አልፋና ዖሜጋ የንጽጽርና የትምህርት መገኛ አደባባይ (አዖተ)
رفتن به کانال در Telegram
በዚህ የንጽጽር አደባባይ በኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልዕክታት የተገለጸው እውነት ሲፈጸምና ይፈጸም ዘንድ በመላው ዓለም ሲንቀሳቀስ የሚከሰቱ ጉዳዮችን እናቀርባለን ! ስለእምነታችን እንማማራለን ! ስለመልዕክታቱ እንነጋገራለን ! ➝ይህ የአልፋና ዖሜጋ ( @christian930 ) ገጽ ቅርንጫፍ የንጽጽርና የመማሪያ ገጽ ነው።
نمایش بیشتر4 823
مشترکین
+324 ساعت
+67 روز
+2430 روز
آرشیو پست ها
አውሮፓን ክፉኛ በመታው የሙቀት ማዕበል በፈረንሳይ፣ ቤልጅየምና ኔዘርላንድ ቢያንስ 3,700 ሰዎች መሞታቸውን ለማወቅ ተችሏል። ቁጥሩ ሊጨምር እንደሚችልም የየሃገራቱ ባለስልጣናት አስጠንቅቀዋል።
እንደ ጎርጎሮሳውያኑ አቆጣጠር በሰኔ ወር ከ20 እስከ 28 ቀን 2026 ባለው ጊዜ የታየው ሙቀት በአውሮፓ ታሪክ ከፍተኛው ነው ተብሎለታል። የሙቀት ማዕበሉ መንገዶችና የባቡር ሃዲዶችን ጨምሮ በርካታ መሰረተ ልማቶች ላይም ጉዳት አድርሷል።
DW
Repost from አልፋና ዖሜጋ የንጽጽርና የትምህርት መገኛ አደባባይ (አዖተ)
🟢🟡🔴
ሰኔ 26 | የሊቀ መላእክት #ቅዱስ_ገብርኤል በዓሉ ነው፨
በዚህች ቀን ኔቅሎን በሚባል አገር በፍዩም ገዳም ቤተ ክርስቲያኑ የተከበረችበት ነው።
በውስጧም ከቤተ ክርስቲያኗ የጣራ ዕንጨት ብዙ ተአምር ይገለጽ ነበር። ጽጋብ በሚሆንባት በዚያች ዓመት ውኃ ይንጠፈጠፋል። ረሀብ ከሆነ ግን ላብ እንኳ አይታይም ነበር።
የዚህ የከበረ የመላእክት አለቃ ገብርኤል ተአምራቶቹ ብዙዎች ናቸው።
እንዲሁም በዚሁ ወር ሰኔ 13 ቅዱስ ዳንኤል ነቢይን ያዳነበት በዓሉ ነው።
ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በአማላጅነቱ ይማረን ረድኤቱም ከእኛ ጋራ ትሁን ለዘላለሙ አሜን።
t.me/Ewnet1Nat
☁️ ዘመነ ክረምት ሰኔ ፳፮–መስከረም ፳፭
ውሃ ሙላት እንዳይወስደን ሲጎድል ሲጎድል ምርኳዝ ይዘን መሻገር ነው።
ባንድ ዐሳብ ተስማሙ፥ አንድ ፍቅር አንድም ልብ አንድም ዐሳብ ይሁንላችሁ፤
ለወገኔ ይጠቅማል በማለት ወይም በከንቱ ውዳሴ ምክንያት አንድ እንኳ አታድርጉ፥ ነገር ግን፥ እያንዳንዱ ባልንጀራው ከራሱ ይልቅ እንዲሻል በትሕትና ይቍጠር፤
እያንዳንዱ ለራሱ የሚጠቅመውን አይመልከት፥ ለባልንጀራው ደግሞ እንጂ።
በክርስቶስ ኢየሱስ የነበረ ይህ ዐሳብ በእናንተ ዘንድ ደግሞ ይሁን።
እርሱ በእግዚአብሔር መልክ ሲኖር ሳለ ከእግዚአብሔር ጋራ መተካከልን መቀማት እንደሚገ፟ባ፟ ነገር አልቈጠረውም፥
ነገር ግን፥ የባሪያን መልክ ይዞ በሰውም ምሳሌ ሆኖ ራሱን ባዶ አደረገ፥
በምስሉም እንደ ሰው ተገኝቶ ራሱን አዋረደ፥ ለሞትም ይኸውም የመስቀል ሞት እንኳ የታዘዘ ሆነ።
ወደ ፊልጵስዩስ ሰዎች 2፥2-8
- በልዩ ሁኔታ የተነገረ ከጽዋ ውጭ የሆኑትንና ቅን የዋህና ትሁት የሆኑትን በዚህ መንገድ ቤተሰቦቻችን በተመለከተ አባት ተብየዎችን አይተው ዋጋ እንደሌላቸው አይተው አውቀው ወደቀናው መንገድ ወደቤታቸው የተመለሱ ቅን የዋህ የሆኑ ቤተሰቦች አሉ። ቀድሞ ጽዋ የነበራቸውም ያልነበራቸውም አሉ ወደቤታቸው በንስሐ የተመለሱ። ከአባቶች ከገዳም አባቶች ሁሉ በአባቶቻችን ጸሎት በብዙ ታግዘውና ተጠብቀው ጥፋትን በጥፋት ላይ ያበዙና በውስጣቸው ምንፍቅና ይዘው የቀጠሉ በዛውም እንደወጡ ይቅሩ እንጅ አባቶቻችን እኛ ከአላማችን አንዛነፍም ብለው በመቀጠላቸው እነሱም በሄዱበት የወጡና በዛው የቀሩ አሉ። ለእነዚህም በአባቶቻችን በተስፋ ይደረግ የነበረው ጸሎትም ትዕግሥትም ቁሟል። ሌሎችም በልምድ የሚመላለሱ ባልቴቶች ውግዘቱን ጥሰው የሚነጉዱት የአባቶች ሱስ እንደ ቡና ሱስ ሆኖባቸው ተጣብቀው የቀሩ ነበሩ። እንደወጡ የሚቀሩ ናቸው። እግዚአብሔር ይሄንን ብሏል የሚያሳዝን ነው። ስለቅን ፍርዱ እግዚአብሔር ይመስገን እንዳትደነግጡ የተዋሕዶ ልጆች ብዙዎች ልናጣ እንችላለንና እየደማንም እየተሰማንም የመጣው ጊዜ አስጨናቂ የፍርድ ጊዜ ስለሆነ አይዟችሁ ። በጸሎት አስቡን እኛ ደካሞች ወንድሞቻችሁን።
https://t.me/Ewnet1Nat/18455
ካዳመጥነው የያዝነው ማስታወሻ ነው።
በተቻላችሁ ደጋግማችሁ አዳምጡት ቤተሰቦቼ!!
- ጽዋ ከ6ወርና አመት በላይ የቀሩ ማውጣት አይችሉም። እስከ እግድ የሚደርስበት ምክንያት ይሄ ጊዜ የሚጠራበት ስለሆነ ነው። ክፉ ቀን ሲመጣማ ሁሉም ይመጣልና።
- ጽዋ አባል ያልሆነ ትልልቅ ሰው ተብሎ እንግዳ ተብሎ ጽዋ መቅመስ አይችልም። ተጋብዞ ግን ዝክር ሊቀምስ ይችላል እንጅ ጽዋ ከአባላቱ ውጭ ማንም አይቀምስም።
- ቆረብን እያሉ ጽዋ የሚጠጡ አሉ ላላችሁን ትጉኃን መማክርት #አመራር ሁነው ውግዘት የማያከብሩ እናግዳለን። አባል ሆነው ውግዘት የማያከብሩ ከትንሽ ጊዜ በኋላ እናግዳለን አሁን ጥቂት ጊዜ ሰጥተናል። አመራር ግን አንታገስም።
- ውግዘትን የማያከብሩ ካህናት ካሉ ይታገዳሉ። ጽዋ የሚጠጡም ብቻ ቢሆኑ ይታገዳሉ። ካህናትን ውግዘት ካላከበሩ አንታገስም። ከእምነት የወጣ አካሄድ የሚሄዱ ካሉ በማስረጃ አሳውቁን ከቤተሰብነት እናግዳለን። አገልጋይ የሚባሉ ካህናትና ሙሴዎች መማክርትን አንታገስም። ተጠራጥረው የሚያጠራጥሩ ክደው የሚያስክዱ ስለሆኑ አንታገስም። መረጃዎችን አሳውቁን።
- የጣዖት አሰራር የሚሰሩ ባሉበት የመንፈስቅዱስ ስራ አይሰምርምና ፀሎታችን እንዲሰማ ውስጣችን ሆነው የበግ ለምድ የለበሱ ተኩላዎች አጋልጡልን። በፍጥነት እናስወግዳለን።
- ጽዋ ከቀመስን በኋላ ስራ መስራት አለመስራት በሚለው እናት አባቶቻችን ጽዋ እንዴት ይጠጡ ነበር ብላችሁ ጠይቁ። እንደቦታና አካባቢያችሁ ማድረግ ትችላላችሁ ። እንደ ባሕልና ወጉ አድርጉ።
- አንዳንድ አመራሮች እኔን መናገር አትችሉም ይሉናል ብዙ ደጋፊ አላቸው ላላችሁን ትዕቢተኛ አገልጋይ የሆነው ዋጋውን ከክርስቶስ ሲቀበል ፍርድና ተግሳጽ ይገጥመዋል። ከእሱም አልፎ ተርፎ ለሌላው ይተርፋልና በትዕቢት አትራመዱ። በአመራርነት የማይስተካከሉ ትዕቢተኞች አምባገነንነት መሄድ አይገባም አባላትን አታስለቅሱ ተስተካከሉ። ንቅለ ተከላ ስላለ ራሳችሁን አስተካክሉ።
- አንዳንድ የሥጋ ቤተሰቦቻችን መናፍቃን ናቸውና አብረን መብላት ወዘተ እንችላለን ወይ ለምትሉ የሚያምን ከማያምን ጋ ሕብረት የለውምና እርኩስ ከሆነው ጋ መቀላቀል የለብንም። የእምነት ምንዝርና አያሳልፍም ስለዚህ ራሳችሁን ከክህደት ከጥርጣሬ ጠብቁ። ይቅርታ የለውምና። ከመናፍቃን ጋ ሕብረት ያላችሁ ከእነሱ ተለዩ። አብሮ የሚኖርም ቢሆን ተለዩ። እግዚአብሔርን ጠይቁና በሚመራችሁ ተጓዙ።
- የእርኩሳን መናፍስት አሰራር ላይ መንፈስ የያዘው ሰው ጽዋ እስከመረበሽ ከደረሱ አንዳንዱ ወዶ አይደለም የሚሰቃይ። አንዳንዱ ደግሞ በእግጥም ድራማ ነውና መንፈስን ሁሉ አትመኑ። እናንተ ከእግዚአብሔር ጠይቃችሁ እውነተኛ ታማሚ ከሆኑ አጥማቂ ወደሌለበት ቦታ ወደፀበል መውሰድ ነው። አባላት ማገዝ ነው። አጋንንት እየረበሸ አመራሮች መፍቀድ የለባችሁም። አባላትን አታሰናክሉ።
- የእርኩሳን መናፍስት አሰራር ላይ አባላት ሁናችሁ በጽዋ የሚረብሽ ካለ እናግደውና ሲድን እንመልሰዋለን። ጽዋው መረበሽ የለበትም። ለምን ይሄ ይደረጋል የምትሉ በተግባር ያየነው ነገር ስላለ እናንተም አስተውሉ።
- ሕልም አየን እየተባለ ያልሆነ መልዕክት የሚያስተላልፉ አባላት አሉ። እገሌ እንዲህ ይሆናል ሲታመም ሊቀጣ ነው በሕልሜ ተነግሮኛል ቅጣት ነው እያሉ መመሪያ የመሰለ ሕልም አየን እያሉ የሚናገሩና ክፍተት የሚፈጥር አለ። ችግሩ፦ አመራር የሆኑት ምስጢር እያሳለፉ በሚሰጡት ምክንያት ነው። ምስክርነት ሙሴና መማክርት ሳይሰማው በፍጹም መመስከር የለበትም። ስለዚህ ሰውን የሚሰብርና የሚጎዳ መልዕክት ምስክርነት እየተባለ መነገር የለበትም።
- አንዳንድ ቦታ ላይ ጥርጥርን ለመፍጠር የሚተጉ እንዳሉ ብርቱም ስላሉ እየታገሳችሁ መኖር መልካም ነው።
- መከራ ስደት ላይ ያላችሁ ቤተሰቦቻችን አመስግኑ ድል አላችሁና። እመቤታችን አምላክን አዝላ በበረሃ ተሰዳለች ። ለእኛ ትልቁ መመሪያ ይሄ ነው። ሙሴ ከንጉሥ ቤት ወጥቶ በበረሃ ከእግዚአብሔር ሕዝብ ጋ መሰደድን የመረጠው ነገን አስቦ ነው። ዳዊትም ፤ ነቢዩ ኤልያስም ተሰድደዋል። መከራ መቀበል እግዚአብሔር አብሮን እንዳለና ሊያከብረን እንደመጣ ማሳያ ነው። በመከራው ጸንታችሁ እያመሰገናችሁ በርቱ።
- ትዕግሥትና ትህትና ባይኖረን የሚሰጠን በዚህ የመከራ ዘመንና ተስፋ ባጣንበት ጊዜና ሰዓት ብቻ ነውና አርማችን መከራችን ነው። ክርስቶስን ማሰብ ነው የሾህ አክሊሉን መጨበጥ ነው። ለዚህ ተመስገን ነው ክፉዎች ተነቅለው መልካመች ሲተከሉ የምንከብርበት ነው። በእምነት እንጠብቃለን።
- ፈቃደ እግዚአብሔር በምን ሁኔታ እንደሚገለጥ ማወቅ አስፈላጊ ነው። ምሳሌ፦ ትዳር እንኳን ሲያዝ ፈቃደ እግዚአብሔር ይጠየቃል። እናት አባትንስ ፈቃድ እንጠይቅ የለም ወይ!? አንዷ መጥታ አንተ የእኔ ነህ እግዚአብሔር ፈቅዶልኛል ሲባል እስኪ እግዚአብሔርን ደግመን እንጠይቅ ማለት እንጅ ዝም ብሎ መቀበል ሳይሆን ሁለቱም በደንብ መጠየቅና በልዩ ልዩ መንገድ ማረጋገጫ ማግኘት አለባቸው። ከእነሱም አልፎ በሌላው በማያውቀው ሊመሰከር ይችላል። ፈቃደ እግዚአብሔር ለመንገድ ፣ ለሥራ፣ ለውሎ ማስባረኪያ፣ ለፀበል መሄድ ሁሉ ለሁሉም ነገር በተቻለ ፈቃደ እግዚአብሔር መጠየቅ አስፈላጊ ነው። ከመጠየቅ በፊት ማድረግ የሚገባን ቅንነትና የዋህነት ባለው ምልልስ ሆነን ትዕግሥተኛ ሆነን ይቅር ተባብለን ፍቅርን ለብሰን የተጣላነውን በሚገባ ታርቀን የመንፈስ ፍሬዎችን ሁሉ እንዲሰጠን ለምነን ነው ፈቃደ እግዚአብሔር መጠየቅ የሚገባን። ሱባኤ ለመግባት ንስሐ ቅድሚያ ግዴታ ነው። እራሳችንን አጽድተን መጠየቅና መልስ ተሰጠንም አልተሰጠንም አመስግነን መጠየቅና የሰማንን አምላክ በተስፋ መጠበቅ ነው። እንደተሰማን ማመን ነው።
- መንፈስቅዱስ አናገረው ማለት እንዴት ነው ለሚለው መጀመሪያ ያ ሰው የእግዚአብሔር እቃ መሆን አለበት ራሱን ክዶ መስቀሉን መከራውን የተሸከመ ሰውና እሱን የተከተለው ሰው አዎ እግዚአብሔር በዚህ ይሰራልና በመንፈስቅዱስ ገላጭነት ያናግራል። ሐዋርያት ላይ የሆነውን ማስታወስ ተገቢ ነው ብዙ ሺ ሕዝብ ያጠምቁ ነበር ምክንያቱም ራሳቸውን ክደው መስቀሉን ተሸክመው ስለነበረ ነው። እቃ ለመሆን ፈቃደኛ መሆንና ከትዕቢትና ከእውቀት ምርኳዝ ርቆ ሲሆን አዎ ፈጣሪያችን በዚህ ሰው ሊጠቀምበትና ሊናገርበት ይችላል።
- ሕልም መፍታትን በተመለከተ እንዴት ነው ለምትሉ ከእግዚአብሔር የተሰጠው ብቻ ነው እንጅ ማንም ሕልምን ሊፈታ አይችልም ። እግዚአብሔር ሲፈቅድ የተሰጣቸው ይፈቱታል። በዘልማድ መንፈሳዊ ሰው ሕልም አይፈታም። የሚያሳስበው እግዚአብሔር የሆነ ሰው ነው የሚፈታው።
- በቤተክርስቲያን አስተምህሮ ውስጥ የተዋሕዶ አማኝ ሆነን ኦርቶዶክሳዊ ኦርቶዶክሳዊ ይባላል ይሄስ እንዴት ታዩታላችሁ ለሚለው ኦርቶዶክስ ማለት ቃሉ የግሪክ ሲሆን ቀጥተኛ ማለት ነው። የእምነታችን ሙሉ ትክክለኛ አጠራሩም ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ወይም ተዋሕዶ ኦርቶዶክስ በሚል ይጠራል እንጅ "ኦርቶዶክስ ኦርቶዶክሳዊ" እያለ በዚህ መንገድ የመቀላቀል ስራ አንቀበልም። የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አማኞች ነን። የኦርቶዶክስነት ዋናው ክብሩ ተዋሕዶ የሚለው የእምነት መሠረት ነው። ተዋሕዶ የሚለው ባልተጠራበት መንገድ ኦርቶዶክስ በሚል እምነታችን አትጠራም አትወከልም። የሚስጥር ማኅበረሰቡ እቅድ ነው የአንድ አለም መንግሥትና ሃይማኖት ለመመስረት የሚያደርጉት ጥረት ዋነኛ አካል ነውና እኛ እንደክርስቲያን ይሄንን አንቀበልም። እምነታችን ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ነው።
👇👇👇
Repost from አልፋና ዖሜጋ የንጽጽርና የትምህርት መገኛ አደባባይ (አዖተ)
🟢🟡🔴
ሰኔ 21 | የመጀመሪያዋ ቤ/ክ ቅዳሴ ሆነ። እንዲሁም #እመቤታችን በልጇ መቃብር ላይ እያነባች ጸልያ ልዩ ቃልኪዳን ተቀብላለች። (ሰኔ ጎልጎታን መጸለይ እንዳትረሱ)
ሰኔ 20 ለስም አጠራሩ ጌትነት ይሁንና ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ሐዋርያት ወረደ። ፊልጵስዩስ በምትባል ሃገር በጴጥሮስ እጅ የመጀመሪያዋን ቤተ ክርስቲያን አነጸ ብለን ነበር።
በዚህች ዕለት ደግሞ አእላፍ መላዕክትን፣ ሰማያውያን ቅዱሳንን እና እናቱን ቅድስት ድንግል ማርያምን ይዟት ወረደ። ሐዋርያቱ አብዛኞቹ እዛው ሲጸልዩ አድረው ነበርና ጌታችን ከቅዳሴው በፊት 2 ነገሮችን አሳየ፦
1. አስቀድሞ ቤተ ክርስቲያኗን በድንግል እናቱ ስም አክብሮ ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንን አሳየ፣
2. ቀጥሎ ደግሞ ሊቀ ሐዋርያት ቅዱስ ጴጥሮስን ከመካከል አቁሞ "አርሳይሮስ" ሲል ሾመው። ይኼውም የዓለም ሁሉ ሊቀ ጳጳሳት (ፓትርያርክ) ማለት ነው።
በዚህ ጊዜ ቅዱሳን መላእክት "አክዮስ" እያሉ 3 ጊዜ አሰምተው ጮሁ። አክዮስ ማለት "ይገባዋል ያሥምርለት" እንደ ማለት ነው። ጌታችን ከዚህ በኋላ ይቀድስ ዘንድ ጀመረ።
☘️ አማናዊት ማኅደሩን ድንግል ማርያምን መንበር አድርጎ
☘️ ቅዱስ ጴጥሮስ እንደ ተራዳኢ ካህን ቆሞ
☘️ ቅዱስ እስጢፋኖስ ሠራኢ ዲያቆን ሆኖ
☘️ ሐዋርያት ድንግልን ከበው፣ መላእክተ ብርሃን በክብራቸው ቁመው ጌታችን ቀድሶ ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ለወዳጆቹ አቀበለ።
በዚያች ቀን በፍጡር አንደበት ተከናውኖ ሊነገር የማይችል ደስታ ተደረገ። ከቅዳሴ በኋላ ጌታችን ሐዋርያትን አዘዛቸው፦
"ከዚህ ቀን ጀምሮ በመላው ዓለም በእናቴ በማርያም ስም አብያተ ክርስቲያናትን እነጹ። ይህችን ዕለት የሚያከብራትን አከብረዋለሁ።" ብሏቸው ከድንግል እናቱ ከመላዕክቱ ጋር ዐረገ።
T.me/Ewnet1Nat
#እንኳን_አደረሳችሁ።
~¤~
እንግዲህ እንደእግዚአብሔር ምርጦች ቅዱሳን ሆናችሁ የተወደዳችሁም ሆናችሁ፥ ምሕረትን፥ ርኅራኄን፥ ቸርነትን፥ ትሕትናን፥ የዋህነትን፥ ትዕግሥትን ልበሱ።
እርስ በርሳችሁ ትዕግሥትን አድርጉ፥ ማንም በባልንጀራው ላይ የሚነቅፈው ነገር ካለው፥ ይቅር ተባባሉ። ክርስቶስ ይቅር እንዳላችሁ እናንተ ደግሞ እንዲሁ አድርጉ።
በእነዚህም ሁሉ ላይ የፍጻሜ ማሰሪያ የሆነውን ፍቅርን ልበሱት።
ባንድ አካልም የተጠራችሁለት ደግሞ የክርስቶስ ሰላም በልባችሁ ይግዛ። የምታመሰግኑም ሁኑ።
ወደ ቆላስይስ ሰዎች 3፥15
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
