cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

አስተምረኝ ጌታዬ ሆይ

. 🇼 🇪 🇱 🇨 🇴 🇲 🇪 #በዚህ_መንፈሳዊ_ቻናል ☞︎︎︎ የእግዚአብሔር ቃል ዳሰሳ፣ ☞︎︎︎ አስተማሪ ታሪኮች፣ ☞︎︎︎ መፅሐፍ ቅዱሳዊ ጥያቄዎች፣ ☞︎︎ መንፈሳዊ ግጥሞች ይቀርባሉ። #የእግዚአብሔር_ቃል_በሙላት_ይኑርባችሁ ◈●ቆላስይስ 3፥16●◈ ➥ @astemiren_bot@from_jesus_to_jesus

نمایش بیشتر
پست‌های تبلیغاتی
1 773
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
-67 روز
-2630 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

ለራሳችን ከራሳችን በላይ አለልን! 📌 አብርሀም ወደ ግብጽ በእንግድነት ሲገባ አንድ ነገር አሰጋው፦ የሚስቱን የሦራን መልከ መልካምነት ያዩ ግብጻው ያን እንዳይገድሉት ፈርቶ ሦራን እህቱ እን ደሆነች ብቻ እንድትናገር አስማማት። ፈርኦንም በአለቆቹ አማካኝነት ውቧን ሦራ የራሱ ማድረግ ቻለ ሚስቱ አደረጋት። እግዚአብሄር ግን ከአብርሀም ጋር ስለ ነበረ በመጨረሻም ፈርኦን ላይ እግዚአ ብሄር መቅሰፍት አመጣ ፈርኦንም አብራ ምን ለምን ሚስትህ እንደ ሆነች አልነገር ከኝም ውሰዳት ብሎ ሰጠው። (ዘፍ.12) 📌 አብርሀም ለራሱ በግሉ ጥንቃቄ አድርጓል ነገር ግን ጥንቃቄው ሚስቱን ከመነጠቅ አላዳነውም ነበር። ከሰው ጥንቃቄ በላይ የእግዚአብሄር ጣልቃ ገብነት እንደሚበልጥ ማሳያው በቀላሉ እንዳሰበው እንደጠበቀው ሳይገድሉት ፈርኦን ሚስቱን እንካ ሲለው ነው። ሰው ለራሴ ይበጀኛል ብሎ ያበጃጀው ነገር ጎጂ የሚሆንበት ጊዜ አለ ዋናው ቁም ነገር ግን አካሄዳችን ከእግዚአብሄ ር ጋር ነው ወይ የሚለው ነው። የአብራ ም አካሄድ ከእግዚአብሄር ጋር ስለነበረ አምላኩ ጥሎ አልጣለውም። ለራሱ ትክክል መስሎ የታየውን የተጠነቀቀው ነገር ለጉዳት አሳልፎ ሲሰጠው ያመነውና ሀገርህን ዘመዶችህን ቤተሰብህን ጥለህ ውጣና እኔ ወደማሳይህ ምድር ገብተህ ለልጅ ልጅ በረከት አደርግሀለሁ ያለውን ጌታ ተማምኖ ስለወጣ ያመነው ህይወቱ ን ኑሮውን ጥሎ የተከለው ጌታ አላሳፈረ ውም! አንተ ሰው አካሄድህ ከእግዚአብ ሄር ጋር ብቻ ይሁን እንጂ ያንተ ነገር አን ድ ቀን ይሆናል! አንድ ቀን ይበዛል!! 📌 አካሄድህ ከእግዚአብሄር ጋር ሲሆን አየህ ከራስህ በላይ እግዚአብሄር ይጠነ ቀቅልሀል! እግዚአብሄር ይዋጋልሀል! አብራም ሚስቴ ናት ቢል እንደሚገድሉ ት ነበር የጠበቀው እግዚአብሄር ካንተ ጋር ሲሆን ግን የተጠበቀው ነገር ቀርቶ ያልተጠበቀው መሆን ይጀምራል🔥🔥 አብራም እንዲ የከበደበት ነገር በእግዚ አብሄር ፊት ቀላል ሆነ ፈርኦን በጣም በቀላሉ ሚስትህን ውሰድ አለው። ከባ ድ የሆነው ተራራ የሆነው ነገር አካሄድህ ን ከእግዚአብሄር ጋር ስታደርግ ሰረጓጉጡ መስተካከል ይጀምራል🔥 ተራራው መና ድ ይጀምራል🔥 የተበላሸው መስተካከል ይጀምራል🔥 ከባዱ ቀላል ይሆናል🔥 በመንገድህ ላይ አንድ ነገር እርግጠኛ ሁን! አካሄዴ ከእግዚአብሄር ጋር ነው?? ወይስ... የሚሳካለት ሰው በራሱ የተጓዘ ሳይሆን ህይወቱን ዘመኑን ለእግዚአብ ሄር የሰጠ ሰው ነው!🔥 📌 እንደ አብራም እግዚአብሄርን ተማ ምኖ የወጣ ሰው አያፍርም!! እግዚአብ ሄርን ተማምነህ በራስህ ነገሮች ላይ ወስን! አብራም በቤተሰቡ ላይ፣በኑሮው ላይ እንደ ወሰነው ወስን አንድ ቀን ጌታ የፈቀደ ቀን ነገርህ መቃናት ይጀምራል🔥 ክርስትና የመደላድል ጉዞ ሳይሆን የመ ሰጠትና የጭንቅ ጉዞ ነው መጨረሻው ግን ድልና ክብር የሆነ ህይወት! የማይን ገጫገጭ ፒስታ የሌለበት መንገድ ጠብ ቀህ ወደጌታ እንዳትመጣ! ነገር ግን አካ ሄድህን ከእግዚአብሄር ጋር በማድረግ ካለህበት ነገር ለመውጣት ወስን! የች ግሩ ቁልፍ አካሄድን ከእግዚአብሄር ጋር ማድረግ ነው!! የችግሩ ቁልፍ አንተ ጋር ነው! በራስህ የመረጥከው መንገድ እን ዳላዋጣህ ራስህ ምስክር ነህ ከዚህ በሁ ዋላ ግን የራስህን መንገድ ትተህ የጌታን መንገድ ወደ ክብር ህይወት የሚያደር ሰው መንገድ ላይ ህይወትህን መንዳት ና መምራት ጀምር የጌታ ፈቃድ ባንተ ላይ ይሰለጥናል🔥
نمایش همه...
👍 11
ለራሳችን ከራሳችን በላይ አለልን! 📌 አብርሀም ወደ ግብጽ በእንግድነት ሲገባ አንድ ነገር አሰጋው፦ የሚስቱን የሦራን መልከ መልካምነት ያዩ ግብጻው ያን እንዳይገድሉት ፈርቶ ሦራን እህቱ እን ደሆነች ብቻ እንድትናገር አስማማት። ፈርኦንም በአለቆቹ አማካኝነት ውቧን ሦራ የራሱ ማድረግ ቻለ ሚስቱ አደረጋት። እግዚአብሄር ግን ከአብርሀም ጋር ስለ ነበረ በመጨረሻም ፈርኦን ላይ እግዚአ ብሄር መቅሰፍት አመጣ ፈርኦንም አብራ ምን ለምን ሚስትህ እንደ ሆነች አልነገር ከኝም ውሰዳት ብሎ ሰጠው። (ዘፍ.12) 📌 አብርሀም ለራሱ በግሉ ጥንቃቄ አድርጓል ነገር ግን ጥንቃቄው ሚስቱን ከመነጠቅ አላዳነውም ነበር። ከሰው ጥንቃቄ በላይ የእግዚአብሄር ጣልቃ ገብነት እንደሚበልጥ ማሳያው በቀላሉ እንዳሰበው እንደጠበቀው ሳይገድሉት ፈርኦን ሚስቱን እንካ ሲለው ነው። ሰው ለራሴ ይበጀኛል ብሎ ያበጃጀው ነገር ጎጂ የሚሆንበት ጊዜ አለ ዋናው ቁም ነገር ግን አካሄዳችን ከእግዚአብሄ ር ጋር ነው ወይ የሚለው ነው። የአብራ ም አካሄድ ከእግዚአብሄር ጋር ስለነበረ አምላኩ ጥሎ አልጣለውም። ለራሱ ትክክል መስሎ የታየውን የተጠነቀቀው ነገር ለጉዳት አሳልፎ ሲሰጠው ያመነውና ሀገርህን ዘመዶችህን ቤተሰብህን ጥለህ ውጣና እኔ ወደማሳይህ ምድር ገብተህ ለልጅ ልጅ በረከት አደርግሀለሁ ያለውን ጌታ ተማምኖ ስለወጣ ያመነው ህይወቱ ን ኑሮውን ጥሎ የተከለው ጌታ አላሳፈረ ውም! አንተ ሰው አካሄድህ ከእግዚአብ ሄር ጋር ብቻ ይሁን እንጂ ያንተ ነገር አን ድ ቀን ይሆናል! አንድ ቀን ይበዛል!! 📌 አካሄድህ ከእግዚአብሄር ጋር ሲሆን አየህ ከራስህ በላይ እግዚአብሄር ይጠነ ቀቅልሀል! እግዚአብሄር ይዋጋልሀል! አብራም ሚስቴ ናት ቢል እንደሚገድሉ ት ነበር የጠበቀው እግዚአብሄር ካንተ ጋር ሲሆን ግን የተጠበቀው ነገር ቀርቶ ያልተጠበቀው መሆን ይጀምራል🔥🔥 አብራም እንዲ የከበደበት ነገር በእግዚ አብሄር ፊት ቀላል ሆነ ፈርኦን በጣም በቀላሉ ሚስትህን ውሰድ አለው። ከባ ድ የሆነው ተራራ የሆነው ነገር አካሄድህ ን ከእግዚአብሄር ጋር ስታደርግ ሰረጓጉጡ መስተካከል ይጀምራል🔥 ተራራው መና ድ ይጀምራል🔥 የተበላሸው መስተካከል ይጀምራል🔥 ከባዱ ቀላል ይሆናል🔥 በመንገድህ ላይ አንድ ነገር እርግጠኛ ሁን! አካሄዴ ከእግዚአብሄር ጋር ነው?? ወይስ... የሚሳካለት ሰው በራሱ የተጓዘ ሳይሆን ህይወቱን ዘመኑን ለእግዚአብ ሄር የሰጠ ሰው ነው!🔥 📌 እንደ አብራም እግዚአብሄርን ተማ ምኖ የወጣ ሰው አያፍርም!! እግዚአብ ሄርን ተማምነህ በራስህ ነገሮች ላይ ወስን! አብራም በቤተሰቡ ላይ፣በኑሮው ላይ እንደ ወሰነው ወስን አንድ ቀን ጌታ የፈቀደ ቀን ነገርህ መቃናት ይጀምራል🔥 ክርስትና የመደላድል ጉዞ ሳይሆን የመ ሰጠትና የጭንቅ ጉዞ ነው መጨረሻው ግን ድልና ክብር የሆነ ህይወት! የማይን ገጫገጭ ፒስታ የሌለበት መንገድ ጠብ ቀህ ወደጌታ እንዳትመጣ! ነገር ግን አካ ሄድህን ከእግዚአብሄር ጋር በማድረግ ካለህበት ነገር ለመውጣት ወስን! የች ግሩ ቁልፍ አካሄድን ከእግዚአብሄር ጋር ማድረግ ነው!! የችግሩ ቁልፍ አንተ ጋር ነው! በራስህ የመረጥከው መንገድ እን ዳላዋጣህ ራስህ ምስክር ነህ ከዚህ በሁ ዋላ ግን የራስህን መንገድ ትተህ የጌታን መንገድ ወደ ክብር ህይወት የሚያደር ሰው መንገድ ላይ ህይወትህን መንዳት ና መምራት ጀምር የጌታ ፈቃድ ባንተ ላይ ይሰለጥናል🔥
نمایش همه...
በተለያየ ምክንያት ማለትም መጽሀፍ ቅዱስ ሳነብ ያቃጥለኛል ያስለቅሰኛል መጸለይ ይከብደኛል የምትሉ ለመንፈሳ ዊ ነገር እንግዳ ነኝ እርዳታ እገዛ ከጌታ ጋር የተጠናከረ ህብረት መመስረት እፈል ጋለሁ የተለያየ የጠላት አሰራር በህይወቴ ላይ ሊሰለጥን ሊታገለኝ ይሞክራል የምት ሉ አብረን እንጸልይ @wbinu በዚህ ሊንክ እንገናኝ ተባረኩ ጌታ ኢየሱስ ከየ ትኛውም አይነት አሰራር ይፈታል!! ሀሌሉያያያያያ!
نمایش همه...
🔥 2
የደሙ ድምጽ! የአዲስ ኪዳን መካከለኛ ወደሚሆን ወደ ኢየሱስ፥ከአቤል ደም ይልቅ የሚሻለውን ወደሚናገር ወደ መርጨት ደም ደርሳች ሁዋል።                 (እብ12፥24) 📌 በቃየን እጅ የነበረው የአቤል ደም ለቃየን የመቅበዝበዝ እና ከምድር በረከት ተካፋይ ያለመሆን የእርግማንን ውጤት አመጣ! የዚያ የንጹህ የጻድቅ ሰው ደም የፍትህ ያለህ እያለ ስለሚጮህ እግዚአ ብሄር ፍርድን ለቃየን ሰጠ! የክርስቶስ ኢየሱስ በአፉ ተንኮል ያልተገኘበት በከሳ ሾቹ እንኳን የረባ ክስ ያልቀረበበትና እንከ ን ያልተገኘበት ከወንበዴዎች ጋር ተቆጥ ሮ በግፍ የፈሰሰው የንጹሁ የፍጹሙ የክ ርስቶስ ደም እንደ አቤል ደም ለፍርድ ሳይሆን ለምህረት ይጮሀል! የደሙ ድ ምጽ 👉 የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው ብቻ ይላል! አንዱ ስለ ሁሉ ሞተ ተብሎ ተጽፏልና በግፍ ለገደ ሉት ለምህረት ይማልዳል! የክርስቶስ ደም የተሻለ ይናገራል ምህረት፣ፍቅር፣ ይቅርታ የደሙ ድምጽ! እግዚአብሄርም ቃየንን አለው ወንድም ህ አቤል ወዴት ነው? እርሱም አለ አላው ቅም፤ የወንድሜ ጠባቂው እኔ ነኝን? አለ ውም ምን አደረግህ? የወንድምህ የደሙ ድምጽ ከምድር ወደ እኔ ይጮሀል። አሁ ንም የወንድምህን ደም ከእጅህ ለመቀ በል አፍዋን በከፈተች በምድር ላይ አንተ የተረገምህ ነህ። ምድርንም ባረስህ ጊዜ እንግዲህ ሀይልዋን አትሰጥህም፤በምድ ርም ላይ ኮብላይና ተቅበዝባዥ ትሆናለህ ። (ኦ.ዘፍ4፥9-12) 📌 የደሙ ድምጽ ውጤት እንደ አቤል ደም አይደለም የተሻለና የተለየ ነው! ዛሬም ለምህረት! ዛሬም ለይቅርታ! ዛሬም ለፍቅር! የአቤል ደም የጮኸው ቃየን ፍርዱን እስኪቀበል ድረስ ነው ከዚያ በሁዋላ ቃየን ሂሳቡ ተወራርዷል! የእኛ ሂሳብ የተወራረደው እንደ ቃየን ዋጋ ከፍ ለን ተረግመን ሳይሆን እርግማናችንን ኢየሱስ ተቀብሎልን ነው! በእንጨት የሚሰቀል ሁሉ የተረገመ ነው ተብሎ ተጽፏልና ክርስቶስ ስለ እኛ እርግ ማን ሆኖ ከህግ እርግማን ዋጀን፤                (ገላትያ 3፥13) 📌 የክርስቶስ ኢየሱስ ደም እንደ አቤል ደም ያይደለ ዘመናትን አመታትን ተሻግሮ ለፍርድ ሳይሆን ለይቅርታ ይጮሀል! እርግማን ሳይሆን በረከትን ይዞ በደጅህ መጥቷል! ከዚህ ከደሙ ድምጽ ማስተጋ ባት የተነሳ ከአማኞች አንደበት እርግማን ና ፍርድ ሊወጣ አይችልም! የደሙ ድም ጽ ለይቅርታ በእኔ ላይ አስተጋብቷል የሚ ል ሰው ለአንድም ሰው ቢሆን ፍርድንና ሞትን ሊማልድ አይችልም! የደሙ ድም ጽ በእኔ ላይ ነው! ልጆቼ ሆይ ሀጢአትን እንዳታደርጉ ይህ ንን እጽፍላችሁዋለሁ።ማንም ሀጢአትን ቢያደርግ ከአብ ዘንድ ጠበቃ አለን እር ሱም ጻድቅ የሆነ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። እርሱም የሀጢአታችን ማስተስረያ ነው።          (1ኛ ዩሀ.መል 2፥1-2) 📌 የደሙ ድምጽ የደሙ ሀይል አንተን/ አንቺን ከዘላለም ሞት፣ከዘላለም ፍርድ ያስመልጣል!! ቃየን ማለት በአዳም የው ርስ ሀጢአት የረከስከው አንተ ነህ! የክር ስቶስ ደም በሀጢአት እንዳትጠፋ የሚጮ ኸውም ስላንተ ነው! በሀጢአታችን ብንናዘዝ ሀጢአታችንንም ይቅር ሊለን ከአመጻም ሁሉ ሊያነጻን የታ መነና ጻድቅ ነው።              (1ኛ ዩሀ.መል1፥9) @christology_GC @christology_GC @christology_GC
نمایش همه...
2
መረጠን👉ወሰነን👉አገኘን!! አለም ሳይፈጠር በፊቱ ቅዱሳንና ነውር የሌለን በፍቅር እንሆን ዘንድ በክርስቶስ መረጠን። በበጎ ፈቃዱ እንደወደደ በኢየ ሱስ ክርስቶስ ስራ ለእርሱ ልጆች ልንሆን አስቀድሞ ወሰነን። በውድ ልጁም እንዲ ያው የሰጠን የጸጋው ክብር ይመሰገን ዘንድ ይህን አደረገ። በውድ ልጁም እንደ ጸጋው ባለጠግነት መጠን በደሙ የተደረ ገ ቤዛነታችንን አገኘን እርሱም የበደላች ን ስርየት። (ኤፌ1፥4-8)በፍቅር፦ ቅዱሳን መሆናችን ቅዱሳን መደረጋችን የእግዚአብሄር ፍቅር ውጤት እንጂ የመልካም ጸባያችን አይደለም! ልጅ ነታችን ልጆች ለመሆን መስፈርት ማሟላ ታችን ሳይሆን የእግዚአብሄር ጥልቅ ፍቅ ር እና በጎ ፈቃድ፣ምህረት፣ቸርነት፣ርህራሄ ነው! ምክንያቱም ምህረት ለወደደም ለሮጠም አይደለም ከሚምር ከእግዚአ ብሄር ነው እንጂ ተብሎ ስለተጻፈ!(ሮሜ 9፥16) 📌 ልጅነታችን ከመፈጠራችን እና አለም ላይ ያሉ ነገሮች በሙሉ ከመፈጠራቸው በፊት ቅድመ አለም ላይ በእግዚአብሄር ልብ መወሰኑ እግዚአብሄር ለሰዎች ምን ያህል ጥልቅ ፍቅር እንዳለው ያሳያል! አስቀድሞ የተወሰነ ሰው ድንገት አይ ጠፋም! አስቀድሞ የተወሰነ ሰው በቀላሉ ከእግዚአብሄር መንግስት አይወጣም! ከእጄ ማንም አይነጥቃችሁም ያለው ጌታ ታማኝ ስለሆነ!!( መዳናችን ከመፈጠራችን በፊት እኛ በሌለ ንበት ጭምር የተወሰነ ጉዳይ እንጂ ድን ገቴ አይደለም! እኛ ከተፈጠርን በሁዋላ ቢሆን ለመዳን የተወሰንነው ምን አልባት የሚመች ነገር ስላለን ነው ለማለት ያመች ነበረ! ነገር ግን እኛ በሌለንበት የአኛ ድርሻ የእኛ አስተዋጽኦ በሌለበት እንዲሁ በእግ ዚአብሄር ፍቅር ተወደናል! በሌለንበት የወ ደደን ጌታ ባለንበት አይሰለቸንምና መዳና ችን እርግጥ ይሁንልን! ሰው በእግዚአብ ሄር ዘንድ ያለው ስፍራ ይሄን ያክል ነው! በሌለበት ለክብር፣ለልጅነት፣ለወራሽነት መወሰን አይገርምም?? አይደንቅም?? እንዴት አይነት ነገር ነው?? Praise lord! 📌 ከመጀመሪያውኑ ስለወደድከኝ ያለ ምክንያት ወደህ በምክንያት ስለማትጠላ ኝ አመሰግንሀለሁ ስለወደድከኝ ወድሀ ለሁ! አስቀድሞ የተወሰነ ነገር እየቆየ ስለማይሻር! ዳኛው ፍርድ ቤት ሆኖ ከወሰነ መዶሻውን አንስቶ ካረጋገጠ በሁዋላ የህግ አካላት ውሳኔውን የማ ጽናትና የማስጠበቅ ሀላፊነት እንዳለባ ቸው ሁሉ እግዚአብሄር በልጁ ስራ በክ ርስቶስ ስራ የሀጢአታችንን ስርየት እንድ ናገኝ ወስኗል! እግዚአብሄር የራሱን ስራ ስለሰራ ያንተን ስራ አይቀበለውም! አይ ጠብቀውምም! ለመዳንህ የሚያስፈል ገውን ስራ ሁሉ ብቻውን መስቀል ላይ ሰርቶልሀል! አብ ብቸኛ የተቀበለው መስ ዋእት የክርስቶስን የቤዛነት ስራ ነው! የተመረጠው አለም ሁሉ ነው! አለም በልጁ እንዲድን ነው እንጂ እንዲፈርድ አላከውምና ተብሎ እንደተጻፈ ነው! 📌 በውድ ልጁ፦ ማለት ስላንተ/ስላንቺ የተከፈለው ዋጋ የክርስቶስ የደም ዋጋ ነው! ዋጋህ በክርስቶስ ደም አማካኝነት ከብሯል! እንደ ጸጋው ባለጠግነት፦ እንደ ፍቅሩ፣ እንደ ምህረቱ፣እንደ ቸርነቱ፣እንደራሱ መልካምነት ብቻ ወዶኛልና አዳነኝ! ሰርቶ ያሳየኝ፣አንዳንድ የቀድሞ መጥፎ Profilዎቹ ይስተካከሉና ብሎ ቀጠሮ ሰጥቶ ጸባዩም ታይቶ ምግባሩ ታይቶ ብሎ ሳይሆን እንደ ጸጋው ባለጠግነት መጠን ብቻ!! ወሰነን! መረጠን! አገኘን! @christology_GC @christology_GC
نمایش همه...
2
ሻሎም ሻሎም ቅዱሳን🙌🙌🙌 በወንጌል እሳት የነደዱ ለወንጌል እስከ መጨረሻው ዋጋ የሚከፍሉ ወጣቶች በfinance እጥረት ምክንያት እግሮቻቸው ተይዘዋል! እነዚህ የምስራቹን የሚያወሩና በቅርቡ በተለይም በከተማችን አ.አ ለሚ መጣው revival ምክንያት የሆኑ ሰዎች ማንም ሳያስተውላቸው አክሊል የሚያስ ገኝላቸውን ትልቅ ዋጋ እየከፈሉ ነው! ሁላ ችንም በአደባባይ ወጥተን ወንጌል መስ ክረን ጌታ የሰጠንን ሂዱ ወንጌልን ለፍጥ ረት ሁሉ ስበኩ የተባልንበትን ተልእኮ መ ፈጸም ባንችል እንኳን ባለን አቅም ትንሽ ትልቅ ሳንል በጸሎት፣በገንዘብ በምንች ለው ነገር በአይነት ድጋፍ ልናደርግላቸው ይገባል! እኔ አቅሙ ስለሌለኝ እናንተን ለመጠየቅ ተገድጃለሁ! መጠየቅም አለ ብኝ! ምክንያቱም ሀላፊነቱ የእኛ ነው! እመኑኝ በቅርብ revival ይመጣል ያ እንዲመጣ በችግር በእጦት የተያዙ የም ስራቹን የሚያወሩ እግሮች መለቀቅ አለ ባቸው ያ ሀላፊነት የማንም አይደለም የቸርች፣የመሪዎች፣የአገልጋዮችና የም እመናን የሁሉም አማኝ ነው! ቃሉ ስለሚ ለን!! እነዚህን የነገ ለውጥ ተሀድሶ አምጪዎ ች መደገፍ ማበረታታት አቅም ጉልበት መሆን እፈልጋለሁ የወንጌል ባላደራ ነኝ ሸክሙ አለብኝ ቢያንስ ሌላው ቢቀር በምችለው የበኩሌን ልወጣ ተልእኮዬን ልፈጽም የሚል ሰው ካለ በ09948399 10 ደውሎ እኔ ወንድማችሁ ቢንያምን ሊያናግረኝ ይችላል!! እመኑኝ በቅርብ በቅርብ በቅርብ ስለሌላ ው ከተማ አላውቅም አ.አ ላይ ግን reviv al ይመጣል!
نمایش همه...
# ለተልእኳችን እንነሳ! ነገር ግን መንፈስ ቅዱስ በእናንተ ላይ በወረደ ጊዜ ሀይልን ትቀበላላችሁ፥በኢየ ሩሳሌምም በይሁዳም ሁሉ በሰማርያም እስከ ምድር ዳርም ድረስ ምስክሮቼ ት ሆናላችሁ አለ። (ሀዋ.ስራ 1፥8) 📌 ተልእኳችን መጨረሻ የለውም! በቃ እዚጋ የሚባልለት አይደለም! ወሰን አልባ ተልእኮ ተሰጥቶናል! ቤተክርስቲያን ያላት ን አቅም፣ጸጋ፣ገንዘብ፣ጉልበት ሁሉ በዋነ ኝነት በትኩረት ለዚህ አለገልግሎት ማዋ ል አለባት! ተልእኳችን ትልልቅ ቸርቾችን መገንባት አይደለም! ችግረኞችን ሰብስቦ መርዳት አይደለም! ምስኪኖችን አንርዳ እያልኩ አይደለም! ነገር ግን የቤ/ን ግም ባር ቀደሙ ተልእኮ ሂዱ ወንጌልን ለፍጥ ረት ሁሉ ስበኩ የተባልንበት ተልእኳችን ነው! ሌላው ሁለተኛ እንጂ 1ኛ አይደለም! አንድ የእ/ር ሰው እንዳለው የዘንድሮዋ ቤ/ን እቃ ገዝተህ ና ተብሎ ተልኮ ሲጫ ወት የተባለውን እንደረሳ ህጻን ልጅ ትመ ስላለች! ዋናውና የመጀመሪያው ተልእኳ ችን ወንጌል ሆኖ ሳለ በእግረ መንገድ መሰራት ያለባቸውን እየሰራን የቅድሚያ ቅድሚያ መሰራት ያለበትን ወንጌል ዘንግ ተነዋል! 📌 ወንጌል በወር አንድ ጊዜ ወይም ከሆ ነ ጊዜ አንዴ የሚሰራ የአልፎ አልፎ ስራ ሳይሆን በየቸርቹ team ተቋቁሞለት ከፍ ያለ በጀት ተመድቦለት አገልጋዮች ወንጌላውያን ተመድበው በትኩረት ያለ መታከት ሊሰራ የሚገባው ስራ ነው!ወን ጌል በትርፍ ጊዜ አይሰራም ሁሌ እንጂ! የቤ/ን የአማኞች ስራ ተልእኮን መፈጸም ነው! ለተልእኮው እያንዳንዱ ክርስቲያን ሀላፊነት ሊሰማው ይገባል! ከአጠገባ ችን ያለው ትውልድ ከጎረቤታችን ጀም ሮ ወንጌልን ሳይሰማ ታሞ እየሞተ ነው! መድሀኒቱን ማቀበል ባለመቻላችን ትው ልድ ሲጠፋ እያየን ነው! ኧረ ተልእኳችንን እንድንፈጽም ጌታ ይርዳን! ስንት ሰው ነው ስለ ወንጌል የሚጸልየው?? በሰሜኑ ጦር ነት ወንጌል ያልደረሳቸው ከ1 ሚሊየን በላይ ዜጎች ወደ እሳት ባህር ተጥለዋል! እኛ ምን እየሰራን ነው? እየጸለይን ነው? ተልእኳችንን ለመፈጸም እየሞከርን ነው?? ሂዱ! ሂዱ ከተባልን መቆሚያ የለውም! መጨረሻ የለውም! አለም ነው መጨረሻ ው! እኔ የተልእኮ ሰው ነኝ!! ቤ/ን ገቢ ከሚያመጣ ንግድ ተቆጥባ አቅሟን ሁሉ ለተልእኮው ለማዋል መነሳት አለባት!የቤ/ ን ምስረታ ዋነኛ አላማ ለፍጥረት ሁሉ ወን ጌልን ለማድረስ ነው! በግል ሸክም ይሰማ ን ይሆን? ጳውሎስ ወገኖቹ ድነው እሱ ቢጠፋ ይመርጥ ነበር! የሸክሙ ልክ ያን ያህል ነው! እኛስ?? ወንጌል የፍቅር መልእክት ስለሆነ ራስ ወዳድነት የሌለበት የፍቅር ለሚወዱት ሰው እንዳይጠፋ የሚነ ገር መልእክት ነው! ትውልድ በጣኦት አም ልኮ፣በሱስ፣በዝሙት፣በመገዳደል ደም በመቃባት እየጠፋ ነው! እኛ ባለንበት መሆኑ ይበልጥ ሊያነሳሳን ይችላል ብዬ አስባለሁ! 📌 የቸርች ውስጥ ዝማሬ ስብከት ሌላ ሌላውም እርስ በራሳችን ከመሟሟቅ ው ጪ ያን ያህል አይደለም... የቸርችን አገል ግሎት እያጣጣልኩ አይደለም!ግን ወደ ቀዝቃዛው አለም ለመግባት እንሞክር! ተልእኳችን ለቀዝቃዛው አለም ነውና! ማንም ሰው ወንጌልን ሳይሰማ ሊፈረድ በት አይችልም! በመጨረሻው ዘመን ወንጌል በአለም ሁሉ ይሰበካል! ሁሉም ጎዳና ላይ ወጥቶ ላይመሰክር ይችል ይሆ ናል ግን ባለው ነገር በጸሎት፣በገንዘብ እና በአስፈላጊ ነገር መተባበር እጅግ አስፈላጊ ነው። ተልእኳችንን እንፈጸም! ለተልእኳችን እንንቃ! ለተሰጠን ተልእ ኮ እንዘጋጅ! ለተልእኳችን ያለንን ሁሉ እንስጥ! ቤ/ን የፈለገው አይነት ራእይ ሊኖራት ይችላል! ነገር ግን ከተልእኳችን የሚቀድም ራእይ ሊኖረን አይገባም! ለወን ጌል አማኞች ጌታ የሰጠው ቀዳሚው ራእይ የወንጌል ተልእኮ ነው! ከዚህ የቀ ደመ ራእይ የትም አያደርስም! ቀዳሚ ራእ ያችን ተልእኳችን ይሁን! ከተልእኮ የሚቀ ድም ወንጌልን የሚተካ አንዳች ነገር የለ ም! ሁላችንም ራሳችንን እንደ missiona ry እንደ ተልእኮ ሰው እንደ ወንጌል amb assader መቁጠር አለብን ተልእኮው ለተወሰኑ ሰዎች ብቻ ሳይሆን ላመኑ ጌታ ን ለተቀበሉ ሁሉ ነውና! እኔ የተልእኮ ሰው ነኝ!
نمایش همه...
1
3👍 2