ASTUECSF official
Ir al canal en Telegram
ዓመታዊ መሪ ቃል: እግዚአብሔርን መፈለግ በመመለስ I በፅድቅ ኑሮ I በመታመን Adama Science & Technology University Evangelical Christian Students Fellowship Official Telegram channel contact us: @ASTUECSF_inbox CBE:1000696321179 Bethelhem & Lidiya &or Aklilu Telebirr:0950267178
Mostrar más2 808
Suscriptores
Sin datos24 horas
-57 días
-130 días
Archivo de publicaciones
2 808
የአላባ (ሃላባ) ህዝብ
💥የአላባ ህዝብ በኢትዮጵያ ማዕከላዊ ደጋማ ስፍራ፣ ከአዲስ አበባ በስተደቡብ ምዕራብ ከ250-300 ኪ.ሜ ርቀት ላይ በሻሸመኔ-ሶዶ መንገድ መስመር ይኖራሉ።አካባቢው ጠፍጣፋና የሳር ምድር ሲሆን፣ በቆሎ፣ ጤፍ እና በርበሬ (በተለይ የአላባ በርበሬ ይታወቃል) ያመርታሉ። የአላባ ቋንቋ ከከምባታ ቋንቋ ጋር በእጅጉ ይመሳሰላል። አኗኗራቸው በጣም ቀላል ነው፤ አብዛኛው የገጠር ነዋሪ ከእንጨትና ጭቃ በተሰሩ፣ ሳር ክዳን በሆኑ እና ወለላቸው ጭቃ በሆነ ቤቶች ከከብቶቻቸው ጋር አብረው ይኖራሉ። የውሃ፣ የመብራት እና የህክምና አገልግሎት አቅርቦት ከፍተኛ ችግር አለባቸው። በየዓመቱ ጥር ላይ "ሴራ" የተሰኘ የመከር በዓል ያከብራሉ። ለውጭ ተጽዕኖ(ወንጌልንም ለመስማት)ክፍት አይደሉም፤ ሆኖም አሁን ልጆቻቸውን ወደ ትምህርት ቤት መላክ ጀምረዋል። አብዛኛው ህዝብ የሱኒ ሙስሊም ሲሆን፣ አሁን አሁን የወንጌል ብርሃን ወደ አካባቢው እየገባ ይገኛል።
እንፀልይ
👉 ስለ ህዝቦችዋ ፣ስለ ቋንቋቸው፣ ስለ ባህላቸው ሰለ መልካም እሴቶችዋ እና በዛ የህዝብ ክፍል ስላለ መልካም ነገር ሁሉ እግዚአብሄርን እናመሰግን
👉 ይህ መለኮተ እስትንፍስ የሆነው መጽሐፍ ቅዱስ በቋንቋቸው ተተርጉሞ በበቂ ሁኔታ ለህዝቡ እንዲደርስ እንጸልይ
👉 የኢየሱስ ፊልም እና ሌሎች የድምፅ ቅጂዎች ለሕዝቡ በተሰናዳ መልኩ እንዲደርስ እና እግዚአብሔርም እነዚህን በመጠቀም ህዝቡን እንዲደርስ እንጸልይ!
2 808
📣📣📣📣📣📣📣📣📣📣📣📣📣
Only 2 hours left
https://youtu.be/LzjYGh7pYqA?si=XJ9d_q0C8BWSPGVA
#astu_ecsf #digital_strategy
2 808
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
Another one dropping today!
10:00 LThttps://youtu.be/LzjYGh7pYqA?si=XJ9d_q0C8BWSPGVA #astu_ecsf #digital_strategy
2 808
ይገዛ ህይወቴ ለአንተ ይኑርልህ አብልጦ ይጠጋ ከፍቃድ መንደርህ፥ ህያው ቅዱስሆኖ ይቅረብ ሰውነቴ ለአዕምሮ የሚመች ይሁን መስዋዕቴ፤ ጌታ እንዳከብርህ በመውጣት መግባቴ፥ ኑሮዬ ይመስክር አልፎ ከአንደበቴ።#literature_and_drama #astu_ecsf #digital_strategy
2 808
ቁጥር 3. እንደማንኛውም ደብዳቤ ጸሀፊ ጳውሎስ በሚፅፋቸው መልዕክቶች(Epistles) ውስጥ ሰላምታ በመስጠት ይጀምራል። ይህም ልባዊ ምኞት ብቻ ሳይሆን ሐዋርያዊ በረከትም ነው ።
ሰላም፡- በነፍስ ውስጥ ያለ ጸጥታ ሲሆን ከአምላክ ጋር ካለ ትክክለኛ ዝምድና የሚገኝ ነው ።
ጸጋ፡- በክርስቶስ በኩል ለምዕመናን የሚሰጠው የእግዚአብሔር ርኅራኄና ደግነት ነው ።
እነዚህም አባታችን ከሆነው ከአብ እና ጌታችን ከሆነው ከክርስቶስ የሚሰጡ ናቸው ።
ቁጥር 4-5. በሰው እና በክርስቶስ መካከል ስላለ ዝምድና ይናገራል። ክርስቶስ ራሱን ስለ ሰው ኃጢኣት ሲል ቤዛ አደረገ( ማቴ.1:21፤ ዮሐ.1:29)።ይህም ከአብ ፈቃድ ውጭ አልነበረም። በአብ ዕቅድ እና ፈቃድ መሠረት እንጂ።
ይህም የሆነው ከዚህ ክፉ ዓለም ያድነን ዘንድ ነው ይላል ጳውሎስ። ዓለም ብሎ የሚጠቅሰው ያለንበትን ጊዜ ወይም ዘመን ሲሆን የዘመኑን ክፋትም አልደበቀም፤(2ቆሮ.4፥4 ፤ ኤፌ.2፥2)። አማኞች በክርስቶስ ሞት ምክንያት ከዚህ በኃጢኣት የረከሰ የዓለም ኑሮ ነፃ መውጣታቸውንና በጽድቅና በቅድስና ይኖሩ ዘንድ እግዚአብሔር እንዳዳናቸው ይናገራል። እግዚአብሔርንም በመባረክ ሰላምታውን ይደመድማል።
ቁጥር 6. ጳውሎስ ሰላምታውን በቡራኬ ከጨረሰ በኋላ ወደ መልዕክቱ ዓላማ በቀጥታ ይገባል።የገላትያ አማኞች የወንጌልን ጥሪ በጳውሎስ አማካኝነት ከእግዚአብሔር ተቀብለዋል። ጳውሎስ ወንጌልን ለውጭ ጆሯቸው ሲያበስር፣ እግዚአብሔር በመንፈስ ቅዱስ አሠራር ለልባቸው አድርሶላቸዋል። ይህም ታላቅ የደህንነት ጥሪ ነው ። የገላትያ ምዕመናን ይህን ጥሪ በእምነትና በንሰሐ ተቀብለው ነበር ። ነገር ግን ከጊዜ በኋላ ፈጥነው ወደ ልዩ ወንጌል አዘንብለዋል። አዎን ሌላ ወንጔል መቀበል የመጀመሪያውን ወንጌል ያስተዋል። ስለዚህም የጠራቸውን እግዚአብሔርን ጥለው ወደ ልዩ ወንጌል ፊታቸውን በፍጥነት ማዞራቸው ጳውሎስ ላይ አግራሞት ፈጥሮበታል። ይሁን እንጂ ይህ ከእግዚአብሔር ማፈግፈግ ገና ጅምር ላይ እንጂ በፍጻሜ ላይ ያለ አይመስልም። ጳውሎስ ይህን መልዕክት በሚጽፍበት ጊዜ ጨርሰው ወንጌልን ክደዋል ለማለት አያስደፍርም ዘንበል ማለትን እንጂ።
ቁጥር 7. "ልዩ ወንጌል" የሚለው አነጋገር በገላትያ አብያተ-ክርስቲያናት የገባውን ሐሰተኛ ትምህርት ባዕድነት(እንግዳነት) እንዲሁም የ እውነተኛው ወንጌል ተጻራሪ መሆንን ያስረዳል። የገላትያ ሰዎች ሁለት ትክክል የሆኑ የወንጌል አስተምህሮዎች እንደምርጫ ሳይሆን የቀረቡላቸው ፤ አንዱን እውነተኛ ወንጌል ጥለው ሐሰተኛውን ወንጌል በመቀበል ሂደት ላይ የነበሩ መሆኑን እናስተውላለን። ትክክለኛ ወንጌል አንድ እንደሆነና እርሱንም የሚፃረር ልዩ ትምህርት በጠቅላላ ፀረ ወንጌል መሆኑንም ጳውሎስ ያስረዳል።
ይህንም ባዕድ ትምህርት ያቀረቡላቸው እነማን እንደሆኑ በጠቅላላው ይገልፃል። ምዕመናንን ከዕምነታቸው ማናወጥ አጋንንታዊ ስራ ሲሆን ይህም ማናወጥ የሀሰት ትምህርቶችን በማቅረብ የ አማኞችን ልብና አእምሮ ወደ ሀሰተኛ አስተሳሰብ መጠምዘዝ ነው (ሐዋ.15፥24) ።
እዚህ ጋር የተጠቀሱት ሐሰተኛ አስተማሪዎች የክርስቶስን ወንጌል የማጣመም ፍላጎት ነበራቸው። ምንም እንኳን የግል ዓላማቸው እውነትን መስበክ መስሎ ቢታያቸውም፥ የተግባር ውጤቱ የክርስቶስን ወንጌል ማጣመም ሆኖ ተገኘ።ለዚህም ተግባራቸው ተጠያቂ ይሆናሉ።
ቁጥር 8-9. "አናቴማ" ትርጓሜው "የተረገመ ይሁን!" ማለት ነው ። የገላትያ ሰዎች እውነተኛውን ወንጌል ተቀብለው ነበር ፥ ሐሰተኞች ግን ልዩ ወንጌል ሰበኩላቸው።ይህ ልዩ ወንጌል የክርስቶስን ወንጌል የሚያጣምም እንዲሁም ምዕመናንን የሚያናውጥ በሙሆኑ ሐዋርያው በእርግማን ሊከላከለው መርጧል። "ከሰበክንላችሁ ወንጌል የተለየ ማንም ቢሰብክላችሁ የተረገመ ይሁን!"በማለት ።
ሀሰተኞቹ አስተማሪዎች ከዋኖቹ ሐዋርያት ፥ከጴጥሮስና ከያዕቆብ ተልከናል በማለት ከጳውሎስ የበለጠ ስልጣን እንዳላቸው ለ ገላትያ ምዕመናን ማሳመን ይፈልጉ ነበር ። ስለዚህም ጳውሎስ "እኛም" ብሎ በጠቅላላው ሐዋርያትን ከጠቀሰ በኋላ ፥ "መላዕክትም" እንኳ ቢሆኑ ብሎ ከተሰበከላቸው ወንጌል እንዳይነቃነቁና የመለወጥ ስልጣንም እንደሌላቸው አጽንኦት ሰቷል።ምክንያቱም ይህ የተሰበከው ወንጌል በማንም ሊታረምና ሊቀየር አይችልምና ነው ።ሐዋርያትም ይሁኑ ወኪልቻቸው አልፎም የሰማይ መላዕክት እንኳ ይህን ወንጌል እንቀይር ቢሉ ከዕርግማን በታች ናቸው(ተረግመዋል)።
ምክንያቱም ይህ የተሰበከው ወንጌል እውነተኛ ፥ ሊታረምና ሊቀየር የማይችል ነው ። ይህንም ወንጌል አጣሞ በሌላ ነገር መተካት እጅግ አስፈሪ ነው ። እግዚአብሔርን ሊያርም የሚሞክር ሁሉ ራሱን በፍርድ ስር ይጥላል።
#summer_bs #galatians
#astu_ecsf #digital_strategy
2 808
" ሐዋርያ" የሚለው ቃል ''የተላከ'' ማለት ሲሆን ይህም የሚሆነው በእግዚአብሔር እንደሆን ልብ ልንል ይገባል።ይህም ሙሉ የውክልና ስልጣን ተሰጥቶት ለአንድ ተግባር የተላከ መልዕክተኛን ያመለክታል። በአዲስ ኪዳን ውስጥ ሁለት ዓይነት ሐዋርያነትን ብንመለከት፡- በጠቅላላ ቤተክርስቲያን የምትልካቸው የወንጌል ሰባኪዎች ሐዋርያት ተብለው ይጠሩ ነበር (ሐዋ.14፥4፡14)። በዋነኝነት ግን ሐዋርያት የሚባሉት ክርስቶስ በቀጥታ የሾማቸው አስራ አንዱ እና ጳውሎስ ናቸው፤ሉቃ.6፥13፤ ገላ.1፥1-12፤ 2ቆሮ.12፥5፡11፤ራዕ.21፥14)።ከመጀመሪያዎቹ አስራ ሁለት ሐዋርያት የአስቆሮቱ ይሁዳ በከሃዲነት ራሱን አስወግዷል።ማትያስ ሐዋርያት በዕጣ የመረጡትና የሾሙት እንጂ እንደ አስራ ሁለቱና እንደ ጳውሎስ ጌታችን በቀጥታ የሾመው አይደለም።ምንም እንኳን ጳውሎስ ከመጀመሪያዎቹ ውስጥ ባይሆንም፥ጌታ ራሱ በቀጥታ ስለሾመው ከአስራሁለቱ ሐዋርያት ያነሰ ስልጣን እንደሌለው ይናገራል።
ይህን ስልጣን በኢየሱስ ክርስቶስና ከሙታን ባስነሳውም በእግዚአብሔር አገኘሁ እያለ ሲፅፍ ታዲያ የገላትያ አብያተ ክርስቲያናት ከክርስቶስ ወንጌል ፈቀቅ ማለታቸው በሞቱና በትንሳኤው ላይ የነበረችውን እምነት የሚቃረን መሆኑን ያስረዳል።
ቁጥር 2. አብረውት እነማን እንደነበሩ በዝርዝር ባይጠቅስም፤በአገልግሎት አብሮ ሰራተኛ የሆኑትን ክርስትያኖች እንደሆኑ ይገመታል(ምናልባትም እንደነ ሲላስ እና ጢምቴዎስ)። ወደ ገላትያ አብያተ ክርስቲያናትም በሚጻፈው መልዕክት አብረውት የነበሩት ረዳቶቹ ሁሉ መስማማታቸውን ይገልጻል ። መልዕክቱም በገላትያ አውራጃ ላሉ አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ የተፃፈ ነበር።
2 808
+4
"ድካምና አገልግሎት"
አንዳንድ ጊዜ በብዙ እያገለገልን እየመሰለን ነገር ግን በውስጣችን ደክመን እንገኛለን::
"ማርታ ግን አገልግሎት ስለ በዛባት ባከነች፤... ኢየሱስም መልሶ፡— ማርታ፥ ማርታ፥ በብዙ ነገር ትጨነቂአለሽ ትታወኪማለሽ፥ የሚያስፈልገው ግን ጥቂት ወይም አንድ ነገር ነው ፥ ..." ሉቃ 10:40👉 ሙሉ ለማንበብ ጠቅ_ያድርጉ 📌ማንኛውም አይነት የማማከር አገልግሎት ለማግኘት ከታች ያለውን የቴሌግራም ቦት ይጠቀሙ፤ለመመለስ ሪፕላይ(REPLY) የሚለውን መጫን እንዳይረሱ! 👇👇 @counselling_CBot #article_05 #counseling_team #friendship #digital_strategy #astu_ecsf INSTAGRAM | YOUTUBE | TIKTOK
2 808
እንጸልይ
🙏ለትግራይ የሕዝብ ክፍል🙏
የሕዝብ ብዛት - 8,322,000
ዋነኛ ቋንቋ - ትግርኛ
ብዙ ተከታይ ያለው እምነት - ክርስትና (96.00%) (ምስራቅ ኦርቶዶክስ)
ክርስትና - 50-100 %
ወንጌላዊ አማኞች- 0-0.1 %
የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጉም - ሙሉ ተተርጉሟል
ወንጌል ተኮር ቅጂዎች - አሉ
የጸሎት ርዕሶች 🙌
👉 በህዝቡ መካከል የሚሰሩ ሚሲዪናዊያንን የመኸሩ ጌታ እንዲያስነሳ፣ እንዲልክ አጥብቀን እንማልድ።
👉 የትግራይ ሕዝብ ልብ ለወንጌል እንዲሸነፍ እንጸልይ ።በተለይ በህመም፣ በጦርነት እና በጭንቀት ውስጥ ለሚገኙ ሰዎች መንፈሳዊ ጥማት እንዲበዛላቸው እንጸልይ!
👉በፍርሃት ወይም በስደት ሳቢያ እምነታቸውን እንዳያጡ እንዲሁም ሌሎችን ወደ ክርስቶስ የሚመሩ አገልጋዮችን እና ወንጌላውያንን አብራዋቸው እንዲሆኑ እና መንፈስ ቅዱስ በስብከታቸው እንዲሰራ እንጸልይ።
2 808
Only 2 hours left❗️❗️❗️❗️❗️
https://youtu.be/m3jujmjoz3c?si=2xFAvoSBnj00eUxz
#astu_ecsf #digital_strategy
2 808
🚨🚨🚨🚨🚨🚨🚨🚨🚨🚨🚨🚨🚨🚨
LAD Night Videos Are Finally Here, starting from tomorrow, at 7:00lt, we'll be releasing the videos.
Here is our first drop:
https://youtu.be/m3jujmjoz3c?si=2xFAvoSBnj00eUxz
- Who's excited? Drop a reaction and let us know👇👇👇
#astu_ecsf #digital_strategy
2 808
https://forms.gle/YUHLPbgHbuTYXruR6
ይህንን የወንጌል ስርጭት መሳተፍ የምትፈልጉ ይህንን google form እንድትሞሉት ይሁን! ተባረኩ
2 808
EvaSUE ያዘጋጀው የምርቃት ፕሮግራም ላይ የምትገኙ ተመራቂ ተማሪዎች ጋውን ለመዉሰድ በእነዚህ ስልኮች መደወል ትችላላችሁ:
0913329595 ገነት 0912026255 ብሩክ
2 808
#Congratulation
“እግዚአብሔርን ከእኔ ጋር ታላቅ አድርጉት፥ በአንድነትም ስሙን ከፍ ከፍ እናድርግ።”
— መዝሙር 34:3
ውድ የ2018 ዓ.ም የህብረታችን ተመራቂ ተማሪዎች እንኳን ደስ አላችሁ።በሁሉም ነገር የረዳችሁ እግዚአብሔር የተመሰገነ ይሁን።
በጊቢ ቆይታቹ ፌሎሺፓችን በብዙ ተጠቅማለች ፣ ብዙዎቻችን ታንጸናል ፤ ያደረጋቹትን ስራ ለስሙም ያሳያቹትን ፍቅር የማይረሳ እግዚአብሔር መጪውን ዘመናቹን የብዙ ድል እና ብዙዎችን የምትጠቅሙበት ያድርግላቹ።
እንወዳቹሀለን! በሕብረታችን ውስጥ ስለነበራቹ ስላወቅናቹ እጅግ ደስ ይለናል! ተባረኩ!
#ማሳሰቢያ :ነገ ከምርቃት ኘሮግራም በኋላ ሁላችንም ምሩቃን Dubai ጋር ተገናኝተን እግዚአብሔርን የምናመሰግንበት ጊዜ ስለሚኖረን ሁላችንም ተገኝተን የረዳንን እግዚአብሔር እናመስግን::
#ASTUECSF
#GC_2026
2 808
ቁጥር 1. ጳውሎስ መልዕክቱን የሚጀምረው በቅድሚያ ማንነቱን እያስተዋወቀ ነው ።በግሪኩ " ከሰዎች" የሚለው በሰዎች እጅ የተሰጠ ማለት ሲሆን ፤ "በሰዎች" የሚለው ደግሞ ሹመቱ ከእግዚአብሔር ሆኖ ሲሰጥ ግን በሰዎች አማካይነት ተሰጥቷል ማለት ነው ። የጳውሎስ ሐዋርያነት ከሰዎች ዘንድም በሰዎች አማካይነትም አልመጣለትም። ይህም ማለት ቀጥታ በአብና በኢየሱስ ክርስቶስ እንደ ተሰጠው ሲያመለክት ሰዎች በምንም ዓይነት መንገድ እጃቸውን እንዳላስገቡበት ማረጋገጫ ነው ።
ጳውሎስ ስለ ሐዋርያነቱ ሊናገር የፈለገበት ምክንያት በገላትያ ቤተ-ክርስትያን ውስጥ የጳውሎስ ሐዋርያነት በሰዎች አማካይነት የተሰጠው መሆኑንና ልክ እንደነ ጴጥሮስ በቀጥታ አልተጠራም ስለዚህም የእርሱ ሐዋሪያነት ሙሉ አይደለም ለሚለው ወሬ መልስ ለመስጠት ነው። ይህን ሐሰተኛ ወሬም ያዛመቱት በኢየሩሳሌም ከጴጥሮስና ዮሐንስ ዘንድ መጣን የሚሉ የገላትያን ምዕመናን ወደ ልዩ ወንጌል የጠመዘዙ ሰዎች ናቸው። ይህንም ያድርጉት ሪሳቸውን ከጳውሎስ ከፍ ለማድረግና የጳውሎስን ትምህርት ዳር በማስያዝ የሐሰት ትምህርቶቻቸውን ለማስፋፋት ነበር። ይህን ማድረጋቸውንም ጳውሎስ በማስተዋል ሐዋርያነቱ በሰው ወይም ከሰው እንዳልሆነ እንዲሁም ከአብና ከሙታን ከተነሳው ከኢየሱስ ክርስቶስ የተቀበለው መሆኑን አስቀድሞ ይናገራል ። (ሐዋ. 9፥2-6)
#summer_bs #galatians
#astu_ecsf #digital_strategy
2 808
የሐዋርያው ጳውሎስ መልዕክት ወደ ገላትያ ሰዎች
ምዕራፍ አንድ
የገላትያ መጽሐፍ በአብዛኛው የሚያተኩረው ስለ ሐዋርያው መለኮታዊ ስልጣን ነው ። ይህም ሆኖ ሳለ አብዛኛው የመልዕክቱ ክፍል የገላትያን ሰዎች ወደ ኋላ እስራት የሚመልሱ አስተምሕሮዎችን ለመቃወም(ለማውገዝ) የተጻፈ ነው ፤ አብዛኛዎቹ ከሕግ ጥላ ስር መሆንን ይሹ ነበርና። ጳውሎስ ለእነዚህ ሰዎች አንድን ነገር ይደነግጋል ፥ ይህንን በመፈጸማቸው ምክንያት ጳውሎስ ከሰበከላቸው ወንጌል እንዴት እራሳቸውን ወደ ልዩ ወንጌል እያዘነበሉ እንደሆነ። ምንም እንኳን ሌላ ወንጌል የሚባል ነገር በገሐድ ባይኖርም ፤ እነርሱ ሲያደርጉት የነበረው የጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን ወንጌል ማጣመም ስለነበር ይህ ስያሜ ተስጥቶታል።
ምንም እንኳን ይህ መልዕክት ለሮም ሰዎች ከተጻፈው ደብዳቤ ቀደም ብሎ ቢጻፍም ጳውሎስ ለ ሮማውያንም ለገላትያውያንም ተመሳሳይ እና ዋና የሆኑ ብዙ ነገሮችን ጽፏል። በአብይነት ሊጠቀስ ከሚችለው መሠረታዊ እውነታም አንዱ በእግዚአብሔር ፊት በአይሁድ እና አህዛብ መካከል ልዩነት አለመኖሩ ነው ። ምንም እንኳን በገላትያ ቤተ-ክርስትያን ብዙ አይሁዳውያን ቢኖሩም ፤ በቁጥር ከአህዛብ ያንሱ ነበር። ዋና ችግር የነበረውም የአይሁድ ሥርዓት ተከታዮች (የመሴን ሕግ አጥባቂዎች) የመገረዝን አስፈላጊነት እያስተማሩ መሆናቸው ነበር። ከአህዛብም እብላጫው ይህንን የይሁዳነት ባህል እንደ ድነት ቅድመ ሁኔታ ሊቀበሉት ዝግጁ ነበሩ። ጳውሎስ ለእነርሱ እንዲህ ሲል ይጠቅሳል፣ ይህንን ባህል ስትቀበሉ ከእኔ ወይም ከክርስቶስ በሆነ መገለጥ አይደለም ነገር ግን ከአይሁድ የወረሳችሁት ባህል ነው ይላቸዋል።
2 808
EvaSUE Graduation 2026
Thanksgiving and Excellence Promotion Ceremony
Date: ሰኔ 14, 2018 ዓ/ም |
Time: (7:30 ከሰዓት) |
⚠️ቦታ :ገርጂ ሙሉ ወንጌል ቤ/ክ
ማሳሰቢያ :በዚህ ፕሮግራም መገኘት የምትችሉ የህብረታችን ተመራቂ ተማሪዎች እንድትገኙ ይሁን እያለን ሌላኛው የጋዉን ክራይን በተመለከተ 100 ብር መሆኑን እንድታዉቁ እና ተመራቂ ተማሪዎች ጋውኑን ለመዉሰድ የምትደውሉበትን ስልክ በዚሁ ቻናል የምንለቅ ይሆናል።
#EvaSUE #AdvancingtheKingdomofGod
2 808
ሰላም ለእናንተ ይሁን የህብረታችን ተማሪዎች
ከሀምሌ 18 ጀምሮ በ GCM የሚዘጋጅ ቦታውን በ ሐረሪ እና በ ሲዳማ ክልል ያደረገ የወንጌል ስርጭት ፕሮግራም ስለሚኖር መሳተፍ የምትፈልጉ ቶሎ እንድታሳውቁን ይሁን
‼️ መመዝገቢያ 1000 ብር
2 808
ሰላም የተወደዳችሁ የህብረታችን አባላት
📖 የክረምት የመፅሐፍ ቅዱስ ጥናታችን በዚህም ሳምንት ይቀጥላል።
📅 ቀን:ሀሙስ
📍 በASTUECSF OFFICIAL ቴሌግራም ቻናል
📌እስከዚያው ሁላችንም የገላትያ መፅሐፍ ምዕራፍ አንድን በግል እያጠናን እንድንቆይ ይሁን ተባረኩ።
#astu_ecsf #summer_bs
¡Ya disponible! Investigación de Telegram 2025 — los principales insights del año 
