ar
Feedback
Arada education office

Arada education office

الذهاب إلى القناة على Telegram

إظهار المزيد
9 339
المشتركون
-524 ساعات
+167 أيام
+9630 أيام
أرشيف المشاركات
ሰላም ር/መምህራን ዩኒፎርም ዛሬ በየት/ቤቱ አስረካቢዎች ይዘው ይመጣሉ። በመሆኑም ከላይ በዝርዝር ላይ ያሉት ት/ቤት ር/መምህራን ንብረት ክፍሎች በየትምህርት ቤት እንድጠብቁ አድርጉ።

Arada Grade 3-4    Key kokeb  Arbegnoch  Atse Fasil  Ethiopia Tikdem  Ethiopian Ediget  New Era  Ras Abebe Aregay  Timhirt Bilchita    Yealem Berhan  Atse Naod Primary  Beherawi Betemengist  Behere Ethiopia  Meskerem  Dagmawi Menelik  Mehal Ginfile 

እንዴት ዋላችሁ ውድ ር/መ/ራንና የልዩ ፍላጎት ባለሙያዎች በ5/01/2019 ዓ.ም በላክነው ቅፅ መሰረት በ6/01/2019 ዓ.ም 6፡00 ድረስ የልዩ ፍላጎት ተማሪዎች መረጃ በቅፁ መሰረት የላካችሁልን ት/ቤቶች ጥቁር አንበሳ ዳ/ሚኒሊክ አንደኛ ደረጃ ህብረት ቀለመወርቅ መሀል ግንፍሌ ብሔረ ኢትዮጵያ ቤቴልሄምና ገነት መስከረም 2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች ብቻ ስትሆኑ እናንተን እያመሰገንን የቀራችሁት መረጃውን ያላካችሁ ት/ቤቶች መረጃው አስቸኳይ ስለሆነ በቅፁ ብቻ ሙልታችሁ ዛሬ 11፡00 ሰዓት ድረስ እንድትልኩልን በጥብቅ እናሳስባለን፡፡

ለመንግሥት ት/ቤት በሙሉ ትላንት 02/1/2019 ዓ.ም በተላለፈው መልዕት መሠረት ደብተር እየገባ ሰለሆነ መጥታችሁ እንድትረከቡ።

ለመንግሥት ት/ቤት በሙሉ ትለንት 02/1/2109 በተላለፈው መልዕት መሠሠት ደብተር እየገባ ሰለሆነ መጥታችሁ እንድትረከቡ።

እንዴት ዋላችሁ ውድ ር/መ/ራን ለቅ/አ/መካከለኛ ደረጃና አንደኛ ደረጃ ት/ቤቶች በ4/1/2019 ዓ.ም  ትምህርት የሚጀመርበት ቀን ሲሆን በዕለቱ ለሚገኙ ተማሪዎች ቁርስና ምሳ ተዘጋጅቶ ተመግበው እንዲሄዱ ከመጋቢ እናቶች ጋር እንደ ክ/ከተማ ተነጋግረናል ፤ር/መ/ምህራንም በዚሁ መሰረት ተግባራዊ እንዲደረግ ከወዲሁ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች መጠናቀቃቸውን በማረጋጥ በዚሁ ቴሌግራም(ዋትሳፕ) ላይ ሪፖርታሁን ግለፁልን፡፡ምገባ ባለሙያዎችም ተግባሩን በቅርበት እየተከታተላችሁ ሪፖርት አድርጉ፡፡ ሰኞ ት/ት ሲከፈት ቁርስና ምሳ አለመዘጋጀት ግን አይቻልም ያስጠይቃል፡፡ ማሳሰቢያ፡-ከምገባ ኤጀንሲ ባገኘነው መረጃ መሰረት የሰኞ ሜኑ ቴስቲሶያ አቅራቢው ድርጅት አያቀርብም ነገር ግን እናቶች በራሳቸው ገዝተው የሚያቀርቡ ይሆናል፤ሸገር ዳቦም በተመሳሳይ እስከ ቅዳሜ አዲስ ነገር ከሌለ መጋቢ እናቶች በራሳቸው ገዝተው ያቀርባሉ፡፡አዲስ መረጃ ካለ ግን መረጃውን እናደርሳችኋለን፡፡ 🌼🌼🌼መልካም አዲስ አመት🌻🌻🌻🌻🌻🌻

በ«ሕብር ቀን» ከ140 በላይ ለሚሆኑ ተማሪዎች የትምህርት መገልገያ ቁሳቁስ ስጦታ ተሰጠ። አራዳ ጳጉሜ 4 ቀን 2018 ዓ.ም የአራዳ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ጽሕፈት ቤት በጎ ፈቃደኞችን በማስተባበር መጪውን አዲስ የትምህርት ዘመን አስመልክቶ በክፍለ ከተማው ለሚገኙ ከ140 በላይ ተማሪዎች የተሟላ የትምህርት ቁሳቁስ እንዲሁም ለአይነ ስውራንና አካል ጉዳት ላለባቸው ተማሪዎች ልዩ መገልገያ ቁሳቁስ ድጋፍ አድርጓል። «የሕብር ቀን»ን በማስመልከት የተከናወነው የበጎ ፈቃድ መርሃ ግብር የመንግሥትን ሰው ተኮርና ማኅበራዊ ሥራዎች የሚያጠናክር ሲሆን፤ ተማሪዎች በምክንያት ሳይገቱ በትምህርት ገበታቸው ላይ እንዲቀጥሉ ለማስቻል ያለመ መሆኑ ል። በዕለቱ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የአራዳ ክፍለ ከተማ ዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ጽሕፈት ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ እንድሪስ አስናቀ እንደገለፁት መርሃ ግብሩ የመረዳዳትና የመደጋገፍ ታሪካዊ የኢትዮጵያዊነት እሴትን የሚያጠናክር ነው ብለው በሕብረታችንና በአንድነታችን ውስጥ ያለውን የቆየ ባህል ማጎልበት ይገባል ብለዋል። አቶ እንድሪስ አክለውም ኢትዮጵያ የብዝኃ ቋንቋ፣ ሃይማኖት፣ ማንነት፣ ታሪክና አስተሳሰብ ባለቤት እንደመሆኗ በብዝኃነት ውስጥ ጠንካራ ሀገር መፍጠር እንደሚቻል ትልቅ ማሳያ ናት" ብለዋል። የአራዳ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ዱጋሳ ፍቃዱ በበኩላቸው ድጋፉ ተማሪዎች አዲሱን የትምህርት ዘመን በተስፋ፣ በአዲስ መንፈስና በደስታ እንዲጀምሩ ለማስቻል የተዘጋጀ መሆኑን ጠቁመዋል። ትምህርት ቤቶች ሕብረት፣ ብዝኃነት፣ አካታችነትና ሕብረ-ብሔራዊነት የሚለመልምበት፣ ፍሬ የሚያፈራበትና የነገ ሀገር ተረካቢ ትውልድ የሚቀረጽበት ዋነኛ ተቋም መሆኑን ገልጸዋል። በዕለቱ ከተለያዩ የአንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የተውጣጡ ድጋፍ የሚሹ ተማሪዎች፣ ሴቶችና አካል ጉዳተኞች ተጠቃሚ ሲሆኑ ለ76 ተማሪዎች የተሟላ የመማሪያ ደብተርና ቁሳቁስ አቅርቦት፤ ለ50 ሴት ተማሪዎች የንጽሕና መጠበቂያዎች ድጋፍ፤ 2 ዘመናዊ ዊልቸሮች፤ 15 የአይነ ስውራን ብሬልና ልዩ ልዩ ረዳት መገልገያ ቁሳቁሶች ተበርክተዋል። መርሃ ግብሩ የ«ሕብር ቀን»ን እሴቶች በተግባር ያንጸባረቀና የትውልድ ግንባታን ታሳቢ ያደረገ መሆኑ ተመላክቷ

photo content
+2

photo content
+9

photo content
+1

ተሳትፎ የሚጠይቅ መሆኑን ገልፀዋል:: አያይዘውም በክፍለ ከተማው ለትምህርት ጥራት ልዩ ትኩረት በመስጠት የመምህራን ተጠቃሚነትንና አቅም ማሳደግ እንዲሁም ተማሪዎች ሰላማዊ በሆነ አካባቢ ትምህርታቸው ላይ ብቻ ትኩረት አድርገው እንዲሰሩ ምቹ ሁኔታ መፈጠሩን አብራርተው እቅዱ ግብ እንዲመታ አስተዋፅኦ ላደረጉ አካላት ምስጋና አቅርበዋል :: በመርሀ ግብሩ ላይ በ2018 የትምህርት ዘመን በትምህርት ዘርፍ የተሰሩ ስራዎችና የተማሪዎች ውጤት ትንተና ሪፖርት እንዲሁም የ2019 እቅድ በክፍለ ከተማው ትምህርት ፅ/ቤት አስተባባሪ ወ/ሮ ደመቁ ገረመው አማካኝነት ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።

የትምህርት ባለድርሻ አካላት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ ከፍተኛ ሚና እንዳላቸው ተገለጸ፡፡ (ነሀሴ 30/2018 ዓ.ም) የአራዳ ክፍለ ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት የ2018 የትምህርት ዘመን 33ኛው የትምህ
+9
የትምህርት ባለድርሻ አካላት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ ከፍተኛ ሚና እንዳላቸው ተገለጸ፡፡ (ነሀሴ 30/2018 ዓ.ም) የአራዳ ክፍለ ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት የ2018 የትምህርት ዘመን 33ኛው የትምህርት ጉባኤውን በዛሬው እለት አካሂዷል። ጉባኤው "ብሩህ ነገን በዛሬው አእምሮዎች!" በሚል መሪ ሃሳብ የተካሄደ ሲሆን በመርሀ ግብሩ ላይ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ አሊ ከማል ፣ የክፍለ ከተማው ምክትል ሥራ አስፈፃሚ አቶ አብዲ ሙሉነህ ፣ የክፍለ ከተማና የወረዳ አመራሮች ፣ የትምህርት አመራሮችና ሱፐርቫይዘሮች ፣ የተማሪ ወላጅና መምህራን ማህበር አመራሮች ፣ መምህራንና ተማሪዎች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ አሊ ከማል የትምህርት ጉባኤው በ2018 ዓ.ም የትምህርት አመት የመማር ማስተማር ስራውን ውጤታማ ለማድረግ የተከናወኑ ተግባራትን በመገምገም ጠንካራ ስራዎችን ለማስቀጠል እና በሂደት የተስተዋሉ ክፍተቶችን በማረም በ2019 ዓ.ም የትምህርት አመት የተሻለ ስራ ለመስራት የሚያስችሉ ሀሳቦች የሚቀርቡበት መሆኑን ጠቁመው በክፍለ ከተማው በ2018 ዓ.ም በ6ኛ ፣ 8ኛ እና 12ኛ ክፍል የተመዘገበው አበረታች ውጤት በቀጣይ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ሁሉም ባለድርሻ ትኩረት አድርጎ መስራት እንደሚገባው አስገንዝበዋል። የክፍለ ከተማው ትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዱጋሳ ፍቃዱ በጉባኤው መክፈቻ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት የከተማ አስተዳደሩና ቢሮው እንዲሁም በየደረጃው ያለው የትምህርት መዋቅር ለተማሪዎች የትምህርት ተደራሽነትና ጥራት ማረጋገጥ ከፍተኛ ሥራ ሲሰራ መቆየቱን ጠቅሰው ለሀገራችን እድገትና ብልፅግና የትምህርት ዘርፉ የጀርባ አጥንት መሆኑን በመገንዘብ የባለድርሻ አካላትን ከፍተኛ

33ኛው ዓመታዊ የትምህርት ጉባኤ

photo content

በካቶሊክ ካቴድራል 2ኛ ደረጃ ት/ቤት የ2ኛ ደረጃ ት/ቤት ሀገር አቀፍ ውጤት ማላቂያ የክረምት ማጠናከሪያ ትምህርት ማጠናቀቂያ መርሃ ግብር ተካሂዷል።

photo content
+4

photo content

ቀን 22/12/2018 ዓ.ም አራዳ ዜና ትምህርት በአራዳ ክፍለ ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት ስር በሚገኙ የ2ኛ ደረጃ ሶስት ክላስተር ማዕከላት ሲሰጥ የነበው የ2018 ዓ.ም የ2ኛ ደረጃ መልቀቂያ ሀገር አ
+3
ቀን 22/12/2018 ዓ.ም አራዳ ዜና ትምህርት በአራዳ ክፍለ ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት ስር በሚገኙ የ2ኛ ደረጃ ሶስት ክላስተር ማዕከላት ሲሰጥ የነበው የ2018 ዓ.ም የ2ኛ ደረጃ መልቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተና ውጤት ማላቂያ ስትራቴጂ የክረምት ማጠናከሪያ ትምህርት በዛሬው ቀን በደማቅ ሁኔታ ተጠናቋል፡፡ በመዝጊያ መርሃ ግብሩ ላይ በማጠናከሪያ ትምህርቱ ላይ ተሳታፊ ለነበሩ ቶፕ 30 ተማሪዎች እና ትምህርቱን በተገቢው ሲያስተምሩ ለነበሩ መምህራን የተሳትፎ ምስክር ወረቀት ለሁሉም ተሰጥቷል፡፡

photo content
+1

እንዴት አረፈዳችሁ ውድ ር/መ/ራን ለቅ/አንደኛ መካከለኛና አንደኛ ደረጃ ት/ቤቶች የመጋቢ እናቶች የጤና ምርመራን ይመለከታል የመጋቢ እናቶች የነፃ ጤና ምርመራ እንዲያደርጉ ከጤና ፅ/ቤት ጋር በመነጋገር ለጤና ጣቢያዎችም ያወረደ በመሆኑ በየት/ቤታችሁ የሚገኙ መጋቢ እናቶችን ስም ዝርዝር በደብዳቤ በየወረዳችሁ ለሚገኙ ጤና ጣቢያዎች በማሳወቅ ከዛሬ ከ20/12/2018 ዓ ም ጀምሮ የጤና ምርመራ እንዲያደርጉና የምርመራ ውጤታቸውን ኮፒ በማድረግ በ27/12/2018 ዓ ም መረጃውን በደብዳቤ እንድትልኩልን ስንል በጥብቅ እናሳስባለን። መልካም ቀን ማሳሰቢያ፡-ምገባ ባለሙያዎችም ይህንን ተግባር እንድትከታተሉና መረጃውን በወቅቱ እንድትልኩ።