ar
Feedback
የደቀ መዝሙርነት ት/ቤት - Classroom

የደቀ መዝሙርነት ት/ቤት - Classroom

الذهاب إلى القناة على Telegram

ይህ የደቀ መዝሙርነት ትምህርት ቤት መማርያ ክፍል ነው!

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام የደቀ መዝሙርነት ት/ቤት - Classroom

تُعد قناة የደቀ መዝሙርነት ት/ቤት - Classroom (@aybcschool) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 16 072 مشتركاً، محتلاً المرتبة 12 522 في فئة التعليم والمرتبة 2 111 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 16 072 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 30 يوليو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار -229، وفي آخر 24 ساعة بمقدار -8، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 24.30‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 7.62‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 3 907 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 1 225 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 37.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
ይህ የደቀ መዝሙርነት ትምህርት ቤት መማርያ ክፍል ነው!

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 31 يوليو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة التعليم.

16 072
المشتركون
-824 ساعات
-467 أيام
-22930 أيام
أرشيف المشاركات
ውድ ተማሪዎች: በትምህርቱ እንደተባረካችሁ ተስፍ አለን:: ውጤታችሁን በሙሉ ደምረን የሚመረቁትን ተማሪዎች ስም ዝርዝር በቅርብ እናስታውቃለን:: በተጨማሪም ለመጠመቅ የእግዚአብሔር መንፈስ ያሳሰባችሁን ካላችሁ የተለየ መመዝገቢያ እንልካለን:: የምረቃ ቀኖችን እና ከተሞችን በሚቀጥሉት ጥቂት ሳምንታት እናስታውቃለን!! ተባረኩ!!

10.3 አዲሲቷ ምድር.pdf6.64 KB

10.2 ሺህ ዓመትና የኃጢአት ፍጻሜ.pdf8.78 KB

10.1 የክርስቶስ_ዳግም_ምጻት.pdf7.94 KB

ትምህርት 10- የታላቁ ተጋድሎ ፍጻሜ እና ሰማያዊቷ አገር ======================== ውድ ተማሪዎች: ወደ 10ኛው ትምህርታችን ደርሰናል:: እስካሁን የረዳንን ጌታ እናመሰግነዋለን:: መልካም የሰንበት እረፍት እንዳሳለፋችሁ እምነታችን ነው:: 10ኛው ትምህርት በክፉ እና በመልካም: በሰይጣን እና በክርስቶስ: በሐሰት እና በእውነት መካከል ለብዙ ሺህ አመታት የተደረገውን የታላቁን ተጋድሎ ድምዳሜ ይዳስሳል:: ምንም እንኳን ክፋት ቢበዛም: ሞት እና ስቃይ ምድሪቱን ቢያጥለቀልቃትም የሕይወትና የሰላም አምላክ ክፋትን አስወግዶ በዩኒቨርስ ላይ ጽድቅን የሚያንሰራፋበት ጊዜ ሩቅ አይደለም:: ኃጢአት እና የኃጢአት ደራሲ የሆነው ሰይጣን ሲወገድ በኢየሱስ ደም ልብሳቸውን ያላጠቡ እና ከኃጢአት ጋር ያልተላቀቁ የዘላለም ሞት ይጠብቃቸዋል:: የሁለተኛው ሞት ተካፋይ እንዳንሆን እውነትን አውቀን ጥሪውን ተቀብለን የሰማይ መንገደኛ የሆነውን እግዚአብሔርን ሕዝብ እንቀላቀል:: መልካም ጥናት

ውድ ተማሪዎች፤ መልካም ሰንበት ይሁንላችሁ! ትምህርታችን ወደ መገባደዱ እየደረሰ ነው። በሚቀይጥለው ሳምንት 10ኛውን እና የመጨረሻውን ትምሀርት እንለጥፋለን። እስካሁን የተማራችሁትን በመከለስ ዋና ዋና ትምህርቶችን እንደገና እንድታጠኑ እንጋብዛለን። መልካም ጊዜ

9.1 ክርስቶስ በሰማያዊው ቤተ መቅደስ.pdf6.52 KB

9.1 ቤተ መቅደስ .pdf1.20 KB

ትምህርት 9:- ክርስቶስ ሊቀ ካህናችን ======================== ውድ ተማሪዎች: የክርስቶስን ምድራዊ ሕይወት: ሞት እና ትንሳኤን ከዚህ በፊት በስፋት ተምረናል። ባለፊት ሳምንታት በተማራችሁአቸው ትምህርቶች እንደተባረካችሁ ሙሉ እምነታችን ነው። አሳልፎ በመስጠት የኃጢአት ዋጋ የሆነውን ሞት በእኛ ፋንታ በመቅመሱ የእሱን ሕይወት ያጋራን ጌታችን የተመሰገነ ይሁን! በጸጋ የዳን ሰው በቅድስና ሕይወት እንዴት መኖር እንዳለበት፡ የእግዚአብሔርን ሕግጋት እንዲሁም አብዛኛው ሕዝብ ሳያውቅ የሚተላለፈውን የሰንበትን እረፍት አጥንተናል። በተጨማሪም ሰው ሲሞት ምን እንደሚሆን፤ ሙታን አሁን ያሉበትን ሁኔታ፤ ነፍስ አትሞትም የሚለው አስተምህሮ ትልቅ ስህተት እንደሆነ እና ከሰይጣን ማታለያ መጠንቀቅ እንዳለብን ባለፉት 2 ሳምንታት ተምረናል። በዚህ ሳምንት ደግሞ በሰማይ አዳኛችን የሚያደርገውን አገልግሎት እናጠናለን፡ ኢየሱስ ክርስቶስ በገዛ ደሙ በሰማይ ወደ ምትገኘው ቤተ መቅደስ ስለ እኛ ሊማልድ በአብ ፋት ቆሟል:: የምድራዊው ቤተ መቅደስ የሰምያዊው ጥላ በመሆኑ ተወግዷል:: የሰማዩ ቤተ መቅደስ ግን አሁንም ለሰዎች ደህንነት የሚሆነው የክርስቶስ ደም ኃጢአትን እየፋቀ ጸጋ እና ምሕረትን ለአማኞት እያዳረሰ ነው! በዚህ ሳምንት - በሰማይ ቤተ መቅደስ የሚደረገውን አገልግሎት እና የክርስቶስን ዳግም ምፃት እንዳስሳለን! መልካም ጥናት!

ከአስተማሪው: ውድ ተማሪዎች: እንደምን ሰነበታችሁ? በዚህ ሳምንት የምንማረው ትምህርት እጅግ ጥልቅ ነው:: ነገር ግን ወተትን እንዲሁም ጠንካራ ምግብን እንድንመገብ የጌታ ፈቃዱ ነውና በመንፈሱ እየታገዝን በክፍት ልቦና እናጥናው:: እንባረክበታለን:: እናንተም በትጋትና በጸሎት እያጠናችሁ እውነተኛው ወደሆነው የእግዚአብሔር ቃል እውቀት እንደምትደርሱ እምነቴና ተስፋየ ነው:: ተባረኩ!! ========================= ከ20 አመት በፊት የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናቴን ስጀምር እኔም ከገጠሙኝ ለማስተዋል ጥልቅ ከሆኑ ትምህርቶች አንዱ ይህ ነው:: በሚገባ ሳስተውለው ለብዙ አደናጋሪ የሚመስሉ ሐሳቦችን ግልጽ አድርጎልኛል:: እጅግ ብዙ የሃይማኖት ድርጅቶች ሳያስቡትም ቢሆን እምነታቸውን የመሰረቱት ነፍስ አትሞትም: ሰው ሲሞት ጽድቅ ካለው ወደ ገነት: ኃጥዕ ከሆነ ደግሞ ወደ ገሃነም ይሄዳል ለዘላለም በቅጣት ይሰቃያል በሚል የተሳሳተ አስተምህሮ ነው:: ይህ አስተምህሮ ለብዙ ማሳሳቻዎች ራሳችንን እንድናጋልጥ ያደርገናል:: ይህ የስህተት አስተምህሮ ሰይጣን በኤድን ገነት "በእርግጥ አትሞቱም" በማለት ለሔዋን ከነገራት ውሸት የመነጨ ነው:: በዚህም የሚከተሉትን መሰረታዊ ነገሮችን ለማሳፋለስ አልሞ ነው:- 1. የእግዚአብሔር ፍቅር እግዚአብሔር ፍቅር ነው:: ለበደለኛውም ለጻድቁም ሁሉ ፍቅር ነው:: ጸሐይና ዝናብን ለሁሉ የሚሰጥ በጸጋ የተሞላ ነው:: ተስፋን የሰጠን እርሱ ነው:: ይህ የፍቅር አምላክ ቅን ፈራጅም ነው:: ያጠፋል ያድናልም:: ነገር ግን ፍጥረቶቹን በማሰቃየት ግን አይደሰትም:: በማይጠፋ እሳት ውስጥ ለዘላለም እያንገበገበ በስቃያቸው መደሰት እና መቅጣት የፍቅሩ ባህርይ አይደለም:: እንኳን በስቃይ ኃጥእ ሞት ደስ የማይሰኝ አምላክ ነው ያለን:: ( ሕዝ 18:23) እግዚአብሔርን ጨካኝና በዘላለም እሳት ፍጥረቱን የሚቀጣ ነው ብለን እንድናስብ የሰይጣን ፍላጎት ነው:: ከኃጢአት ካልተመለስን ለዘላለም እንሞታለን:: ካመንን ለዘላለም በሕይወት እንኖራለን:: ግልፅና ቀላል ነው:: የዘላለም ስቃይ አስተምህሮ ከእግዚአብሔር ፍቅር ጋር በቀጥታ ይጋጫል! እግዚአብሔር ትናንትም ዛሬም ነገም ለዘላለም ፍቅር ነው:: 2. የክርስቶስ ዳግም ምፃት ስንሞት ነፍሳችን ወደ ገነት ገብታ በደስታ የምትኖር ከሆነ የክርስቶስ ዳግም ምጻት ለምን አስፈለገ? ሄጄም ስፍራ ባዘጋጅላችሁ፥ እኔ ባለሁበት እናንተ ደግሞ እንድትሆኑ ሁለተኛ እመጣለሁ ወደ እኔም እወስዳችኋለሁ። የዮሐ 14:3 ስንሞት በመቃብር እናርፋለን:: እኛ ምንም አናውቅም:: ሕይወታችን በታማኙ በእግዚአብሔር እጅ ነው:: በዳግም ምጻቱ ጊዜ በጌታ አምነው ያረፉት የመለከቱን ድምጽ ሲሰሙ ይነሳሉ:: ጌታን በአየር ለመቀበል መቃብር ሁሉ ይከፈታል:: ወደ ሰማይ እንሄዳለን (1ኛ ተሰ 4) ጌታችን ግልጽ ነው:: ስትሞቱ ገነት ትመጡና ቦታ እሰጣችሁዋለሁ አላለም:: ቦታን አዘጋጅላችሁዋለሁ አብራችሁኝ እንድትሆኑ ተመልሼ እመጣለሁ እወስዳችሁዋለሁ ነው ያለን:: ስለዚህ ግሩም ተስፋ የጌታ ስም ይባረክ!! 3. ክርስቶስ ብቻ አማላጅነት ነፍስ አትሞትም የሚለው ትምህርት ቅዱሳን ለኃጢአት ምልጃና ልመና ያቀርቡልናል (ያማልዱናል) የሚለውን የስህተት ትምህርት ወልዷል:: ቅዱሳን ቢሞቱን በገነት ስለሚኖሩ ሊያማልዱን ይችላሉ የሚለው ትምህርት ከዚህ የስህተት ትምህርት የመነጨ ስህተት ነው:: በተለየ መነጠቅ ( ኤልያስና ሔኖክ) እንዲሁም ትንሳኤ ( ሙሴ) በሰማይ ያሉ ቢሆኑም ሌሎች ቅዱሳን ግን በመቃብር ትንሳኤን የሚጠብቁ ናቸው:: ሙታን ስለሆኑ እንዳች አያውቁም ሊያማልዱን አይችሉም:: ብቸኛውና በአብ ፊት ለኃጢአታችን የሚማልደው ጠበቃችን ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው:: ሌሎቹ ሙታን ናቸው ምንም አያውቁም!! 4. ሙታን አንዳች አያውቁም (መክ 9:5) ብዙ ሰዎች በምድር እያሉ ከሞት ተነስተዋል:: አላዛር ትልቁ ምሳሌ ነው:: ነገር ግን ከሞት ከተነሱ በሁዋላ ስለ ገነት ሲያወሩ አልተጻፈም:: ነፍሳቸው ገነት ሄዳ ቢሆን ኖሮ ስለውበቱ: ስለድምቀቱ ያዩትን ባወሩ ነበር:: ነገር ግን እንቅልፍ በሚመስል የሞት ጸጥታና እረፍት ውስጥ ስለነበሩ ስለሰማይ ያሉት ነገር የለም:: በዚህ ዘመን ሙታንን ማነጋገር ይቻላል የሚል አደገኛ ትምህርት እየመጣ ነው:: በቅርቡ በየቤተክርስትያኑ በሐሰተኛ ነብያት አማካኝነት ተስፋፍቶ የሞተውን አባት እናት ወንድም እህት አናግሩ የምትባሉበት ጊዜ ይመጣል:: እኔ በምኖርበት አገር በጣም ተስፋፍቷል:: ይህ የሰይጣን አደገኛ ማሳሳቻ ስለሆነ ተጠንቀቁ :: አስታውሱ ሙታን አንዳች አያውቁም:: ሰይጣም የአባትና የእናትን ድምፅ በማስመሰል ሊያሳሳችሁና ገደል ሊከታችሁ ይሻል:: መልካም ጥናት!!

ውድ ተማሪዎች: "እውነት እውነት እልሃለሁ ዛሬ በገነት ከእኔ ጋራ ትሆናለህ" ይህ ጥቅስ በመጠቀም ብዙዎች ጌታ እንዲሁም ሌባው ሲሞቱ በዚያው ቀን በገነት ነፍሳቸው ሄዳለች ይላሉ:: 1. "ዛሬ" የሚለውን ቃል በoriginal አጠቃቀሙ ዛሬ በገነት ትሆናለህ ለማለት ሳይሆን "እውነት እውነት እልሃለሁ ዛሬ" የተስፋውን እርግጠኝነት ለመግለጥ ጥቅም ላይ የዋለ ነው:: ምክንያቱን አርብ ቀን ጌታችን ከሞተ በሁዋላ ወደ ሰማይ አልወጣም:: በትንሳኤ ማለት በደስታ ልታቅፈው የተጠጋችውን ማርያምን ወደ ሰማይ እንዳልወጣ በግልጥ እንዲህ አላት:- ኢየሱስም፦ ገና ወደ አባቴ አላረግሁምና አትንኪኝ፤ ነገር ግን ወደ ወንድሞቼ ሄደሽ፦ እኔ ወደ አባቴና ወደ አባታችሁ ወደ አምላኬና ወደ አምላካችሁ ዓርጋለሁ፡ ብለሽ ንገሪአቸው፡ አላት። የዮሐንስ ወንጌል 20:17

8.7 የሚጣረሱ ጥቅሶች ?.pdf6.79 KB

8.6 የገሃነም እሳቶች .pdf6.50 KB

8.5 ገሃነም ምንድነው?.pdf1.49 KB