en
Feedback
የደቀ መዝሙርነት ት/ቤት - Classroom

የደቀ መዝሙርነት ት/ቤት - Classroom

Open in Telegram

ይህ የደቀ መዝሙርነት ትምህርት ቤት መማርያ ክፍል ነው!

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel የደቀ መዝሙርነት ት/ቤት - Classroom

Channel የደቀ መዝሙርነት ት/ቤት - Classroom (@aybcschool) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 16 386 subscribers, ranking 12 380 in the Education category and 2 048 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 16 386 subscribers.

According to the latest data from 17 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -450 over the last 30 days and by -7 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 26.70%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 8.11% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 4 376 views. Within the first day, a publication typically gains 1 329 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 35.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
ይህ የደቀ መዝሙርነት ትምህርት ቤት መማርያ ክፍል ነው!

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 18 June, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Education category.

16 386
Subscribers
-724 hours
-687 days
-45030 days
Posts Archive
ሐሰተኛ ነብያት እና የመጨረሻው ዘመን ======================== ነብይነት በጣም የተለየ ጥሪ ነው:: መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ስማቸው የተጠቀሱትን የአብዛኞቹን ነብያት አገልግሎት ስናጠና እግዚአብሔር እንዴት በግልፅ እንደመረጣቸው እንጂ በራሳቸው ወይስ በሰዎች ያገኙት ሹመት ወይም ማዕረግ አለመሆኑን እንረዳለን:: የተለየ አገልግሎት ስለሆነ የተለየ ጥሪ ያስፈልገዋል:: የኢሳይያስን: የኤርምያስን: የዳንኤን: የመጥምቁ ዮሐንስን ሕይወት ማጥናት ለዚህ በቂ ነው:: እውነትን በየዘመናቸው ለማስተዋል ዋጋ የከፈሉ: በመከራ ማዕበል ለእውነት ጸንተው የቆሙ እንዲሁም ዘመን ተሻጋሪ የሆኑ ትንቢቶችን እና መንፈሳዊ በረከቶችን ጥለው ያለፉ ነብያት ናቸው:: በዘመናችን በተለይ በኢትዮጵያ ባለፉት 10 አመታት ብዙ ሽህ ነብይ ነን የሚሉ ሰዎች ፈልተዋል:: እነዚህ ግለሰቦች የእግዚአብሔርን ትእዛዛት በግልፅ እየሻሩ: በተንደላቀቀ ሕይወት እየኖሩ: ሕዝቡን በትንቢትና በፈውስ ስም እየበዘበዙ ይኖራሉ:: ተማሪዎቻችን: ከእነዚህ አይነት ሐሰተኛ ነብያት እና አስተምህሮዎቻቸው ትጠበቁ ዘንድ የእውነተኛ ነብይ መስፈርቶች ምን ምን እንደሆኑ በጥንቃቄ ታጠኑ ዘንድ እንጋብዛለን:: በመጨረሻው ዘመን ሰይጣን የአለምን ሕዝብ በተሳሳት ትምህርት ውስጥ ጠፍሮ ለመያዝ እጅግ ብዙ ሐሰተኛ ነብያትን ያስነሳል:: እነዚህ የሰይጣን መልእክተኞች ደግሞ ድንቅና ታምርን ማድረግ የሚችሉበትን ኃይል ይሰጣቸዋል:: በክርስትና ስም የሚድረጉትን እነዚህ ታምራት የሰዎቹን የሐሰት ትምህርት እና የረከሰ ሕይወት ይደብቃሉ:: እንጠንቀቅ!! ዮሐንስ በራእይ በመጨረሻው ዘመን ይህን የሰይጣን እኩይ ተግባር ሲገልጥ እንዲህ በማለት ነበር: "ከዘንዶውም አፍና ከአውሬው አፍ ከሐሰተኛውም ነቢይ አፍ ጓጕንቸሮች የሚመስሉ ሦስት ርኵሳን መናፍስት ሲወጡ አየሁ:: ምልክት እያደረጉ የአጋንንት መናፍስት ናቸውና፥ በታላቁም ሁሉን በሚገዛ በእግዚአብሔር ቀን ወደ ሚሆነው ጦር እንዲያስከትቱአቸው ወደ ዓለም ሁሉ ነገሥታት ይወጣሉ።" ራእይ 16:13-14 ከዚህ ምልክትን እያደረገ ከሚመጣው የአጋንንት መንጋ: ከእግዚአብሔር እውነት አርቆን ወደ ሰይጣን የጦር ሰፈር ከሚወስድ ማሳሳቻ እግዚአብሔር ይጠብቀን!! ተባረኩ!!

7_5_በልሳን_መናገር_ትርጉምና_አጠቃቀሙ.pdf2.36 KB

7.4 የዘመኑ ነቢያትና ሐዋርያት.pdf3.89 MB

7_3_የነብያት_አገልግሎት_እና_መመዘኛው.pdf4.03 MB

7.2 የአገልግሎት መንፈሳዊ ሥጦታዎች .pdf2.60 MB

7.1 እግዚአብሔርን ማገልገል ሕይወት.pdf1.60 MB

ትምህርት 7- በመንፈሳዊ ስጦታዎች እግዚአብሔርን ማገልገል ======================== ውድ ተማሪዎች: እንደምን ሰነበታችሁ? ባለፉት 2 ሳምንታት በጸጋ የዳነ ሰው በምን መልኩ መመላለስ እንደሚገባው በሚገባ አጥንተናል:: እግዚአብሔርን መታዘዝ ያለውን በረከት አይተናል። እውነተኛው የእግዚአብሔር ሰንበት ሰባተኛው ቀን ቅዳሜ መሆኑን አጥንተናል:: በዚህ ሳምንት ደግሞ መንፈሳዊ ስጦታዎች በክርስትና ሕይወት ላይ ያላቸውን ሚና እናጠናለን:: በተጨማሪም የትንቢት ስጦታን በስፋት እንመረምራለን:: ዘመናችን ራሳቸውን በነብይ ስም የሚጠሩ ነገር ግን በሕይወታቸው የእግዚአብሔርን ትእዛዝ የሚሽሩ: በቀድሞ የእግዚአብሔር ነብያት መስፈርት ቢመዘኑ የሚወድቁ ናቸው:: ስለዚህ ራሳችንን ከሐሰተኛ ነብያትና እና ከስሕተት ትምህርታቸው ለመጠበቅን እውነተኛ ነብያትን መለያ መስፈርቶች ምን ምን እንደሆኑ ለይተን ማወቅ ያስፈልገናል:: በዚህ ትምህርት እነዚህን ዋና ዋና ሐሳቦች እንዳስሳለን! ተባረኩ!!

ሰንበት_ ክፍል-2.mp38.81 MB

የእግዚአብሔር ፀጋ እና የእግዚአብሔር ሕግ ======================== አንዳንዶች በብሉይ ኪዳን ጊዜ ሰዎች ይድኑ የነበረው ሕግን በመጠበቅ ሲሆን በአዲስ ኪዳን ዘመን ግን ሕጉ ስለተሻረ የሚድኑት በፀጋ ነው ብለው ያስተምራሉ:: ይህ አስተምህሮ ፍጹም የተሳሳተ ነው:: ድሮም: አሁንም ወደፊትም ሰው የሚድነው በእምነት በሚገኘው ፀጋ እንጂ ሕግን በመጠበቅ ወይም መልካም ሥራ በመስራት አይደለም:: ሕግን በመጠበቅ ካልዳንን "ሕግ በክርስትያን ሕይወት ላይ ያለው አስተዋጽኦ ምንድነው?" ብለን መጠየቅ ያስፈልጋል:: የእግዚአብሔር ትዕዛዛት ዘላለማዊ ናቸው:: አስርቱ ትዕዛዛት አምላክን በፍጹም ልብ መውደድ እና ባልጀራችንን መውደድን ያስተምሩናል:: ፍቅር ደግሞ የሕግ ፍጻሜ ነው:: እነዚህ ቅዱስ ቃላት ፍቅርን እንድንለማመድ ያበረታቱናል:: ነገር ግን አያድኑንም:: ጳውሎስ በመገረዝ ለመዳን ያሰቡትን የገላትያ ሰዎች ለመዳን የመገረዝ ሕግ አስፈላጊ እንዳልሆነ: አህዛብ እንዲድኑ የአይሁድን የመንጻትና የመገረዝ ሕግ መጠበቅ እንደማያስፈልጋቸው ያስተምራቸዋል:: መዳን የፀጋ ስጦታ ነው:: ነገር ግን በፀጋ ለምንድን ለእኛ ሕግ ኃጢአት የሚጠቁም መስታዎት ነው:: ጳውሎስ እንዳለው" እንግዲህ ምን እንላለን? ሕግ ኃጢአት ነውን? አይደለም፤ ነገር ግን በሕግ ባይሆን ኃጢአትን ባላወቅሁም ነበር፤ ሕጉ፦ “አትመኝ፡” ባላለ ምኞትን ባላወቅሁም ነበርና። ሮሜ 7:7፤ ያለ ሕግ ኃጢአት አይታወቅም:: ከአስርቱ ትእዛዛት አንዱ ሁሉም ወይም ተሽሯል ማለት ኃጢአትን የምናውቅበት መንገድ ተወገደ ማለት ነው:: ይህ ደግሞ ኃጢአተኛው ኃጢአቱ ተገንዝቦ ወደ ንስሐ እንዳይመጣ ይከለክላል:: ንስሐ ከሌለ ደግሞ በፀጋ የሚገኘውን መዳን ማጣጣም አይችልም:: ስለዚህ ሕግ በፀጋ እንድንድን ኃጢአታችንን የሚያስታውቀን መስታውት ነው:: ወደ ፀጋ የሚያመጣን ሞግዚት ነው:: እንደዚህ በእምነት እንጸድቅ ዘንድ ሕግ ወደ ክርስቶስ የሚያመጣ ሞግዚታችን ሆኖአል፤ ገላትያ 3:24 በፀጋው ድኛለሁ የሚለው ሕዝብ የእግዚአብሔርን ትእዛዛት ችላ ስላለ አገራችን የክፋት አረንቋ ውስጥ ናት:: የእግዚአብሔር ትእዛዛትን በፀጋው ሐይል ለመጥበቅ ብንተጋ በሕዝባችን የሚታየው ስርአት አልበኝነት: አልቂት: ሰቆቃ: ሌብነት: ነፍሰ ገዳይነት: አመንዝራነት እንዴት በተቃለለ! ሰላምና ፀጋ ይብዛላችሁ! አስተማሪው!

ሕግጋቱ በሁለት ይጠቃለላሉ ======================== አስርቱ ትእዛዛት በሁለት ይከፈላሉ:: የመጀመሪያዎቹ አራቱ በሰውና በእግዚአብሔር መካከል ሊኖር የሚገባውን ግንኙነት የሚያስተምሩ ሲሆኑ የቀሩት ስድስቱ ደግሞ በሰዎች መካከል ሊኖር የሚገባውን ግንኙነት ያስታውሳሉ:: የመጀመሪያዎቹ አራቱ እግዚአብሔርን እንድንወድ የሚያዝዙ ሲሆኑ የቀሩት ስድስቱ ደግሞ ሰዎችን መውደዳችን እና ማክበራችን ላይ ያተኩራሉ:: ይህን የተረዳ አንድ ሕግ አዋቂ ጌታችንን ከትእዛዛት ሁሉ የትኛይቱ ታላቅ ናት ብሎ ሲጠይቀው ኢየሱስም እንዲህ አለው፦ “ጌታ አምላክህን በፍጹም ልብህ በፍጹም ነፍስህም በፍጹም አሳብህም ውደድ። ታላቂቱና ፊተኛይቱ ትእዛዝ ይህች ናት። ሁለተኛይቱም ይህችን ትመስላለች፥ እርስዋም፦ ባልንጀራህን እንደ ነፍስህ ውደድ፡ የምትለው ናት። በእነዚህ በሁለቱ ትእዛዛት ሕጉም ሁሉ ነቢያትም ተሰቅለዋል።” ማቴዎስ 22:36-39 ሁሉም አስፈላጊ ናቸው:: ሁሉም የሕይወት መመሪያ ይሆናሉ:: አራተኛው የሰንበት ትእዛዝ በተደጋጋሚ የተነሳው አብዛኛው ሕዝበ ክርስትያን በማወቅም ሆነ ባለማወቅ የሚጥሰው ትእዛዝ ስለሆነ ይህን ለማሳሰብ ነው:: እንግዲህ ከነዚህ ከሁሉ ካነሱት ትእዛዛት አንዲቱን የሚሽር ለሰውም እንዲሁ የሚያስተምር ማንም ሰው በመንግሥተ ሰማያት ከሁሉ ታናሽ ይባላል፤ የሚያደርግ ግን የሚያስተምርም ማንም ቢሆን እርሱ በመንግሥተ ሰማያት ታላቅ ይባላል። ማቴዎስ 5:19፤ ተባረኩ!!

6.7 የአለም ሕዝብ የሚተላለፈው ሕግ.pdf1.39 KB

6.6 የሰንበት መለዎጥ.pdf1.61 KB

6_5_ታሪክ_የረሳው_ቀን_ጊዜው_መጽሔት_በፋንታሁን_መላኩ.pdf1.32 MB

6.4 ግር አለህ እንዴ ስለ ሰንበት?.pdf3.11 MB

ሕግ ሁሉ የተሰጠው እንዲጣስ ነው። . . . ነው እንዴ? በትምህርታችን እየተከታተልን እንዳለነው በኃጥአት ለወደቀው አለም ሕግ አስደሳች ነገር እንዳልሆነ ነው። በሥጋዊ ኑሮ አድማስ ውስጥ መታዘዝ ገደብ አለው። በተለይ ለኃጢአት ባሪያ በሆነ አዕምሮ ልክ የሚመስሉ ነገሮች ከእግዚአብሔር ሐሳብ በፍፁም የራቁ በመሆናቸው በእግዚአብሔር ሐሳብ ልክ መታዘዝ እንዲሁም እርሱን ማስደሰት አይችሉም። ስለዚህም ሰው በሐገ-ጠልነቱ ይታወቃል። ከእርሱ በላይ የሕይወቱን አቅጣጫ የሚወስንለትን ሌላ አካል አይፈልግም። ስለ ሥጋ ማሰብ በእግዚአብሔር ዘንድ ጥል ነውና፤ ለእግዚአብሔር ሕግ አይገዛምና፥ መገዛትም ተስኖታል፤ በሥጋ ያሉትም እግዚአብሔርን ደስ ሊያሰኙት አይችሉም (ሮሜ 8፡ 7ና 8)። በእግዚአብሔር ሕግ ለመደሰት እግዚአብሔር ማን እንደሆነ ማስተዋል ያስፈልጋል። እግዚአብሔር ፍቅር ነው። ፍቅር በሚለው ቃል ውስጥ ምሕረት እና እውነት ይገኛሉ [መዝ 85፥10]። እውነት የእግዚአብሔርን ፍትሐዊ አገዛዝ ይወክላል። ምሕረት ደግሞ ለሰዎች ልጆች ሁሉ ሳይለያይ የፈሰሰውን ጸጋውንና ይቅርታውን ያሳያል። እግዚአብሔር ሕግን እንድንጠብቅ የሚሻው ከዚህ መነፅር አኳያ ነው። የሰውን አልታዘዝ ባይነት በሀይል ወይም በፍርሃት ከማስገዛት ይልቅ በፍቅር ብቻ የተነሳሳ የመታዘዝ ሕይወት እንዲኖረን አስቀድሞ ወደደን። ፍቅር ለባልንጀራው ክፉ አያደርግም፤ ስለዚህ ፍቅር የሕግ ፍጻሜ ነው (ሮሜ 13፥ 10)። አንድ ጉልበተኛ ሰው ነበር አሉ። ይህ ሰው በጊዜው የባሪያ ንግድ የተፋፋመበት ጊዜ ነበርና ጉልበቱን ሊበዘብዙ ሰዎች ይፈልጉት ነበር። ኃይለኝነቱ በሥራ ብቻ ሳይሆን በባሕርይም ጭምር ነበር። ጉልበት ቢኖረውም ፀባይ ግን አልነበረውም። ታዲያ በገዢዎቹ ፊት ለጨረታ በሚቀርብበት ጊዜ [እንኳንም ያ ጊዜ አለፈ] ለማናቸውም እንደማይታዘዝ፣ ጉልበቱን ለማንም አሳልፎ እንደማይሰጥ እየዛተ ነበር። ጨረታው ተጀመረ። ይህ እንግዲህ በዙ ዋጋ የሚያወጣ ሰው በመሆኑ ብዙ ሰዎች ከፍ ያለ ዋጋ በመስጠት ለመውሰድ ተሽቀዳደሙ። ድንገት ከበስተኋላ አንድ በፍፁም ሊደርሱበት የማይችሉት ዋጋ አንድ ሰው ጠራ። በዚያ የሚገኙት ሁሉ በመገረም የቱንም ያህል ሀብታሞች ቢሆኑም አንድ ባሪያ ላይ ግን ይህን ያህል ገንዘብ ማፍሰስ አስፈላጊ ስላልመሰላቸው ተውት። ይህን አመፀኛ ባሪያ ከነሰንሰለቱ የተረከበው ገዢ ቁልፉን ከተቀበለ በኋላ ወደ ቤቱ ይወስደው ጀመር። በመንገዳቸው በውድ ዋጋ መገዛቱ ለርሱም ምኑም እንዳይደለ፣ ለመሥራት ከመለገም ወደኋላ እንደማይል እየዛተ መንገዳቸውን ቀጠሉ። ድንገት ከሰዎች እይታ ውጪ ሲሆኑ ባለቤቱ የባሪያውን ሰንሰለት በመፍታት በነፃ እንዲሄድ ነገረው። በውድ ዋጋ የገዛውም የእርሱን ሥራ እንዲሰራለት ሳይሆን በነፃነት እንዲኖር መሆኑን አሳወቀው። ይህ አመፀኛ ባሪያ በድንጋጤ ቆመ። ለመጀመሪያ ጊዜ የነፃነትን አየር ተነፈሰ። ይህ ሰው ለምን እንዲህ እንዳደረገ ባያስተውልም የነፃነቱ ምክንያት ግን ገዢው እንደሆነ ተገነዘበ። ወዴት ይሄዳል ታዲያ? ከዚህ ሰው ጋር ለመኖር ወሰነ። ጉልበቱን ሳይሰስት ሊያገለግለው፣ በደስታ ሊሰራለት በጊዜ ያልተገደበ አገልግሎት ሊሰጠው ቃል ገባለት። መታዘዝ ነጻ የመውጣት ውጤት ነው። መታዘዝ የመዳን ፍሬ ነው። እግዚአብሔርን መታዘዝ እድል ነው

6.3 የሰንበት ዕረፍት.pdf1.67 MB