fa
Feedback
Dej.Balcha Abanefso General Secondary School

Dej.Balcha Abanefso General Secondary School

رفتن به کانال در Telegram
5 273
مشترکین
+424 ساعت
+597 روز
+16330 روز
آرشیو پست ها
ለ11ኛ እና ለ12ኛ ክፍሎች በሙሉ በክረምት ማጠናከሪያና ተያያዥ ጉዳዮች ተማሪዎች ተመዝግበው ባለመጠናቀቃቸው የክፍል ድልድል ስላልተጠናቀቀ 25-26/12/2018 ድረስ በተለያየ ምክንያት ያተመዘገባችሁ እንድትመዘገቡ እያሳወቅን ማክሰኞ 26/12/2018 ከሰዓት የክፍል ድልድሉ ተሰርቶ ከረቡዕ-አርብ የመጽሐፍ እደላ የሚከናወን መሆኑን ከይቅርታ ጋር እናሳውቃለን።

የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲዎች የ2019 ዓ.ም መግቢያ ፈተና የምዝገባ ጥሪ =============================== በአገራችን እየተመዘገበ ያለውን የኢኮኖሚ እድገት ለማስቀጠልና ብልፅግናን ለማረጋገጥ የአገሪቱን በሳይንስና ቴክኖሎጂ የሰለጠነ የሰው ሀይል ፍላጎት ለማሟላት በመንግስት ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት ከፍተኛ የለውጥ እንቅስቃሴ እየተደረገ ይገኛል፡፡ ይህንንም እውን ለማድረግ ልዩ ተልዕኮ ተሰጥቷቸው የተደራጁትን የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እና የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የትምህርት ጥራት ማዕከላት በማድረግ በዘርፉ ብቃት ያላቸውን ሙያተኞችን እያፈሩ ይገኛሉ፡፡ በመሆኑም በ2019 ዓ.ም የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እና የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ገብተው በአፕላይድ ሳይንስ እና በኢንጂነሪንግ የትምህርት ዘርፎች ትምህርታቸውን መከታተል ለሚፈልጉ በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ወስደው 50% እና ከዚያ በላይ ያስመዘገቡ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎችን ተጨማሪ የመግቢያ ፈተና ኦንላይን (Online) በመስጠት መቀበል ይፈልጋሉ፡፡ የትምህርት መስኮች፡- አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ኢንጂነሪንግ - አርክቴክቸር - ሲቪል ኢንጂነሪንግ - ወተር ሪሶርስ ኢንጂነሪንግ - ኬሚካል ኢንጂነሪንግ - ሜካኒካል ኢንጂነሪንግ - ማቴሪያል ሳይንስና ኢንጂነሪንግ - ኤሌክትሪካል ፓወር እና ኮንትሮል ኢንጂነሪንግ - ኤሌክትሮኒክስ እና ኮሚኒኬሽን ኢንጂነሪንግ - ኮምፒዩተር ሳይንስና ኢንጂነሪንግ - ሶፍትዌር ኢንጂነሪንግ አፕላይድ ሳይንስ - አፕላይድ ባዮሎጂ - አፕላይድ ኬሚስትሪ - ኢንዱስትሪያል ኬሚስትሪ - ፋርማሲ - አፕላይድ ፊዚክስ - አፕላይድ ጂኦሎጂ - አፕላይድ ማቲማቲክስ አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ኢንጂነሪንግ - አርክቴክቸር - ሲቪል ኢንጂነሪንግ - ኬሚካል ኢንጂነሪንግ - ሜካኒካል ኢንጂነሪንግ - ኤሌክትሪካል እና ኮምፒዩተር ኢንጂነሪንግ - ኤሌክትሮሜካኒካል ኢንጂነሪንግ - ሶፍትዌር ኢንጂነሪንግ - ኢንቫይሮሜንታል ኢንጂነሪንግ አፕላይድ ሳይንስ - ኢንዱስትሪያል ኬሚስትሪ - ፉድ ሳይንስና አፕላይድ ኒዩትሪሽን - ጂኦሎጂ - ባዮቴክኖሎጂ የምዝገባ ጊዜ፡- - ከነሐሴ 25 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ ጳጉሜ 3 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ ለሊቱ 6 ሰዓት ይሆናል፡፡ የምዝገባ ቦታ፡ - የምዝገባ መስፈርቱን የሚያሟሉ አመልካቾች በማንኛውም ስፍራ በኢንተርኔት (online) በ https://stu.astu.edu.et ወይም www.aastu.edu.et; www.astu.edu.et ድህረ ገፅ በመጠቀም መመዝገብ ይችላሉ፡፡ ፈተናው የሚሰጥበት ቀን፡- በድህረ ገፃችን የምዝገባው ቀን ካበቃበት በኋላ እናሳውቃለን ፡፡ ፈተናው የሚሰጥበት ቦታ፡- - በምዝገባ ወቅት በመረጡት የፈተና ጣቢያ በአካል በመቅረብ ይሆናል፡፡ ማሳሰቢያ፡- · የፈተና ጣቢያዎቹ ያላቸው የመፈተኛ ቦታ ውስን በመሆኑ ይህንኑ አውቃችሁ ቅድሚያ እንድትመዘገቡ እናሳስባለን፡፡ · በቂ አመላካቾች የሌሉባቻው የፈተና ጣቢያዎች በቅርበት ወደሚገኙ የፈተና ጣቢያዎች ሊታጠፉ እንደሚችሉ እናሳውቃለን፡፡ · ለፈተና የሚቀርቡት የአመልካቾች ስም ዝርዝራቸው እና የፈተና ጣቢያዎች በሚከተሉት ድረ-ገፆች፡- www.aastu.edu.et ; www.astu.edu.et እንደአመቺነቱም በe-mail የሚገለፅ ይሆናል፡፡ · አመልካቾች ከወዲሁ ፈተናው በሚሰጥባቸው የትምህርት ዓይነቶች፣ ማለትም (ከ9ኛ እስከ 12ኛ ክፍል) ባዮሎጂ፣ ኬሚስትሪ፣ ፊዚክስ፣ ሂሳብና እንግሊዝኛ እንዲዘጋጁ ይመከራል፡፡ · ፈተና የሚሰጠው በቀጥታ (online) ስለሆነ አመልካቾች በፈተና ጊዜ ሊያጋጥም የሚችል ግራ መጋባትን ለማስቀረት በምዝገባ ጊዜ ከመመዝገቢያ ፎርማቱ ጋር ተያይዞ የቀረበውን የሙከራ ፈተና እንዲለማመዱ ይመከራል፡፡ · አመልካቾች ለፈተና ሲቀርቡ የ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ውጤት፣ የሀገር አቀፍ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና አድሚሽን ካርድ (ወይም መታወቂያ) እና የምዝገባ ማረጋገጫ ኮፒ መያዝ ይጠበቅባቸዋል፡፡ · የመግቢያ ፈተናውን የሚያልፉ አመልካቾች በትምህርት ሚኒስቴር በኩል በሚደረገው የዩኒቨርሲቲ ምደባ ውስጥ አይካተቱም፡፡ · በውጤታቸው የተመረጡ ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ ምደባ ከላይ በተጠቀሱት ድህረ-ገፆች ይገለፃል፡፡ · በመስፈርቱ መሰረት ያልተመረጡ አመልካቾች ከዚህ በፊት እንደሚደረገው በትምህርት ሚኒስቴር በኩል በሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች የሚመደቡ ይሆናል፡፡ · በፈተናው ዕለት ማንኛውንም የሞባይል ስልኮችን ይዞ ወደ ፈተና ጣቢያ መግባት የተከለከለ ነው፡፡ · በፈተና ወቅት ያልተገባ ተግባር መፈፀም በጥብቅ የተከለከለ ነው፡፡ ለተጨማሪ ማብራሪያ ከታች የተጠቀሱትን ድረ-ገፆች እና ቴሌግራም ቻናላችንን መጎብኘት ይቻላል፡፡ www.astu.edu.et; www.aastu.edu.et Telegram:https://t.me/AdamaSTU_ASTU የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እና የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ

Repost from ATC NEWS
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በ2019 የትምህርት ዘመን በቅድመ-ምረቃ መደበኛ መርሐግብር (በመንግሥት ስኮላርሺፕ እና በግል ክፍያ) እንዲሁም በማታና ተከታታይ መርሐግብር አዲስ ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተማር
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በ2019 የትምህርት ዘመን በቅድመ-ምረቃ መደበኛ መርሐግብር (በመንግሥት ስኮላርሺፕ እና በግል ክፍያ) እንዲሁም በማታና ተከታታይ መርሐግብር አዲስ ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተማር ይፈልጋል። መስፈርቶች ➻ በ2015፣ 2016፣ 2017 እና 2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ መልቀቂያ ፈተና ወስደው የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ነጥብ ያመጡ ወይም ደረጃ 4 አጠናቀው (COC) ያለፉ ➻ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሚሰጠውን የመግቢያ ፈተና (UAT) ይወስዳሉ የምዝገባ ጊዜ 👇 እስከ ነሐሴ 29/2018 ዓ.ም ድረስ ኦንላይን ይመዝገቡ 👇 https://admission.aau.edu.et የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የመግቢያ ፈተና (UAT) ከጳጉሜን 02-04/2018 ዓ.ም ይሰጣል፡፡ ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot ➡️ https://t.me/atc_news

ማስታወቂያ! (ነሀሴ 22/2018 ዓ.ም) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ባወጣው ማስታወቂያ መሰረት በምስራቅ ጎህ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የሳይንስ ልህቀት ማዕከል ለመማር ለተመዘገባች
ማስታወቂያ! (ነሀሴ 22/2018 ዓ.ም) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ባወጣው ማስታወቂያ መሰረት በምስራቅ ጎህ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የሳይንስ ልህቀት ማዕከል ለመማር ለተመዘገባችሁና ፈተና ለወሰዳችሁ ተማሪዎች ከዛሬ ከ22/12/2018 ዓ.ም ጀምሮ በተመዘገባችሁበት ሊንክ እየገባችሁ ውጤታችሁን ማየት የምትችሉ መሆኑን እየገለፅን የተመረጣችሁ ተማሪዎች የፊታችን እሮብ በ27/12/2018 ዓ.ም በምስራቅ ጎህ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የሳይንስ ልህቀት ማዕከል በመገኘት እንድትመዘገቡ እናሳውቃለን። ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://linktr.ee/aacaebc

የ2019 ዓ.ም መጽሐፍት መውሰጃ ፕሮግራም ማስቸካከያ የ10ኛ ክፍሎች በፕሮግራም መደራረብ ምክንያት ዘግይቶ መሰጠት ስለጀመረ ሐሙስ ያልወሰዳችሁ አርብ ነሐሴ 22/2018 ከ 3:00-7:00 እንድትወስዱ እናሳውቃለን። (መጽሐፍ ስለመመለሳችሁ የሚገልጽ ማስረጃ ይዞ መገኘት) 11ኛ እና 12ኛ ክፍሎች አርብ የነበረው በቀጣይ ሳምንት ሰኞ ነሐሴ 25/2018 የ11ኛ እና ማክሰኞ ነሐሴ 26/2018 የ12ኛ ክፍሎች እንድትወስዱ እናሳውቃለን። (መጽሐፍ ስለመመለሳችሁ የሚገልጽ ማስረጃ እና የክረምት ማላቂያ ስለመከታተላችሁ የሚገልጽ ሰርተፊኬት ይዛችሁ እንድትገኙ ለ Top 30 ብቻ)

ለአይን ምርመራ የተመዘገባችሁ ነገ ጠዋት 4:00 ት/ቤት እንድትገኙ

በጣም አስቸኳይ የክረምት ትምህርት የምስክር ወረቀት ስለመጣ ሁሉም ተሳታፊ ተማሪዎች ነገ ጠዋት2:30 ላይ ዩኒፎርም በመልበስ ተገኝታችሁ እንድትወስዱ እና በእለቱ በየትቤታችሁ ወስዳችሁ ለመዝጋቢዎች በማሳየት ድልደላ በማድረግ መፅሃፍ እንድትወስዱ ምደባችሁ ስለዘገየ በተባለው ስዓት በመገኘት እንድትጨርሱ እናሳስባለን ነገ ያልተገኙ ቅዳሜና እሁድ ምደባውን ስለምንሰራ እንዳትቸገሩ ለአጭር ስዓት እንድትገኙ ከአደራ ጭምር እንገልፃለን

Grade 11 & G-12 new section placement .... coming soon.....

የ 10ኛ ክፍል አዲስ ምደባ፣ ሀሙስ በ 21/12/2018 መጽሀፍ ለመውሰድ ስትመጡ የ2018 ሰርተፊኬት እና አእራትዮሽ ፊርማ ገቢ ማድረግ ይኖርባቹሃል፡፡

ቅሬታ/Complaint ላላችሁ ተማሪዎች የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ተፈታኞች ቅሬታ ሲኖራቸው በአካል መምጣት ሳያስፈልጋችሁ https://result.eaes.et/complaint የሚለውን ማስፈንጠሪያ በመጠቀም ቅሬታቸሁን ከነሐሴ 19 እስከ 26/2018 ዓ/ም ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ድረስ ማቅረብና ምላሹንም በዛው ማስፈንጠሪያ መከታተል እንደምትችሉ ገልጿል። @Ethiopian_Digital_Library @Ethiopian_Digital_Library

Congra Haile
Congra Haile

Congra Kalkidan !
Congra Kalkidan !

Congra Kidist
Congra Kidist

Congra Ruhama
Congra Ruhama

Woow Congratulation. Tesfalem አምና ተፈትኖ ውጤት ሳይሞላለት ቀርቶ በዘንድረ አመት Private ተፈትኖ 401 ያመጣ። ተስፋ ሳይቆረጥ ከተሰራ ይሄም ይቻላል። ለእሱና አመቱን ሙሉ አ
Woow Congratulation. Tesfalem አምና ተፈትኖ ውጤት ሳይሞላለት ቀርቶ በዘንድረ አመት Private ተፈትኖ 401 ያመጣ። ተስፋ ሳይቆረጥ ከተሰራ ይሄም ይቻላል። ለእሱና አመቱን ሙሉ አብራ ስጨነቁ ለነበሩት እናቱ እንኳን ደስ አላችሁ

Congra Selamawit
Congra Selamawit

Congratulations !
+4
Congratulations !