1 291
Suscriptores
-224 horas
-37 días
+130 días
Archivo de publicaciones
1 291
ለሰርቪስ ተጠቃሚዎች፡
እንደሚታወቀው ሰርቪሱ ለብዙ ሰዎች አገልግሎት ስለሚሰጥ የሁሉንም ሰው ፍላጎት ማሟላት አይችልም፡፡ ስለዚህ በተቀመጠው ጊዜ ገደብ ውስጥ ለመገኘት ቅድመ ዝግጅት አድርጉ፡፡
እንደ መጀመሪያ ጊዜ ጥቂት ሊዘገይ ወይም ሊፈጥን ከቻለ በትዕግስት እንድትጠብቁት እንጠይቃለን፡፡
1 291
ለትምህርት ቤቱ አዲስ ለሆኑ ተማሪዎች ወላጆች በሙሉ፡
· ነገ ትምህርት ሲጀመር ልጅዎን ትምህርት ቤት አስገብተው ሲመለሱ የተማሪውን መታወቂያ መቀበልን እንዳይዘናጉ፡፡
· ከሰዓት ተማሪው/ዋን ሊወስዱ ሲመጡ ይህንኑ መታወቂያ ይዘው ካልመጡ ተማሪውን የማንሰጥ መሆኑን ተገንዝበው ጥንቃቄ ያድርጉ፡፡
· ይህን መታወቂያ እንዳይጠፋ በጥንቃቄ መያዝ ያስፈልጋል፡፡
· መታወቂያውን ለሌላ ሰው አሲዘው ተማሪው/ዋን እንዲወስድ ከላኩ ትምህርት ቤት ባስመዘገቡት ስልክ ለትምህርት ቤቱ በመደወል ተማሪውን የሚወስደውን ሰው ስም እና ልዩ መገለጫ ለትምህርት ቤቱ አስተዳደር ማሳወቅ ያስፈልጋል፡፡
1 291
እንኳን ለ 2019 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በሰላም አደረሳችሁ እያልን የሚከተለውን መልዕክት እናስተላልፋለን፡
1. የዩኒፎርም ሹራብ ስለመጣ ከነገ ሰኞ መስከረም 4 ቀን 2019 ዓ.ም ጀምሮ በሚማሩበት ግቢ ውስጥ እየመጣችሁ ምግዛት ትችላላችሁ ፡፡
2. የትምህርት ቤቱ አስተዳደር በአካል ተገኝቶ ተማሪዎቹን መቀበል ስለሚፈልግ በየቅርንጫፉ ያሉትን ትምህርት ቤቶች በየተራ ይከፍታል፡፡በዚህም መሠረት
ሀ. ቁጥር አንድና ቁጥር 2 ወይም መካኒሳ አካባቢ የሚገኙትን ትምህርት ቤቶች ማክሰኞ መስከረም 5 ቀን 2019 ዓ.ም ይከፍታል
ለ. አዲሱን ቅርንጫፍ ማለትም ጀሞ ሚካኤል የሚገኘውን ቅርንጫፍ ረቡ ዕ መስከረም 6 ቀን 2019 ዓ.ም እንከፍታለን፡፡
መልካም የትምህርት ዘመን
1 291
ቅድመ ዝግጅት ለአፀደ ህፃናት ተማሪዎች
1. ደብተር እና እርሳስ ያላስገባችሁ ወላጆች እስከ ሰኞ ድረስ አጠናቃችሁ እንድታስገቡ፡፡ ማክሰኞ የተማሪ ቅበላ ቀን በመሆኑ ሌሎች አገልግሎቶችን አንሰጥም፡፡
2. ጀማሪ ተማሪዎች በመጀመሪያው ቀን ሊያስቸግሩ ስለሚችሉ የመምህራን ትኩረት ሙሉ በሙሉ በነሱ ላይ ይሆናል፡፡ ወላጆችን ይህንን ተገንዝባችሁ ልጆቻችሁን ለመምህራኖች ካስረከባችሁ በኋላ በትምህርት ቤት ግቢ ውስጥ መቆየት አይቻልም፡፡ ህፃናት ወላጆቻቸውን ሲያዩ ያስቸግራሉ፡፡ ኃላፊነቱን ለእኛ ስለሰጣችሁ እኛም በፍጹም ሃላፊነት ልጆቹን ስለምንከባከብ ወደ ቤታችሁ መመለስ ይጠበቅባቸኃል፡፡ በእለቱ ምንም አይነት ወላጅ በትምህርት ቤት ግቢ ውስጥ እንዲቆይ አይፈቅድ ም፡፡ ከአቅም በላይ የሆነ ችግር ካለ( ካልተረጋጉ) በስልክ ደውለን እናሳውቃለን፡፡
3. በተማሪዎች ቦርሳና ምሳ ዕቃ ላይ አስቀድማችሁ ስማቸውን ጻፉላቸው፡፡ በዩኒፎርም ሹራባቸውም ላይ ስማቸውን በክር በውስጥ በኩል ምልክት አድርጉላቸው፡፡
4. አስተማሪዎቻቸው የትምህርት ቤት እናቶቻቸው እንደሆኑ እና እንዳይፈሯቸው ምክር ለገሷቸው ሲመጡ ደግሞ እኛ በተግባር እናሳያቸዋለን፡፡
5. ከሁሉም በላይ ደግሞ አደራ የምንላችሁ ከአቅማቸው በላይ የሆነ ምግብ አሲዛችሁ እንዳትልኳቸው ነው፡፡ ገና በመጀመሪያዎቹ ሳምንታት ከመምህራኖቻቸው ጋር በምግብ የሚጨቃጨቁ ከሆነ ግንኙነታቸው የተበላሸ ይሆናል፡፡ እሺ ያሉትን ያህል ብቻ ነው አብልተን የምንልካቸው ፡፡የመጀመሪያዎቹ ሳምንታት ልጆቹን ትምህርት ቤት ማለመድ ስለሆነ ከአላስፈላጊ ጭቅጭቅ እና ቁጣ ነጻ ማድረግ ያስፈልጋል፡፡ አመጋገብ ላይ ችግር ካለ በሂደት የምናየው እና የሚስተካከል ይሆናል፡፡ በአጸደ ህጻናት ውስጥ የመጀመሪያ ሳምንት በጣም አስቸጋሪ ነው ስለዚህ ወላጆች መምህራኖቻቸው የሚሏችሁን በመስማት ፣ስህተት እንኳን ቢኖር በትግስት በማለፍ ልታግዛዋቸው ይገባል፡፡
መልካም ጊዜ
1 291
ትምህርት የሚጀመረው
ማክሰኞ መስከረም 5 ቀን 2019 ዓ.ም ነው፡፡
። ከማክሰኞ እስከ አርብ ድረስ ትምህርት የሚኖረው ለግማሽ ቀን ማለትም እስከ 6፡30 ብቻ ነው፡፡
። በእነዚህ ቀናቶች ተማሪዎች ቁርስ ብቻ ይዘው ይምጡ፡፡
። የትምህርት መሣሪያዎቻቸውንና የደንብ ልብሳቸውን አሟልተው መምጣት አለባቸው፡፡
፡፡ ከሰኞ መስከረም 11 ቀን ጀምሮ ትምህርት ለሙሉ ቀን ይሰጣል፤እስከ 9፡15 ይቆያሉ፡፡
1 291
ለተማሪዎቻችን እና ለቤተሰቦቻቸው በሙሉ፡
እንኳን ለ 2019 ዓመተ ምህረት ትምህርት ዘመን በሰላምና በጤና አደረሳችሁ፡፡ አዲሱን ዓመት የሰላም የፍቅር እና የደስታ ያድርግልን፡፡ በአዲሱ አመት ተማሪዎቻችን ፣ ወላጆቻቸው ፣ መምህራንና ሠራተኞቻችን በሙሉ በሰላም ወተው በሰላም እንዲመለሱ ፣ከመካከላችን አንድም ሰው ሳይጎድል ዓመቱን እንዲያስጨርሰን ሮበስት አካዳሚ አጥብቆ ይመኛል፡፡ ለዚህም መሳካት ይረዳ ዘንድ ሁላችሁም የትምህርት ቤቱ አካላት በያላችሁበት በየሃይማኖታቸሁ በፀሎት እንድታግዙት ሮበስት አጥብቆ ይጠይቃል፡፡
መልካም አዲስ አመት
1 291
ለወላጆች እና ተማሪዎች በሙሉ
በመጀመሪያ እንኳን ለ 2019 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በሰላም አደረሳችሁ እንላለን፡፡ በመቀጠልም የሚከተሉትን መልዕክቶች እናስተላልፋለን፡
1. ሰርቪስ ተጠቃሚ የሆናችሁ የቁጥር1 እና ቁጥር 2 ወላጆች ( መካኒሳ አካባቢ)፡
* ከነገ ሰኞ ጳጉሜ 2 ጀምሮ እስከ ሐሙስ ጳጉሜ አምስት ቀን 2019 ዓ.ም ድረስ ከአንደኛ እስከ ስምንተኛ ክፍል ያሉ ተማሪዎች በሚማሩበት ግቢ እየሄዳችሁ እንድትመዘገቡ እናሳስባለን፡፡
1. ዘሪሁን፡ 093761451
2. ጆኒ….. 0911439452
2. ሁላችሁም የፀደ ህጻናትና የአንደኛ እና መካከለኛ ደረጃ ተማሪ ወላጆች ( መካኒሳ አካባቢ ) የመማሪያ መጽሐፍት ለሌላችሁ ለይተን መግዛት እንድንችል ክፍያ ከአንደኛ እስከ ስምንተኛ ክፍል በሚማሩበት ግቢ ሄዳ ችሁ ቀጥሎ በተላከው የዋጋ ሰንጠረዥ መሰረት እስከ ሀሙስ ድረስ እንድትከፍሉ እሳስባለን፡፡
ለተጨማሪ መረጃ፡
ዘሪሁን፡ 093761451
1 291
ለወላጆች በሙሉ
በቅድሚያ እንደምን ሰነበታችሁ፡፡ በመቀጠልም የሚከተለውን መልዕክት እናስተላልፋለን።
1. ነገ ቅዳሜ ነሐሴ 9 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡30 እስከ ቀኑ 6፡30 ፣ ከሰዓት በኋላ ከ8፡00 - 11፡00 ድረስ
2. ከሰኞ ሴ 11 ቀን እስከ አርብ ነሐሴ 18 ቀን 2018 አመተ ምህረት ድረስ ደግሞ ሁለት ሰአት ተኩል እስከ ቀኑ አስር ሰአት ተኩል ድረስ ከምሳ ሰዓት ውጪ የዩኒፎርም ሹራብ የሚሸጡት ሰዎች ትምህርት ቤት ስለሚገኙ እንድትገዙ መልዕክት ማስተላለፍ እንወዳለን።
