uz
Feedback
ASTU-ECSF

ASTU-ECSF

Kanalga Telegram’da o‘tish

ዓመታዊ መሪ ቃል: እግዚአብሔርን መፈለግ  በመመለስ  I በፅድቅ ኑሮ  I በመታመን Adama Science & Technology University Evangelical Christian Students Fellowship Official  Telegram channel contact us: @ASTUECSF_inbox CBE:1000696321179 Bethelhem & Lidiya &or Aklilu Telebirr:0950267178

Ko'proq ko'rsatish
2 821
Obunachilar
+224 soatlar
+307 kun
+2730 kun
Postlar arxiv
#QuestionsandAnswers የዛሬውን የጥያቄና መልስ ውድድር በትክክል እና በፍጥነት በመመለስ አሸናፊዎች የሆኑት 🥁🥁🥁 🥇Israel Ashenafi 4th year, choir 🥈Lidia k
#QuestionsandAnswers የዛሬውን የጥያቄና መልስ ውድድር በትክክል እና በፍጥነት በመመለስ አሸናፊዎች የሆኑት 🥁🥁🥁 🥇Israel Ashenafi 4th year, choir 🥈Lidia kibret 3rd year 🥉Kirubel kero Graduate, Lovaid አሸናፊዎች #Card_Gift (100 birr ,50birr ,50birr )🎁 📌 በጥያቄና መልሱ የተሳተፋችሁ ሁሉ ጌታ ይባርካችሁ! Telegram | INSTAGRAM | YOUTUBETIKTOK

#QuestionsandAnswers ⏳ ⏰ሰዓት አልቋል ❌ 👉ለአሸናፊዎች የካርድ ስጦታ የሚበረከት ሲሆን አሸናፊዎቹን ለይተን ስንጨርስ በዚሁ channel የምናሳውቅ ይሆናል። Telegram | INSTA
#QuestionsandAnswers ⏳           ⏰ሰዓት አልቋል ❌ 👉ለአሸናፊዎች የካርድ ስጦታ የሚበረከት ሲሆን አሸናፊዎቹን ለይተን ስንጨርስ በዚሁ channel የምናሳውቅ ይሆናል። Telegram | INSTAGRAM | YOUTUBETIKTOK

1) ጳውሎስ ሐዋሪያነቱን እንዴት መከተ(ተከላከለ)? ሀ) የተማረ ሰው መሆኑን በመናገር ለ) የተላከው በጴጥሮስ መሆኑን በመግለፅ ሐ) የተሾመው በክርስቶስ መሆኑን በመግለፅ መ) ምንም ዓይነት ምካቴ አላቀረበም  2) ጳውሎስ ከተለወጠ ከምን ያህል ጊዜ በኃላ ሐዋሪያትን ሊያገኝ ወደ እየሩሳሌም ሄደ? ሀ) 1 ዓመት  ለ) 5 ዓመት  ሐ) 3 ዓመት  መ) 7 ዓመት   3) ጳውሎስ በአንጾኪያ ማንን ተቃወመ?  ሀ) ጴጥሮስን ለ) በርናባስን ሐ) ያዕቆብን መ) ዮሐንስን  4) በገላትያ ምዕራፍ 2 ጳውሎስ ጴጥሮስን ለምን ተቃወመ? ሀ) የተለየ ወንጌል በመስበኩ ለ) ከአህዛብ ጋር በመብላቱ ሐ) ሕግን ባለመጠበቁ መ) ከአህዛብ ጋር ለመብላት ባለመፈለጉ  5) ጽድቅን አስመልክቶ ጳውሎስ ስለ ሕግ ስራ እና በክርስቶስ ስለማመን ምን ይላል? ሀ) ሁለቱም ለመዳን ያስፈልጋሉ ለ) የሕግ ስራ ብቻውን በቂ ነው ሐ) ሕጉ እና እምነት እኩል ናቸው መ) ጽድቅ የሚገኘው በክርስቶስ በማመን ነው  6) በገላትያ 2፥20 በክርስቶስ ያገኘውን አዲስ ሕይወት ጳውሎስ እንዴት ይገልፀዋል? ሀ) በሙሴ ሕግ ኖራለው ለ) ከክርስቶስ ጋር ተሰክያለው ሐ) ክርስቶስ ሀይሌ ነው መ) መንፈሱ ሕይወትን ሰጠኝ  7) በገላትያ 3 መሰረት እውነተኛ የአብርሃም ልጆች እነማን ናቸው? ሀ) ሕጉን የሚጠብቁ ለ) አይሁዶች ሐ) በክርስቶስ ያመኑ መ) የተገረዙ  8) ሕጉ የተሰጠበት ምክንያት ምንድ ነው? ሀ) ድነትን ሊሰጥ ለ) ክርስቶስ እስኪመጣ ሞግዚት እንዲሆነን ሐ) እምነትን እንዲተካ መ) ሕጉ ጥቅም የለውም  9) በገላትያ 4 ጳውሎስ የሁለቱ ኪዳኖች ምሳሌ በማድረግ የተጠቀማቸው 2 ሴቶች እነማን ናቸው? ሀ) ማርያም እና ማርታ ለ) ሊያ እና ራሔል ሐ) ሩት እና ኑሀሚን መ) ሳራ እና አጋር  10) በገላትያ 5 መሰረት አማኞች እንዴት በመንፈስ ይኖራሉ? ሀ) ታምራትን በመስራት ለ) ሕጉን በመጠበቅ ሐ) በመንፈስ በመመላለስ መ) በጸጋ ስጦታዎች በማገልገል 

#QuestionandAnswer ⁉️ የጥያቄና የመልስ ጊዜ ደርሷል!      ⚠️ የውድድር ህግ ⚖️ 🙅‍♂ አንድ ጊዜ የተላከውን መልስ ባለበት Edit ማድረግ ፈጽሞ አይቻልም 🚫 ⏳ውድድሩ የ20 ደቂቃ ቆይታ ብቻ ይኖረዋል 👉 መልሶችን የምትልኩት በ  @Sammek27 ላይ ብቻ ነው።

📣 Quiz Night❓ 📌 የጥያቄና መልስ ጊዜ ዛሬ ማታ 3:00 ይኖራል 📖 ከገላትያ መፅሐፍ ⚠️ ለአሸናፊዎች ሽልማት 🎁 ይኖራል! #astu_ecsf #digital_strategy OUR SOCIAL
📣 Quiz Night❓ 📌 የጥያቄና መልስ ጊዜ ዛሬ ማታ 3:00 ይኖራል 📖 ከገላትያ መፅሐፍ ⚠️ ለአሸናፊዎች ሽልማት 🎁 ይኖራል! #astu_ecsf #digital_strategy OUR SOCIALS: INSTAGRAM | YOUTUBE | TIKTOK

Google formኡን እየሞላችሁ ስለሆነ ጌታ ይባርካችሁ። 📌 ነገር ግን አሁንም ይሄን form ያልሞላ ብዙ ሰው ስላለ ያልሞላችሁ እባካችሁ በፍጥነት እንድትሞሉ ይሁን! 👉Google formኡ የተዘጋጀው 2018 አ.ም በግቢያችን የነበሩ ክርስቲያን ተማሪዎች በግቢ ውስጥ እንዲሁም በፌሎ ከነበራቸው ቆይታ አንፃር እንዲሞሉት ታስቦ የተዘጋጀ መጠይቅ ስለሆነ በዚህ አመት (2019 አ.ም) ግቢያችንን የምትቀላቀሉ ተማሪዎች መጠይቁን መሙላት አይጠበቅባችሁም።

🔶🔶🔶🔶🔶🔶🔶🔶🔶🔶🔶🔶🔶🔶🔶 ሰላም በጌታ የተወደዳችሁ የህብረታችን ተማሪዎች፣ እንደምን ቆያችሁ? 👉 ከታች የምታገኙት google form በ2019 አመት ለምናደርጋቸው ፕሮግራሞች የሚረዳንን  መረጃ ለማግኘት ታስቦ የተዘጋጀ የተለያዩ መጠይቆች ስለሆኑ ሁላችሁም የህብረታችን ተማሪዎች እንድትሞትሉት ይሁን።
‼️Attention ይህንን የGoogle form ስትሞሉ anonymous ስለሆነ የሚሞላው ሰው ማንነት አይገልጽም፤ ስለዚህ በነፃነት እንድትሞሉ ስንል በትህትና እንጠይቃለን።
 📌 ከህብረታችን ተማሪ ያልሞላ እንዳይኖር! ተባረኩ❤️ https://forms.gle/X5yu7ZLhoHTpErHaA

🌼እንኳን ለ2019 እግዚአብሔር በሰላም አደረሳችሁ ፣ አደረሰን🌼 ነፍሴ ሆይ፥ ወደ ዕረፍትሽ ተመለሺ፥ እግዚአብሔር መልካም አድርጎልሻልና፤ መዝ 116:7 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼�
🌼እንኳን ለ2019 እግዚአብሔር በሰላም አደረሳችሁ ፣ አደረሰን🌼
ነፍሴ ሆይ፥ ወደ ዕረፍትሽ ተመለሺ፥ እግዚአብሔር መልካም አድርጎልሻልና፤ መዝ 116:7
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 ይህ ዓመት እንደ ሕብረት እግዚአብሔር ለሃሳቡ በይበልጥ አኛን መጠቀሚያ የሚያደርግበት ፣ ወደ እርሱ በይበልጥ የምናድግበት እና እርሱን የምንመስልበት እንዲሁም እርሱን በይበልጥ የምንታመንበት እና የምንፈልግበት ይሁንልን! መልካም በዐል! በይበልጥ ተባረኩ😁 ✨ ASTUECSF 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 #2019 #astu_ecsf #digital_strategy OUR SOCIALS: INSTAGRAM | YOUTUBE | TIKTOK

ጷጉሜ 05 📣 ዛሬ ደግሞ ስለ ህብረታችን እንፀልያለን፤ አንዳንዶች ማድረጉን እንደተዉት መሰብሰባችንን አንተው፤ ይልቁንም ቀኑ እየተቃረበ መምጣቱን ስታዩ እርስ በርሳችን እንበረታታ። ዕብ 10:25 �
ጷጉሜ 05 📣 ዛሬ ደግሞ ስለ ህብረታችን እንፀልያለን፤
አንዳንዶች ማድረጉን እንደተዉት መሰብሰባችንን አንተው፤ ይልቁንም ቀኑ እየተቃረበ መምጣቱን ስታዩ እርስ በርሳችን እንበረታታ። ዕብ 10:25
🌼 የሕብረታችንን አንድነት አንድንጠብቅ ጌታ አንዲረዳን ወደ ክርስቶስም ፍፁም ሙላት ማደግ አንድንችል በመያያዝና በመደጋገፍ አንድናድግ በጌታ ፊት አንፀልይ::
ፍጹም ትሑታንና ገሮች ሁኑ፤ እርስ በርሳችሁም በፍቅር እየተቻቻላችሁ ትዕግሥተኞች ሁኑ። በሰላም ማሰሪያ የመንፈስን አንድነት ለመጠበቅ ትጉ። ኤፌ 4:2-3
🌼 መፅናናትን እግዚአብሔር በእኛ መካከል አንዲያበዛ : ፀንተንም የወንጌሉን ስራ በትጋት አንድንሰራ::
ስለዚህ በርግጥ አሁን እንደምታደርጉት ሁሉ እርስ በርሳችሁ ተጽናኑ፤ አንዱም ሌላውን ያንጽ። 1ኛ ተሰ 5:11
በህብረታችን ለጠፉ ልጆች አንፀልይ ደግሞ ጌታ አንድመልሳቸው ማስተዋልም ጌታ አንዲሰጣቸው አንማልድላቸው በጌታ ፊት :: 🌼 ለህብረታችን መሪዎች አንፀልይ ጌታ በማስተዋል እና በጥበብ ህብረቱን መምራት አንዲችሉ እና በመጪውም ዘመን የእግዚአብሔር ድምፅን በመስማት እና በመታዘዝ ጌታ አንዲረዳቸው አንፀልይላቸው:: 🌼 ሕብረታችንን ሊያፈርስ ያለ የክፉ ስራን አያፈረስን አንፀልይ ምክንያቱም ስንቃወመው ከኛ ይሸሻል ::
እንግዲህ ራሳችሁን ለእግዚአብሔር አስገዙ፤ ዲያብሎስን ተቃወሙት፤ ከእናንተም ይሸሻል። ያዕ 4:7
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 #pray_week #pagume_2018 #astu_ecsf #digital_strategy OUR SOCIALS: INSTAGRAM | YOUTUBE | TIKTOK

የአማራ ህዝብ ክፍል 💥እጅግ አብዛኛው የአማራ ሕዝብ ከ4ኛው ክፍለ ዘመን ዓ.ም ጀምሮ ከዕለታዊ ህይወቱ፣ ከማንነቱና ከማኅበራዊ እቅዱ ጋር በጥብቅ የተዋሐደውን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ክርስቲያ
የአማራ ህዝብ ክፍል 💥እጅግ አብዛኛው የአማራ ሕዝብ ከ4ኛው ክፍለ ዘመን ዓ.ም ጀምሮ ከዕለታዊ ህይወቱ፣ ከማንነቱና ከማኅበራዊ እቅዱ ጋር በጥብቅ የተዋሐደውን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ክርስቲያናዊ እምነት ይከተላል። እንዲሁም እንደ ወሎ ባሉ ምሥራቃዊ አካባቢዎች ጥቂት የማይባል የአማራ ሕዝብ የሱኒ እስልምና እምነት ተከተይ ሲሆን፣ እዚያም የእስልምና ትምህርትና የሱፊ መንገድ ከአጎራባች ኦርቶዶክሶች ጋር ለዘመናት ጎን ለጎን ቆይቷል። የጸሎት ርዕሶች 🙏 👉በእምነታቸው ምክንያት ከቤተሰብ፣ ከማኅበረሰብ ወይም ከተለያዩ አካላት ጫናና ስደት የሚደርስባቸው አማኞች በክርስቶስ ፍቅርና ጽናት እንዲቆሙ፣ ከጥቃትም እንዲጠበቁ እንጸልይ። 👉 ስለ አማራ ሕዝብ መዳን፣ ሰላምና መንፈሳዊ መነቃቃት ቀንና ሌሊት የሚጾሙና የሚጸልዩ የጸሎት ቡድኖች በየቦታው እንዲቋቋሙ፤ የእግዚአብሔርም ታላቅ ጉብኝት በምድሪቱ ላይ እንዲሆን እንጸልይ። 👉በአማራ ክልል የሚታየው ግጭትና አለመረጋጋት በሰላማዊ መንገድ እንዲፈታ፣ የእግዚአብሔር ሰላም በምድሪቱ ላይ እንዲነግስ እንጸልይ።

ቀን 4 📣 ክርስቶስን ላላመኑት እና አምነው ወደ ኋላ ለተመለሱት ወንድሞችና እህቶች እንጸልያለን::
"እውነተኛ አምላክ ብቻ የሆንህ አንተን የላክኸውንም ኢየሱስ ክርስቶስን ያውቁ ዘንድ ይህች የዘላለም ሕይወት ናት።" ዮሐ17:3
🌼 መንፈስ ቅዱስ ልባቸውን እንዲከፍት፣ እግዚአብሔር ሲጠራቸው እንዲሰሙ፣ የሰሙትንም አስተውለው እንዲረዱ እንጸልይ፤
"ከትያጥሮን ከተማም የመጣች ቀይ ሐር ሻጭ እግዚአብሔርን የምታመልክ ልድያ የሚሏት አንዲት ሴት ትሰማ ነበረች፤ ጳውሎስም የሚናገረውን ታዳምጥ ዘንድ ጌታ ልቧን ከፈተላት።" ሐዋ 16:14
🌼 የዘላለም ሕይወት የሆነውን ክርስቶስን ላላወቁት ምስኪን የዶርም ጓደኞቻችን እግዚአብሔር ወደ እርሱ እንዲያመጣቸው፣ ደግሞም እግዚአብሔር በእኛ እንዲጠቀም እንጸልይ፤
"የእግዚአብሔርም ልጅ እንደ መጣ፥ እውነተኛም የሆነውን እናውቅ ዘንድ ልቡናን እንደ ሰጠን እናውቃለን፤ እውነተኛም በሆነው በእርሱ አለን፥ እርሱም ልጁ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። እርሱ እውነተኛ አምላክና የዘላለም ሕይወት ነው።" 1ኛ የዮሐ 5:20
🌼 ክርስቶስን አምነው ወደ ኋላ ለተመለሱ ወንድሞችና እህቶች ልጅነታቸውን ማስታወስ እንዲችሉ፣ ወደ አባታቸው ቤት ለመመለስ መወሰን እንዲችሉ ጌታ እንዲረዳቸው እንጸልይ፤
"ወንድሞቼ ሆይ፥ ከእናንተ ማንም ከእውነት ቢስት አንዱም ቢመልሰው፥ ኃጢአተኛን ከተሳሳተበት መንገድ የሚመልሰው ነፍሱን ከሞት እንዲያድን፥ የኃጢአትንም ብዛት እንዲሸፍን ይወቅ።" ያዕ 5:19-20
🌼 ከወዴት እንደወደቁ አውቀው በንስሐ መመለስ እንዲችሉና ጌታ የቀድሞ ሕይወታቸውን እንዲያድስላቸው እንጸልይ፤
"አቤቱ፥ ንጹሕ ልብን ፍጠርልኝ፥ የቀናውንም መንፈስ በውስጤ አድስ። ከፊትህ አትጣለኝ፥ ቅዱስ መንፈስህንም ከእኔ ላይ አትውሰድብኝ። የማዳንህን ደስታ ስጠኝ፥ በእሽታ መንፈስም ደግፈኝ።" መዝ 51:10-12
🌼 በእነዚህ የፀሎት ርዕሶችና በቃሉ መሰረት በእግዚአብሔር ፊት በምልጃ እና በምስጋና እንቅረብ። 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 #pray_week #pagume_2018 #astu_ecsf #digital_strategy OUR SOCIALS: INSTAGRAM | YOUTUBE | TIKTOK

photo content

ቀን 3 📣 ራሳችንን ሙሉ በሙሉ ለክርስቶስ መስጠት
“ከዚያም ለሁሉም እንዲህ አላቸው፦ ‘በኋላዬ ሊመጣ የሚፈልግ ማንም ቢኖር ራሱን ይካድ፣ መስቀሉንም በየዕለቱ ተሸክሞ ይከተለኝ።’”ሉቃ 9፥23
🌼 ዛሬ ደግሞ ፈቃዳችንን፣ ወጣትነታችንን፣ ምኞታችንንና ሕይወታችንን ሙሉ በሙሉ ለጌታ እንድንሰጥ፣ በክርስቲያናዊ ጉዟችንም በንጽሕናና በቅድስና እንድንመላለስ እንጸልያለን። 🌼 የራሳችንን ፈቃድና ምኞት ከመከተል ይልቅ የጌታን ፈቃድ እንድንመርጥ፣ ያለንን ሁሉ ለእርሱ በመስጠት ለክርስቶስ ብቻ የተለየ ሕይወት እንድንኖር እንማልዳለን ፤ በጉዟችን እየተቀደስንና እየታነጽን እስከ መጨረሻ በንጽሕና እንድንጸና እንጸልያለን፤
“የሰላም አምላክ ራሱ ሁሉንተናችሁን ይቀድስ፣ መንፈሳችሁ፣ ነፍሳችሁና ሥጋችሁ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሚመጣበት ጊዜ ያለ ነቀፋ ይጠበቁ።” 1 ተሰ 5፥23
ጌታ ከሚያረክስ ነገር ሁሉ እንዲያነጻን፣ ልባችንንና ምኞታችንን እንዲቀድስ፣ በቅድስና እያደግን ክርስቶስን የሚያሳይ ሕይወት እንድንኖር እንጸልያለን። 🌼 የጌታን መምጣት በማሰብ በቅድስናና በእግዚአብሔር ፊት በሚገባ እንድንኖር እንጸልያለን፤
“የጌታ ቀን ግን እንደ ሌባ ይመጣል፣ በዚያች ቀን ሰማያት በታላቅ ድምፅ ያልፋሉ፣ ፍጥረትም በታላቅ ግለት ይጠፋል፣ ምድርና በርሷም ላይ ያለ ነገር ሁሉ ወና ይሆናል። እንግዲህ ሁሉም ነገር በዚህ ሁኔታ የሚጠፋ ከሆነ፣ እናንተ እንዴት ዐይነት ሰዎች ልትሆኑ ይገባችኋል? አዎን፣ በቅድስናና በእውነተኛ መንፈሳዊነት ልትኖሩ ይገባችኋል።” 2 ጴጥ 3፥10-11
የዚህ ዓለም ነገር ጊዜያዊ መሆኑን አውቀን፣ ልባችንን በዓለም ነገር ሳንይዝ ለጌታ በመለየት በቅድስና፣ በንጽሕናና እግዚአብሔርን በመፍራት እንድንኖር እንጸልያለን። 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 #pray_week #pagume_2018 #astu_ecsf #digital_strategy OUR SOCIALS: INSTAGRAM | YOUTUBE | TIKTOK

photo content

📣 OUT NOW❗️ https://youtu.be/5Aln-MhH9hM 📌 ትምህርቱን እንደገና ማጤን ብሎም በዙሪያችሁ ላሉ ማጋራት እንዳትረሱ😊 ተወዳጆች ናችሁ💛 #astu_ecsf #digital_str
📣 OUT NOW❗️ https://youtu.be/5Aln-MhH9hM 📌 ትምህርቱን እንደገና ማጤን ብሎም በዙሪያችሁ ላሉ ማጋራት እንዳትረሱ😊 ተወዳጆች ናችሁ💛 #astu_ecsf #digital_strategy

ጷጉሜ 02 📣 በንስሃ ፣ በመመለስ እግዚአብሔር እንፈልግ "እግዚአብሔር በሚገኝበት ጊዜ ፈልጉት፥ ቀርቦም ሳለ ጥሩት፤ክፉ ሰው መንገዱን በደለኛም አሳቡን ይተው፤ ወደ እግዚአብሔርም ይመለስ እርሱም ይ
ጷጉሜ 02 📣 በንስሃ ፣ በመመለስ እግዚአብሔር እንፈልግ
"እግዚአብሔር በሚገኝበት ጊዜ ፈልጉት፥ ቀርቦም ሳለ ጥሩት፤ክፉ ሰው መንገዱን በደለኛም አሳቡን ይተው፤ ወደ እግዚአብሔርም ይመለስ እርሱም ይምረዋል፥ ይቅርታውም ብዙ ነውና ወደ አምላካችን ይመለስ።" ኢሳ 55:6-7
🌼 በተለያዩ ድረግቶች ሀሳቦች እግዚአብሔር ባሳዘንበት ነገር ንሰሐ በመግባት እግዚአብሔር ይቅር እንድለን እንፀልይ፤
ኃጢአቴን ለአንተ አስታወቅሁ፥ በደሌንም አልሸፈንሁም፤ ለእግዚአብሔር መተላለፌን እነግራለሁ አልሁ፤ አንተም የልቤን ኃጢአት ተውህልኝ። መዝ 32:5
🌼 በስንፍናና በችላ ባይነት ስናደርግ ሰለቀረንባቸዉ ነገር ላይ (ለቃሉ እና ለፀሎት....) ፤ የ እግዚአብሔር ሀሳብ በልሰመንበት ነገር ላይ  እግዚአብሔር ይቅር እንድለን በፍቱ በመቅረብ እንፀልይ፤
እንግዲህ በጎ ለማድረግ አውቆ ለማይሠራው ኃጢአት ነው። ያዕ 4:17
🌼 በዝኛዉ አመት እንደ ህበረታች ጌታን በበደልንበት ነገር ላይ ጌታ ይቅር እንድለን ደግሞም የትጋር እንዲወድቅን አዉቀን መነሳት እንድንችል ጌታ እንድረዳን እንፀልይ፤
እንግዲህ ከወዴት እንደ ወደቅህ አስብ ንስሐም ግባ የቀደመውንም ሥራህን አድርግ፤ አለዚያ እመጣብሃለሁ ንስሐም ባትገባ መቅረዝህን ከስፍራው እወስዳለሁ። ራእ 2:5
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 #pray_week #pagume_2018 #astu_ecsf #digital_strategy OUR SOCIALS: INSTAGRAM | YOUTUBE | TIKTOK

👋 ስላም የተወደዳችሁ ወጣቶች አንዴት ቆያችሁ ፤ ከነገ ጀምሮ "መንፈስ ቅዱስ ማነው" የሚለውን ትምህርት በዩትዩብ ገፃችን ላይ ማግኘት ትችላላችሁ። https://youtu.be/5Aln-MhH9hM 📌
👋 ስላም የተወደዳችሁ ወጣቶች አንዴት ቆያችሁ ፤ ከነገ ጀምሮ "መንፈስ ቅዱስ ማነው" የሚለውን ትምህርት በዩትዩብ ገፃችን ላይ ማግኘት ትችላላችሁ። https://youtu.be/5Aln-MhH9hM 📌 ትምህርቱን እንደገና ማጤን ብሎም በዙሪያችሁ ላሉ ማጋራት እንዳትረሱ😊 ተወዳጆች ናችሁ💛 #astu_ecsf #digital_strategy

ጷጉሜ 01 📣 እግዚአብሔርን እያመሰገንን እንጸልያለን። “መልሶም፦ ለዘሩባቤል የተባለው የእግዚአብሔር ቃል ይህ ነው። በመንፈሴ እንጂ በኃይልና በብርታት አይደለም፥ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር።
ጷጉሜ 01 📣 እግዚአብሔርን እያመሰገንን እንጸልያለን።
“መልሶም፦ ለዘሩባቤል የተባለው የእግዚአብሔር ቃል ይህ ነው። በመንፈሴ እንጂ በኃይልና በብርታት አይደለም፥ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር።” ዘካ 4፥6
🌼 መዳናችንን እያሰብን፤
‎“አሁን ግን እናንተ በፊት ርቃችሁ የነበራችሁ በክርስቶስ ኢየሱስ ሆናችሁ በክርስቶስ ደም ቀርባችኋል።” ‎ኤፌ 2፥13
🌼 ዛሬም በክርስቶስ የመስቀል ስራ ወደ እግዚአብሔር አብ አባ አባት ብለን የምጠራበት የልጅነት መንፈስ ስለተሰጠን፤
“አባ አባት ብለን የምንጮኽበትን የልጅነት መንፈስ ተቀበላችሁ እንጂ እንደገና ለፍርሃት የባርነትን መንፈስ አልተቀበላችሁምና።” ሮሜ 8፥15
🌼 በግቢ በነበረን ቆይታ ሁሉ በድካምም ሆነ በብርታት በትምህርታችን፣ በመንፈሳዊ ህይወታችን፣ ምልልሳችን ሁሉ እግዚአብሔር ስለረዳን፣ ምህረትና ጸጋዉን ስላበዛልን እያመሰገንን እንጸልያለን፤
“መልሶም፦ ለዘሩባቤል የተባለው የእግዚአብሔር ቃል ይህ ነው። በመንፈሴ እንጂ በኃይልና በብርታት አይደለም፥ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር።” ዘካ 4፥6
🌼 እንደ ህብረት ደግሞ የአገልግሎት ዘርፎችን እግዚአብሔር ስለረዳቸው፣ በተካሄዱ በወንጌል ስርጭቶች፣ በአጠቃላይ ህብረታችን ጌታ በብዙ ስለረዳ፣ መሪዎችም ሚቆረስ ህይወት እንዲኖራችው ጸጋዉን ስላበዛላችው እግዚአብሔርን እያመሰገንን እንጸልያለን። 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 #pray_week #pagume_2018 #astu_ecsf #digital_strategy OUR SOCIALS: INSTAGRAM | YOUTUBE | TIKTOK

ስላም ሰላም የጌታ ውዶች እንደምን ቆያችሁ ፤ ይኸው በጌታ ትከሻ 2019 ሊያልቅ ነው እናም እኛ እንደ ሕብረት የረዳንን እግዚአብሔር በጋራ የምናመሰግንበት፣ምህረት እንደገና ምንጠይቅበት ብሎም ከፊታች
ስላም ሰላም የጌታ ውዶች እንደምን ቆያችሁ ፤ ይኸው በጌታ ትከሻ 2019 ሊያልቅ ነው እናም እኛ እንደ ሕብረት የረዳንን እግዚአብሔር በጋራ የምናመሰግንበት፣ምህረት እንደገና ምንጠይቅበት ብሎም ከፊታችን ላለው ዓመት የጌታን ፈቃድ የምንሰማበትና እርሱንም የምናደርግበት አቅምን የምንጠይቅበት የጾም እና ጸሎት ፕሮግራም አዘጋጅተናል። ይህም የሚሆነው ከጷጉሜ 1-5 ሲሆን በጋራ የምንቆይባቸውን የተመረጡ የየቀኑን ሃሳቦች በማህበራዊ ሚዲያዎቻችን የምናጋራ ይሆናል። 📌ሁላችንም በያለንበት በሚለቀቁት ርዕሶች ለይ እንድንፀልይ ይሁን። እንወዳችኋለን🤗 #pray_week #pagume #astu_ecsf #digital_strategy

ቁ.14 የክርስቶስ መስቀል አለም ለእኛ የተሰቀለበት ፣እኛም ለአለም የተሰቀልንበት ነው ። የስጋን ፈቃድ እና ምኞት በመስቀሉ ገድለናል( ገላ 2:20)። ቁ.15-17 የዳነ ሰው ምልክቱ የተለያዪ ሥረአቶችን መፈፀሙ ፣ ቤተክርስቲያን መመላለሡ ሣይሆን አዲስ ፍጥረት መሆኑ፣ ዳግም መወለዱ ነው። ቁ.18 የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ፀጋ ከሁላችን ጋር ይሁን።አሜን። 🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉 የክረምት የመፅሐፍ ቅዱስ ጥናታችንን አጠናቀናል፤የረዳን እግዚአብሔር ይመስገን፣አብራችሁንም ስታጠኑ የነበራችሁ በሙሉ ጌታ ይባርካችሁ፤በጣም በቅርቡ ደግሞ በአዲስ ነገር እንከሰታለን ተከታተሉ!😉 እንወዳችኋለን🤗 OUR SOCIALS: INSTAGRAM | YOUTUBE | TIKTOK #summer_bs #galatians #astu_ecsf #digital_strategy