ᴇʟɪᴀꜱ ᴍᴇꜱᴇʀᴇᴛ
📈 تحلیل کانال تلگرام ᴇʟɪᴀꜱ ᴍᴇꜱᴇʀᴇᴛ
کانال ᴇʟɪᴀꜱ ᴍᴇꜱᴇʀᴇᴛ (@eliasmeseret) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 133 033 مشترک است و جایگاه 1 606 را در دسته اخبار و رسانهها و رتبه 210 را در منطقه أثيوبيا دارد.
📊 شاخصهای مخاطب و پویایی
از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 133 033 مشترک جذب کرده است.
بر اساس آخرین دادهها در تاریخ 05 سپتامبر, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 851 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 43 بوده و همچنان دسترسی گستردهای حفظ شده است.
- وضعیت تأیید: تأیید شده (به صورت رسمی توسط تلگرام)
- نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 33.22% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 20.61% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب میکند.
- دسترسی پستها: هر پست به طور میانگین 44 200 بازدید دریافت میکند. در اولین روز معمولاً 27 414 بازدید جمعآوری میشود.
- واکنشها و تعامل: مخاطبان بهطور فعال حمایت میکنند؛ میانگین واکنش به هر پست 2 323 است.
📝 توضیح و سیاست محتوایی
نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاههای شخصی توصیف میکند:
“Journalist-at-large”
به لطف بهروزرسانیهای پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 06 سپتامبر, 2026)، کانال همواره بهروز و دارای دسترسی بالاست. تحلیلها نشان میدهد مخاطبان بهطور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته اخبار و رسانهها تبدیل کردهاند.
در حال بارگیری داده...
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 07 سپتامبر | 0 | |||
| 06 سپتامبر | +9 | |||
| 05 سپتامبر | +43 | |||
| 04 سپتامبر | +79 | |||
| 03 سپتامبر | +56 | |||
| 02 سپتامبر | +68 | |||
| 01 سپتامبر | +64 |
| 2 | አቶ ገዱ አንዳርጋቸውን ያሳያል የተባለ አንድ ቪድዮ ሲዘዋወር ተመለከትኩ፣ ቪድዮውን የለጠፉት ሰዎች ደግሞ 'የቀድሞው የክልል ፕሬዝደንት አሁን ላይ ይህን ስራ አሜሪካ እየሰሩ ነው' በሚል ለማሸማቀቅ ያሰቡ ይመስላል።
ቪድዮው የእውነት ከሆነ ትክክለኛ መልዕክቱ ግለሰቡ እንደ ሌላው ሳይዘርፉ፣ በውጭ ሀብት ሳያካብቱ እንዲሁም በዱባይ፣ በናይሮቢ፣ በአውሮፓ እና በአሜሪካ የህዝብ ሀብት ይዘው እንዳልሸሹ፣ አሁን ላይ ደግሞ በነፃ ህሊና ስራ ሰርተው እየኖሩ እንደሆኑ የሚያሳይ ነው።
ይህን መልዕክት የለቀቁ ሰዎች ስራ ሰርቶ ከሚኖር አንድ ባለስልጣን ከነበረ ግለሰብ ይልቅ የህዝብን ሀብት ዘርፎ ዱባይ ላይ ቪላ በመግዛት የሚንደላቀቅ ባለስልጣንን አክብረው እና አድንቀው የሚኖሩ ለመሆናቸው ምስክር አይሻም።
@EliasMeseret | 55 956 |
| 3 | ፎቷቸውን ትኩር ብዬ ተመለከትኩት፣ ህይወታቸው ገና ከፊታቸው የሚጠብቃቸው ወጣቶች እንደሆኑ ያስታውቃሉ። መሀል ላይ ያለው ወጣት ድንጋጤው ይጋባል፣ ሰው ባላጠፋው ጥፋት ሲከሰስ የሚሰማው ስሜት።
ሁሉም 'ፋኖ ናችሁ' ተብለው ተረሸኑ፣ አስከሬናቸው እንኳን እንዳይነሳ ለቀናት ተከለከለ።
ተመስገን ጌታቸው፣ ይታገሱ አሰግደው፣ ግዛው ግርማዬ!
ነፍስ ይማር!
https://www.meseretmedia.org/p/346 | 97 536 |
| 4 | መንግስትን መቃወም እና የህዝብ ተቋማትን ማጥቃት ሙሉ በሙሉ የተለያዩ ነገሮች ናቸው!
እንደ የኢትዮጵያ አየር መንገድ እና ንግድ ባንክ ያሉ የህዝብ ሀብቶች ላይ ያተኮሩ ጥቃቶች ድንቁርና ካልሆኑ ምን ሊባሉ ይችላሉ? መንግስታት ይመጣሉ፣ ይሄዳሉ: ተቋማቱ ግን የህዝብ ሆነው ይኖራሉ። የሀገራችንን ሰንደቅ አላማ ይዞ አለምን የሚዞርን ታላቅ አየር መንገድ አርማ መሬት ላይ ጥሎ መርገጥ ከቀውስነት የዘለለ ትርጉም ያለው አይመስለኝም።
@EliasMeseret | 110 548 |
| 5 | ከአሜሪካዋ Maine ግዛት ዋና ገዢ (Governor) ጃኔት ሚልስ ጋር ትናንት በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ቃለ-መጠይቅ አርጌ ነበር፣ ዝርዝሩን ከታች ይገኛል ⤵️
https://www.amjamboafrica.com/amjambo-exclusive-gov-mills-vows-to-protect-maines-immigrant-communities-after-fatal-ice-shooting/ | 121 740 |
| 6 | የቀድሞው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስፈፃሚ፣ አሁን ላይ ደግሞ በአሜሪካ የግዙፉ Delta Air Lines ስትራቴጂክ አማካሪ የሆኑት አቶ ተወልደ ገብረማርያም ከአየር መንገዳችን ከለቀቁ ወዲህ የመጀመርያውን ሰፊ ቃለ መጠይቅ ከ LTM- Network/Amjambo Africa ሚድያችን ጋር ቆይታ አድርገዋል።
ሙሉው ቃለ መጠይቅ ከቀናት በኋላ በድረ-ገፃችን እና ሶሻል ሚድያ ገፆቻችን ላይ ይለቀቃል፣ ይጠብቁን amjamboafrica.com
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/share/1JeWXnEfkK/
ኤክስ: https://x.com/AmjamboAfrica
ዋትሳፕ: Follow the Amjambo Africa channel on WhatsApp: https://whatsapp.com/channel/0029VbCHMDG0AgWGXjzVk03K
ኢንስታግራም: https://www.instagram.com/amjamboafrica?igsh=MWt2eDV1aWx0OHIyYg== | 104 498 |
| 7 | 'ሀገር እየመከረ ነው' በሚባልበት ወቅት ንፁሀን ዜጎች ላይ እንዲህ አይነት የጭካኔ ተግባር መፈፀም ምን ማለት ነው?
https://t.me/meseretmedia/1787 | 90 851 |
| 8 | #የግልምልከታ
"ጽምዶ" የተባለው ስብስብ በጋራ ጥቅምና በሰላም ላይ የተመሰረተ ሳይሆን የውስጥ ችግሮችን በኃይል ለመፍታት ከውጭ ኃይል ጋር መጣመርን የመረጠ ሀይል መሆኑን እያሳየ ነው፣ ይህ አካሄድ ደግሞ ታሪካዊ ስህተት እና የሕዝብ እልቂት ምንጭ መሆኑ የማይቀር ነው።
የውስጥ የፖለቲካ ልዩነቶችንና ቅራኔዎችን በውይይት፣ በዕርቅና በሰላማዊ መንገድ በሀገር ውስጥ ከመፍታት ይልቅ የውጭ ኃይላትን ጦርና ጋሻ ጋብዞ የገዛ ወገንን ለማስጨፍለቅ ማሰብ እኩይ ተባር ነው።
ቀደም ሲል የኢትዮጵያ መንግሥት ከኤርትራ ጋር በመጣመር በራሳችን ሕዝብ ላይ ያደረሰውን ሰብአዊ ቀውስና ስቃይ ስንተች የነበረውም ለዚሁ ነው ምክንያቱም እንዲህ ያሉ አሰላለፎች የሕዝብን ሕልውና የሚያጠፉ፣ ሀገርን ለባዕድ ጣልቃ ገብነት አሳልፈው የሚሰጡና ጠባሳቸው ለትውልድ የማይሻር በመሆኑ ነው።
በመሆኑም አሁንም ሆነ ወደፊት ማንኛውም አካል በየትኛውም ስም “ጽምዶ” የሚል ስብስብ ፈጥሮ የሕዝብን ስቃይና መከራ የሚያበዛ ከሆነ በምንም ዓይነት መመዘኛ ተቀባይነት ሊኖረው አይችልም። የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ሲባል የሰላማዊ ሰዎችን ሕይወት መገበሪያ ማድረግና ሀገርን ማፈራረስ የታሪክ ተጠያቂነትን ያስከትላል።
እውነተኛ መፍትሔ ሊመጣ የሚችለው ከውጭ ኃይላት በሚገኝ የጦር ድጋፍ ሳይሆን በሀገር ውስጥ ኃይሎች መካከል በሚደረግ እውነተኛና ሁሉን አቀፍ ውይይት ብቻ እንደሆነ በጽኑ አምናለሁ፣ ሰላም የሚገነባው በጠመንጃ አፈሙዝ ሳይሆን በሰላማዊ ድርድር ነው።
@EliasMeseret | 105 684 |
| 9 | ካለፉት ሶስት ወራት ወዲህ በ Editor-in-Chief (ዋና አርታዒ) የስራ መደብ የሙሉ ግዜ ስራ የጀመርኩበት LTM-Network የአሜሪካዋ ሜይን ግዛት ውስጥ በሰባት ቋንቋዎች መረጃ የሚያቀርብ ብቸኛው እና በአይነቱ ትልቁ ጋዜጣ ነው። አሁን የተቋሙ ዋና ትኩረት የዲጂታል አቅሙን ማስፋት እንዲሆን አቅጣጫ አስቀምጠን እየሰራን ነው፣ አንዱ ደግሞ በወር ሁለት ግዜ *በነፃ* በቀጥታ ወደ አንባቢዎች ኢሜይል የምንልካቸው እና እኔ ራሴ የማዘጋጃቸው Newsletter ናቸው።
ዛሬውኑ ተመዝግበው መረጃዎቻችንን በነፃ ያንብቡ: ሊንክ ⤵️
https://www.amjamboafrica.com/newsletter/ | 110 408 |
| 10 | Happy 250th Birthday, America! 🇺🇸
Most of us are grateful to now call this great nation home. While no country is without its challenges, the United States remains a place where people can pursue opportunity, are treated with dignity, and enjoy freedoms that inspire hope.
Here's to the enduring ideals that continue to bring people from around the world together.
Happy Independence Day!
@EliasMeseret | 113 983 |
| 11 | Stepping into age 43 with gratitude!
Thank you everyone for the warm birthday wishes 🙏🏽
@EliasMeseret | 104 829 |
| 12 | Having an incredible time at the JRAD and Joe Russo's Almost Dead concert at Thompson's Point here in Portland, Maine!
So grateful for all the amazing people stopping by to show love for our publication. Portland, you have a beautiful community!
#PortME #AmjamboAfrica #Maine
https://whatsapp.com/channel/0029VbCHMDG0AgWGXjzVk03K/216 | 100 300 |
| 13 | ድሬዳዋ ላይ በግሉ ለፓርላማ ሊወዳደር እንቅስቃሴ ጀምሮ የነበረው ዶ/ር ሀብታሙ አለሙ በምስሉ ላይ በሚታየው መልኩ የስም ማጥፋት፣ ዛቻ እንዲሁም ማስፈራርያዎች ከደረሱት በኋላ ራሱን ከምርጫው አገለለ። ለምርጫ ቦርድ በተከታታይ አቤቱታ ቢያስገባም ምንም ሊፈይዱ አልቻሉም፣ አሁን ደግሞ ከምርጫው እንዲወጣ ያስገደዱት የከተማው አመራሮች ለስራ ወደ ድል ጮራ ሆስፒታል ሲያመራ አፍነው ወስደውታል።
ፖሊሶቹ ምንም አይነት የፍርድ ቤት የፍተሻም ሆነ የመያዣ ማዘዣ ሳይኖራቸው "በስልክ የተሰጠን የበላይ አመራር ትዕዛዝ ነው" የሚል ምላሽ ሰጥተዋል። ከሶስት ቀን በፊት ፍርድ ቤት አቅርበውት ዳኞቹ "አንተን ብሎ ዶክተር..." በማለት ሲያንቋሽሹት ነበር።
እንኳን ሰው ምርጫ ተወዳድሮ ሊያሸንፍ ለመወዳደር በማሰቡ ብቻ ስቃይ የሚያይበት የድሬዳዋ አመራር አቶ ከድር ጁሀር ምላሽ ሊሰጥበት ይገባል።
በስምሉ ላይ የሚታዩትን ቅንብሮች በመስራት ሲለቁ የነበሩት ከተማው ያደራጃቸው የቀን እና የለሊት የታክሲ ማህበራት አባላት የሆኑ ካድሬዎች ናቸው።
@EliasMeseret | 80 053 |
| 14 | ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2005፣ 2008፣ 2009፣ 2010፣ 2012 በቀድሞው ጠ/ሚር አቶ መለስ ዜናዊ ዘመን እንዲሁም በ2015 እና በ2017 በቀድሞው ጠ/ሚር አቶ ሐይለማርያም ደሳለኝ ዘመን በቡድን ሰባት (G 7) ሀገራት ስብሰባ ላይ ተሳትፋ ነበር። ዘንድሮ በፈረንሳይ እየተካሄደ ባለው ስብሰባ ኬንያ በፕሬዝደንቷ ስትወከል ግብፅ ደግሞ በታሪኳ ለሁለተኛ ግዜ በመሪዋ ተወክላ ተገኝታለች።
ኢትዮጵያ በዚህ ጉባዔ ላይ አለመሳተፏ እና ሙሉ በሙሉ መቅረቷ በዲፕሎማሲውና በኢኮኖሚው ረገድ ስጋት ይፈጥራል። ይህ ይበልጥ አሳሳቢ የሚሆነው የዓለምን የፖለቲካና የኢኮኖሚ አቅጣጫ የሚወሰኑ ዋና ዋና ዓለም አቀፍ ውሳኔዎች፣ የዕዳ ቅነሳ ስትራቴጂዎችና የልማት አጀንዳዎች በሚቀረጹበት በዚህ ተፅዕኖ ፈጣሪ መድረክ ላይ የኢትዮጵያ ድምፅ ሳይሰማ በመቅረቱ ነው።
ጎረቤት አገር ኬንያ በተደጋጋሚ የክብር እንግዳ ሆና ጥሪ እየተደረገላት ባለበት እና ሌላው ቀርቶ ግብፅ በታሪኳ ለሁለተኛ ጊዜ ብቻ በፈረንሳዩ የኤቪያን (Évian) የG7 ጉባኤ ላይ እንድትሳተፍ በተጋበዘችበት ወቅት ኢትዮጵያ አለመገኘቷ የዲፕሎማቲክ የቤት ስራ እንደሚጠብቀን አመላካች ነው።
የኢትዮጵያ ከዚህ መድረክ መራቅ አገሪቱ ቀደም ሲል በአፍሪካ ቀንድ የነበራትን የጂኦፖለቲካዊ መሪነት ሚና እና በዓለም አቀፍ ደረጃ የነበራትን ዲፕሎማሲያዊ ተሰሚነት ዝቅ ማድረጉ አይቀርም። እንደ የአየር ንብረት ለውጥ፣ የፋይናንስ ድጋፍ እና የቀጣናው ደህንነት ባሉ ወሳኝ አጀንዳዎች ላይ ያላትን የመሰማት አቅም ይቀንሳል።
የኢትዮጵያ ድምፅ ከፍ ብሎ እንዲሰማ የቤት ስራው በደንብ ይሰራ።
@EliasMeseret | 68 781 |
| 15 | ብዙ አትሌቶች የውጭ ሀገር ማናጀሮቻቸውን ይፈራሉ፣ በደል ሲፈፀምባቸው እንኳን ውጠው ያልፋሉ እንጂ መልሰው አይናገሩ። Not Kenenisa Bekele!
ከጥቂት አመታት በፊት የቀነኒሳ ማናጀር ጆስ ሔርመንስ ለሚድያ የማይመጥን እና ወደ ሚድያ የማይወጣ ጉዳይ ሚድያ ላይ አወጣ። ቀነኒሳ ይህን አካሄድ ዝም ብሎ መመልከት አልፈለገም፣ እውነትም ከእርሱ ጋር ነበረች። በበርካቶች ዘንድ ግርምትን የፈጠረ እና በአትሌቲክስ ተንታኞች 'ደፋር' ያስባለ ቃለ መጠይቅ አድርጌለት በወቅቱ ትልቅ ዜና ሆነ፣ ጆስ ሔርመንስ ምላሽ አልሰጠም።
"With those remarks, Jos Hermens acted like someone who lost a gamble."
ቀነኒሳ ኋላ እንደነገረኝ ግንኙነታቸው ከዛ በኋላ ክብሮ (respectful) ሆኖ ቀጠለ (ዜናው: https://www.letsrun.com/news/2017/10/kenenisa-bekele-dismayed-jos-hermens-comments-professionalism-berlin-marathon-vows-break-world-record/)
"ብዙ ደሀዎች መንገድ ላይ በበዙበት በዚህች ሀገር ውስጥ በጣም ውድ እና ውብ መኪና ይዞ ከቤት መውጣት እጅግ ከባድ ነው፣ ህሊናህ አይፈቅድም። ያንን መኪና ለማን ነው የማሳየው?። እዚያ መንገድ ላይ ፈስሰው ያሉት አባትህ፣እናትህ፣ወንድም እህትህ ፣ ዘመድ አዝማዶችህ ናቸው" ያለው ንግግሩም የብስለቱን ጥግ ያሳያል።
መልካም ልደት አንበሳው!
@EliasMeseret | 73 059 |
| 16 | በአንዳንድ ጉዳዮች አስተያየት ስሰጥ 'በወያኔ ግዜ የት ነበርክ?' የሚሉ አስተያየቶችን አልፎ አልፎ አያለሁ። በወያኔ ግዜ አሁን ላይ በድምር 1 ሚልዮን ገደማ የደረሰው የማህበራዊ ሚድያ ገፆቼ (ፌስቡክ፣ ኤክስ፣ ቴሌግራም እና ዋትሳፕ) አልነበሩኝም፣ ትንሽ ተከታይ ያለው አንድ የፌስቡክ ገፅ ነበረኝ። ታድያ በዛን ግዜ የመንግስትን ግድያ፣ አፈና፣ ሰብዓዊ መብቶች ጥሰት ወዘተ በአለም ዙርያ ለሚገኙ ቢሊዮኖች የማጋልጠው በሶሻል ሚድያ ሳይሆን በምሰራቸው ዜናዎች ነበር። ያኔ የት ነበርክ ለምትሉ ምላሹ በጥቂቱ ይኸው ⤵️
1. Several dozen shot dead in weekend protests across Ethiopia
https://apnews.com/general-news-6b3ca469c63941ebbfbbd321705aece1
2. Group: Ethiopia's security forces killed over 400 protesters
https://www.ksl.com/article/40229325/group-ethiopias-security-forces-killed-over-400-protesters
3. HRW: Media suppression in Ethiopia curbing democratic space
https://www.sandiegouniontribune.com/2015/01/22/hrw-media-suppression-in-ethiopia-curbing-democratic-space/
4. Ethiopia: At least 11 students killed in violence
https://www.yahoo.com/news/ethiopia-least-11-students-killed-violence-105243525.html?guccounter=1&guce_referrer=aHR0cHM6Ly93d3cuZ29vZ2xlLmNvbS8&guce_referrer_sig=AQAAAMq2WlBdAf1NcDJCHmtvM0ma-HBF8HXZx5-x9akKLeP6s_XJnAf5eA6Pi7OGlNdTc3lGlEkQKDwKoD--yzudyAu9Es9fGZpLdoxdK2HqO9vQ_nCF8H4TceZT3XOTrnuk2J30NaWZ2JZKxTsrS5XTHl0bOJzFdNsZWv0PkLtr2h6Z
5. Ethiopia targets opposition who met with European lawmakers
https://gebremariam3.rssing.com/chan-50763547/article1865.html?nocache=0
6. Ethiopia jails 20 Muslims that it accused of pursuing Sharia state
https://apnews.com/general-news-e65d8d01cf6146038b5cf37385111d34
7. New report says Ethiopia blocked social media, news sites
https://www.njherald.com/story/news/nation-world/2016/12/13/new-report-says-ethiopia-blocked/3127598007/
8. Ethiopia detains foreign pilots in a vintage air rally
https://www.foxnews.com/world/2016/11/24/ethiopia-detains-foreign-pilots-in-vintage-air-rally.html
9. Ethiopia arrests blogger, academic critical of government
https://www.heraldonline.co.zw/ethiopia-arrests-blogger-critical-of-government/
10. Fifty two confirmed dead in stampede at Ethiopia religious event
https://www.timesofisrael.com/52-confirmed-dead-in-stampede-at-ethiopia-religious-event/
11. Ethiopian marathoner remains in US on visa after protest
https://apnews.com/general-news-af404d3dbc4e4ab0b048f4f423c7649e
12. Groups urge UN Human Rights Council over Ethiopia protests
https://www.sandiegouniontribune.com/2016/09/08/groups-urge-un-human-rights-council-over-ethiopia-protests/
... በመቶዎች የሚቆጠሩ ሌሎች የወቅቱን መንግስት ድርጊት በተመለከተ የተሰሩ ዜናዎችን ማቅረብ ይቻላል።
ያኔም፣ ዛሬው እዛው አቋም ላይ ነን። መንግስት ቢቀያየር ለህዝብ እና ሀገር እውነት መቆም የሙያው ግዴታ ነው።
@EliasMeseret | 71 309 |
| 17 | بدون متن... | 58 149 |
| 18 | 100 ፐርሰንት እውነት የሆነ ግሩም አባባል ነው!
ቁጭ ብሎ ለመነጋገር መቼም አይረፍድም፣ በንግግር የሚያምን ትውልድ የሰው ልጅ ህይወት እንዳይጠፋ ያደርጋል። ተነጋገሩ፣ የቤት ችግራችሁን በቤት ውስጥ ፍቱ።
@EliasMeseret | 71 994 |
| 19 | 2 ቢልየን ብር የሚሸጥ የሆስፒታል መሬት አፈፍ ያረገ ሰው አሸዋ መድፊያ አይቸግረውም እኮ!
አፍንጫ ዳበስ፣ ዳበስ አይሰራም። አሁን የጋንዲ ሆስፒታልን መሬት ትመልሳለህ ወይስ አትመልስም?
ልጅቷ ግን... "ከንክኖሀል" 😂
@EliasMeseret | 62 387 |
| 20 | ለስራ ወደተዛወርኩበት ስቴት ከጥቂት ሳምንታት በፊት አዲስ ታርጋ አውጥቼ ነበር፣ ስንት ከፈልኩ? 25 ዶላር (4,200 ብር ገደማ)! ታርጋውን ለማተም ስንት ይሆን ብዬ ስጠይቅ "ምናልባት 5 ዶላር ቢሆን ነው፣ ቀሪው ፕሮሰስ ማረጊያ ነው" የሚል ምላሽ አገኘሁ።
ከዛ ወደ ቻይና የታርጋ አከፋፋዮች ድረ-ገፅ ገባ ብዬ ስማትር እጅግ ዘመናዊ የፊት እና የኋላ ታርጋ ከአንድ እና ሁለት ዶላር ጀምሮ እስከ 5 ዶላር ይሸጣል። ታድያ ታርጋ ኢትዮጵያ ውስጥ ለምንድነው 350 ዶላር ወይም 60,000 ብር የሚሸጠው?
መንግስት ከአይ ኤም ኤፍ ብድር ጋር በተያያዘ እየተከተለው ያለው አቅጣጫ ብድር ለማግኘት ከየትኛውም ህዝብን ለማገልገል ከተቋቋሙ ተቋማት በመቶዎች እና ሺዎች እጥፍ ዋጋ በማስከፈል ትርፍ ማግኘት ነው። የተሽከርካሪ አገልግሎት፣ የኢሚግሬሽን አገልግሎት፣ የኤሌክትሪክ፣ የውሀ... ወዘተ ዋና አላማቸው ትርፍ ሳይሆን ለህዝብ አገልግሎት መስጠት ነበር፣ እየሆነ ያለው ግን በአመቱ መጨረሻ ህዝብን የሚያሳብድ ክፍያ ጠይቀው የትርፍ ሪፖርት ማቅረብ ሆኗል።
በመጪው አመት 1.5 ትሪሊየን ብር ታክስ ይሰበሰባል ተብሏል፣ ይህ ከአምና የመንግስት አጠቃላይ በጀት በላይ ነው። በተያዘው አካሄድ ሊሳካ ይችላል፣ አብዛኛው ህዝብ ግን ከአመት አመት ከድህነት ወደ ድህነት ወለል እየወረደ ይገኛል።
@EliasMeseret | 71 185 |
