fa
Feedback
የደቀ መዝሙርነት ት/ቤት - Classroom

የደቀ መዝሙርነት ት/ቤት - Classroom

رفتن به کانال در Telegram

ይህ የደቀ መዝሙርነት ትምህርት ቤት መማርያ ክፍል ነው!

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام የደቀ መዝሙርነት ት/ቤት - Classroom

کانال የደቀ መዝሙርነት ት/ቤት - Classroom (@aybcschool) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 16 242 مشترک است و جایگاه 12 410 را در دسته آموزش و رتبه 2 086 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 16 242 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 08 ژوئیه, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر -233 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -9 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 32.61% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 7.93% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 5 297 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 1 288 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 25 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
ይህ የደቀ መዝሙርነት ትምህርት ቤት መማርያ ክፍል ነው!

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 09 ژوئیه, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته آموزش تبدیل کرده‌اند.

16 242
مشترکین
-924 ساعت
-547 روز
-23330 روز
آرشیو پست ها
9.1 ክርስቶስ በሰማያዊው ቤተ መቅደስ.pdf6.52 KB

9.1 ቤተ መቅደስ .pdf1.20 KB

ትምህርት 9:- ክርስቶስ ሊቀ ካህናችን ======================== ውድ ተማሪዎች: የክርስቶስን ምድራዊ ሕይወት: ሞት እና ትንሳኤን ከዚህ በፊት በስፋት ተምረናል። ባለፊት ሳምንታት በተማራችሁአቸው ትምህርቶች እንደተባረካችሁ ሙሉ እምነታችን ነው። አሳልፎ በመስጠት የኃጢአት ዋጋ የሆነውን ሞት በእኛ ፋንታ በመቅመሱ የእሱን ሕይወት ያጋራን ጌታችን የተመሰገነ ይሁን! በጸጋ የዳን ሰው በቅድስና ሕይወት እንዴት መኖር እንዳለበት፡ የእግዚአብሔርን ሕግጋት እንዲሁም አብዛኛው ሕዝብ ሳያውቅ የሚተላለፈውን የሰንበትን እረፍት አጥንተናል። በተጨማሪም ሰው ሲሞት ምን እንደሚሆን፤ ሙታን አሁን ያሉበትን ሁኔታ፤ ነፍስ አትሞትም የሚለው አስተምህሮ ትልቅ ስህተት እንደሆነ እና ከሰይጣን ማታለያ መጠንቀቅ እንዳለብን ባለፉት 2 ሳምንታት ተምረናል። በዚህ ሳምንት ደግሞ በሰማይ አዳኛችን የሚያደርገውን አገልግሎት እናጠናለን፡ ኢየሱስ ክርስቶስ በገዛ ደሙ በሰማይ ወደ ምትገኘው ቤተ መቅደስ ስለ እኛ ሊማልድ በአብ ፋት ቆሟል:: የምድራዊው ቤተ መቅደስ የሰምያዊው ጥላ በመሆኑ ተወግዷል:: የሰማዩ ቤተ መቅደስ ግን አሁንም ለሰዎች ደህንነት የሚሆነው የክርስቶስ ደም ኃጢአትን እየፋቀ ጸጋ እና ምሕረትን ለአማኞት እያዳረሰ ነው! በዚህ ሳምንት - በሰማይ ቤተ መቅደስ የሚደረገውን አገልግሎት እና የክርስቶስን ዳግም ምፃት እንዳስሳለን! መልካም ጥናት!

ከአስተማሪው: ውድ ተማሪዎች: እንደምን ሰነበታችሁ? በዚህ ሳምንት የምንማረው ትምህርት እጅግ ጥልቅ ነው:: ነገር ግን ወተትን እንዲሁም ጠንካራ ምግብን እንድንመገብ የጌታ ፈቃዱ ነውና በመንፈሱ እየታገዝን በክፍት ልቦና እናጥናው:: እንባረክበታለን:: እናንተም በትጋትና በጸሎት እያጠናችሁ እውነተኛው ወደሆነው የእግዚአብሔር ቃል እውቀት እንደምትደርሱ እምነቴና ተስፋየ ነው:: ተባረኩ!! ========================= ከ20 አመት በፊት የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናቴን ስጀምር እኔም ከገጠሙኝ ለማስተዋል ጥልቅ ከሆኑ ትምህርቶች አንዱ ይህ ነው:: በሚገባ ሳስተውለው ለብዙ አደናጋሪ የሚመስሉ ሐሳቦችን ግልጽ አድርጎልኛል:: እጅግ ብዙ የሃይማኖት ድርጅቶች ሳያስቡትም ቢሆን እምነታቸውን የመሰረቱት ነፍስ አትሞትም: ሰው ሲሞት ጽድቅ ካለው ወደ ገነት: ኃጥዕ ከሆነ ደግሞ ወደ ገሃነም ይሄዳል ለዘላለም በቅጣት ይሰቃያል በሚል የተሳሳተ አስተምህሮ ነው:: ይህ አስተምህሮ ለብዙ ማሳሳቻዎች ራሳችንን እንድናጋልጥ ያደርገናል:: ይህ የስህተት አስተምህሮ ሰይጣን በኤድን ገነት "በእርግጥ አትሞቱም" በማለት ለሔዋን ከነገራት ውሸት የመነጨ ነው:: በዚህም የሚከተሉትን መሰረታዊ ነገሮችን ለማሳፋለስ አልሞ ነው:- 1. የእግዚአብሔር ፍቅር እግዚአብሔር ፍቅር ነው:: ለበደለኛውም ለጻድቁም ሁሉ ፍቅር ነው:: ጸሐይና ዝናብን ለሁሉ የሚሰጥ በጸጋ የተሞላ ነው:: ተስፋን የሰጠን እርሱ ነው:: ይህ የፍቅር አምላክ ቅን ፈራጅም ነው:: ያጠፋል ያድናልም:: ነገር ግን ፍጥረቶቹን በማሰቃየት ግን አይደሰትም:: በማይጠፋ እሳት ውስጥ ለዘላለም እያንገበገበ በስቃያቸው መደሰት እና መቅጣት የፍቅሩ ባህርይ አይደለም:: እንኳን በስቃይ ኃጥእ ሞት ደስ የማይሰኝ አምላክ ነው ያለን:: ( ሕዝ 18:23) እግዚአብሔርን ጨካኝና በዘላለም እሳት ፍጥረቱን የሚቀጣ ነው ብለን እንድናስብ የሰይጣን ፍላጎት ነው:: ከኃጢአት ካልተመለስን ለዘላለም እንሞታለን:: ካመንን ለዘላለም በሕይወት እንኖራለን:: ግልፅና ቀላል ነው:: የዘላለም ስቃይ አስተምህሮ ከእግዚአብሔር ፍቅር ጋር በቀጥታ ይጋጫል! እግዚአብሔር ትናንትም ዛሬም ነገም ለዘላለም ፍቅር ነው:: 2. የክርስቶስ ዳግም ምፃት ስንሞት ነፍሳችን ወደ ገነት ገብታ በደስታ የምትኖር ከሆነ የክርስቶስ ዳግም ምጻት ለምን አስፈለገ? ሄጄም ስፍራ ባዘጋጅላችሁ፥ እኔ ባለሁበት እናንተ ደግሞ እንድትሆኑ ሁለተኛ እመጣለሁ ወደ እኔም እወስዳችኋለሁ። የዮሐ 14:3 ስንሞት በመቃብር እናርፋለን:: እኛ ምንም አናውቅም:: ሕይወታችን በታማኙ በእግዚአብሔር እጅ ነው:: በዳግም ምጻቱ ጊዜ በጌታ አምነው ያረፉት የመለከቱን ድምጽ ሲሰሙ ይነሳሉ:: ጌታን በአየር ለመቀበል መቃብር ሁሉ ይከፈታል:: ወደ ሰማይ እንሄዳለን (1ኛ ተሰ 4) ጌታችን ግልጽ ነው:: ስትሞቱ ገነት ትመጡና ቦታ እሰጣችሁዋለሁ አላለም:: ቦታን አዘጋጅላችሁዋለሁ አብራችሁኝ እንድትሆኑ ተመልሼ እመጣለሁ እወስዳችሁዋለሁ ነው ያለን:: ስለዚህ ግሩም ተስፋ የጌታ ስም ይባረክ!! 3. ክርስቶስ ብቻ አማላጅነት ነፍስ አትሞትም የሚለው ትምህርት ቅዱሳን ለኃጢአት ምልጃና ልመና ያቀርቡልናል (ያማልዱናል) የሚለውን የስህተት ትምህርት ወልዷል:: ቅዱሳን ቢሞቱን በገነት ስለሚኖሩ ሊያማልዱን ይችላሉ የሚለው ትምህርት ከዚህ የስህተት ትምህርት የመነጨ ስህተት ነው:: በተለየ መነጠቅ ( ኤልያስና ሔኖክ) እንዲሁም ትንሳኤ ( ሙሴ) በሰማይ ያሉ ቢሆኑም ሌሎች ቅዱሳን ግን በመቃብር ትንሳኤን የሚጠብቁ ናቸው:: ሙታን ስለሆኑ እንዳች አያውቁም ሊያማልዱን አይችሉም:: ብቸኛውና በአብ ፊት ለኃጢአታችን የሚማልደው ጠበቃችን ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው:: ሌሎቹ ሙታን ናቸው ምንም አያውቁም!! 4. ሙታን አንዳች አያውቁም (መክ 9:5) ብዙ ሰዎች በምድር እያሉ ከሞት ተነስተዋል:: አላዛር ትልቁ ምሳሌ ነው:: ነገር ግን ከሞት ከተነሱ በሁዋላ ስለ ገነት ሲያወሩ አልተጻፈም:: ነፍሳቸው ገነት ሄዳ ቢሆን ኖሮ ስለውበቱ: ስለድምቀቱ ያዩትን ባወሩ ነበር:: ነገር ግን እንቅልፍ በሚመስል የሞት ጸጥታና እረፍት ውስጥ ስለነበሩ ስለሰማይ ያሉት ነገር የለም:: በዚህ ዘመን ሙታንን ማነጋገር ይቻላል የሚል አደገኛ ትምህርት እየመጣ ነው:: በቅርቡ በየቤተክርስትያኑ በሐሰተኛ ነብያት አማካኝነት ተስፋፍቶ የሞተውን አባት እናት ወንድም እህት አናግሩ የምትባሉበት ጊዜ ይመጣል:: እኔ በምኖርበት አገር በጣም ተስፋፍቷል:: ይህ የሰይጣን አደገኛ ማሳሳቻ ስለሆነ ተጠንቀቁ :: አስታውሱ ሙታን አንዳች አያውቁም:: ሰይጣም የአባትና የእናትን ድምፅ በማስመሰል ሊያሳሳችሁና ገደል ሊከታችሁ ይሻል:: መልካም ጥናት!!

ውድ ተማሪዎች: "እውነት እውነት እልሃለሁ ዛሬ በገነት ከእኔ ጋራ ትሆናለህ" ይህ ጥቅስ በመጠቀም ብዙዎች ጌታ እንዲሁም ሌባው ሲሞቱ በዚያው ቀን በገነት ነፍሳቸው ሄዳለች ይላሉ:: 1. "ዛሬ" የሚለውን ቃል በoriginal አጠቃቀሙ ዛሬ በገነት ትሆናለህ ለማለት ሳይሆን "እውነት እውነት እልሃለሁ ዛሬ" የተስፋውን እርግጠኝነት ለመግለጥ ጥቅም ላይ የዋለ ነው:: ምክንያቱን አርብ ቀን ጌታችን ከሞተ በሁዋላ ወደ ሰማይ አልወጣም:: በትንሳኤ ማለት በደስታ ልታቅፈው የተጠጋችውን ማርያምን ወደ ሰማይ እንዳልወጣ በግልጥ እንዲህ አላት:- ኢየሱስም፦ ገና ወደ አባቴ አላረግሁምና አትንኪኝ፤ ነገር ግን ወደ ወንድሞቼ ሄደሽ፦ እኔ ወደ አባቴና ወደ አባታችሁ ወደ አምላኬና ወደ አምላካችሁ ዓርጋለሁ፡ ብለሽ ንገሪአቸው፡ አላት። የዮሐንስ ወንጌል 20:17

8.7 የሚጣረሱ ጥቅሶች ?.pdf6.79 KB

8.6 የገሃነም እሳቶች .pdf6.50 KB

8.5 ገሃነም ምንድነው?.pdf1.49 KB

8.4 ሙታን ሊያነጋግሩን ይችላሉን ?.pdf1.72 MB

8.3 ሙታን የት ናቸው? .pdf1.51 KB

8.1 ሞትና ትንሳኤ.pdf9.13 KB

8.1 ሕያው ነፍስ ማለት ምን ማለት ነው?.pdf5.85 KB

ትምህርት 8- ነፍስ : ሞት: ገሃነም ======================== ውድ ተማሪዎች: እንደምን ሰነበታችሁ? መልካም ሰንበት እንዳሳለፋችሁ ተስፋ አለን! እስካሁን ድረስ ጥሩ ጥሩ መፅሐፍ ቅዱሳዊ ትምህርቶችን ተምረናል:: ለምታደርጉት ተሳትፎ እግዚአብሔር ይባርካችሁ! 👉🏽በዚህ ሳምንት ስለ ነፍስ: ሞት እና ገሃነም በጥልቀት እናጠናለን!! ይህ ትምህርት ለ2 ሳምንታት ይቆያል!! =====••=======••======== በዚህ ትምህርት - ነፍስ ማለት ምን ማለት ነው? - ሰው ሲሞት ምን ይሆናል? - ገሃነም ምንድነው? - የፍቅር አምላክ በውኑ ኃጢአተኞችን ለዘላለም በእሳት በማሰቃየት ይደሰታል? - ሰው ሲሞት "በጌታ እቅፍ አብሮ እየኖረ ነው" የሚባለው አባባል መጽሐፍ ቅዱስ መሰረት አለው? እነዚህን እና መሰል ጥያቄዎችን በጥልቀት እንዳስሳለን!! በጸሎትና በተከፈተ ልብ ትመረምሩ ዘንድ መንፈስ ቅዱስ ይብዛላችሁ!! ጥያቄዎቻችሁን በውስጥ መስመር ልኩልን! ተባረኩ!!

ሐሰተኛ ነብያት እና የመጨረሻው ዘመን ======================== ነብይነት በጣም የተለየ ጥሪ ነው:: መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ስማቸው የተጠቀሱትን የአብዛኞቹን ነብያት አገልግሎት ስናጠና እግዚአብሔር እንዴት በግልፅ እንደመረጣቸው እንጂ በራሳቸው ወይስ በሰዎች ያገኙት ሹመት ወይም ማዕረግ አለመሆኑን እንረዳለን:: የተለየ አገልግሎት ስለሆነ የተለየ ጥሪ ያስፈልገዋል:: የኢሳይያስን: የኤርምያስን: የዳንኤን: የመጥምቁ ዮሐንስን ሕይወት ማጥናት ለዚህ በቂ ነው:: እውነትን በየዘመናቸው ለማስተዋል ዋጋ የከፈሉ: በመከራ ማዕበል ለእውነት ጸንተው የቆሙ እንዲሁም ዘመን ተሻጋሪ የሆኑ ትንቢቶችን እና መንፈሳዊ በረከቶችን ጥለው ያለፉ ነብያት ናቸው:: በዘመናችን በተለይ በኢትዮጵያ ባለፉት 10 አመታት ብዙ ሽህ ነብይ ነን የሚሉ ሰዎች ፈልተዋል:: እነዚህ ግለሰቦች የእግዚአብሔርን ትእዛዛት በግልፅ እየሻሩ: በተንደላቀቀ ሕይወት እየኖሩ: ሕዝቡን በትንቢትና በፈውስ ስም እየበዘበዙ ይኖራሉ:: ተማሪዎቻችን: ከእነዚህ አይነት ሐሰተኛ ነብያት እና አስተምህሮዎቻቸው ትጠበቁ ዘንድ የእውነተኛ ነብይ መስፈርቶች ምን ምን እንደሆኑ በጥንቃቄ ታጠኑ ዘንድ እንጋብዛለን:: በመጨረሻው ዘመን ሰይጣን የአለምን ሕዝብ በተሳሳት ትምህርት ውስጥ ጠፍሮ ለመያዝ እጅግ ብዙ ሐሰተኛ ነብያትን ያስነሳል:: እነዚህ የሰይጣን መልእክተኞች ደግሞ ድንቅና ታምርን ማድረግ የሚችሉበትን ኃይል ይሰጣቸዋል:: በክርስትና ስም የሚድረጉትን እነዚህ ታምራት የሰዎቹን የሐሰት ትምህርት እና የረከሰ ሕይወት ይደብቃሉ:: እንጠንቀቅ!! ዮሐንስ በራእይ በመጨረሻው ዘመን ይህን የሰይጣን እኩይ ተግባር ሲገልጥ እንዲህ በማለት ነበር: "ከዘንዶውም አፍና ከአውሬው አፍ ከሐሰተኛውም ነቢይ አፍ ጓጕንቸሮች የሚመስሉ ሦስት ርኵሳን መናፍስት ሲወጡ አየሁ:: ምልክት እያደረጉ የአጋንንት መናፍስት ናቸውና፥ በታላቁም ሁሉን በሚገዛ በእግዚአብሔር ቀን ወደ ሚሆነው ጦር እንዲያስከትቱአቸው ወደ ዓለም ሁሉ ነገሥታት ይወጣሉ።" ራእይ 16:13-14 ከዚህ ምልክትን እያደረገ ከሚመጣው የአጋንንት መንጋ: ከእግዚአብሔር እውነት አርቆን ወደ ሰይጣን የጦር ሰፈር ከሚወስድ ማሳሳቻ እግዚአብሔር ይጠብቀን!! ተባረኩ!!

7_5_በልሳን_መናገር_ትርጉምና_አጠቃቀሙ.pdf2.36 KB