fa
Feedback
ASTUECSF official

ASTUECSF official

رفتن به کانال در Telegram

ዓመታዊ መሪ ቃል: እግዚአብሔርን መፈለግ  በመመለስ  I በፅድቅ ኑሮ  I በመታመን Adama Science & Technology University Evangelical Christian Students Fellowship Official  Telegram channel contact us: @ASTUECSF_inbox CBE:1000696321179 Bethelhem & Lidiya &or Aklilu Telebirr:0950267178

نمایش بیشتر
2 807
مشترکین
-124 ساعت
+97 روز
+230 روز
آرشیو پست ها
የሱሪ ህዝብ ክፍል 💥ሱርማ ወይም ሱሪ በመባል የሚታወቁት ሕዝቦች የሚኖሩት በኢትዮጵያ ደቡብ ምዕራብ ዳርቻ አካባቢ ነው። በእነዚህ ሕዝቦች መካከል የሚስዮን አገልግሎት የተጀመረው በ1970ዎቹ መጀመሪ
የሱሪ ህዝብ ክፍል 💥ሱርማ ወይም ሱሪ በመባል የሚታወቁት ሕዝቦች የሚኖሩት በኢትዮጵያ ደቡብ ምዕራብ ዳርቻ አካባቢ ነው። በእነዚህ ሕዝቦች መካከል የሚስዮን አገልግሎት የተጀመረው በ1970ዎቹ መጀመሪያ አካባቢ ነበር። ሆኖም ግን፣ በተለያዩ ውጫዊ ተጽዕኖዎች ምክንያት አገልግሎቱ ለጥቂት ዓመታት ብቻ ቆይቶ ሊቋረጥ ችሏል። የፀሎት ርዕሶች 👉የሱሪ ህዝብ ኢየሱስ ክርስቶስን እንዲያውቁና በእርሱ ከዘላለም ጥፋት እንዲያመልጡ እንጸልይ! 👉ወደዛ አከባቢ የሚላኩ የወንጌል ሰራተኞች እግዚአብሄር እንዲያብዛ እንጸልይ! 👉በዛ አከባቢ ያሉት ጥቂት ደቀመዝሙራት ለሌሎች ይህን ብርሃን እንዲገልጡ እንፀልይ!

https://youtu.be/mHNfvZDlYE8?si=_7-R02m5xIQQJQMr Out now! #astu_ecsf #digital_strategy #lad

📣 Our final drop hits thursday, stay tuned!
https://youtu.be/mHNfvZDlYE8?si=EGFd05caA9E5gVXw
Who is excited, drop🔥 INSTAGRAM | YOUTUBE | TIKTOK #astu_ecsf #digital_strategy #LAD

ለቱርካና የሕዝብ ክፍል 💥የቱርካና ሕዝቦች የሚኖሩባቸውን ቤቶች የሚገነቡት ከእንጨት በተሠሩ የዶሜድ ቡቃያዎች (ፍሬሞች) ላይ የዶም ፓልም ዛፍ ‘ሃይፋኔን ቴባይካ’፣ ቆዳ ወይም ሌጦ እና ሳር በማልበ
ለቱርካና የሕዝብ ክፍል 💥የቱርካና ሕዝቦች የሚኖሩባቸውን ቤቶች የሚገነቡት ከእንጨት በተሠሩ የዶሜድ ቡቃያዎች (ፍሬሞች) ላይ  የዶም ፓልም ዛፍ ‘ሃይፋኔን ቴባይካ’፣ ቆዳ ወይም ሌጦ እና ሳር በማልበስ ነው። ቤቶቻቸው በአማካኝ ስድስት የቤተሰብ አባላትን ለማኖር በቂ እንዲሆኑ ተደርገው ይሰራሉ። ብዙውን ጊዜ በእርጥበት ወቅት ፍሬሞቹ ረዣዥም ይደረጉ እና በጭቃዎች ይሸፈናሉ። በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት አብዛኛው ቱርካና ማህበረሰብ ክፍሎች ከባህላዊ የከብት እርባታ ወደ ዘመናዊ አርብቶ አደርነት ለመቀየር ተገደዋል። የማህበረሰብ አለቃዎች ወይም ሽማግሌዎች የሏቸውም። የፖለቲካ ተጽእኖ ማሳደር የሚችሉት እድሜ፣ ሀብት፣ ጥበብ እና የንግግር ችሎታ ያላቸው  ግለሰቦች እንደሆኡ ይነገራሉ። ጋብቻ ወይም ትዳር መመስረት  በቱርካና ሕዝብ ማካከል ትልቅ ቦታ የሚሰጠው ነው፤ ከግዜያት ወዲህ ግን ባልተለመደ መልኩ በጨመረው  ከፍተኛ የጥሎሽ ይዘት ምክንያት አንድ ወንድ አባቱ ሞቶ የእንስሳት እርባታውን እስኪወርስ ድረስ ማግባት ፈጽሞ የማይቻል ነገር እየሆነ መጥቷል።   የጸሎት ርዕሶች 👉በቱርካና ህዝብ መሃል ያሉ አንዳንድ እግዚአብሔር የማይከብርባቸው ባህሎች ከዚህ ሕዝብ ክፍል እንዲወገዱ አጥብቀን እንጸልይ! 👉ቱርካና ጎሳ መካከል ያሉ ጥቂት የኢየሱስ ተከታዮች ለጌታ እየዘመሩ እና እያዜሙ የተቀደሰ ህይወት እንዲኖሩ እንጸልይ! 👉ለቱርካና ህዝብ በመንፈስ የተሞሉ ብርቱ የወንጌል ሰራተኞች እንዲላኩ  እግዚአብሔርን እየለመንን እንጸልይ!

ለህብረታችን ምሩቃን በሙሉ ... 📌 ሰላም የተወደዳችሁ የህብረታችን የምሩቃን የASTUECSF Graduates ቴሌግራም ግሩፕ join በማድረግ ከ ምሩቃን (graduates) ጋር በተያያዘ የሚለቀቁ መረጃዎችን ማግኘት ትችላላችሁ። https://t.me/astuecsf_graduates

ቁጥር 17-18. ጳውሎስ የሚሰብከው ከሕግ ነፃ የሆነ ወንጌል አንድ ጥያቄን ሊያስነሳ እንደሚችል በማወቅ አስቀድሞ መልስ ሰጥትበታል።ጥያቄውም: ወንጌል ከሕግ ባርነት ሰውን ነፃ የሚያወጣ ከሆነ ሰው ሀጥያትን እንዲያደርግ ፈቃድን አይሰጥም?፣ እኛስ በክርስቶስ የምናምን ሀጥያተኛ ሆነን ከተገኘን ክርስቶስ የሀጥያት አገልጋይ ነው? አይደለም።  ቁጥር 19-20. ጳውልስ እንዲህ በማለት መልስ ይሰጣል።ከክርስቶስ ጋር ተሰቂያለው፣እኔም አሁን ህያው ሆኜ አልኖርም ክርስቶስ ግን በእኔ ይኖራል፣አሁንም በስጋ የምኖርበት ኑሮ በወደደኝ እና ስለእኔ ራሱን በሰጠው በእግዚአብሔር ልጅ ላይ ባለእምነት የምኖረው ነው። ->ከክርስቶስ ጋር ተሰቅያለው ሲል አሮጌውን ማንነት፣የስጋን ሀሳብ እና ፈቃድ በመስቀል ገድያለው ማለቱ ሲሆን(ኤፌ 4:22) አሁን የምኖረው ሕይወት ደግሞ ስለወደደኝ እና ስለእኔ እራሱን በሰጠ በክርስቶስ ባለእምነት ነው በማለት ይመልሳል።  ቁጥር 21. ጽድቅ በሕግ በኩል ቢሆን የክርስቶስ መሞት ከንቱ ነበር ማለት ነው።ነገር ግን ጽድቅ የሚገኘው በክርስቶስ በኩል ብቻ ነው። #summer_bs #galatians #astu_ecsf #digital_strategy

ምዕራፍ 2:11-21 ጳውሎስ ጴጥሮስን ተቃወመ ቁጥር 11-12. አንጾኪያ በሶርያ ውስጥ የምትገኝ ከእየሩሳሌም 480KM ርቀት በስተ ሰሜን የምትገኝ ከተማ ናት።በአንጾኪያ ብዙ አህዛብ የሚገኙ ሲሆን ብ
ምዕራፍ 2:11-21 ጳውሎስ ጴጥሮስን ተቃወመ     ቁጥር 11-12. አንጾኪያ በሶርያ ውስጥ የምትገኝ ከእየሩሳሌም 480KM ርቀት በስተ ሰሜን የምትገኝ ከተማ ናት።በአንጾኪያ ብዙ አህዛብ የሚገኙ ሲሆን ብዙ የወንጌል ሰባኪዎች ከአንጾኪያ ወደተለያዩ አህዛብ የሚገኙባቸው ስፍራዎች ይላኩ ነበር (ሐዋ 13:1-3)።   -> በሐዋርያት ስራ 10(10:28) እግዚኣብሔር ጴጥሮስን ከአህዛብ ጋር ሕብረት ማድረግን ካስተማረው በኃላ ጴጥሮስ ከአህዛብ ጋር ማዕድ ይቆርስ ነበር።ነገር ግን አይሁድ የሆኑ የሐዋርያው ያዕቆብ ተከታዮች ወደ እርሱ በመጡ ጊዜ እነርሱን በመፍራት ከአህዛብ ጋር ለማዕድ አንድ ላይ መቀመጥ አቆመ።    • እግዚኣብሔር ለአይሁድ የሰጠው የአመጋገብ ሕግ (dietary laws) /ዘሌዋውያን 11/ ስላለ አህዛብ ደግሞ ይሄን ሕግ ይከተሉ ስላልነበር በአይሁዶች ዘንድ ከአህዛብ ጋር ለማዕድ መቀመጥ እንደ ሀጥያት ይቆጠር ነበር። ቁጥር 13. ይሄ የጴጥሮስ ድርጊት ብዙ አይሁዶችን በርናባስን ጨምሮ ወደ ስህተት መንገድ መርትዋል።  ቁጥር 14. ጳውሎስ ይሄን ድርጊታቸውን ባስተዋለ ጊዜ ጴጥሮስን በሁሉ ፊት ተቃወመ።  ቁጥር 15. በአይሁዶች ዘንድ በሕጉ ስር የማይኖር ማንኛውም ሰው ሀጥያተኛ ነው።አህዛብ የሕጉ ተቀባይ ባለመሆናቸው(በሕጉ ስለማይኖሩ) በአይሁድ ዘንድ እንደ ሀጥያተኛ ይታያሉ።  ቁጥር 16. ሰው በእግዚኣብሔር ፊት የሚጸድቀው በክርስቶስ በማመን ብቻ ነው።በሕግ ስራ በእግዚኣብሔር ፊት ጸድቆ ለመታየት መሞከር በራስ ስራ በእግዚኣብሔር ፊት ልክ ሆኖ ለመታየት መሞከር ነው።የእኛ ስራ የእኛን ሀጥያት እንጂ የእኛን ጽድቅ ሊያሳዩ አይችሉም።ይልቁኑ ሰው ሊጸድቅ የሚችለው እኛ በእግዚኣብሔር ፊት እንጸድቅ ዘንድ ስለ እኛ ሀጥያት በሆነው በክርስቶስ በማመን ነው(2ቆሮ 5:21)።

ቁጥር 17-18. ጳውሎስ የሚሰብከው ከሕግ ነፃ የሆነ ወንጌል አንድ ጥያቄን ሊያስነሳ እንደሚችል በማወቅ አስቀድሞ መልስ ሰጥትበታል።ጥያቄውም: ወንጌል ከሕግ ባርነት ሰውን ነፃ የሚያወጣ ከሆነ ሰው ሀጥያትን እንዲያደርግ ፈቃድን አይሰጥም?፣ እኛስ በክርስቶስ የምናምን ሀጥያተኛ ሆነን ከተገኘን ክርስቶስ የሀጥያት አገልጋይ ነው? አይደለም።  ቁጥር 19-20. ጳውልስ እንዲህ በማለት መልስ ይሰጣል።ከክርስቶስ ጋር ተሰቂያለው፣እኔም አሁን ህያው ሆኜ አልኖርም ክርስቶስ ግን በእኔ ይኖራል፣አሁንም በስጋ የምኖርበት ኑሮ በወደደኝ እና ስለእኔ ራሱን በሰጠው በእግዚአብሔር ልጅ ላይ ባለእምነት የምኖረው ነው። ->ከክርስቶስ ጋር ተሰቅያለው ሲል አሮጌውን ማንነት፣የስጋን ሀሳብ እና ፈቃድ በመስቀል ገድያለው ማለቱ ሲሆን(ኤፌ 4:22) አሁን የምኖረው ሕይወት ደግሞ ስለወደደኝ እና ስለእኔ እራሱን በሰጠ በክርስቶስ ባለእምነት ነው በማለት ይመልሳል።  ቁጥር 21. ጽድቅ በሕግ በኩል ቢሆን የክርስቶስ መሞት ከንቱ ነበር ማለት ነው።ነገር ግን ጽድቅ የሚገኘው በክርስቶስ በኩል ብቻ ነው። #summer_bs #galatians #astu_ecsf #digital_strategy

ምዕራፍ 2:11-21 ጳውሎስ ጴጥሮስን ተቃወመ ቁጥር 11-12. አንጾኪያ በሶርያ ውስጥ የምትገኝ ከእየሩሳሌም 480KM ርቀት በስተ ሰሜን የምትገኝ ከተማ ናት።በአንጾኪያ ብዙ አህዛብ የሚገኙ ሲሆን ብ
ምዕራፍ 2:11-21   ጳውሎስ ጴጥሮስን ተቃወመ     ቁጥር 11-12. አንጾኪያ በሶርያ ውስጥ የምትገኝ ከእየሩሳሌም 480KM ርቀት በስተ ሰሜን የምትገኝ ከተማ ናት።በአንጾኪያ ብዙ አህዛብ የሚገኙ ሲሆን ብዙ የወንጌል ሰባኪዎች ከአንጾኪያ ወደተለያዩ አህዛብ የሚገኙባቸው ስፍራዎች ይላኩ ነበር (ሐዋ 13:1-3)።   -> በሐዋርያት ስራ 10(10:28) እግዚኣብሔር ጴጥሮስን ከአህዛብ ጋር ሕብረት ማድረግን ካስተማረው በኃላ ጴጥሮስ ከአህዛብ ጋር ማዕድ ይቆርስ ነበር።ነገር ግን አይሁድ የሆኑ የሐዋርያው ያዕቆብ ተከታዮች ወደ እርሱ በመጡ ጊዜ እነርሱን በመፍራት ከአህዛብ ጋር ለማዕድ አንድ ላይ መቀመጥ አቆመ።    • እግዚኣብሔር ለአይሁድ የሰጠው የአመጋገብ ሕግ (dietary laws) /ዘሌዋውያን 11/ ስላለ አህዛብ ደግሞ ይሄን ሕግ ይከተሉ ስላልነበር በአይሁዶች ዘንድ ከአህዛብ ጋር ለማዕድ መቀመጥ እንደ ሀጥያት ይቆጠር ነበር። ቁጥር 13. ይሄ የጴጥሮስ ድርጊት ብዙ አይሁዶችን በርናባስን ጨምሮ ወደ ስህተት መንገድ መርትዋል።  ቁጥር 14. ጳውሎስ ይሄን ድርጊታቸውን ባስተዋለ ጊዜ ጴጥሮስን በሁሉ ፊት ተቃወመ።  ቁጥር 15. በአይሁዶች ዘንድ በሕጉ ስር የማይኖር ማንኛውም ሰው ሀጥያተኛ ነው።አህዛብ የሕጉ ተቀባይ ባለመሆናቸው(በሕጉ ስለማይኖሩ) በአይሁድ ዘንድ እንደ ሀጥያተኛ ይታያሉ።  ቁጥር 16. ሰው በእግዚኣብሔር ፊት የሚጸድቀው በክርስቶስ በማመን ብቻ ነው።በሕግ ስራ በእግዚኣብሔር ፊት ጸድቆ ለመታየት መሞከር በራስ ስራ በእግዚኣብሔር ፊት ልክ ሆኖ ለመታየት መሞከር ነው።የእኛ ስራ የእኛን ሀጥያት እንጂ የእኛን ጽድቅ ሊያሳዩ አይችሉም።ይልቁኑ ሰው ሊጸድቅ የሚችለው እኛ በእግዚኣብሔር ፊት እንጸድቅ ዘንድ ስለ እኛ ሀጥያት በሆነው በክርስቶስ በማመን ነው(2ቆሮ 5:21)።

ወለኔ የሕዝብ ክፍል 💥የወላኔ ተወላጆች ከአዲስ አበባ በስተደቡብ 160 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በሰሜን ምስራቅ ጉራጌ ክልል ቀቤናን፣ ኦሮሞ እና ሙር ህዝቦች አቅራቢያ ይኖራሉ። አብዛኞች ግን አዲስ አ
ወለኔ የሕዝብ ክፍል 💥የወላኔ ተወላጆች ከአዲስ አበባ በስተደቡብ 160 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በሰሜን ምስራቅ ጉራጌ ክልል ቀቤናን፣ ኦሮሞ እና ሙር ህዝቦች አቅራቢያ ይኖራሉ። አብዛኞች ግን አዲስ አበባ አከባቢ በንግድ ስራ ላይ ተሰማርተው ይኖራሉ። አዲስ አበባ የሚኖሩት ወለኔዎች በመርካቶ ነጋዴ ሆነው ኑሯቸውን የሚመሩ ናቸው ። በጉራጌ ክልል የሚኖሩ ግን በግብርና እና አርብቶ አደሮች ናቸው። እንፀልይ 👉  የወለኔ ሕዝብ  በእግዚአብሔር ዘላለማዊ አጀንዳ እንደታሰቡ እንዲያውቁ እና ፍቅሩን ማየት ይችሉ ዘንድ ወደ እግዚአብሔር ፊት እያቀረብን   እንጸልይ። 👉 የወለኔን ማህበረሰብ ትኩረት አድርጎ የሚሰራ ቤተ-ክርስትያን ወይንም ሰራተኞች መኖራቸውን የሚጠቁም  ምንም አይነት መረጃ  የለም፣ በእግዚአብሔር ሓይል እና መንፈስ የተሞሉ፣ ብርቱ ሰራተኞችን እግዚአብሔር እንዲልክ እንጸልይ። 👉 የወለኔ ሕዝብን በመጨረሻው የሰማይ ጉባዬ ለታረደው በግ በቋንቋቸውና ባህላቸው ክብር ሲያመጡለት እናይ ዘንድ እንማልድ!

⚠️⚠️⚠️⚠️⚠️⚠️⚠️⚠️⚠️⚠️⚠️⚠️⚠️⚠️ This drama is out now make sure to check it! 🔗here is the link: https://youtu.be/MbP3UDyjFVo?si=p4fkJ2VLLZHWxe6q #astu_ecsf #digital_strategy

ቁጥር 6. "አለቆች" የሚለው በእየሩሳሌም የሚገኙ ሐዋርያትን ሲሆን ምንም ታላቅ ሐዋርያት ቢሆኑም ጳውሎስ ከሰው ሀሳብ ይልቅ የእግዚአብሔርን ሀሳብ ያስቀድም ነበር።እነርሱም ጳውሎስ ይህን ወንጌል እንደተቀበለ ስላወቁ በጳውሎስ ትምህርት ላይ አንድም ነገር አልጨመሩም። ቁጥር 7-8. ጴጥሮስ የአይሁድ ሐዋርያ በመሆን ሲታወቅ፣ጳውሎስ የአህዛብ ሐዋርያ በመሆን ይታወቃል።የጴጥሮስና የጳውሎስ አገልግሎት እኩል ሲሆን አንዱ ለአይሁድ፣አንዱ ለአህዛብ የተሾመ ነበር። ቁጥር 9-10. ይህን አገልግሎት በመረዳት አዕማድ የሆኑት ሐዋርያት ለጳውልስና ለበርናባስ ቀኝ እጃቸውን ሰጥተዋል። • ኬፋ የጴጥሮስ አረማይክ ስም፣ጴጥሮስ ደግሞ በግሪክ ሲሆን ትርጉሙም ዓለት ማለት ነው።

ምዕራፍ 2 2፥1-10 ጳውሎስን ሐዋርያት ተቀበሉት በምዕራፍ 1 ጳውሎስ ሐዋሪያነቱንና ወንጌልን በቀጥታ ከእግዚአብሔር እንደተቀበለ አስታውቆ ነበር።በዚህ ምዕራፍ ሐዋርያነቱና ለሚሰብከው ወንጌል (ለአህ
ምዕራፍ 2 2፥1-10 ጳውሎስን ሐዋርያት ተቀበሉት በምዕራፍ 1 ጳውሎስ ሐዋሪያነቱንና ወንጌልን በቀጥታ ከእግዚአብሔር እንደተቀበለ አስታውቆ ነበር።በዚህ ምዕራፍ ሐዋርያነቱና ለሚሰብከው ወንጌል (ለአህዛብ ወንጌልን መስበክ) ትክክለኝነት አዕማድ ከሆኑት በእየሩሳሌም ከሚገኙ ሐዋርያት (ያዕቆብ፣ኬፋ፣ዮሐንስ) ጭምር ማረጋገጫ እንዳገኘ ይጠቅሳል። ጳውሎስ እነዚህን ማብራሪያዎች መስጠቱ አስፈላጊ የነበረበት ምክንያት ወደ ገላትያ የገቡት ሐሰተኛ አስተማሪዎች የጳውሎስ ሹመትና ስብከት ላይ በሰዎች ዘንድ ጥያቄ እንዲነሳ በማድረጋቸው ምክንያት ነው። በዚህ ክፍል የተጠቀሰው የእየሩሳሌም ስብሰባ በሐዋ 15 የተጠቀሰው የእየሩሳሌም ስብሰባ እንደሆነ ይገመታል። በዚህ የእየሩሳሌም ጉባኤ ሐዋርያት በእየሩሳሌም ተሰብስበው ተወያይተው አህዛብ ይድኑ ዘንድ እና ወደ ኪዳን ሕዝብ ይቀላቀሉ ዘንድ ሕጉን ሊጠብቁና ሊገረዙ ይገባል ለሚለው የስህተት ትምህርት ሰው ሊድን የሚችለው በእግዚአብሔር ልጅ በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን ብቻ እንደሆነ መልስ ሰጥተዋል። ቁጥር 1. በሶሪያና በኪልቅያ 14 ዓመት ከቆየ በኃላ ጳውሎስ አብረውት ከሚያገለግሉት ከበርናባስና ከቲቶ ጋር ወደ እየሩሳሌም ተመለሱ። • በርናባስ በአንደኛውና ሁለተኛው የወንጌል ጉዞ ከጳውሎስ ጋር አብሮ ተጉዝዋል።በርናባስ ጳውሎስ በእየሩሳሌም ከሚገኙ ሐዋርያት ተቀባይነት እንዳገኘ የተመለከተ ምስክር ነው። • ቲቶ ግሪካዊ ሲሆን ከጳውልስ ጋር አብሮ አገልጋይ ነው። ቁጥር 2. ጳውሎስ ለአህዛብ የሚሰብከውን ወንጌል ትክክለኝነት ማረጋገጫ ያገኝ ዘንድ በእየሩሳሌሜ ለሚገኙ ሐዋርያት ትምህርቱን አስታወቃቸው። ቁጥር 3. በእየሩሳሌም የሚገኙ ሐዋርያት አብሮት የነበረውን አህዛብ የሆነውን ቲቶን እንዲገረዝ አላስገደዱትም ነበር።

📣ይህ ሚገርም ድራማ ነገ ከቀኑ 6:00ላይ በyoutube ቻናላችን ይለቀቃል፤ሁላችሁም ማየት እንዳትረሱ። ተባረኩ! #astu_ecsf #digital_strategy
📣ይህ ሚገርም ድራማ ነገ ከቀኑ 6:00ላይ በyoutube ቻናላችን ይለቀቃል፤ሁላችሁም ማየት እንዳትረሱ። ተባረኩ! #astu_ecsf #digital_strategy

የአርቦሬ ህዝብ 💥የአርቦሬ ህዝቦች በደቡብ ኢትዮጵያ የሚኖሩ ሲሆን፣ ኑሯቸውንም በከብት፣ ፍየልና በግ እርባታ እንዲሁም ከሌሎች ጎረቤት ብሄረሰቦች ጋር የንግድ ልውውጥ በማድረግ የሚመሩ ንቁ ማህበረሰ
የአርቦሬ ህዝብ 💥የአርቦሬ ህዝቦች በደቡብ ኢትዮጵያ የሚኖሩ ሲሆን፣ ኑሯቸውንም በከብት፣ ፍየልና በግ እርባታ እንዲሁም ከሌሎች ጎረቤት ብሄረሰቦች ጋር የንግድ ልውውጥ በማድረግ የሚመሩ ንቁ ማህበረሰቦች ናቸው። አብዛኛዎቹ እስልምናን እና ከዛም የጠነከረውን የራሳቸውን ባህላዊ እምነት አቀላቅለው የሚከተሉ ሲሆን፣ «ዋቅ» ብለው በሚጠሩት ፈጣሪ ያምናሉ፤ አሉታዊ መንፈስንም በዘፈን እና በጭፈራ ማስወገድ እንደሚችሉ ያስባሉ። በኢየሱስ ክርስቶስ ብቻ የሚገኘውን የተትረፈረፈ ህይወት እና እውነተኛውን የህይወት ብርሃንም ስለማያውቁ ወንጌል በእጅጉ ያስፈልጋቸዋል። እንፀልይ 👉 የአርቦሬ ህዝቦች ጌታ ኢየሱስን እንዲያውቁ ልባቸው እንዲከፈት እግዚአብሄር እንዲረዳችው እንፀልይ! 👉ወደዛ አከባቢ የሚሄዱ የወንጌል ሰራተኞችን እግዚአብሔር እንዲያስነሳ እንፀልይ!

📌Internship የምትወጡ የህብረታችን አባላት . . . ሰላም ዉድ የሕብረታችን ተማሪዎች በዚህ ክረምት internship የምንወጣ ሁላችን ከ intern ብር የፍቅር ስጦታ ለህብረታችን እንድትሰጡ በጌታ ፍቅር ልናሳስባችሁ እንወዳለን። 👉ለመስጠትና ሕብረቱን ለመደገፍ ይህን አካውንት ይጠቀሙ  CBE:1000696321179 Bethelhem & Lidiya &or Aklilu telebirr:0950267178 ✨ይህንንም ስለምታደርጉ እግዚአብሔር ይባርካችሁ! #ASTUECSF

📣Out now! https://youtu.be/Wcu_W_9nx8k?si=m4TDZQYP6h2wTj4V #astu_ecsf #digital_strategy

ቁጥር 18. ጳውሎስ ሕይወት ለውጥ ካገኘ ከሶስት ዓመታት በኋላ ከጴጥሮስ ጋር ተገናኘ። ይህንም ያደረገው የሐዋርያነትን ስልጣን ለመቀበል ወይም ለመማር አልነበረም። ከላይ እንደተገለጸው በስደቱ ምክንያት እና ጴጥሮስን ለመጠየቅና ለመተዋወቅ እንጂ(ሐዋ.9፥26-30)። ቁጥር 19. ጳውሎስ ሌሎቹን የኢየሩሳሌም ሐዋርያት (የአስቆሮቱን ይሁዳ ሳይጨምር)  እንዳላየ ይናገራል። በዚህ ክፍል የተጠቀሰው ያዕቆብ ምናልባት የእልፍዮስ ልጅ ነው ተብሎ ይገመታል። እልፊዮስ ከማርያም እህት ያዕቆብን ወልዷል። በስጋ ዝምድና የጌታችን የአክስት ልጅ ስለሆነ የጌታ ወንድም ተብሏል። ያዕቆብ በኢየሩሳሌም ቤተክርስቲያን ዋና መሪ ነበር (ሐዋ.21፥18) ። በዚህ ስፍራ ጳውሎስ እንደሚለው ከሆነ በኢየሩሳሌም ጉዞው ያገኘው ጴጥሮስን እና ያዕቆብን ብቻ ነበር። ቁጥር 20. የመሃላ አነጋገር ነው ። ጳውሎስ ስለ ራሱ የሚናገረው መሉ በሙሉ እውነት እንደሆነ የእግዚአብሔርን ስም ጠርቶ ያረጋግጥላቸዋል። ቁጥር 21-24.  ጳውሎስ በኢየሩሳሌም የቆየው ለ15 ቀናት ብቻ ነበር።በይሁዳ ዙሪያ ባሉት አካባቢዎች አልሰበከም።ነገር ግን ይህን አካባቢ ትቶ ከአይሁድ ወገን ውጪ ለሆኑት ለመስበክ ወደ ሶሪያና ኪልቅያ ሄደ። በደቡባዊው የእስራኤል ክፍል በይሁዳ ያሉ አብያተክርስቲያናት ጳውሎስን በአሳዳድነቱ ነበር የሚያስታውሱት። የይሁዳ ማህበሮች የሚላቸው የአይሁድን ሃይማኖት ትተው የክርስቶስን ወንጌል የሚከተሉትን ነው። ስለ ክፉ ስራው በሙሉ ሰምተው ነበር ።ጳውሎስ በይሁዳ ወንጌልን ባለመስበኩ የይሁዳ ክርስቲያኖች የተለወጠውን ጳውሎስ የማየት አጋጣሚ አልነበራቸውም ። ሆኖም ግን በሶሪያ እና ኪልቅያ የሰበከውን ስለ ሰሙ ስለ እርሱ እግዚአብሔርን ያመሰግኑ ነበር።

ቁጥር 15-17. ጳውሎስ ከመወለዱ በፊት ሐዋርያው እንዲሆንለት እግዚአብሔር መርጦት ነበር ።በዚህ ስፍራ ጳውሎስ በጸጋው የጠራኝ ይላል (2ቆሮ.15፥9-10)። ጥሪ መሠረት የሚያረገው የሰውን ስራ ወይ
ቁጥር 15-17. ጳውሎስ ከመወለዱ በፊት ሐዋርያው እንዲሆንለት እግዚአብሔር መርጦት ነበር ።በዚህ ስፍራ ጳውሎስ በጸጋው የጠራኝ ይላል (2ቆሮ.15፥9-10)። ጥሪ መሠረት የሚያረገው የሰውን ስራ ወይም ጠቃሚነት ሳይሆን የእግዚአብሔርን ቅድመ እይታ እና እቅድ ነው ። ስለዚህም አስቀድሞ የመጣው የእግዚአብሔር ነው ማለት ነው ።የእግዚአብሔር ጥሪ በጸጋውና በጎ ፈቃዱ ላይ እንጂ በሰው በጎነት ወይም ፍላጎት ላይ አይመሠረትም(ሮሜ. 9፥10-11)። ጳውሎስ በእናቱ ማህፀን ሳለ የተለየ ነው፤ ይህም የእግዚአብሔር የጥሪ አሰራር ነው (ኤር.1፥5)። ይሁን እንጂ ጳውሎስ ይህን ያወቀው ጌታ ወደ ደህንነት ከጠራው በኋላ ነው ። ጳውሎስ ሐዋርያ እንዲሆን የጌታ ጥሪ በመጣለት ጊዜ አላመነታም እንዲሁም ከዚህ ቀደም ከነበሩት ሐዋርያት ምክርና በረከት ሊጠይቅ ወደ ኢየሩሳሌም አልሄደም። የእግዚአብሔር ዓላማ ልጁን ኢየሱስ ክርስቶስን በጳውሎስ የወንጌል ስብከት ለመግለጥ ነበር ። ጳውሎስ ከስጋና ደም ጋር አልተማከርኩም ሲል ሐዋርያነቱን በቀጥታ ከጌታ የተቀበለ መሆኑንና የበፊቶቹ ሐዋርያት ጥገኛ አለመሆኑን አፅንኦት ለመስጠት ነው ። ጳውሎስ ሕይወት ለውጥ ካገኘ በኋላ ለሦስት ዓመት እንደ ጴጥሮስ እና የጔታ ወንድም ከሆነው ያዕቆብ ካሉት ሐዋርያት ማንንም አልተገናኘም። ከሌላም ሰው ምንም ትምህርት አልተቀበለም። በሕይወቱ ለውጥ በኋላ ለተወሰነ ጊዜ ወደ አረብ አገር ሄዶ ነበር ፤ ምንም እንኳ በሐዋ.9 ላይ ባይጠቀስም ። ወደ ኢየሩሳሌም ከመሄዱ በፊት ለጸሎትና ለጥሞና ወደ አረብ አገር ሄዶ ነበር ማለት ነው ።ከዚያም ተመልሶ በደማስቆ ክርስቶስን መስበክ ጀመረ ። ሦስት ዓመታት በደማስቆ ከቆየ በኋላ በስደት ምክንያት ወደ ኢየሩሳሌም መጣ (ሐዋ.9፥19-25)።

Another poem is dropping tonight at 12:00lt✨✨✨✨✨✨✨✨ https://youtu.be/Wcu_W_9nx8k?si=CSqluyyoT7TtvIZ5 #astu_ecsf #digital_stra
Another poem is dropping tonight at 12:00lt✨✨✨✨✨✨✨✨ https://youtu.be/Wcu_W_9nx8k?si=CSqluyyoT7TtvIZ5 #astu_ecsf #digital_strategy