1 286
Підписники
-124 години
+47 днів
+2530 день
Архів дописів
1 286
ለነበር ተማሪ ወላጆች
በቅድሚያ እንደምን ሰነበታችሁ። በመቀጠልም የ2019 ዓ.ም ነባር ተማሪ ምዝገባ እስከ ሐምሌ 20 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ እንደሆነ መግለፃችን ይታወሳል። በመሆኑም እስካሁን ያላስመዘግባችሁ ወላጆች ካላችሁ ዛሬ ተመዝግባችሁ እንድታጠናቀቁ። ከነገ ሐምሌ 21 ቀን 2018 ዓመተ ምህረት ጀምሮ ባለን ክፍት ቦታ ላይ ሁሉ አዲስ ተማሪዎችን የምንመዘግብ መሆኑን መግለጽ እንወዳለን።
1 286
ለወላጆች በሙሉ
የክረምት ትምህርትን ይመለከታል
። ሮበስት ቁጥር 1 መካኒሳ አቦ ማዞሪያ አካባቢ ቅርንጫፍ ሐሙስ ሐምሌ 9 ቀን 2018 ዓ.ም የክረምት ትምህርት ይጀምራል።
ትምህርቱ የሚሰጠው በሳምንት አራት ቀናት ማለትም ሰኞ ማክሰኞ ሐሙስ እና አርብ እስከ ሰባት ሰአት ድረስ ብቻ ነው፡፡
። ከአንደኛ ክፍል እስከ ስድስተኛ ክፍል ያሉ ተማሪዎች በሳምንት አራት ትምህርት ይማራሉ።
። 7ኛ እና ስምንተኛ ክፍሎች ደግሞ አምስት ትምህርቶችን ይማራሉ።
። ለክፍያና ሌላ ተጨማሪ ማብራሪያ ሲፈልጉ የስልክ ቁጥር 0937611451 ይጠቀሙ፡፡
1 286
ለወላጆች በሙሉ
የክረምት ትምህርትን ይመለከታል
። ሮበስት ቁጥር 1 መካኒሳ አቦ ማዞሪያ አካባቢ ቅርንጫፍ ሐሙስ 9 ሐምሌ 9 ቀን 2018 ዓ.ም የክረምት ትምህርት ይጀምራል።
ትምህርቱ የሚሰጠው በሳምንት አራት ቀን ማለትም ሰኞ ማክሰኞ ሐሙስ እና አርብ እስከ ሰባት ሰአት ድረስ ብቻ ነው፡፡
። ከአንደኛ ክፍል እስከ ስድስተኛ ክፍል ያሉ ተማሪዎች በሳምንት አራት ትምህርት ይማራሉ።
። 7ኛ እና ስምንተኛ ክፍሎች ደግሞ አምስት ትምህርቶችን ይማራሉ።
። ለክፍያና ሌላ ተጨማሪ ማብራሪያ ሲፈልጉ የስልክ ቁጥር 0937611451 ይጠቀሙ፡፡
1 286
1 286
ለነበር ተማሪ ወላጆች በሙሉ
ከላይ ያስቀመጥነው መረጃ ግልጽ ያልሆነላቸው ወላጆች እንዳሉ በስልክ በስልክ ደውለው ጠይቀውናል።
ግልጽ ለማድረግ ያክል ነባር ተማሪዎች የሚማሩበት ቦታም ሆነ የክፍያው መጠን ወይም ያከፋፈል ስርዓቱ የተቀየረ ነገር የለም። እንደተለመደው በየወሩ ነው የሚከፈለው።
አዲስ ተከፈተ ያልናችሁ ትምህርት ቤት ተጨማሪ እንጂ ነባሩን ትምህርት ቤት የሚተካ አይደለም። እስካሁን ስትከፍሉት የነበረውን ወርሃዊ ክፍያም ሆነ መዝገበያ ክፍያ አልተቀየረም በነበረበት ነው የሚቀጥለው። ያከፋፈል ርዓቱም ቢሆን እስከ ዛሬ እንደምትከፍሉት በየወሩ የሚከፈል ነው።
በተርም ወይም በዓመት 4 ጊዜ ይከፈላል ብለን ከላይ የገለጽነው ለአዲሱ ትምህርት ቤት ብቻ ነው። በዚ ላይ ግልጽ ያልሆነላችሁ ወላጆች ካላችሁ አሁንም ደውላችሁ ተጨማሪ ማብራሪያ ማግኘት ትችላላችሁ።
መልካም ቀን
1 286
ለወላጆች
ትምህርት ቤታችን ሮበስት አካዳሚ በ 2019 ዓ.ም ጀሞ ሚካኤል አካባቢ አዲስ ትምህርት ቤት ከፍቷል፡፡ ለዚህም የትምህርት ቤቱ ማህበረሰብ በሙሉ እንኳን ደስ ያላችሁ ማለት እንወዳለን። ከ20019 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ጀምሮም በቦታው ላይ ስራ የምንጀምር ሲሆን በዛሬው እለት በይፋ ምዝገባ መጀመራችንን እናሳውቃለን።የዚህ ትምህርት ቤት የቢሮ አደረጃጀት የተወሰኑ ቀናቶችን የሚፈልግ በመሆኑ ለጊዜው ምዝገባውን የምናካሂደው በነባሩ ግቢያችን ወይም ነባር ተማሪዎቻችንን በምንመዘግብበት መካኒሳ አቦ መዞሪያ አካባቢ የሚገኘው አንደኛ እስከ ስምንተኛ ክፍል በሚማበት ግቢ ነው።
የአዲሱ ትምህርት ቤት መረጃ፡
1. የትምህርት ቤቱ ደረጃ፡ ከአንደኛ እስከ ስድስተኛ ክፍል
2. የክፍያ ሁኔታ፡ በተርም ወይም በዓመት አራት ጊዜ የሚከፈል
3. የክፍያው መጠን፡
። በተርም 18,000 ብር
። የመመዝገቢያ ክፍያ በዓመት አንድ ጊዜ ብቻ የሚከፈል፡ ብር 1,800.00
አዲስ ለሚመዘገቡ ተማሪዎች የሚያስፈልጉ መረጃዎች፡
1. ከነበሩበት ትምህርት ቤት ወደሚቀጥለው ክፍል የተዛወሩበትን የትምህርት ማስረጃ ወይም ካርድ
2. ከነበሩበት ትምህርት ቤት የተሰጣቸውን መልቀቂያ ወይም መሸኛ
3. የልደት ካርድ
4. ብሔራዊ መታወቂያ / National ID /
አድራሻ፡
1. በህብር ትምህርት ቤት በኩል የኮብል ስቶን መንገዱን ይዘው ወደ ታች ሲወርዱ ዋናው የአየር ጤና መንገድ ላይ በሚያገኙት አዲሱ የትራፊክ መብራትስር፡፡
። ከፊት ለፊቱ ፌዴሬሽን ሜዳ አለ
። ከአጠገቡ ደግሞ የሙሉ ወንጌል ቤተክርስቲያን አለ፡፡ ወይም
2. ከጀሞ ሚካኤል መብራት ወደ አየር ጤና በሚወስደው መንገድ ቀኝ ይዘው 200ሜ ከተጓዙ በኋላ አዲሱ መብራት አጠገብ ያገኙታል። ከጎኑም የሙሉ ወንጌል ቤተ ክርስቲያን ይገኛል።
1 286
ለወላጆች በሙሉ
በቅድሚያ እንኳን ለ 2019 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ምዝገባ ጊዜ በሰላም አደረሳችሁ እንላለን፡፡ በመቀጠልም የሚከተሉትን የምዝገባ መረጃዎች እናስተላልፋለን።
1. ነባር ተማሪዎች ከዛሬ ሐምሌ 1 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ሐምሌ 20 2018 ዓ.ም ድረስ ተመዝግበው መጨረስ አለባቸው።
2. በምዝገባ ወቅትንም የመስከረምን ክፍያና የዓመቱን የመመዝገቢያ ክፍያ መክፈል ይጠበቅባችኋል።
3. አዲስ ተማሪ ለማስመዝገብ የምትፈልጉ ነባር ወላጆች ባለን ክፍት ቦታ ላይ ለእናንተ ቅድሚያ ስለምንሰጥ ቦታው ከመያዙ በፊት ቀደም ብላችሁ መጣችሁ በማስመዝገብ በኋላ ላይ የሚፈጠረውን የቦታ እጥረት እንድታስወግዱ በአክብሮት እንጠይቃለን። በተለይ ጀማሪ ወይም ነርሰሪ ተማሪዎችን የምታስመዘግቡ ወላጆች ቀደም ብላችሁ በማስመዝገብ በየአመቱ የሚገጥመንን ችግር እንድንቀርፍ በአክብሮት እንጠይቃለን።
ማሳሰቢያ፡
1. ነባር ተማሪዎች ቀደም ሲል በምትከፍሉበት መለያ ቁጥር ተጠቅማችሁ ኦሮምያ ኢንተ. ባንክ በመክፈል የከፈላችሁበትንም ደረሰኝ ትምህርት ቤት ድረስ ይዛችሁ በመምጣት ተማሪዎችን ከአስመዘገባችሁ በኋላ የትምህርት ቤቱን ደረሰኝ መዉሰድ ይጠበቅባችኋል።
2. አዲስ ተማሪዎች የባንክ መክፈያ መለያ ቁጥር ስላልተሰጣቸው ክፍያውን የምትፈጽሙት በካሽ ለትምህርት ቤቱ መዝጋቢዎች ሲሆን ለከፈሉት ክፍያ ግን ከካሽ ሬጅስተር የወጣ ህጋዊ ደረሰኝ ወዲያውኑ ይቀበሉ።
1 286
የስድስተኛ ክፍል ተማሪዎች
የመጀመሪያ ስም የሚለው ላይ ስማችሁን መጻፍ ያለባችሁ በአማርኛ ነው እንግሊዘኛ ከሆነ ውጤቱን አያወጣላችሁም፡፡
1 286
ክፍል ተማሪዎች ወላጆች በሙሉ
የተፈተኑ ተማሪዎች ሁሉም በማለፋቸው በቅድሚያ እንኳን ደስ አላችሁ ማለት እንወዳለን።
ከተፈተኑት ሃምሳ ሁለት ተማሪዎች ውስጥ 24 ተማሪዎች ከ90 በላይ ውጤት አስመዝግበዋል። ውጤታቸውንም የሚከተለውን ማስፈንጠሪያ በመጠቀም ማየት ትችላላችሁ
1 286
Repost from Addis Ababa Education Bureau
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2018 የትምህርት ዘመን የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና ውጤት ነገ ጠዋት ይፋ ይሆናል፡፡
(ሰኔ 28/2018 ዓ.ም) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2018 የትምህርት ዘመን የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና ውጤት ነገ ጠዋት ይፋ ይደረጋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የ2018 የትምህርት ዘመንን የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና በአጭር ጊዜ አርሞ ይፋ ማድረጉ ተማሪዎች ለቀጣዩ የትምህርት አመት ከወዲሁ በቂ ዝግጅት እንዲያደርጉ የሚያስችል ነው፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2018 የትምህርት ዘመን የ6ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ከሰኔ 8 -10 /2018 ዓ.ም ድረስ በከተማ አስተዳደሩ በሚገኙ 199 የመፈተኛ ጣቢያዎች ለተከታታይ ሶስት ቀናት መሰጠቱ ይታወሳል፡፡
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://linktr.ee/aacaebc
1 286
ለወላጆች በሙሉ
በቅድሚያ እንኳን ለ 2018 ዓመተ ምህረት ትምህርት መጨረሻ ጊዜ በሰላም አደረሳችሁ። በመቀጠልም ሐሙስ ሰኔ 25 ቀን 2018 ዓመተ ምህረት ካርድ የሚሰጥ መሆኑን ማሳወቃችን ይታወሳል። በመሆኑም በእለቱ ከጠዋቱ ሁለት ሰዓት እስከ ቀኑ ዘጠኝ ድረስ በአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግቢ መገኘት የልጅዎን ሪፖርት ካርድ እንዲወስዱ በአክብሮት እንጠይቃለን።
ማሳሰቢያ
የትምህርት ቤት የሰርቪስ እና የጥናት ክፍያ ክፍለው ላልጨረሱ ተማሪዎች የሪፖርት ካርድ የማይሰጥ መሆኑን አውቃችሁ ያለባቸሁን ክፍያ ከወዲሁ ክፍላችሁ እንድታጠናቅቁ በአክብሮት እናሳስባለን።
