1 257
مشترکین
+124 ساعت
-37 روز
-1230 روز
آرشیو پست ها
1 258
የስድስተኛ ክፍል ተማሪዎች
የመጀመሪያ ስም የሚለው ላይ ስማችሁን መጻፍ ያለባችሁ በአማርኛ ነው እንግሊዘኛ ከሆነ ውጤቱን አያወጣላችሁም፡፡
1 258
ክፍል ተማሪዎች ወላጆች በሙሉ
የተፈተኑ ተማሪዎች ሁሉም በማለፋቸው በቅድሚያ እንኳን ደስ አላችሁ ማለት እንወዳለን።
ከተፈተኑት ሃምሳ ሁለት ተማሪዎች ውስጥ 24 ተማሪዎች ከ90 በላይ ውጤት አስመዝግበዋል። ውጤታቸውንም የሚከተለውን ማስፈንጠሪያ በመጠቀም ማየት ትችላላችሁ
1 258
Repost from Addis Ababa Education Bureau
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2018 የትምህርት ዘመን የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና ውጤት ነገ ጠዋት ይፋ ይሆናል፡፡
(ሰኔ 28/2018 ዓ.ም) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2018 የትምህርት ዘመን የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና ውጤት ነገ ጠዋት ይፋ ይደረጋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የ2018 የትምህርት ዘመንን የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና በአጭር ጊዜ አርሞ ይፋ ማድረጉ ተማሪዎች ለቀጣዩ የትምህርት አመት ከወዲሁ በቂ ዝግጅት እንዲያደርጉ የሚያስችል ነው፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2018 የትምህርት ዘመን የ6ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ከሰኔ 8 -10 /2018 ዓ.ም ድረስ በከተማ አስተዳደሩ በሚገኙ 199 የመፈተኛ ጣቢያዎች ለተከታታይ ሶስት ቀናት መሰጠቱ ይታወሳል፡፡
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://linktr.ee/aacaebc
1 258
ለወላጆች በሙሉ
በቅድሚያ እንኳን ለ 2018 ዓመተ ምህረት ትምህርት መጨረሻ ጊዜ በሰላም አደረሳችሁ። በመቀጠልም ሐሙስ ሰኔ 25 ቀን 2018 ዓመተ ምህረት ካርድ የሚሰጥ መሆኑን ማሳወቃችን ይታወሳል። በመሆኑም በእለቱ ከጠዋቱ ሁለት ሰዓት እስከ ቀኑ ዘጠኝ ድረስ በአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግቢ መገኘት የልጅዎን ሪፖርት ካርድ እንዲወስዱ በአክብሮት እንጠይቃለን።
ማሳሰቢያ
የትምህርት ቤት የሰርቪስ እና የጥናት ክፍያ ክፍለው ላልጨረሱ ተማሪዎች የሪፖርት ካርድ የማይሰጥ መሆኑን አውቃችሁ ያለባቸሁን ክፍያ ከወዲሁ ክፍላችሁ እንድታጠናቅቁ በአክብሮት እናሳስባለን።
1 258
ለወላጆች በሙሉ
በቅድሚያ እንደምን ዋላችሁ።
በ 2018 ዓ.ም ካስፈተናቸው 32 ተማሪዎች ውስጥ 31 ተማሪዎች ያለፉ ሲሆን 1 ተማሪ ግን ሳትዛወር ቀር ታለች። በተዛወሩት ተማሪዎች ደስ ያለን ቢሆንም መውደቅ በማይገባት እንዷ ተማሪያችን ግን ያዘንን መሆኑን መግለጽ እንወዳለን።
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
