አልፋና ዖሜጋ የንጽጽርና የትምህርት መገኛ አደባባይ (አዖተ)
Відкрити в Telegram
በዚህ የንጽጽር አደባባይ በኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልዕክታት የተገለጸው እውነት ሲፈጸምና ይፈጸም ዘንድ በመላው ዓለም ሲንቀሳቀስ የሚከሰቱ ጉዳዮችን እናቀርባለን ! ስለእምነታችን እንማማራለን ! ስለመልዕክታቱ እንነጋገራለን ! ➝ይህ የአልፋና ዖሜጋ ( @christian930 ) ገጽ ቅርንጫፍ የንጽጽርና የመማሪያ ገጽ ነው።
Показати більше4 868
Підписники
+224 години
-47 днів
+4730 день
Архів дописів
Repost from አልፋና ዖሜጋ የንጽጽርና የትምህርት መገኛ አደባባይ (አዖተ)
+1
🟢🟡🔴
ሐምሌ 22 | መልአኩ #ቅዱስ_ዑራኤል በዓሉ ነው፨
በዚህች ቀን ቅዳሴ ቤቱ የሚከበርበትና ለነቢዩ ዕዝራ ሱቱኤል የዕውቀትን ጽዋ ያጠጣበት ነው።
▬
ዳግመኛም ኢትዮጵያዊው ሰማዕት ብፁዕ ወቅዱስ #አቡነ_ጴጥሮስ ዐረፉ።
ሰማዕቱ አቡነ ጴጥሮስ ከልጅነታቸው ጀምረው ትምህርት ትኅርምትና ደግነት ወዳጅ እንደ ነበሩ ይነገራል።
ወቅቱ ኢትዮጵያ የራሷን ጳጳሳት የምትሻበት ጊዜ ነበርና በፈቃደ እግዚአብሔር ለመጀመሪያ ጊዜ ግንቦት 18 ቀን 1921 ዓ/ም ሰማዕቱን ጨምሮ የሃገራችን አራት አባቶች ጵጵስናን ተሾሙ።
አቡነ ጴጥሮስ ከተሾሙ በኋላ በሐዋርያዊ አገልግሎትና በጸሎት ተግተው ኑረዋል።
በ1928 ዓ/ም ፋሺስት ጣልያን ሃገራችንን በወረረች ጊዜ ቆራጡ ጳጳስ በዱር በገደል ለመሔድ ተነሱ። በየበርሃው እየሔዱ አርበኞችን ሲያጽናኑ ሲናዝዙ ሲባርኩም ቆይተዋል። ለሃገራቸውና ለሃይማኖታቸው ረሃብ ጥም እንግልትን ታግሠዋል።
በተያዙባት በዚያች ሌሊትም በጣልያኖች ለሮም እምነትና ለአገዛዙ እንዲያጎበድዱ ተጠየቁ። ቆራጡ ሰው ግን እንቢ ቢሉ የሚደርስባቸውን እያወቁ "አይደረግም" አሉ። በማግስቱ በአደባባይ መትረየስ ተደግኖባቸው ጥያቄ ድጋሚ ቀረበላቸው።
አቡነ ጴጥሮስ አፋቸውን ከፍተው ሊናገሩ ጀመሩ "የሃገሬ ሕዝብ ሆይ! ለሃገርህ ለሃይማኖትህ ባትጋደል ትውልድ ይፋረድህ። ለጣልያን ግን እንኳን ሰው ዛፍ ቅጠሉ መሬቱ እንዳይገዛለት አውግዣለሁ" አሉ። በደቂቃዎች ልዩነት በግራዚያኒ ትዕዛዝ የመትረየስ ጥይት ዘነበባቸው።
አካላቸው ተበሳስቶ በሰንሰለት እንደ ታሠሩ መሬት ላይ ወደቁ። አንዱ ወታደር ቀርቦ ቢመለከት ትንሽ ትንፋሽ ነበረቻቸው። "ይኼ ቄስ አልሞተም" ብሎ ጭንቅላታቸው ላይ ተኮሰባቸው።
አቡነ ጴጥሮስ ለሃገራቸውና ሃይማኖታቸው ተሠው። ነገሩ በአርበኞች ዘንድ ሲሰማ ትግሉ ተቀጣጠለ።
◦🌿◦
T.me/Ewnet1Nat
Repost from አልፋና ዖሜጋ የንጽጽርና የትምህርት መገኛ አደባባይ (አዖተ)
+1
🟢🟡🔴
ሐምሌ 21 | በቅድስት ቤ/ክ ትውፊት መሠረት ቅዱስ ዑራኤል #ድንግል_ማርያምን በአካለ ሥጋ እያለች ወደ ሰማይ አሳርጎ፣ በሠረገላ ብርሃን ጭኖ፣ በክንፎቹም ተሸክሞ፣ አስቀድሞ ገነትን ቀጥሎም ሲዖልን አስጎብኝቷታል።
በዚህም ምክንያት እመ ብርሃን ስለ ኃጥአን የምታለቅስ፣ የምትለምንና የምትማልድ ሆናለች። ለምናም አልቀረች የምሕረት ቃል ኪዳን ተቀብላለች።
● እመቤታችን ተገልጻ በሕዝቡ ሁሉ ፊት ጽድቁን የመሰከረችለት ጻድቁ ንጉሥ #አቡነ_ላዕከ_ማርያም ዕረፍቱ ነው፡፡ እርሱም የዐፄ ናኦድ ልጅ ሲሆን መንግሥቱን ንቆ የመነነ ነው፡፡
● በክፉዎች ምክር ተታሎ ንጉሥ አምደ ጽዮን የአባቱን ቅምጥ በማግባቱ እንደ ኤልያስና መጥምቁ ዮሐንስ ሄዶ ንጉሡን ስለገሠጸው በግዞት ብዙ ያሠቃየው ታላቁ አባት #አቡነ_በጸሎተ_ሚካኤል ዕረፍታቸው ነው፡፡
በዚህም መከራ የተነሣ ከጾም፣ ከጸሎትና ከስግደት ባሻገር እንደ ሰማዕትም ይቆጠራሉ። ከብዙ የገድል ዓመታት በኋላም በ1330 ዓ.ም ሐምሌ 21 ትግራይ ውስጥ ዐርፈዋል።
● አጽፋቸውን እንደጀልባ ተጠቅመው የኢያሪኮን ባሕር ከደቀ መዛሙርቶቻቸው ጋር የተሻገሩት ታላቁ ኢትዮጵያዊ ጻድቅ #አቡነ_ኤዎስጣቴዎስ ከፋሌ ባሕር ልደታቸው ነው፡፡
አባታቸው ክርስቶስ ሞዐ እና እናታቸው ሥነ ሕይወት ይባላሉ።
● ከንጉሥ ቴዎዶስዮስ መኳንቶች ውስጥ አንዱ የሆነውና ነዳያንን ይመግብ የነበረው ጃንደረባው #ቅዱስ_ሱስንዮስ ዕረፍቱ ነው፡፡
● በሉቃስ ወንጌል ላይ (ሉቃ 23፥47) የምናገኘው የመቶ አለቃው #ቅዱስ_ዮራኖስ መታሰቢያው ነው።
● ፍጹማን መነኮሳትን በተጋድሎ እስኪበልጣቸው ድረስ ከሚስቱ ጋር የተጋ #አቡነ_አወ_ክርስቶስ ዕረፍቱ ነው፡፡
እንግዶችን በመቀበል፣ ምጽዋትን በመስጠት፣ በመጾም በመጸለይ ኖሩ፡፡ በሌሊትም ማቅ ለብሰው ለየብቻቸው ይተኙ ነበር፡፡
t.me/Ewnet1Nat
"ኢየሱስ ግን ዐሳባቸውን ዐውቆ እንዲህ አላቸው፦ ርስ በርሷ የምትለያይ መንግሥት ዅላ ትጠፋለች፥ ርስ በርሱ የሚለያይ ከተማም ዅሉ ወይም ቤት አይቆምም። ማቴዎስ ወንጌል ፲፪፥፳፭
///በጽኑ ቃሉ፦ መንግሥት፣ ከተማ፣ ቤት.... በሚለው ውስጥ ሁሉ ብዙ ነገሮች ይካተታሉና!! መለያየትን ከእኛ እናርቅ ጽኑ ቃሉ! ጽኑ ነውና።///
Repost from አልፋና ዖሜጋ የንጽጽርና የትምህርት መገኛ አደባባይ (አዖተ)
+1
🟢🟡🔴
ሐምሌ 19 | የትንሣኤ ዘመን አሻጋሪ ሊቀ መልእክ #ቅዱስ_ገብርኤል በዓሉ ነው።
በዚህችም ቀን ሕፃኑ #ቅዱስ_ቂርቆስና እናቱ #ቅድስት_ኢየሉጣ በሰማዕትነት መከራ ተቀበሉ። እርሱም ከእቶን እሳት አዳናቸው።
#ቅዱስ_ቂርቆስ 3 ዓመቱ ሳለ እናቱ መከራን ሸሽታ ወደ ሮሜ ሄደች። እዛም ግን መከራ ጠበቃት።
ከዚህም መኰንኑ በታላቅ የናስ ጋን ውስጥ ውኃ ጨምረው በእሳት ያፈሉት ዘንድ አዘዘ። የፍላቱም ድምጽ እንደ ክረምት ነጎድጓድ ሆነ። ያን ጊዜም ፍርሀትና የሃይማኖት ጉድለት በእናቱ ላይ ደረሰባት። ሕፃኑም ስለ እናቱ ወደ እግዚአብሔር ጸለየ።
ያን ጊዜ ጌታችን ልቧን ወደ ሰማይ አሳርጎ ለቅዱሳን ሰማዕታት የተዘጋጁ የብርሃን ማደሪያዎችን አየች። ከዚህም በኋላ ጸናች፤ እግዚአብሔርንም አመሰገነችው። ልጇንም "ልጄ ሆይ ከእንግዲህ አንተ አባቴ ነህ፤ እኔም ልጅህ ነኝ" አለችው።
ያቺ ከኔ የተወለድክባትም ቀን የተባረከች ናት አለች። ወደዚያ ወደ ጋኑ ውስጥ በገቡ ጊዜም የውኃው ፍልሐት እንደ ንጋት ጊዜ ውርጭ ቀዘቀዘ። ከእግዚአብሔር የታዘዘ የመላእክት አለቃ #ቅዱስ_ገብርኤል ከሰማይ ወርዶ የእሳቱን ኃይል አቀዝቅዞታልና።
ከዚህም በኋላ መኰንኑ ሥጋቸው ተቆራርጦ እስከሚወድቅ ድረስ በመቃጥን ውስጥ አድርገው እንዲጎትቷቸው አዘዘ። ከእግዚአብሔርም የታዘዘ #መልአክ አዳናቸው።
መኰንኑም በታላቅ ሥቃይ ያሠቃያቸው ዘንድ አስቦ እስኪመክር ድረስ በወህኒ ቤት ዘጋባቸው።
● ኢትዮጵያውያን ጻድቃን አባቶቻችን #አቡነ_አፍቅረነ_እግዚእ የልደት በዓል #አቡነ_እፍረተ_ጊዮርጊስ የዕረፍት በዓላቸው ነው።
አምላከ #ቅዱስ_ገብርኤል እኛንም ከመከራ እሳት፣ ከኃጢአት ስጥመት ያድነን።
#እንኳን_አደረሳችሁ።
▸ T.me/Ewnet1Nat ◂
በደቡባዊ ምዕራብ ፈረንሳይ የተቀሰቀሰው የሰደድ እሳት በከፍተኛ ሁኔታ እየተስፋፋ መምጣቱን ተከትሎ ባለስልጣናት ነዋሪዎችን ከአካባቢው ማስለቀቅ መጀመራቸውን አስታወቁ። በተለይ ቦርዶ ከተማ አቅራቢያ የተጠናከረውን ሰደድ እሳቱን ለመቆጣጠር በሚደረገው ጥረት የሀገሪቱ ጦር ወደ አካባቢው መሰማራቱ ተሰምቷል። የእሳቱ ኃይል እየጨመረ መምጣቱን ተከትሎ በጭስ መታፈን የሚያስከትለውን አደጋ ለመቋቋም የሀገሪቱ መንግስት ከ 1.5 ሚሊዮን በላይ የፊት ጭንብሎች ወደ አካባቢው መላኩ ተገልጿል።
የጅሮንድ ክልል አስተዳደር የቦርዶ አውሮፕላን ማደሪያ የሚገኝበትን ጨምሮ በሦስት የምዕራባዊ የከተማ ዳርቻዎች የሚኖሩ ነዋሪዎች በአስቸኳይ አካባቢውን ለቀው እንዲወጡ አዟል። በዚህም ምክንያት ቀደም ሲል በአካባቢው ከተፈናቀሉት 141,000 ሰዎች በተጨማሪ፣ በአጠቃላይ በፈረንሳይ እና በስፔን ከ200,000 በላይ ሰዎች ከቀያቸው ለመፈናቀል ተገደዋል ነው የተባለው።
የፈረንሳይ ጠቅላይ ሚኒስትር ሴባስቲያን ለኮርኑ እንዳሉት «የእሳቱ ኃይል እጅግ ከመበርታቱ የተነሳ የራሱን የንፋስ አቅጣጫ እስከመፍጠር ደርሷል»። ዋናው ትኩረታችን «የሰዎችን ሕይወት መታደግ» ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ነዋሪዎች የተሰጣቸውን የደህንነትና የመልቀቂያ ትዕዛዝ ያለማወላወል እንዲተገብሩም አሳስበዋል።
በአደጋው በርካታ የእሳት አደጋ ሠራተኞች ለጉዳት የተዳረጉ ቢሆንም እስካሁን የሰው ሕይወት ማለፉ አልተረጋገጠም። አደጋው በከፍተኛ ሙቀትና በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት የተከሰተ መሆኑን የገለጠው የፈረንሳይ ዜና አገልግሎት በድንገተኛነቱና በፍጥነቱ ለአሳት አደጋ ተከላዮች ብርቱ ፈተና መሆኑን አመልክቷል።
Repost from አልፋና ዖሜጋ የንጽጽርና የትምህርት መገኛ አደባባይ (አዖተ)
📌 ልዩ ልዩ link የያዙ ያልታወቁ መልዕክቶች በቴሌግራም ፤ በዋትሳፕ.... ከምታውቁቱም ከማታውቁትም ሰዎች እየተላኩ የሰዎች አካውንት እየተጠለፈ፡ እንዲጠፋ እየተደረገ ስለሆነ ምንም ይዘት ይኑረው ሕጋዊ ያልሆኑ links ከሰው ሲላክላችሁ #አትክፈቱት።
በትግራይ ክልል የተከሰተ የከፋ የአየር ሁኔታ የሕይወትና የንብረት ጉዳት አድረሰ
በማዕከላዊ ዞን ቀይሕ ተኽሊ እና አሕፈሮም ወረዳዎች በጣለው ከባድ በረዶ አዘል ዝናብ የአንድ ሕፃን ሕይወት ያለፈ ሲሆን በአዝእርት፣ በመስኖ እና በአትክልት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ወድቋል።
በሌላ በኩል ደግሞ የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ጥበቃ ቢሮ እንደገለጸው፣ በክልሉ ከሚገኙ 600 ቀበሌዎች ውስጥ 176 ቀበሌዎች እስካሁን ምንም ዓይነት የክረምት ዝናብ አላገኙም።
በአንዳንድ አካባቢዎች የጣለው ከመጠን ያለፈ ዝናብ ጉዳት እያደረሰ ባለበት ሁኔታ፣ በሌሎች አካባቢዎች ያለው የዝናብ እጥረት በእርሻና በምርት ላይ ከፍተኛ ስጋት ደቅኗል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
Repost from ራዕይ ዮሐንስ 20 የንፅፅር ቻናል
+2
የዝናብ እጥረት በጃንአሞራ‼️
በጃናሞራ ወረዳ በድርቅ ምክንያት ከ19 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ሳይዘራ ቀረ፤ ከ96 ሺህ በላይ ዜጎች ለችግር ተጋልጠዋል‼️
በአማራ ክልል ሰሜን ጎንደር ዞን በሚገኘው የጃናሞራ ወረዳ፣ በዘንድሮው የመኸር እርሻ ወቅት ባጋጠመው ከፍተኛ የዝናብ እጥረት ምክንያት ከባድ ድርቅ እየገጠመው መሆኑን የወረዳው ኮሙኒኬሽን ጽሕፈት ቤት አስታውቋል።
በወረዳው ከሚገኙት 36 የገጠር ቀበሌዎች መካከል በ19ኙ ቀበሌዎች እስከ አሁን ድረስ ምንም ዓይነት ዝናብ ባለመጣሉ፣ አርሶ አደሩ ማሳውን አርሶና አዘጋጅቶ ቢጠብቅም ዘሩን መሬት ላይ ማሳረፍ አልቻለም።የወረዳው ግብርና ጽሕፈት ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ መልስ አደላድለው እንደገለጹት፣ ዝናብ ባለመጣሉ ምክንያት ከ19 ሺህ 4 መቶ ሄክታር በላይ መሬት ሳይዘራ "ጦሙን አድሯል"።
በዚህም ሳቢያ ከ96 ሺህ በላይ የአካባቢው ዜጎች ለከፍተኛ ችግር እንደሚጋለጡ ኃላፊው አሳስበዋል። በሌሎች የቀሩት የወረዳው ቀበሌዎችም ቢሆን ዝናቡ እጅግ ዘግይቶ መዝነቡን ጠቁመዋል።በድርቁ ክፉኛ ከተጎዱት አካባቢዎች መካከል በተለይ የበየዳ እና የሰሃላ ሰየምት ወረዳዎችን የሚያዋስኑት ቀበሌዎች በከፍተኛ ሁኔታ ተጠቂ መሆናቸው ታውቋል።የዋሰል ቀበሌ ነዋሪ የሆኑ አርሶ አደሮች በሰጡት አስተያየት፣ በአሁኑ ወቅት አካባቢው አረንጓዴ ለብሶ እሸት የሚበላበትና ተራሮች በጉም የሚሸፈኑበት ወቅት ቢሆንም፣ በተቃራኒው ግን እጅግ ከባድ ሙቀትና ፀሐይ ነግሦ አካባቢው በድርቅ መጎዳቱን ይናገራሉ።
ዝናብ ይጥላል በሚል ተስፋ በደረቁ መሬት ላይ የተዘራው ዘርም ሳይበቅል የውኃ ሽታ ሆኖ ቀርቷል።
ትዕቢተኛ አገልጋይ ሁሌም ክርስቶስን ሳይሆን ራሱን እንዳገለገለ ነው። ዋጋውንም በሥጋ ተቀብሏልና ከክርስቶስ የሚያገኘው ቅጣት ካልሆነ በቀር ምንም በጎ ነገር አይኖርምና። ራስን መመልከት መልካም ነው። በተለይ መማክርት አመራርና ሙሴዎች፡ በልዩ ልዩ ምድብ የምናገለግል ሁሉ።
🌄 ከእምነት መሰል የልምድ ካባ ተላቃችሁ፡ ማመን በሚመስል ጥርጥር ከመኖር ወጥታችሁ፣ የአብርሃሙ ሥላሴን ፈጣሪያችንን በማመን ለፈቃዱም በመታመን ለመኖር በመንፈስ የተወለዳችሁ ለመራመድም ዳዴ የምትሉ የተዋሕዶ እውነተኛ የቁርጥ ቀን ልጆቿ፡ የሕይወት ትምህርታችሁን በመውደቅና በማለፍ ሁሉ ግን በጽናት እየተማራችሁ ያላችሁ፡ እናታችን ለታላቁ የቃልኪዳን ሕዝብነት አጭታ የመረጠቻችሁ በየኑሮው የምታስተምራችሁ ፡ በፈተና ብዛት ማማረር ጭንቀት መሰልቸት ያልሰበራችሁ ፤ ከዳዴ ባይነት ለመራመድና ለመሮጥ የበቃችሁም የኢትዮጵያና የተዋሕዶ አርበኞች ጀግኖቿ እንቁና ተወዳጅ ተናፋቂ ቤተሰቦቼ፡ በስደት ፣ በመከራ፣ በመገፋት፣ በመታሰር፣ በማጣት፣ በውጣ ውረድ በደምም ያለደምም ሰማዕትነት የታመናችሁ በፅናት በየስፍራው ያላችሁ ሁሉ በርቱ አይዟችሁ !! እምነትም ተስፋ ያደረግነውን ሁሉ የሚያስጨብጥ በጣታችን እንዳለ ቀለበት የተያዘና የተገኘ መሆኑን የሚያስረግጥ በመሆኑ በፍቅር ደስስስስ ይበላችሁ።
