8 632
مشترکین
+324 ساعت
+267 روز
+19430 روز
آرشیو پست ها
ለሁሉም ወረዳ ትምህርት ጽ/ቤቶች እና 2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች ከላይ በተላከው የሪፖርት ቢጋር መሠረት የ2018 ዓ.ም ማጠቃለያ ሪፖርት በተባለው ቀን ገቢ እንድታደርጉ እናሳስባለን።
+8
በዳግማዊ ሚኒሊክ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በከተማ ግብርና ስራ ውጤት እየተመዘገበ እንደሚገኝ ተገለጸ፡፡
(ሰኔ 3/2018 ዓ.ም) አራዳ ክፍለ ከተማ የሚገኘው የዳግማዊ ሚኒሊክ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ከመደበኛው የመማር ማስተማር ስራ ባሻገር በከተማ ግብርና ስራ ውጤታማ በመሆን ላይ እንደሚገኝ አስታውቋል።
በትምህርት ቤቱ ተግባራዊ የሆነው የከተማ ግብርና በዋናነት በመምህራን ተግባራዊ እየተደረገ መሆኑን የትምህርት ቤቱ ርዕሰ መምህርት ጋዲሴ ደረሰ ገልጸው ፕሮግራሙ በትምህርት ቤቱ ተግባራዊ መደረጉ ተማሪዎች በንድፈ ሀሳብ የተማሩትን ትምህርት በተግባር የማየት እድል እደፈጠረላቸው አመላክተዋል።
ቀን 01/10/2018 ዓ.ም
ለሁሉም የመንግስት ተቋማት ሀላፊዎች (የመ/ደረጃ፣ 2ኛ ደረጃ እና ለወረዳ ት/ጽ/ቤት)
ከነገ ማክሰኞ 2/2018 ዓ.ም ጀምሮ ከሪፎርም፣ አገልግሎት አሰጣጥና ከኬፒአይ አንፃር ድጋፍ ክትትልና ምዘና ስለሚደረግ በተቋማችሁ ተመድበው የሚመጡ ባለሙያዎች ጋር በጥሩ ተግባቦት እንድታጠናቅቁ እያልን አስፈላጊውን መረጃ አደራጅታችሁ እንድትጠብቁ እናሳስባለን፡፡
ለሁሉም የመንግስት ት/ቤት በዚህ በላክንላችሁ የኮምባይንድ ዴስክ ድልድል መሠረት እንድትረከቡ።ነገር ግን ከዚህ ከተመደበላችሁ ውጪ አልፋችሁ ብትረከቡ ለሚፈጠረዉ ቸግር ሀላፊነቱን የምትወስዱ መሆኑን ለማሳወቅ እንወዳለን።
ማሳሰቢያ፡ ከላይ የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ባስቀመጠዉ አቅጣጫ መሰረት እስከ ግንቦት 28 2018 ዓ.ም እስከ 6 ስአት ድረስ የትምህርት ቤታችሁን አፈጻጸም በማየት ከላይ የተጠቀሱትን ጉዳዮች በማካተት በደብዳቤ እንድታሳዉቁን እናሳስባለን፡፡
የአንደኛ ሴሚስተር ውጤት ያላስገቡ ትምህርት ቤቶችን በተመለከተ
እንደሚታወቀው የ2018 ዓ.ም የአንደኛ ሴሚስተር ውጤት በተቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ሁሉም ትምህርት ቤቶች እንዲያስገቡ በተደጋጋሚ የግዜ ሰሌዳን በማራዘም መመሪያ ተሰጥቶ ነበር። ይሁን እንጂ፣ እስካሁን ድረስ ውጤት ያላስገቡ ትምህርት ቤቶች መኖራቸው ተረጋግጧል።
ስለሆነም ይህ መልህክት እንደደረሳችሁ የሚከተሉትን ነጥቦች በአስቸኳይ እንድትፈጽሙ እናሳውቃለን፦
1. ውጤት ያላስገቡ ትምህርት ቤቶች በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ለምን ውጤት ማስገባት እንዳልቻሉ በደብዳቤ ማብራሪያ እንዲሰጡ ማድረግ፤
2. ትምህርት ቤቶቹ በሚሰጣቸው ተጨማሪ የጊዜ ገደብ ውስጥ ውጤቱን እንደሚጨርሱ የሚገልጽ ደብዳቤ እዲያስገቡ ይደረግ፤
3. ውጤት የሚገባበትን ቀጣይ የጊዜ ሰሌዳ በቀጣይ የምናሳውቅ ይሆናል፤
4. ማሳሰቢያ፡ ይህን አሰራር ተከትለው ውጤት በማያስገቡ ትምህርት ቤቶች ላይ ለሚከሰተው ማናቸውም ችግር ወይም መዘግየት ትምህርት ቤቱ ኃላፊነቱን የሚወስድ መሆኑን እናሳውቃለን።
ለመምህራን የባስ ዲጂታል መታወቂያ ተጠቃሚዎች በሙሉ፦
የዲጂታል መታወቂያ አገልግሎቱ የሚሰጠው ከሰኞ እስከ ቅዳሜ ብቻ መሆኑን አውቃችሁ፣ ከዚህ ቀደም በነበረው አሰራር መሰረት እንድትጠቀሙበት እናሳስባለን።
የስብሰባ ጥሪ
ውድ የመም/ራን ልማት እና የት/ቤት መሻሻል ም/ር/መምህራን እንደምን አደራችሁ ነገ አርብ 21/9/2018 ዓ.ም ወርሀዊ የግንኙነት ቀናችን ስለሆነ ሁላችንም በ3፡00 ሰዓት በዳ/ሚኒሊክ የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት እንድትገኙ
የመወያያ አጀንዳ
1.የተከታታይ ሙያ ማሻሻያ
2.የሂሳብና እንግሊዘኛ ትምህርት
3.ሰላማዊ የመማር ማስተማር
4.ምገባ እና ዩኒፎርም በተማሪዎች መቅረት እና ማቋረጥ ላይ ያመጣው ተጽዕኖ
የስልጠና ጥሪ!!
ለ11 ክ/ከ ተወማ
ጉዳዩ የስልጠና ጥሪን ይመለከታል
በሁሉም የመንግስት 1ኛ እና መካከለኛ ደረጃ እንዲሁም 2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች እሚገኙ የተማሪ ወላጆች ማህበር ሠብሳቢዎች ቅዳሜ 22/09/2018 ት/ቢሮ 12ኛ ፎቅ ከጠዋቱ 2:30 እንዲገኙ በየክፍለ ከተማችሁ ባሉ ት/ቤቶች ጥሪ እንድተላለፍ አሳውቃለሁ።
አመሠግናለሁ
ሀሠን ሺፋ
የአአከአ ተማሪ ወላጆች ማህበር ፕሬዚዳንት
የሥልጠና ጥሪ
ለሁሉም የመንግስት ት/ቤት ዋና ርዕሳነ መምህራን ሐሙስ በቀን20/9/2018ዓ.ም የአራዳ ክፍለ ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት ሥልጠና ስለሚሰጥ ከጥዋቱ 2፡00 እንድትገኙ ለመግለፅ እንወዳለን፡፡
1. ሥልጠና የሚሰጥበሀት ቦታ ትምህርት ጽ/ቤት፡፡
2. በሥልጠና ቦታ መቅረትም ሆነ ማርፈድ አጥብቆ የተከለከለ ነው፡፡
የሥልጠና ጥሪ
ለሁሉም የመንግስት ት/ቤት ዋና ርዕሳነ መምህራን ሐሙስ በቀን20/9/2018ዓ.ም የአራዳ ክፍለ ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት ሥልጠና ስለሚሰጥ ከጥዋቱ 2፡00 እንድትገኙ ለመግለፅ እንወዳለን፡፡
1. ሥልጠና የሚሰጥበሀት ቦታ ትምህርት ጽ/ቤት፡፡
2. በሥልጠና ቦታ መቅረትም ሆነ ማርፈድ አጥብቆ የተከለከለ ነው፡፡
ለሁሉም የመንግስት እና የግል ት/ቤቶች
ነገ ጥዋት ተማሪዎች በቅዳሜ የውጤት ማላቂያ ላይ እንድገኙ አድርጉ።
ከከተማ ምልከታ ይደረጋል
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
