ch
Feedback
የደቀ መዝሙርነት ት/ቤት - Classroom

የደቀ መዝሙርነት ት/ቤት - Classroom

前往频道在 Telegram

ይህ የደቀ መዝሙርነት ትምህርት ቤት መማርያ ክፍል ነው!

显示更多

📈 Telegram 频道 የደቀ መዝሙርነት ት/ቤት - Classroom 的分析概览

频道 የደቀ መዝሙርነት ት/ቤት - Classroom (@aybcschool) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 16 386 名订阅者,在 教育 类别中位列第 12 380,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 048

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 16 386 名订阅者。

根据 17 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -450,过去 24 小时变化为 -7,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 26.70%。内容发布后 24 小时内通常能获得 8.11% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 4 376 次浏览,首日通常累积 1 329 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 35

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
ይህ የደቀ መዝሙርነት ትምህርት ቤት መማርያ ክፍል ነው!

凭借高频更新(最新数据采集于 18 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 教育 类别中的关键影响点。

16 386
订阅者
-724 小时
-687
-45030
帖子存档
ሐሰተኛ ነብያት እና የመጨረሻው ዘመን ======================== ነብይነት በጣም የተለየ ጥሪ ነው:: መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ስማቸው የተጠቀሱትን የአብዛኞቹን ነብያት አገልግሎት ስናጠና እግዚአብሔር እንዴት በግልፅ እንደመረጣቸው እንጂ በራሳቸው ወይስ በሰዎች ያገኙት ሹመት ወይም ማዕረግ አለመሆኑን እንረዳለን:: የተለየ አገልግሎት ስለሆነ የተለየ ጥሪ ያስፈልገዋል:: የኢሳይያስን: የኤርምያስን: የዳንኤን: የመጥምቁ ዮሐንስን ሕይወት ማጥናት ለዚህ በቂ ነው:: እውነትን በየዘመናቸው ለማስተዋል ዋጋ የከፈሉ: በመከራ ማዕበል ለእውነት ጸንተው የቆሙ እንዲሁም ዘመን ተሻጋሪ የሆኑ ትንቢቶችን እና መንፈሳዊ በረከቶችን ጥለው ያለፉ ነብያት ናቸው:: በዘመናችን በተለይ በኢትዮጵያ ባለፉት 10 አመታት ብዙ ሽህ ነብይ ነን የሚሉ ሰዎች ፈልተዋል:: እነዚህ ግለሰቦች የእግዚአብሔርን ትእዛዛት በግልፅ እየሻሩ: በተንደላቀቀ ሕይወት እየኖሩ: ሕዝቡን በትንቢትና በፈውስ ስም እየበዘበዙ ይኖራሉ:: ተማሪዎቻችን: ከእነዚህ አይነት ሐሰተኛ ነብያት እና አስተምህሮዎቻቸው ትጠበቁ ዘንድ የእውነተኛ ነብይ መስፈርቶች ምን ምን እንደሆኑ በጥንቃቄ ታጠኑ ዘንድ እንጋብዛለን:: በመጨረሻው ዘመን ሰይጣን የአለምን ሕዝብ በተሳሳት ትምህርት ውስጥ ጠፍሮ ለመያዝ እጅግ ብዙ ሐሰተኛ ነብያትን ያስነሳል:: እነዚህ የሰይጣን መልእክተኞች ደግሞ ድንቅና ታምርን ማድረግ የሚችሉበትን ኃይል ይሰጣቸዋል:: በክርስትና ስም የሚድረጉትን እነዚህ ታምራት የሰዎቹን የሐሰት ትምህርት እና የረከሰ ሕይወት ይደብቃሉ:: እንጠንቀቅ!! ዮሐንስ በራእይ በመጨረሻው ዘመን ይህን የሰይጣን እኩይ ተግባር ሲገልጥ እንዲህ በማለት ነበር: "ከዘንዶውም አፍና ከአውሬው አፍ ከሐሰተኛውም ነቢይ አፍ ጓጕንቸሮች የሚመስሉ ሦስት ርኵሳን መናፍስት ሲወጡ አየሁ:: ምልክት እያደረጉ የአጋንንት መናፍስት ናቸውና፥ በታላቁም ሁሉን በሚገዛ በእግዚአብሔር ቀን ወደ ሚሆነው ጦር እንዲያስከትቱአቸው ወደ ዓለም ሁሉ ነገሥታት ይወጣሉ።" ራእይ 16:13-14 ከዚህ ምልክትን እያደረገ ከሚመጣው የአጋንንት መንጋ: ከእግዚአብሔር እውነት አርቆን ወደ ሰይጣን የጦር ሰፈር ከሚወስድ ማሳሳቻ እግዚአብሔር ይጠብቀን!! ተባረኩ!!

7_5_በልሳን_መናገር_ትርጉምና_አጠቃቀሙ.pdf2.36 KB

7.4 የዘመኑ ነቢያትና ሐዋርያት.pdf3.89 MB

7_3_የነብያት_አገልግሎት_እና_መመዘኛው.pdf4.03 MB

7.2 የአገልግሎት መንፈሳዊ ሥጦታዎች .pdf2.60 MB

7.1 እግዚአብሔርን ማገልገል ሕይወት.pdf1.60 MB

ትምህርት 7- በመንፈሳዊ ስጦታዎች እግዚአብሔርን ማገልገል ======================== ውድ ተማሪዎች: እንደምን ሰነበታችሁ? ባለፉት 2 ሳምንታት በጸጋ የዳነ ሰው በምን መልኩ መመላለስ እንደሚገባው በሚገባ አጥንተናል:: እግዚአብሔርን መታዘዝ ያለውን በረከት አይተናል። እውነተኛው የእግዚአብሔር ሰንበት ሰባተኛው ቀን ቅዳሜ መሆኑን አጥንተናል:: በዚህ ሳምንት ደግሞ መንፈሳዊ ስጦታዎች በክርስትና ሕይወት ላይ ያላቸውን ሚና እናጠናለን:: በተጨማሪም የትንቢት ስጦታን በስፋት እንመረምራለን:: ዘመናችን ራሳቸውን በነብይ ስም የሚጠሩ ነገር ግን በሕይወታቸው የእግዚአብሔርን ትእዛዝ የሚሽሩ: በቀድሞ የእግዚአብሔር ነብያት መስፈርት ቢመዘኑ የሚወድቁ ናቸው:: ስለዚህ ራሳችንን ከሐሰተኛ ነብያትና እና ከስሕተት ትምህርታቸው ለመጠበቅን እውነተኛ ነብያትን መለያ መስፈርቶች ምን ምን እንደሆኑ ለይተን ማወቅ ያስፈልገናል:: በዚህ ትምህርት እነዚህን ዋና ዋና ሐሳቦች እንዳስሳለን! ተባረኩ!!

ሰንበት_ ክፍል-2.mp38.81 MB

የእግዚአብሔር ፀጋ እና የእግዚአብሔር ሕግ ======================== አንዳንዶች በብሉይ ኪዳን ጊዜ ሰዎች ይድኑ የነበረው ሕግን በመጠበቅ ሲሆን በአዲስ ኪዳን ዘመን ግን ሕጉ ስለተሻረ የሚድኑት በፀጋ ነው ብለው ያስተምራሉ:: ይህ አስተምህሮ ፍጹም የተሳሳተ ነው:: ድሮም: አሁንም ወደፊትም ሰው የሚድነው በእምነት በሚገኘው ፀጋ እንጂ ሕግን በመጠበቅ ወይም መልካም ሥራ በመስራት አይደለም:: ሕግን በመጠበቅ ካልዳንን "ሕግ በክርስትያን ሕይወት ላይ ያለው አስተዋጽኦ ምንድነው?" ብለን መጠየቅ ያስፈልጋል:: የእግዚአብሔር ትዕዛዛት ዘላለማዊ ናቸው:: አስርቱ ትዕዛዛት አምላክን በፍጹም ልብ መውደድ እና ባልጀራችንን መውደድን ያስተምሩናል:: ፍቅር ደግሞ የሕግ ፍጻሜ ነው:: እነዚህ ቅዱስ ቃላት ፍቅርን እንድንለማመድ ያበረታቱናል:: ነገር ግን አያድኑንም:: ጳውሎስ በመገረዝ ለመዳን ያሰቡትን የገላትያ ሰዎች ለመዳን የመገረዝ ሕግ አስፈላጊ እንዳልሆነ: አህዛብ እንዲድኑ የአይሁድን የመንጻትና የመገረዝ ሕግ መጠበቅ እንደማያስፈልጋቸው ያስተምራቸዋል:: መዳን የፀጋ ስጦታ ነው:: ነገር ግን በፀጋ ለምንድን ለእኛ ሕግ ኃጢአት የሚጠቁም መስታዎት ነው:: ጳውሎስ እንዳለው" እንግዲህ ምን እንላለን? ሕግ ኃጢአት ነውን? አይደለም፤ ነገር ግን በሕግ ባይሆን ኃጢአትን ባላወቅሁም ነበር፤ ሕጉ፦ “አትመኝ፡” ባላለ ምኞትን ባላወቅሁም ነበርና። ሮሜ 7:7፤ ያለ ሕግ ኃጢአት አይታወቅም:: ከአስርቱ ትእዛዛት አንዱ ሁሉም ወይም ተሽሯል ማለት ኃጢአትን የምናውቅበት መንገድ ተወገደ ማለት ነው:: ይህ ደግሞ ኃጢአተኛው ኃጢአቱ ተገንዝቦ ወደ ንስሐ እንዳይመጣ ይከለክላል:: ንስሐ ከሌለ ደግሞ በፀጋ የሚገኘውን መዳን ማጣጣም አይችልም:: ስለዚህ ሕግ በፀጋ እንድንድን ኃጢአታችንን የሚያስታውቀን መስታውት ነው:: ወደ ፀጋ የሚያመጣን ሞግዚት ነው:: እንደዚህ በእምነት እንጸድቅ ዘንድ ሕግ ወደ ክርስቶስ የሚያመጣ ሞግዚታችን ሆኖአል፤ ገላትያ 3:24 በፀጋው ድኛለሁ የሚለው ሕዝብ የእግዚአብሔርን ትእዛዛት ችላ ስላለ አገራችን የክፋት አረንቋ ውስጥ ናት:: የእግዚአብሔር ትእዛዛትን በፀጋው ሐይል ለመጥበቅ ብንተጋ በሕዝባችን የሚታየው ስርአት አልበኝነት: አልቂት: ሰቆቃ: ሌብነት: ነፍሰ ገዳይነት: አመንዝራነት እንዴት በተቃለለ! ሰላምና ፀጋ ይብዛላችሁ! አስተማሪው!

ሕግጋቱ በሁለት ይጠቃለላሉ ======================== አስርቱ ትእዛዛት በሁለት ይከፈላሉ:: የመጀመሪያዎቹ አራቱ በሰውና በእግዚአብሔር መካከል ሊኖር የሚገባውን ግንኙነት የሚያስተምሩ ሲሆኑ የቀሩት ስድስቱ ደግሞ በሰዎች መካከል ሊኖር የሚገባውን ግንኙነት ያስታውሳሉ:: የመጀመሪያዎቹ አራቱ እግዚአብሔርን እንድንወድ የሚያዝዙ ሲሆኑ የቀሩት ስድስቱ ደግሞ ሰዎችን መውደዳችን እና ማክበራችን ላይ ያተኩራሉ:: ይህን የተረዳ አንድ ሕግ አዋቂ ጌታችንን ከትእዛዛት ሁሉ የትኛይቱ ታላቅ ናት ብሎ ሲጠይቀው ኢየሱስም እንዲህ አለው፦ “ጌታ አምላክህን በፍጹም ልብህ በፍጹም ነፍስህም በፍጹም አሳብህም ውደድ። ታላቂቱና ፊተኛይቱ ትእዛዝ ይህች ናት። ሁለተኛይቱም ይህችን ትመስላለች፥ እርስዋም፦ ባልንጀራህን እንደ ነፍስህ ውደድ፡ የምትለው ናት። በእነዚህ በሁለቱ ትእዛዛት ሕጉም ሁሉ ነቢያትም ተሰቅለዋል።” ማቴዎስ 22:36-39 ሁሉም አስፈላጊ ናቸው:: ሁሉም የሕይወት መመሪያ ይሆናሉ:: አራተኛው የሰንበት ትእዛዝ በተደጋጋሚ የተነሳው አብዛኛው ሕዝበ ክርስትያን በማወቅም ሆነ ባለማወቅ የሚጥሰው ትእዛዝ ስለሆነ ይህን ለማሳሰብ ነው:: እንግዲህ ከነዚህ ከሁሉ ካነሱት ትእዛዛት አንዲቱን የሚሽር ለሰውም እንዲሁ የሚያስተምር ማንም ሰው በመንግሥተ ሰማያት ከሁሉ ታናሽ ይባላል፤ የሚያደርግ ግን የሚያስተምርም ማንም ቢሆን እርሱ በመንግሥተ ሰማያት ታላቅ ይባላል። ማቴዎስ 5:19፤ ተባረኩ!!

6.7 የአለም ሕዝብ የሚተላለፈው ሕግ.pdf1.39 KB

6.6 የሰንበት መለዎጥ.pdf1.61 KB

6_5_ታሪክ_የረሳው_ቀን_ጊዜው_መጽሔት_በፋንታሁን_መላኩ.pdf1.32 MB

6.4 ግር አለህ እንዴ ስለ ሰንበት?.pdf3.11 MB

ሕግ ሁሉ የተሰጠው እንዲጣስ ነው። . . . ነው እንዴ? በትምህርታችን እየተከታተልን እንዳለነው በኃጥአት ለወደቀው አለም ሕግ አስደሳች ነገር እንዳልሆነ ነው። በሥጋዊ ኑሮ አድማስ ውስጥ መታዘዝ ገደብ አለው። በተለይ ለኃጢአት ባሪያ በሆነ አዕምሮ ልክ የሚመስሉ ነገሮች ከእግዚአብሔር ሐሳብ በፍፁም የራቁ በመሆናቸው በእግዚአብሔር ሐሳብ ልክ መታዘዝ እንዲሁም እርሱን ማስደሰት አይችሉም። ስለዚህም ሰው በሐገ-ጠልነቱ ይታወቃል። ከእርሱ በላይ የሕይወቱን አቅጣጫ የሚወስንለትን ሌላ አካል አይፈልግም። ስለ ሥጋ ማሰብ በእግዚአብሔር ዘንድ ጥል ነውና፤ ለእግዚአብሔር ሕግ አይገዛምና፥ መገዛትም ተስኖታል፤ በሥጋ ያሉትም እግዚአብሔርን ደስ ሊያሰኙት አይችሉም (ሮሜ 8፡ 7ና 8)። በእግዚአብሔር ሕግ ለመደሰት እግዚአብሔር ማን እንደሆነ ማስተዋል ያስፈልጋል። እግዚአብሔር ፍቅር ነው። ፍቅር በሚለው ቃል ውስጥ ምሕረት እና እውነት ይገኛሉ [መዝ 85፥10]። እውነት የእግዚአብሔርን ፍትሐዊ አገዛዝ ይወክላል። ምሕረት ደግሞ ለሰዎች ልጆች ሁሉ ሳይለያይ የፈሰሰውን ጸጋውንና ይቅርታውን ያሳያል። እግዚአብሔር ሕግን እንድንጠብቅ የሚሻው ከዚህ መነፅር አኳያ ነው። የሰውን አልታዘዝ ባይነት በሀይል ወይም በፍርሃት ከማስገዛት ይልቅ በፍቅር ብቻ የተነሳሳ የመታዘዝ ሕይወት እንዲኖረን አስቀድሞ ወደደን። ፍቅር ለባልንጀራው ክፉ አያደርግም፤ ስለዚህ ፍቅር የሕግ ፍጻሜ ነው (ሮሜ 13፥ 10)። አንድ ጉልበተኛ ሰው ነበር አሉ። ይህ ሰው በጊዜው የባሪያ ንግድ የተፋፋመበት ጊዜ ነበርና ጉልበቱን ሊበዘብዙ ሰዎች ይፈልጉት ነበር። ኃይለኝነቱ በሥራ ብቻ ሳይሆን በባሕርይም ጭምር ነበር። ጉልበት ቢኖረውም ፀባይ ግን አልነበረውም። ታዲያ በገዢዎቹ ፊት ለጨረታ በሚቀርብበት ጊዜ [እንኳንም ያ ጊዜ አለፈ] ለማናቸውም እንደማይታዘዝ፣ ጉልበቱን ለማንም አሳልፎ እንደማይሰጥ እየዛተ ነበር። ጨረታው ተጀመረ። ይህ እንግዲህ በዙ ዋጋ የሚያወጣ ሰው በመሆኑ ብዙ ሰዎች ከፍ ያለ ዋጋ በመስጠት ለመውሰድ ተሽቀዳደሙ። ድንገት ከበስተኋላ አንድ በፍፁም ሊደርሱበት የማይችሉት ዋጋ አንድ ሰው ጠራ። በዚያ የሚገኙት ሁሉ በመገረም የቱንም ያህል ሀብታሞች ቢሆኑም አንድ ባሪያ ላይ ግን ይህን ያህል ገንዘብ ማፍሰስ አስፈላጊ ስላልመሰላቸው ተውት። ይህን አመፀኛ ባሪያ ከነሰንሰለቱ የተረከበው ገዢ ቁልፉን ከተቀበለ በኋላ ወደ ቤቱ ይወስደው ጀመር። በመንገዳቸው በውድ ዋጋ መገዛቱ ለርሱም ምኑም እንዳይደለ፣ ለመሥራት ከመለገም ወደኋላ እንደማይል እየዛተ መንገዳቸውን ቀጠሉ። ድንገት ከሰዎች እይታ ውጪ ሲሆኑ ባለቤቱ የባሪያውን ሰንሰለት በመፍታት በነፃ እንዲሄድ ነገረው። በውድ ዋጋ የገዛውም የእርሱን ሥራ እንዲሰራለት ሳይሆን በነፃነት እንዲኖር መሆኑን አሳወቀው። ይህ አመፀኛ ባሪያ በድንጋጤ ቆመ። ለመጀመሪያ ጊዜ የነፃነትን አየር ተነፈሰ። ይህ ሰው ለምን እንዲህ እንዳደረገ ባያስተውልም የነፃነቱ ምክንያት ግን ገዢው እንደሆነ ተገነዘበ። ወዴት ይሄዳል ታዲያ? ከዚህ ሰው ጋር ለመኖር ወሰነ። ጉልበቱን ሳይሰስት ሊያገለግለው፣ በደስታ ሊሰራለት በጊዜ ያልተገደበ አገልግሎት ሊሰጠው ቃል ገባለት። መታዘዝ ነጻ የመውጣት ውጤት ነው። መታዘዝ የመዳን ፍሬ ነው። እግዚአብሔርን መታዘዝ እድል ነው

6.3 የሰንበት ዕረፍት.pdf1.67 MB