትህ ውስጥ ጠቃሚ እና ትርጉም ያለው ነገር ማግኘት ምናልባት ጊዜህን እና ጉልበትህን ውጤታማ በሆነ መንገድ መጠቀም ያስችልሃል። ያንን ትርጉም ያለው ነገር ካላገኘህ ግን፣ የአንተ ጭንቀቶች ትርጉም ለሌላቸው እና ለማይረቡ ምክንያቶች የተሰጡ ይሆናሉ። join us...    @Ab_book    @Ab_book    @Ab_book

ለካ እችላለሁ! በአንድ ወቅት የተከናወነ አስቂኝና አስገራሚ ታሪክ እንደሆነ ይነገራል፡፡ በአሜሪካ ግዛት ውስጥ ባለች አንዲት ከተማ ውስጥ በሚገኝ አንድ የሕዝብ መናፈሻ ውስጥ ለሚዝናኑ ሰዎች መገልገያነት በተዘጋጀው የእንጨት አግዳሚ ወንበር ላይ አንድ እድሜው በአርባዎቹ አካባቢ ያለ ሰው በትካዜ አቀርቅሮ ተቀምጧል፡፡ ይህ ሰው በንግድ ስራ የተወሰኑ አመታትን አሳልፏል፡፡ በዚያ ተቀምጦ የሚያስበው በወቅቱ ስላለበት የገንዘብ ሁኔታ ነው፡፡ ይህ ነጋዴ ብዙ በገንዘብ የማደግ ሙከራዎችን አድርጎ ያልተሳካለት ሰው ነው፡፡ በአሁኑ ወቅት ግን ምንም እንኳን የተወሰነ የገንዘብ አቅም ቢኖረውም ምናልባት አንድን ነገር ሞክሬ እንዳልከስርና ያለችኝን እንዳላጣ በማለት በባንክ ውስጥ አስቀምጦ በስራ ፈትነት ወዲህና ወዲያ ይንከራተታል፡፡ ነጋዴው ወደ እርሱ ቀረብ ያለ የኮቴ ድምጽ ስለሰማ አንገቱን ካቀረቀረበት ቀና አድርጎ ሲመለከት አጠገቡ አንድ ሰው ቆሞ ያይና ከነበረበት ተመስጦ ይባንናል፡፡ ይህ ሰው ጥሩ የለበሰና መልከ መልካም ገጽታ ያለው ሰው ነው፡፡ ሰውየው፣ “አንገትህን አቀርቅረህ የተቀምጥከው ለምድን ነው?” ብሎ ጠየቀው፡፡ ነጋዴውም፣ “ብዙ ሙከራዎችን አድርጌ ስላልተሳካልኝ ትንሽ አዝኛለሁ፡፡ ስላለፈው ታሪኬና አሁን ስላለሁበት ሁኔታ እንዲሁ በትካዜ እያሰብኩ ነው” አለው፡፡ ሰውየው፣ “ሮክፌለር (Rockefeller) ስለሚባል የአሜሪካ ቀንደኛ ሚሊየነርና የበጎ አድራጎት ሰው ሰምተህ ታውቃለህ?” አለው፡፡ ነጋዴውም፣ “ስለዚህ ሚሊየነር ሰው ያልሰማ አሜሪካዊ አለ ብለህ ነው? አዎን፣ እኔም ቢሆን በስምና በዝና አውቀዋለሁ እንጂ ምን እንደሚመስል እንኳ አላውቅም” በማለት መለሰለት፡፡ ሰውየውም በመቀጠል፣ “ሮክፌለር ማለት እኔ ነኝ፡፡ አንዳንድ ጊዜ በእንደዚህ አይነት መናፈሻዎች በመዘዋወር ያዘኑና ለብቻቸው የተቀመጡ ሰዎችን በማነጋገር ችግራቸውን ማቃለል እወዳለሁ፡፡ ምን ማድረግ እንደፈለክ ብትነግረኝ ለዚያ የሚሆን በቂ ገንዘብ እሰጥሃለሁ” አለው፡፡ ነጋዴው የሚሰማውን በማመንና ባለማመን ሃሳብ መካከል እየታገለ ቀስ በቀስ የልቡን ያለፈበትን አስቸጋሪ ጎዳናና ያለውን ምኞት ሁሉ ዝክዝክ አድርጎ አጫወተው፡፡ ሰውየው ምንም ሳይወላውል አጠገቡ ከተቀመጠ በኋላ በእጁ ያንጠለጠለውን የሰነድ ቦርሳ በጉልበቱ ላይ አስቀምጦ በመክፈት አንድን የቼክ ደብተር አወጣ፡፡ በዚያም ቼክ ላይ የነጋዴውን ስም ጠይቆ ካሰፈረ በኋላ አንድ ሚልየን ዶላር ጽፎ በመስጠት እንዲህ አለው፡፡ “ይህንን አንድ ሚልየን ዶላር በምትፈልገው የንግድ መስክ ላይ አውለውና ሕይወትህን አሻሽል፡፡ እቅድ ለማውጣት ጊዜ ስለሚፈጅ እስከ አንድ አመት ድረስ ይህንን ቼክ ባታወጣውም ችግር የለውም፡፡ ብሩ ለአንተ ተቀምጦ ይጠብቅሃል” አለውና ወዲያው ከፊቱ ተሰወረ፡፡ የሚያስበውንና የሚያደርገውን ያጣው ይህ ነጋዴ በደስታ ተነስቶ ወደቤቱ በመሄድ ማሰብ ጀመረ፡፡ ለራሱም እንዲህ አለ፣ “አሁን ይህንን አንድ የሚሊየን ዶላር ቼክ በቤቴ አስቀምጥና ባንክ ያለኝን ገንዘብ በድፍረት በማውጣት አንድን ንግድ እጀምራለሁ”፡፡ ቀደም ብሎ ያስብ የነበረው ንግድ ስለነበረ ቼኩን እቤቱ አስቀምጦ ባንክ ያለውን ገንዘብ በማውጣት በድፍረት መነገድ ጀመረ፡፡ አመት ባልሞላው ጊዜ ውስጥ በጣም ብዙ ብር አተረፈ፡፡ በእጁ ላይ ባለው የገንዘብ መጠን በሚገባ ከተደላደለ በኋላ አንድ ቀን ቼኩን ለማውጣት ወደባንክ ሲሄድ ቼኩ እውነተኛ ቼክ እንዳልሆነ ነገሩት፡፡ በነገሩ ተደናግጦ ወደቤቱ ሲመለስ እግረ መንገዱን ወደዚያ መናፈሻ ቦታ ጎራ ብሎ ስለሆነበት ነገር ትንሽ ማሰብ ፈለገና ወደመናፈሻው ሲሄድ፣ ያንን ቼክ የሰጠውን ሰው ለሌላ ሰው ተመሳሳይ ነገር ሲያደርግ ተመለከተው፡፡ በማየት ላይ ባለው ነገር ተገርሞ ጠጋ ብሎ ማዳመጥ ሲጀምር በእርሱ ላይ የሆነው ነገር በሌላም ሰው ላይ እየተደገመ እንደሆነ ተመለከተ፡፡ ምን ማድረግ እንዳለበት ሲያስብ ሶስት በእድሜ ጠና ያሉ ሰዎች እየተሯሯጡ መጥተው ይህንን “ሮክፌለር ነኝ” ባይ ሰው እጁን ይዘው፣ “እንደዚህ አይነት ነገር ሁለተኛ እንዳታደርግ አልተነገረህም?” በማለት እያዋከቡ ወሰዱት፡፡ ለካስ ይህ ሰው የአእምሮ ሕመምተኛ ሰው ነበር፡፡ ይህንን ሮክፌለር ነኝ በማለት የሚያታልልበትን ቼክ የት እንዳሳተመው ባይታወቅም ቼኩን ለሰዎች እየሰጠ የውሸት ተስፋ በመስጠትና በማታለል ይታወቃል፡፡ ነጋዴው ሁኔታው ቢያበሳጨውም አንድ እውነታ ግን ፍንትው ብሎ በራለት፡፡ በእጁ ያለውን ገንዘብ አውጥቶ እንዳይከስር በመፍራት ከመንቀሳቀስ ታስሮ በነበረበት ጊዜ በዚህ ሰው የውሸት ተስፋ ምክንያት ልክ ብዙ ገንዘብ እንዳለው ወደማመን በመምጣቱ በድፍረት ስራ ውስጥ ገባ፡፡ ከዚህ የተነሳ አትራፊ የሆነን ንግድ በአንድ አመት ውስጥ መሰረተ፡፡ ምንም እንኳን “አንድ ሚልየን ዶላር” የሚለው ቼክ ባዶ ቢሆንም፣ ምንም እንኳን ሰውየው የዋሸው ውሸት ቢያበሳጨውም፣ በዚያ ምክንያት ግን በመነሳሳት አሁን ያለበት ትልቅ ደረጃ ደርሷል፡፡ ይህ ታሪክ አንዳንድ ጊዜ የሚያስፈልገን የገንዘብ ብዛት ሳይሆን የውስጥ መነሳሳትና የአመለካከት ለውጥ እንደሆነ ጠቋሚ ነው፡፡ “የገንዘብ ነጻነት አምዶች” ከተሰኘው የዶ/ር ኢዮብ ማሞ መጽሐፍ የተወሰደ፡፡ join us...    @Ab_book    @Ab_book    @Ab_book

ጀምሮ የመጨረስ ጥቅሞች! (“ጀምሮ መጨረስ” ከተሰኘው የዶ/ር ኢዮብ ማሞ መጽሐፍ የተወሰደ) “የሚከፈልህ ለጀመርከው ነገር አይደለም . . . ጀምረህ ለጨረስከው ነገር ብቻ ነው የሚከፈልህ” – Gary Ryan Blair 1. በራስ መተማመን፡፡ አንድን ነገር ጀምረው የማይጨርሱ ሰዎች የሚደርስባቸው ክስረት ድርብ ክስረት ነው፡፡ በአንድ ጎኑ ተጀምሮ ያልተጨረሰው ስራ ክስረት ሲያደርስባቸው በሌላ ጎኑ ደግሞ ጀምረው ባለመጨረሳቸው ምክንያት በራሳቸው ላይ ያላቸው ግምትና አመለካከት እየወረደ ይሄዳል፡፡ ከዚህ በተቃራኒ አንድን ነገር ጀምረው ካልጨረሱ በስተቀር ያለማቆም ልማድ ያላቸው ሰዎች ይህ ነው የማይባል በራስ የመተማመን የስነ-ልቦና ድልን ያገኛሉ፡፡ ይህ ድል ለሚቀጥለው ስራቸው የተማመኑና የተረጋጉ ስለሚያደርጋቸው አንድን ነገር ጀምሮ የመጨረስ እንድርድረት (Momentum) ውስጥ ራሳቸውን ያገኙታል፡፡ 2. በሰዎች ተቀባይነት፡፡ አንድን ነገር ጀምሮ ሳይጨርስ አንጠልጥሎ ዘወር የሚልና ሌላ ነገር ደግሞ የሚጀምር ሰው በማንም ሰውም ሆነ ተቋም ያለው ተፈላጊነት እጅግ የወረደ ነው፡፡ ስለሆነም፣ ጀምረው የማይጨርሱ ሰዎች በሕብረተሰቡ መካከል ተቀባይነት የማጣት አዙሪት ውስጥ ራሳቸውን ያገኙታል፡፡ በተቃራኒ አንድን ነገር ጀምረው የሚጨርሱ ሰዎች ቀድሞውኑ እጅግ ተፈላጊና ዋጋቸውም የከበረ ሰዎች ናቸው፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በገቡበት ቦታ ሁሉ ይዘው የሚመጡት አንድን ነገር በጥራትና በብቃት የመጨረስ ልማድ የሚሰጣቸው የእድገት ፍጥነት ይህ ነው አይባልም፡፡ 3. ተወዳዳሪነት፡፡ ጀምሮ የመጨረስ ነገር ያልበራለትና ያንንም ልማድ ያላዳበረ ሰው በሄደበት ስፍራ ሁሉ ሲጀምር መካከለኛ ሆኖ ሲያጠናቅቅ ደግሞ መጨረሻ ሆኖ ራሱን ያገኘዋል፡፡ እንዲህ አይነቱ ሰው አሁን ባለንበት ውድድር እጅጉን በተስፋፋበት ዘመን ቀደም ብሎ የመገኘት ጉዳይ ካሳሰበው በመጀመሪያ ሊያዳብር የሚገባው ጀምሮ የመጨረስን ልማድና ክህሎት ነው፡፡ ጀምሮ የመጨረስ ምስጢር ቀድሞውኑ የገባቸውና ያንንም ያዳበሩ ሰዎች በሕብረተሰቡ መካከል ያላቸው ተወዳዳሪነት እጅግ የላቀ ነው፡፡ ከዚህ ተወዳዳሪነታቸው የተነሳ ካለማቋረጥ የእድገትን መሰላል ሲወጡ ራሳቸውን ያገኙታል፡፡ 4. ሌላ በር መከፈት፡፡ አሁን በእጁ ያለው ነገር ደግሞ ሌላ ነገር ወልዶና ተባዝቶ ማየት የማይመኝ ሰውም አይገኝም፡፡ አንድን ነገር ጀምሮ የመጨረስ ብቃቱን ያላዳበረ ሰው ይህን ሁኔታ ቢመኘውም የሕልም እንጀራ ሆኖ ያገኘዋል እንጅ በእጁ ማስገባት ያስቸግረዋል፡፡ ጀምሮ የመጨረስ ብልሃት የገባው ሰው በፍጹም  በአንድ የእድገት ደረጃ መክረም የማይችል ሰው ነው፡፡ እንዲህ አይነቱ ሰው በእጁ ያለውን ተግባር በብቃት ሲያጠናቅቅ ወደደም ጠላም ያጠናቀቀው ስራ የሚወልደውን ሌላ የላቀ ስራ መረከቡ አይቀርም፡፡ join us...    @Ab_book    @Ab_book    @Ab_book

ከመራራነት ውጣ! “ጥላቻና መራራነት ማለት አንዲትን አይጥ ለመግደል ቤትህን በእሳት ማቃጠል ማለት ነው” - Henry Fosdick የልጅነት አስተዳደጋችን በወደፊት ማንነታችን ላይ ምን ያህል ተጽእኖ አለው? የልጅነትንና የለጋነትን ዘመን ፍጹም ፍቅር በተሞላበት ቤት ለማደግ የበቃ ልጅ የታደለ ነው፡፡  ብዙዎች ግን ይህንን እድል አያገኙትም፡፡ አንዳንዶች ርህራሄ በሌላቸው ቤሰቦች እጅ ሲያድጉ፣ ሌሎች ደግሞ ከቤተሰባቸው ጋር እንኳን የማደግ እድል አያገኙም፡፡ የመደብደቡ፣ የአስገድዶ መደፈሩ፣ በማያፈናፍን ችግር ውስጥ ማለፉ … ብዙዎች ወደ  አቅመ-አዳም (አቅመ-ሄዋን) ሲደርሱ በውስጣቸው ተሸክመው የሚመጡት አሉታዊ ተጽእኖ ቀላል አይደለም፡፡ የቀናውና የሚያደርገውን ያወቀው ብቻ ከዚያ ተጽእኖ ይላቀቃል፡፡ የአዶልፍ ሂትለር ታላቅ ወንድም የአባቱ ጨካኝነትን ለማምለጥ በ13 አመቱ ነበር ከቤቱ በርሮ የጠፋው፡፡ ይህ ልጅ ከቤቱ ከሄደ በኋላ የሂትለር አባት ክፋቱን በሰባት አመቱ ለጋ ልጅ በሂትለር ላይ በእጥፍ ጨመረው፡፡ ሂትለር በአባቱ እጅ አሰቃቂ አመታትን አልፏል፡፡ ምርጫውን ተከልክሎአል፡፡ አርቲስት ለመሆን ይመኝ የነበረው ሂትለር በአባቱ አስገዳጅነት የሲቪል ሰራተኛነት አቅጣጫን እንዲከተል ተገደደ፡፡ የሂትለር ትምህርት ውጤቱ አጥጋቢ ስላልነበር የአባቱን የቁጣ እጅግ አባባሰው፡፡ የአይሁድ ዘር እንዳለበት የሚነገረው የሂትለር አባት ክፋት በሂትለር ልብ ውስጥ አይሁድን የመጥላት ዘርም እንደዘራበት ይነገራል፡፡ አባቱ ከሞተ በኋላ፣ ሂትለር በ13 አመቱ የቤት ሃላፊትን በጫንቃው ላይ ተሸከመ፡፡ በእናቱ ሞት ምክንያት በኋላ በጉዲፈቻ ያድግ የነበረው ሂትለር ያንን ገቢ በመከልከሉ የጎዳናን ሕይወት ቀምሷል፡፡ በብዙዎች እንደሚታመነው፣ ሂትለር በልጅነቱ ያሳለፈው ስቃይ ውስጡ ከጨመረበት መራራነት እንዳልተላቀቀና በሕይወቱ ያደረጋቸው አሰቃቂ ተግባሮች የዚያ ልምምድ ተጽእኖ እንደሆኑ ይታመናል፡፡ ሂትለር ቢያንስ ለ46 ሚልየን ሰዎች መሞትና  ለብዙ  ንብረት መውደም ምክንያት የሆነ ሰው ነው፡፡ አንዳንድ የስነ-ልቦና ጥናቶች፣ አንድ ልጅ በአምስት አመቱ የወደፊቱን የሚወስነውን ብዙውን ማንነቱን ገንብቶ እንደሚጨርስ ይጠቁሙናል፡፡ አዋቂዎች ሁሉ የሚስማሙበት እውነታ፣ አንድ ልጅ በመጀመሪያዎቹ አምስትና አስር አመታት የሚያሳልፋቸው ሁኔታዎች በወደፊት ማንነቱ ላይ ታላቅ አስተዋጽኦ እንዳለው ነው፡፡ አንድ ሰው በእድሜ እያደገ ሲሄድ በለጋነቱ የደረሰበትን አስከፊ ሁኔታ ወደ ኋላ ለመጣልና ከመራራነት ለመውጣት አስፈላጊውን እርምጃ ካልወሰደ የወደፊት ማንነቱ መራራና ለሕብረተሰብ ጠንቅ የሚሆኑ ባህሪያትን የሚያንጸባርቅ ሊሆን ይችላል፡፡ አንዳንድ ሰዎች የልጅነታቸውን  አሉታዊና ጤና ቢስ ልምምድ በስሜታቸው ላይ ካመጣው ተጽእኖ ሳይላቀቁ ወደ ትዳር አለም ውስጥ ይገባሉ፡፡ ቁጣን፣ ጸበኝነትን፣ ጠርጣራነትንና የመሳሰሉትን ለትዳር ጠንቅ የሆኑ መራራ ነገሮች ይዘው ስለሚገቡ ብዙም ሳይቆዩ ለመለያየት ምክንያት ይሆናሉ፡፡ ሌሎች መራራነትን፣ ጥላቻንና በአስተዳደግ ዘመናቸው የተጎነጩትን የውስጥ ቂም ይዘው ወደ አመራር ይዘልቃሉ - እንዴት አይነት ስህተት! ካለፈው ሕይወት ተጽእኖ በስኬታማ ሁኔታ ራሱን መርቶ ያላወጣ ሰው ሌላውን ለመምራት ሲሞክር ሊያስከትለው የሚችለው ጉዳት ቀላል አይደለም፡፡ ወደፊት ለመዝለቅና ስኬታማ ሕይወት ውስጥ ለመግባት ካለፈው መፋታት የግድ ነው፡፡ ይህንን ለማድረግ የሚጠቅሙ ሃሳቦች እነሆ፡- ሙሉ ሃላፊነትን ውሰድ:- “ስለ ህይወትህ በግልህ ሃላፊነትን መውሰድ አለብህ፡፡ በዙሪያህ የሚከናወነውን ነገር፣ የአየሩን ጸባይና ነፋሱን መቆጣጠርና መለወጥ አትችልም፣ ራስህን ግን መለወጥ ትችላለህ” – Jim Rohn ሰዎችን ይቅር በል:- “ደካማው ይቅር ሊል አይችልም፡፡ ይቅርታ ማድረግ የብርቱዎች ባህሪይ ነው” - Mahatma Gandhi ልምምዶችህን ለመልካም ለውጣቸው :-  “ሌሎች ተራ ሕይወትን ይኑሩ፣ አንተ ግን አትኑር፡፡ ሌሎች ባልሆነ በሆነ ይጨቃጨቁ፣ አንተ ግን አታድርገው፡፡ ሌሎች በጥቃቅን ጉዳቶች ያልቅሱ፣ አንተ ግን አታልቅስ፡፡ ሌሎች የሕይወታቸውን ጉዳይ ለሰው አሳልፈው ይስጡ፣ አንተ ግን አትስጥ” – Jim Rohn join us...    @Ab_book    @Ab_book    @Ab_book

#ከተማሩ_ሰዎች_ይልቅ_በመከራ_ያለፉ_ሰዎችን_አከብራለሁ! አልማዝ በተፈጥሮ መንገድ እንዴት እንደሚሰራ ልንገራችሁ። አልማዝ የሚሰራው HPHT በሚባል Process ነው። HPHT ማለት High Pressure High Temperature ማለት ነው። አንድ አልማዝ አልማዝ ከመሆኑ በፊት አራት ደራጃዎችን ማለፍ ይኖርበታል። አንደኛ ከምድር በታች ከ300 እስከ 600 ኪሎ ሜትር ዝቅ ብሎ መቀመጥ። ሁለተኛ ከፍተኛ ሙቀት መታደል፣ ከ1200 ዲግሪ ሴንቲ ግሬት ቃጠሎ ውስጥ መቀመጥ። ሶስተኛ ከፍተኛ ጭነት ማግኘት። አራተኛ ለረዥም ጊዜ ውስጥ በነዚህ ሁኔታዎች ውስጥ መቆየት ! እንግዲህ አንድን የድንጋይ ከሰል ወስዳችሁ ከምድር በታች 600 ኪሎ ሜትር ብታወርዱት፣ 1200 ዲግሬ ሴንቲ ግሬት ቃጦሎ ውስጥ ብታኖሩት፣ በከፍተኛ ፕሬዠር ውስጥ ብታስቀምጡት እና ለረዥም ጊዜያት በዚህ ሁኔታ ውስጥ ብትተዉት። ከሰሉ አልማዝ ይሆናል ! ከሰሉ ወደ ዳይመንድነት ይለወጣል። አንዳንዶቻችሁ በህይወታችሁ ግራ ይገባችኋል፣ በጣም የሚወዳችሁ አምላካችሁ ከጓደኞቻችሁ በታች 600 ኪሎ ሜትር አውርዷችሁ ይሆናል። በማይገባችሁ ፈተና 1200 degree cent great ቃጠሎ ውስጥ አስቀምጧችሁ ፤ በማጣት፣ በመገለል፣ በመገፋት ለረዥም ጊዚያት እየፈተናችሁ "ምንድነው እየተካሄደ ያለው?" ብላችሁ እስክትጠይቁ ድረስ ለአምስት አመት፣ ለአስር አመት ከሰው፣ ከወዳጅ፣ ከዘመድ፣ ከጓደኛ ዝቅ አድርጓችሁ ይሆናል። .... "ምን ማለት ነው የሚወደኝ አምላክ ይሄን የሚፈቅደው" ስትሉ .... አልማዝ አድርጎ ሊሰራችሁ፣ ውብ አድርጎ፣ ሊሰራችሁ፣ የምታበሩ አድርጎ ሊያበጃችሁ፣ እንቁ፣ ዳይመንድ፣ አልማዝ ሊያደርጋችሁ ስላሰበ ነው ! አልማዝ ሰባት ባህሪዎች አሉት:- አንደኛ ጠንካራ ነው። ወስዳችሁ በድንጋይ ቀጥቅጡት አይሰበርም። በሰይፍ ምቱት አይሰነጠቅም። በመጋዝ ገዝግዙት አይቆረጥም። በአልማዝ ግን ብረት ይቆረጣል፣ በአልማዝ ግን ሰይፍ ይቆረጣል። በአልማዝ ግን ድንጋይ ይፈርሳል። አልማዝ የሚቆረጠው በሌላ አልማዝ ነው። ሁለተኛ የአልማዝ ባህሪ ልንገራችሁ። ከፍተኛ የማንጸባረቅ ባህሪ አለው። refractive index ይባላል። የተቀበለውን ብርሃን መልሶ የማብራት ባህሪ አለው። ያንጸባርቃል። ሶስተኛው የአልማዝ ባህሪ የተቀበለውን የጸሐይ ብርሃን፣ ነጩን ብርሃን ወደ የተለያዩ በርካታ ቀለማት የመበተን ችሎታ አለው። አራተኛውን የአልማዝ ባህሪ ልንገራችሁ። እጅግ በጣም ንጹህ ነው። አልማዝ የሚታወቀው በንጹህነቱ ነው። አምስተኛውን የአልማዝ ባህሪ ልንገራችሁ። አልማዝ በእሳት አይቃጠልም። አንድ ቤት ውስጥ አልማዝ አለ እንበል፤ ያ አልማዝ ያለበት ቤት ሙሉ ለሙሉ ቢቃጠል አልማዙ ምንም አይሆንም። ምንም። በነበረው ቅርጹ፣ በነበረው ንጽህናው እናገኘዋለን። የሚያስገርመኝን ስድስተኛውን የአልማዝን ባህሪ ልንገራችሁ። ወርቅ ላይ አሲድ ድፉበት ወርቁ ይበላሻል። አልማዝ ላይ አሲድ አፍስሱበት ምንም አይሆንም። አይበላሽም። የመጨረሻው እና ሰባተኛው የአልማዝ ባህሪ በጣም ውድ ነው። በጣም ውድ ነው። የአውራጣትህን ራስ የምታክል ዳይመንድ አንድ ትልቅ ፎቅ ይገዛል። በጣም ውድ ነው። ከጓደኞቻችሁ በታች 600 ኪሎ ሜትር ወርዳችሁ ፣ በ1200 ዲግሪ ሴንቲ ግሬት ስቃይ ውስጥ ያለፋችሁ፣ በፕሬዠር ውስጥ ለበርካታ አመታት ያለፋችሁ እናንተ አልማዝ ሁናችሁ የተሰራችሁ ሰዎች ናችሁ። ሰዎች ጠጠር ብትመስሏቸውም አልማዞች ናችሁ። ዋጋችሁ በጣም ውድ ነው። ... ከተማሩ ሰዎች ይልቅ፣ ብዙ ድግሪ ከተሳካላቸው ሰዎች ይልቅ፤ በመከራ ያለፉ ሰዎችን አከብራለሁ። ዋጋ የከፈሉ ሰዎችን አከብራለሁ። በስቃይ ውስጥ ያለፉ ሰዎችን አከብራለሁ። ምክንያቱም ዋጋቸው በጣም ውድ ነው። (ዶክተር ወዳጀነህ) join us...    @Ab_book    @Ab_book    @Ab_book

#ድረሱልኝ! 📗 አንድ አባት ልጁን እንዲህ ሲል አዘዛት ''ልጄ ዛሬ ደስ ስላለኝ ድግስ አዘጋጂ፤ ወዳጅ ጎረቤቶቻችን ዘመዶቻችንን ሁሉ ጥሪያቸው፤ እኔ ከስራ ስመለስ አብረን እንሆናለን እስከዛ ከእነሱ ጋር ተደሰቺ '' በማለት ወደ ስራው ሄደ። ብልሁዋ ልጅም ከቤት ወጣችና እንዲህ ስትል ጩኸት አሰማች፡፡ ''እባካችሁ እርዱን ቤታችን ውስጥ እሳት ነዷል አባቴን ከእሳቱ አውጡት እባካችሁ።'' ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ዘመድ እና ጎረቤት የሆኑ ሰዎች መጡ። ነገር ግን የድረሱልን ጥሪዋን እንዳልሰሙ ሆነው አለፉ። ነገር ግን የማታውቃቸው አንዳንድ ሰዎች የድረሱልኝ ጥሪዋን ሰምተው አባቷን ለማዳን ወደ ቤቱ ዘለው ገቡ። ያጋጠማቸው ግን ባማረ ሁኔታ የተዘጋጀ መብል እና መጠጥ ነበር። ከዛም እየበሉ፣ እየጠጡ፣ እየተጨዋወቱ አባቷ ደረሰ። ባየው ነገር ግራ በመጋባትም እንዲህ ሲል ጠየቃት ''ልጄ እኒህን ሰዎች ብዙም አላውቃቸውም፤ ዘመዶቻችን እና ጎረቤቶቻችን የታሉ?'' ሲል ጠየቃት... ብልህ የሆነችው ልጅም ያደረገችውን ከነገረችው በኋላ ''ሊደርሱልህ አልመጡም'' አለችው። አባትም በልጁ አድራጎት እየተደነቀ ሰፈሩ ውስጥ ብዙም ከማያውቃቸው ሰዎች ጋር በመቀላቀል ጥሩ ጊዜ አሳለፈ። ☑️ ቁምነገሩ~ አንዳንዴ ዘመዶቼ ናቸው ወዳጆቼ ናቸው የምትላቸው ሰዎች በችግርህ ጊዜ እንደማይደርሱ ማወቅ አለብህ። እንዲሁም እንብዛም የማታውቃቸው ሰዎች ለችግርህ ጊዜ ደራሽ ሆነው ታገኛቸዋለህ። ስለዚህ በዙሪያህ ላሉ ሰዎች ሁሉ ክብር ይኑርህ። እንዲሁም አንድ የመጽሐፍ ቅዱስ ነገርን አስብ ''ትንሽ ቁስል ለራስህ ስጥና ወዳጅ እና ጠላትህን ለይ'' ሁሌ ብሉልኝ ጠጡልኝ የምትል ከሆነ ወዳጅህም፣ ጠላትህ በፈገግታ ወደ አንተ ይቀርባሉ፤ ''ድረሱልኝ!'' ስትል የደረሰልህ እሱ በትክክል ወዳጅህ እንደሆነ እወቅ። join us...    @Ab_book    @Ab_book    @Ab_book

#እንደ_አንበሳ_ሁን! 👑 አንበሳ የመሪነት መንፈስ ያለው እንሰሳ ነው። መንፈስ ማለት ደሞ አመኔታ ያለው አመለካከት ነው። እስኪ በውስጥህ 'አመለካከት' በል። አንተ ስለመሪነት ምን አይነት አመለካከት አለህ? 👑 የመሪነት አመለካከት እሱን ወይም እሷን ከተከታዮች የሚለይ ብልጫ ነው። አሁን አንበሳን ብንመለከት የየትኛውም አለም ጫካ ንጉስ ነው። ስለዚህ አንበሳ ለሁላችንም ብርታት እና ትምህርት የሚሰጥ አመለካከት አለው። እኒህን ነገሮች በቁም ነገር አስባቸው እስኪ #አንደኛ አንበሳ በጫካ ከሚኖሩት እንሰሳት ውስጥ በቁመት እረጅሙ አይደለም ! ( ቀጭኔ የት ሄዳ ?) #ሁለተኛ አንበሳ በጫካ ከሚኖሩት እንሰሳት ውስጥ በትልቀት ግዙፉ አይደለም ( ዝሆን የት ሄዶ? ) #ሶስተኛ አንበሳ በጫካ ከሚኖሩት እንሰሳት ውስጥ ከባዱ አይደለም ( ጎሽ የት ሄዶ ?) #አራት አንበሳ በጫካ ከሚኖሩት እንሰሳት ውስጥ ብልሁ አይደለም ( ጦጣ የት ሄዳ? ) ነገር ግን አንበሳ በታየ ጊዜ ሁሉም እንሰሳት በሩጫ አይገኙም። ምክንያቱም አንበሳ የመሪነት  መንፈስ ያለው ፍጥረት ስለሆነ። ☑️  አንተም መሪ መሆን ከፈለክ፣ ከስርህ በየአይነቱ የሚበልጡህ ብዙ ሞያተኞች እንዳሉ አትርሳ- እንዲሁም አትስጋ። እንደ መሪ ልዩ የሚያደርግህ አንድ አቅም ብቻ ይኑርህ እሱም ጠንካራ የሆነ መንፈስ ነው -አመለካከት። join us...    @Ab_book    @Ab_book    @Ab_book

ምን ላቁም? አንድ ታዋቂ የአመራርና የማኔጅመንት አስተማሪ እንዲህ አለ፣ “መሪዎችን ስናሰለጥን ብዙውን ጊዜአችንን የምንፈጀው ማድረግ የሚገባቸው ነገር ምን እንደሆነ በመንገር ነው፡፡ መሪዎች ማቆም ያለባቸው ነገር ምን እንደሆነ ለመንገር ግን በቂ ጊዜን አናሳልፍም፡፡ ካገኘኋቸው መሪዎች መካከል ግማሾቹ ሊማሩ የሚገባቸው ማድረግ ያለባቸው ምን እንደሆነ አይደለም፡፡ በተቃራኒው መማር ያለባቸው ማቆም ያለባቸውን ነገር ነው”፡፡ ይህ አባባል የብዙዎቻችንን የሕይወት ዘይቤ አመልካች ነው፡፡ ሁል ጊዜ፣ “ምን ባደርግ ጥሩ ነው?” ከሚል ሃሳብ ጋር ስንሟገትና ይህንና ያንን ለማድረግ ስንሯሯጥ ምናልባት በመተው የምናከናውናቸው ነገሮች ያመልጡናል፡፡ አስተዳደጋችን አንድን ነገር አድርገን የማስመስከርን አቅጣጫ ብቻ አሳይቶን ነው ያደግነው፡፡ ስለዚህ መሻሻልን፣ ማደግን፣ ስኬትንና የመሳሰሉትን የምንመኛቸውን መልካም ነገሮች ለማግኘጥ ካለማቋረጥ እንጦዛለን፡፡ አንዳንድ ጊዜ ግን ስኬታችን ያለው ማቆም ያለብንን ነገር ከማቆም አንጻር ሊሆን ይችላል፡፡ አየህ፣ እጅግ በረዷማ በሆነ አካባቢ የሚኖሩ አንዳንድ እንስሶች፣ “የበረዶውን ወቅት ለማለፍ የሚያስችለኝን ምግብ እንዳገኝ ምን ላድርግ?” የሚለው ጥያቄ አላዛልቅ ሲላቸው፣ “የተመገብኩት ምግብ በቶሎ እንዳይቃጠልና ጉልበት እንዳላጣ ምን ማድረግ ላቁም?” በማለት “ሽሸጋ” (Hibernation) ውስጥ ይገባሉ፡፡ ባለማድረግ ይኖራሉ፣ በመተው ይሰነብታሉ፡፡ ዛሬ እስቲ ይህንን አስፈላጊና ወሳኝ ጥያቄ ራስህን ጠይቅ፣ “ማቆም ያለብኝ ነገር ምንድን ነው?”    “የተሻለ ገቢ ለማግኘት ምን ተጨማሪ ስራ ልጀምር?” የሚል ሰው ምናልባት፣ “የትኛውን አላስፈላጊ ወጪ ላቁም” በማለት ራሱን ቢጠይቅ፣ የተሻለ ገቢ እስከሚያገኝ ድረስ የተሻለ ገንዘብን የማጠራቀምና የማቆየት ስኬት ውስጥ ሊገባ ይችላል፡፡ “ከዚህ የተሻለ ሰላምና መረጋጋት እንዳገኝ ምን ላድርግ?” የሚል ሰው ምናልባት፣ “ከማን ጋር መገናኘት ላቁም?” ብሎ ራሱን ቢጠይቅ ሰላሙና መረጋጋቱ ይመለስለት ይሆናል፡፡ “ጊዜዬን በአግባቡ ለመጠቀም ምን ላድርግ?” የሚል ሰው ምናልባት፣ “ጊዜዬን በከንቱ እንዳላስበላ ማቆም ያለብኝ ጊዜ አባካን ሁኔታ ምንድን ነው?” ብሎ ራሱን ቢጠይቅ አንዱን የጊዜ አጠቃቀም ዘይቤ ይደርስበታል፡፡ አንዳንድ ጊዜ፣ “የት ልሂድ?” ከሚለው ጥያቄ ይልቅ፣ “ከየት ቦታ ልቅር?” የሚለው ጥያቄ የበለጠ ስኬታማ ያደርገናል፡፡ አንዳንድ ጊዜ፣ “ከማን ጋር ላውራ?” ከሚለው ጥያቄ ይልቅ፣ “ከማን ጋር ያለኝን ንግግር ላቁም ወይም ልቀንስ?” የሚለው ጥያቄ የበለጠ ፍሬያማ ያደርገናል፡፡ አንዳንድ ጊዜ ከምንናገረው ይልቅ ዝም ለማለት የመርጠነው ነገር የበለጠ ስኬታማ ያደርገናል፡፡ ይህንን ምስጢር በሚገባ ስንገነዘብ ራሳችንን በመሰብሰብ፣ በመቀነስና በመልቀቅ ልቀን የምንገኝባቸው ሁኔታዎች ይበሩልናል፡፡ ዶር እዮብ ማሞ join us...    @Ab_book    @Ab_book    @Ab_book

#ዓለም_እንደምታያት_ናት! ከተፈጥሮ በስተቀር ከአንተ በላይ የሆነ ምንም ኃይል አጋጥሞህ አያውቅም፡፡ በከፍተኛ ጉልበት የሚነፍሰውን ነፋስ ያስጀመርከው አንተ አይደለህም፡፡  ተፈጥረህ ተገኘህ እንጂ ራስህንም የፈጠርከው አንተ አይደለህም፡፡ ከአንተ በላይ ያለ ኃይል ወይም የሆነ ነገር ባይኖር ኖሮ ምንም ነገር ሊከሰት አይችልም ነበር፡፡  አንተን የፈጠረህ ነገር  ምን እንደሆነ  ስለማታውቅ፥ ቀጥሎ የምትለው ነገር የሰራኝ ፈጣሪ መሆን አለበት ነው፡፡  ፈጣሪ የመጣው ከየት ነው? አንተ ሰው ስለሆንክ፥ ፈጣሪ በሰው መልክ የተሰራ ትልቅ አካል እንደሆነ ታስባለህ፡፡ ጎሽ ብትሆን ኖሮ ደግሞ፥ ፈጣሪ በጎሽ መልክ የተሰራ ትልቅ አካል እንደሆነ ታስብ ነበር፡፡ ስለ ፈጣሪ ያለህ አመለካከት በሙሉ የመጣው ስለ ማንነትህ ካለህ ውስን ተሞክሮና ውስን ምናብ ነው፡፡  በሰው መልክ ስለተሰራህ፥ ፈጣሪ የሰው መልክ የያዘ ትልቅ አካል እንደሆነ ታስባለህ፡፡ ስለዚህ ፈጣሪ ወይም ኃይል ብለህ የምትጠራው የትኛውም ነገር አንተ ወይ የምታስበው አለዚያም የምታልመው በአእምሮህ ውስጥ ብቻ ያለ ነገር ነው፡፡ በእውነት መለማመድ የምትችለው ብቸኛው ነገር በውስጥህ ያለውን ነው፡፡ በውስጥህ ያለውን ደግሞ በጥልቀት አይተኸው አታውቅም፡፡  እስካሁን የምታውቃቸውን ነገሮች የተለማመድካቸው በአምስቱ የስሜት ህዋሳት የተወሰኑ ናቸው፡፡  አለምንም ይሁን ራስህን በተመለከተ እስካሁን የምታውቃቸው ነገሮች ሁሉ፥ የመጡት በማየት፥ በመስማት፥ በመንካት፥ በመቅመስና በማሽተት ብቻ ነው፡፡ እነዚህ ስሜት ህዋሳት ባይሰሩ፥ አለምንም ሆነ ራስህን አታውቅም ነበር፡፡ የስሜት ህዋሳት ሁሉንም ነገሮች የሚነግሩን ከሌላ ነገር ጋር በማነጻጸር ነው፡፡  ለምሳሌ ብረት ብትነካና ቅዝቃዜ ቢሰማህ የሰውነትህ ሙቀት  ከብረቱ ሙቀት መጠን የበለጠ ስለሆነ ነው፡፡ የሰውነትህን ሙቀት ከብረቱ ሙቀት እጅግ ያነሰ ብታደርገው ብረቱ ሞቃት እንደሆነ ይሰማሃል፡፡ ስለዚህ ይህ የምትተማመንበት ልምምድ ሳይሆን በአካላዊ እውነታ ውስጥ ለመኖር ብቻ በቂ የሆነ ልምምድ ነው፡፡   በአምስቱ የስሜት ህዋሳት ግንዛቤዎች ምንም አይነት ተሞክሮ ቢኖርህ፥ ያ ተሞክሮ በዚህ ህልውና ውስጥ ለመኖር ብቻ በቂ የሆነ ልምድ ነው፡፡ join us...    @Ab_book    @Ab_book    @Ab_book

የሚወለዱት ህጻናት ብቻ ናቸው! አንዲትን ከብዙዎች ሰዎች እይታ ርቃ የምትገኝን መንደር በመጎብኘት ላይ የነበሩ ሰዎች ገና እንደደረሱ የገረማቸው የዚያች መንደር ርቀት ነው፡፡ ከዚህ በፊት ብዙ ጎብኚዎች የመጡባት አትመስልም፡፡ በዚህች መንደር በመዘዋወር እያሉ በአንድ ሜዳ ላይ የሚጫወቱትን ወጣቶች ቁጭ ብለው የሚያዩ አንድ አዛውንት አገኙና ሰላምታ ከተለዋወጡ በኋላ እንዲህ የሚል ጥያቄ ጠየቋቸው፣ “በዚህ መንደር ታላላቅ ሰዎች ተወልደው ያውቃሉ?” ጥያቄው ግልጽ ቢሆንም፣ አዛውንቱ፣ “ምን አይነት ጥያቄ ነው” በሚል እይታ ከቃኟቸው በኋላ አጅግ ቀላልና ግልጽ የሆነ መልስ ሰጧቸው፡፡ የእኝህ አዛውንት ፈጣን መልስ ጎብኚዎቹን አስገረማቸው፡፡ መልሳቸው፣ “በዚህች መንደር የሚወለዱት ህጻናት ብቻ ናቸው”፡፡ አስገራሚ መልስ! ወደዚህች ምድር በውልደት የመጣ ሰው ሁሉ የመጀመሪያ ስሙ “ሰው” ይባላል - ከዚህ ውጪ ማንነት የለም፡፡ ሁሉም እኩል የመተንፈስ እድል ይዞ ነው የተወለደው፡፡ ለሁሉም የተሰጠው አንድ አስገራሚ ስጦታ “ህይወት” ይባላል፡፡ ከዚህ ውጪ ሌላ የለም፡፡ እውነት ነው፣ ብዙ ሃብት ባለበት ቤት ውስጥ የመወለድ እድል ያጋጠማቸው ሰዎች አሉ፡፡ በተቃራኒው ደግሞ በእጦት ተወልደው በእጦት ያደጉም አሉ፡፡ በሃብት ተወልደው በድህነት ኖረው የሞቱ፣ በድህነት ተወልደው ደግሞ በብልጽግና ኖረው የሞቱም ያንኑ ያህል ቁጥራቸው ብዙ ነው፡፡ አንድ ሰው ከምን አይነት ቤተሰብ ሊወለድ እንደሚፈልግ ምርጫ ባይኖረውም ከተወለደ በኋላ ምን አይነት ጎዳና መከተል እንደሚችል ግን የመወሰን ምርጫ አለው፡፡ የትኛው ይሻላል? የአወላለድን ሁኔታ መርጦ ከተወለዱ በኋላ ለእድል ታልፎ መሰጠት ወይስ የአወላለድን ሁኔታ የመምረጥ እድል ሳያገኙ ከተወለዱ በኋላ የሚሄዱበትን ጎዳና የመምረጥ እድል? እኔ ሁለተኛው ያጓጓኛል! አንድ ሰው ጾታውን፣ ቤተሰቡን፣ የቆዳ ቀለሙንና ዜግነቱን መርጦ አይወለድም ከተወለደ በኋላ ግን በእነዚህ ልዩ ስጦታዎች ተጠቅሞ ወደየት እንደሚሄድ የመወሰን መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡ ይህንን መብት ለማስከበር ማስታወስ የሚገቡን ሶስት እውነታዎች አሉ፡፡ 1ኛ እውነታ - ወሳኙ ነገር አመጣጥህ (Background) ሳይሆን አካሄድህ (Your future) ነው፡- “ተሸናፊዎች በትናንትና ውስጥ ይኖራሉ፡፡ አሸናፊዎች ግን ከአለፈው በመማር፣ በዛሬዋ ቀን ላይ ሆነው በደስታ ለወደፊቱ ይሰራሉ” (Denis Waitley)፡፡ 2ኛ እውነታ - ወሳኙ ነገር እለድኛ መሆንህና አለመሆንህ ሳይሆን በእድል ላይ ያለህ አለካከት ነው፡- “በእድል አጽንቼ አምናለሁ፣ ጠንክሬ በሰራሁ ቁጥር ብዙ እድል እንደማገኝም አምናለሁ” (Thomas Jefferson)፡፡ “ትጋት የእድሎች ሁሉ እናት ነች” (Benjamin Franklin)፡፡ 3ኛ እውነታ - ወሳኙ ነገር ውስንነትህና ገደብህ ሳይሆን በዚያ ላይ የምትወስደው እርምጃ ነው፡- “ውስንነትህን ለይተህ እወቅ፣ ነገር ግን በፍጹም አትቀበለው”(Unknown Source)፡፡ join us...    @Ab_book    @Ab_book    @Ab_book

ለማን እንደምትሰጡ አስቡበት ጊዜያችሁን፣ ገንዘባችሁን፣ ትኩረታችሁን . . . ለማን እንደምትሰጡ በሚገባ አስቡበት፡፡ ሰዎቹ ብትሰጧቸው፣ ብትሰጧቸው የማይበቃቸውና በሰጣችኋቸው መጠን እንደገና የሚጠይቁ ከሆኑ ምናልባት እነዚህን እንቁ የሆኑ ሃብቶቻችሁን ትክክለኛ ባልሆነ ሰው ላይ እያፈሰሳችሁ ነው፡፡ ትክክለኛዎቹ ሰዎች . . . •  የምትሰጧቸውን ነገር ያከብራሉ እናንተንም ያመሰግኗችሁማል፡፡ •  የምትሰጧቸውን ነገር እንድ እድል እንጂ እንደመብታቸው አይቆጥሩትም፡፡ •  መስጠት ባልፈለጋችሁ ወይም ባልቻላችሁ ጊዜ አይነጫነጩም፣ አይከሷችሁም፡፡  •  በሰጣችኋቸው ነገር ተጠቅመው ያድረጉበታል እንጂ ባሉበት አይረግጡም፡፡ •  በተቻላቸውና አቅማቸው በፈቀደ መጠን ለእናንተም አንድን ነገር ለማድረግ ይሞክራሉ፡፡ አብዛኛውን ጊዜ ከላይ የተጠቀሱትንና መሰል ውብ ነገሮቻችሁን ካለፍላጎታችሁ ለሰዎች የመስጠት ሁኔታው ውስጥ ካገኛች . . . 1.  ምናልባት በሰዎች ተቀባይነት የማግኘት የማይሞላ ጥማት ስላለባችሁ ያንን ለማግኘት እየሞከራችሁ ነው 2.  ምናልባት ሰዎች እንደ ክፉ እና ጨካኝ ሰው ያዩኛል የሚል መሰረተ-ቢስ ፍርሃት ይኖርባችኋል ለአንዳንድ ሰዎች ካለምን ቅድመ-ሁኔታ ሁሉን ነገር ለመስጠት የመፈለጋችሁ ትክክለኛነት እንደተጠበቀ ሆኖ፣ ተገቢውን ነገር ለተገቢው ሰው፣ በተገቢው ጊዜና በተገቢው መጠን መስጠትን ካልተለማመዳችሁ ሁኔታው አንድ ቀን ሊጎዳችሁ ይችላል፡፡ join us...    @Ab_book    @Ab_book    @Ab_book

#ሰውን_ሰው_ያደረገው_ሕልም_ነው! አንድን ሀገር ታላቅ የሚያደርገው የያዘው ህልም ነው፡፡ ዕድሎች እንዲፈጠሩም የሚያደርገው ይህ ህልም ነው፡፡ ዜጎች ጠንክረው እንዲሰሩ የሚያደርጋቸው ይህ ህልም ነው፡፡ ዜጎች ስራ ፈጣሪዎች እንዲሆኑ የሚያደርጋቸው ይህ ህልም ነው፡፡ እንደ ሀገር ትልቅ ህልም ማስቀመጥ እና ዜጎች ያን ህልም የራሳቸው እንዲያደርጉት ማስረፅ ሀገርን ወደ ታላቅነት የሚወስድ መንገድ ነው፡፡ በልጆቻችን አእምሮ ውስጥ የምናስቀምጠው ህልም ምንድን ነው? የሀገራችን ህልም ብለን የምናስቀምጠው የዜጎቻችን ህልም ምንድን ነው? “ተስፋ የቆረጡ ሰዎች ተስፋ የሌላቸውን ነገሮች ያደርጋሉ፡፡” ችግረኛ ሰዎች የማይረቡ ነገሮችን ያደርጋሉ፡፡ ሰዎች ችግርን የሚታገሱት ሕልም ሲኖራቸው ነው! “ሰዎች ከታች ተነስተው ወደላይ መውጣት ከቻሉ፣ ከድህነት ወደ መካከለኛ መደብ መሸጋገር የሚችሉ ከሆነ ብሎም እጅግ በጣም የናጠጡ ሀብታሞች እንደሚሆኑ ተስፋ እና ዕድል ካላቸው፣ በሀብታሞች እና በድሆች መካከል ያለውን ልዩነት ይታገሱታል፡፡” አንተስ ወዳጄ ሕልምህ ምንድነው? ወዴትስ እየወሰደህ ነው? join us...    @Ab_book    @Ab_book    @Ab_book

ያን  ጊዜና አሁን ከዚህ በፊት … ያን ጊዜ … ማድረግ ያቅታችሁ የነበረ፣ አሁን ግን ማድረግ ወደመቻል የመጣችሁትን ቢያንስ አንድ ነገር ጥቀሱልኝ፡፡ ከዚህ በፊት … ያን ጊዜ … በፍጹም አያያዙ ያቅታችሁ የነበረና ሰላማችሁን ይነሳው የነበረ ሰው፣ አሁን ግን አያያዙን በሚገባ ወደማወቅ ብስለት ከማደጋችሁ የተነሳ ተረጋግታችሁና አስቸጋሪነቱን አልፋችሁ የምትሄዱትን ቢያንስ አንድ ሰው ጥቀሱልኝ፡፡ ከዚህ በፊት … ያን ጊዜ … መቆጣጠር ያቅታችሁ የነበረና አሁን ግን በቁጥጥር ስር እስከማድረግ የደረሳችሁትን አንድ የስሜታችሁን ሁኔታ ጥቀሱልኝ፡፡ ከዚህ በፊት … ያን ጊዜ … ብዙ ሞክራችሁ ማቆም ያቃታችሁንና አሁን ግን አቁማችሁት ራሳችሁን ያገኛችሁትን አንድ አጉል ልማድና ልምምድ ጥቀሱልኝ፡፡ ከዚህ በፊት … ያን ጊዜ … መጀመር አቅቷችሁ የተነበረና አሁን ግን ከብዙ ጥረት በኋላ የጀመራችሁትን አንድ መልካም ነገር ወይም ልምምድ ጥቀሱልኝ፡፡ ከዚህ በፊት … ያን ጊዜ … ከሰው እርዳታ ወይም አይዞህ ባይነት ውጪ መወጣት ያቅታችሁ የነበረና አሁን ግን በራሳችሁ ተነሳሽነት የምትወጡትን ሃላፊነት ጥቀሱልኝ፡፡ ከላይ ለተጠቀሱት ስድስት የእድገት ጠቋሚች ቢያንስ ለሶስቱ፣ “አዎን! አለኝ” የሚል መልስ ከሌላችሁ እድሜያችሁ በቆጠረ መጠንና ወራትና አመታት ባለፉ ቁጥር ከዚያው ጋር ሁለንተናዊ በሚባል ደረጃ የማደጋችሁ ሁኔታ አጠራጣሪ ነው፡፡ ይህንን ሁኔታ ዛሬውኑ ለመቀልበስ ካልወሰናችሁና እርምጃ ካልወሰዳችሁ ከጥቂት አመታት በኋላ ትጸጸታላችሁ፡፡ ችግራችሁን ለዩ … የማሸነፊያውን መንገድ እወቁ … የእርምጃ እቅድ አውጡ … ራሳችሁን አሳድጉ … የሚደግፋችሁ ሰው ፈልጉ … ጸሎት አድርጉ … ተንቀሳቀሱ … እደጉ … ተለወጡ! join us...    @Ab_book    @Ab_book    @Ab_book

#በፍጹም_ተስፋ_አትቁረጥ የKFC መስራች አይበገሬው አዛውንት ኮሎኔል ሳንደርስ:- ☞በ5 ዓመቱ አባቱ ሞተ ☞በ16 ዓመቱ ትምህርቱን አቋረጠ ☞በ17 ዓመቱ 4 የተለያዩ ስራዎቹን አጥቶ ነበር ☞ከ18 እስከ 22 ዓመቱ የባቡር ትኬት ቆራጭ ሆኖ ሰራ ነገር ግን አልተሳካለትም ☞የሀገሩን መከላከያ ቢቀላቀልም ተባረረ ☞ህግ ለመማር አመለከተ አልተሣካለትም ☞ለአንድ ኢንሹራንስ ድርጅት ግብይት ሰራተኛ ሆነ… ይህም አልተሳካለትም፡፡ ☞በ19 ዓመቱ ደግሞ ልጅ ወልዶ ነበር 2ዐ ዓመቱ ላይ ሚስቱ ልጃቸውን ይዛ ጥላው ሄደች፡፡ ☞በአንዲት ትንሽዬ ካፌ ምግብ አብሳይና ሰሃን አጣቢነት መስራት ጀመረ . . . ☞65 ዓመት ሲሞላው ጡረታ ወጣ ☞ጡረታ በወጣ በመጀመሪያው ቀን የ$105 ቼክ ከመንግስት ደረሠው... እሱ ግን የተረዳው መንግስት "ራስህን መመገብ አትችልም" እንዳለው ነበርና ከዚህ በኋላ መኖሩ ጥቅም እንደሌለው ራሱን አሣምኖ ራሱን የማጥፋት ሙከራ አደረግ... ይህም ሳይሆን ቀረ፡፡ ☞አንድ እለት ዛፍ ስር ቁጭ ብሎ ምኞቶቹን ወረቀት ላይ ማስፈር ፈለገ፤ የፃፈው ግን በህይወቱ ሊያደርጋቸው እየቻለ ሳያደርጋቸው ስለቀሩ ነገሮች ነበር... ከዚያም በእርግጠኝነት ማድረግ እንደሚችለው የሚያውቀውን አንድ ነገር አሰበ... ምግብ ማብሰል፡፡ ☞ወዲያውም የመንግስትን የውለታ ቼክ መልሶ $87 ተበደረ፡፡ ☞በዚያች ብድርም ቅመሞቹን ሸምቶ ፍራይድ ችክን አዘጋጀ... እናም በኬንታኬይ ለሚኖሩ ጎረቤቶቹ በራቸው ድረስ እየሄደ መሸጥ ጀመረ፡፡ ☞ግን በ68 ዓመቱ የኬንታኬይ ፍራይድ ችክን KFC ኢምፓየር መስራች ቢሊየነር ሆነ፡፡ #ቁምነገሩ- እድሜዬ ገፋ ብለህ በፍጹም ተስፋ እንዳትቆርጥ- በ68 አመትህም ታሪክ መስራት ትችላለህ፡፡ join us...    @Ab_book    @Ab_book    @Ab_book

የሀያኛው ምዕተ ዓመት ፈላስፋ ኤማኑል ሌቪነስ “The Face Of Others” ወይም “ሌላኛው ፊት” የሚል ሐሳብ ነበረው። አንድምታው በሌሎች ሰዎች ውስጥ ራስን ስለማግኛት መንገድን ይጠቁማል። “ሌላኛው ፊት” ሲል ከእኛ ውጪ ያለ “የሰው ገጽታ”ን ማለቱ ነው። ፊት የማንነት መገለጫ ዋና ይዘት የሰፈረበት ዐቢይ አካላዊ ስፍራ ነው። በመልካችን ከሌላው ሰው እንለያለን። ፊታችን ከኹሉ ቀድመው የሚታዩ እንደግንባር፣ ሽፋል፣ ዓይን፣ ጉንጭ፣ አፍ፣ አፍንጫ፣ ጆሮ፣ አገጭ… ያሉትን ይይዛል። ቀሪ አካላችንን በልብስ ስንሸፍን አብዛኛውን ጊዜ ከአንገት በላይ ገሃድ ነን። ይህም ማንነታችን በገጽታችን ላይ የተጻፈ መታወቂያ በመሆኑ ነው። በአገራችን ከፊት ጋር በተያያዘ የሚታወቅ አንድ ምሳሌያዊ አነጋገር አለ። እርሱም “ከፍትፍቱ ፊቱ” የሚል ነው። አባባሉ ከተነገረበት ዐውድ ውጪ ገጽታችን ያለ ድምፅ፣ ያለ ቃል ትርጉም ሰጪ መልእክትን እንደሚያስተላልፍ ይናገራል። ኤማኑኤል ፊት ለፊታችን ላለ “ፊት” ቦታ ይሰጣል። በቀን ውስጥ ብዙ የምናገኛቸው ፊቶች አሉ። እነዚያ ገጽታዎች በድን አይደሉም። በእስትንፋስ ይናገራሉ። ትላንት ላይ ሳይሆኑ ሕያው አሁን (living Presence) እና ኗሪ ናቸው። ያዩናል፣ ይሰሙናል፣ ይናገሩንማል። ራሳቸውን የሚገልጹት በቀላሉ አጠገባችን በመሆን ነው። ልክ እንደ መስታወት ናቸው። ራሳችንን ይበልጥ እንድናውቅ ዕድል ይሰጡናል። ፊት ለፊታችን ከተቀመጠ ሰው ጋር ጊዜ ስናሳልፍ ስለራሳችን ያለን ግንዛቤ ይዳብራል። የተጠመድንባቸውን ነገሮች ተወት አድርገን ቅርባችን ያለን ሰው እንመልከት። አጠገባችን የተቀመጠው ሰው በሕይወት መሥመር ላይ አንድ ጊዜ ብቻ የሚያልፍ ይሆናል። ስለዚህ በምን ዓይነት መንገድ ነው ልናስተናግደው የምንሻው? እንዲያወራ ዕድል እንሰጠዋለን? ወይስ ድምፁን ሳንሰማ፣ በተጠመድንበት ስልክ ተይዘን እንዳቀረቀርን መልኩን እንኳን በውል ሳናይ እናልፈዋለን? በምንሳፈርባቸው መጓጓዣዎች ላይ ሆነን ጎናችን ለተቀመጠ ሰው ሰላምታንና ፈገግታን አንቸርም። አኗኗራችን ከጥንቱ ፍጹም ተቀይሯል። ምናልባት በእድሜ የገፉ አዛውንት ያጋጥሙናል። አሥሬ እያዩን ሊያወሩን በአባታዊ ፈገግታ ቢመለከቱንም ጆሯችን ላይ የሙዚቃ ማዳመጫ ሰክተናል። ማኅበራዊ ግንኙነት የለንም። ወደ ሞት የምንገሰግሰው ትርጉም ሰጪ ሕያው ቅጽበታቶችንን እንደዋዛ እያሳለፍን ነው። አሁን ሰዎች እርስ በእርስ ለመለያየት የዘር ቆጠራ ውስጥ ገብተዋል። ለመወዳጀት ሳይሆን ለመለያየት ነጥቦች ይደረደራሉ። በአንድ ጠረጴዛ ዙሪያ መቼም መቀመጥ የማይችሉ ሰዎች እንዳሉ እንሰማለን። ጽንፍ የወጣ መለያያት ከየት እንደሚያደርስ አናውቅም። ነገር ግን ያስገርማል። ወደ ኋላ ነው ወይስ ወደ ፊት ነው የምንጓዘው? የሰው አካል ይዞ የእስስት ልብ የያዘ ለስም አጠራር የሚከብድ አካል አለ ወይ? ጀርባ ተሰጣጥተን በተለያየንባቸው የአስተሳሰብ አቋሞች ስንቆዝም፤ ቢያንስ ቢያንስ ሰው መሆናችን እንዴት አንድ አያደርገንም? አርስጣጣሊስ “Things are contained of both essential and accidental qualities” ይላል። መሠረታዊ መለያ (essential quality) ያለን ሰዎች ነን። ድንገታዊ መለያ (Accidental quality) ላይ ግን እያንዳንዳችን እንለያያለን። ሰውነታች ለሁላችንም መሠረታዊ መለያችን (essential) ነው። የተወለድንበት ስፍራ፤ ብሔራችን፤ አካላዊ ቁመናችን፤ የቆዳ ቀለማችን… ድንገተኛ መለያ ነው። ሰው መሆን ግን በመሠረታዊነት ያገኘነው ነው። በሥጋ ከመገለጣችን በፊት የምናውቀው ነገር የለም። ስንወለድ ያገኘናቸው ተዋረዳዊ ማንነቶች ልዕለ ሰብእ አያደርጉንም። የትኛውም ብሔርና የቆዳ ቀለም ሰው ከመሆን አይበልጥም። ሰው ለመሆን ከምንሰጠው ትርጓሜ በላይ ለጾታችን፣ ለቀለማችን፣ ለብሔራችን፣ ለሃይማኖታችን… ያለን አስተሳሰብ ከአመዘነ እንጠፋፋለን። አንዳችን ከአንዳችን ጋር የሥጋዊ እንጂ የመንፈስ ዝምድና አይኖረንም። ከእኛ በተለየ ስፍራ የተወለደን፣ ያደገን ሰው በመጤነት እንፈርጀዋለን። ዓይኖቻችን እንደ እኛው ሥጋ የለበሰ ሰው ሳይሆን ብሔርና ሃይማኖት ያያሉ። ከእኛ የተለየ የመሰለንን ሰው ቤት ለእንግዳ ብለን አንቀበልም። ይልቁንም ፊታችንን ኮሶ እናደርግበታለን። ሳይውል ሳያድር ከተማችንን ለቅቆ እንዲወጣ እንገፋዋለን። በዓይኖቻችን ፊት “መጤ” ነው። ነገር ግን እዚህ ዓለም ላይ መጤ ያልሆነ ማን ነው?” ብሎ ፈገግ አለና ሰዓቱን ተመለከተ። ቀና ሲል ጥግ ላይ ጸጉሩን እየጠቀለለ ውይይቱን ሲያደምጥ የነበረው ግሩም በጣቱ የጥያቄ አለኝ ምልክት አሳየው። “ሰዓታችን ተገባዷል። ጥያቄውን ሰምተን ምላሹን በይደር እናቆየዋለን” ብሎ ዕድል ሰጠው። “ሰው እንዴት ይወድቃል?” ሲልም ጠየቀ። “ቆንጆ ጥያቄ ነው። ምላሹን በቀጣይ ስንገናኝ ረዘም ካለ ተረክ ጋር አሰናስለን እናያለን። አያይዘንም ስለድርጊት እናወራለን።” ብሎ ተሰናብቷቸው ወጣ። Yonas zewde kebede ፍልስፍና join us...    @Ab_book    @Ab_book    @Ab_book