es
Feedback
ASTU-ECSF

ASTU-ECSF

Ir al canal en Telegram

ዓመታዊ መሪ ቃል: እግዚአብሔርን መፈለግ  በመመለስ  I በፅድቅ ኑሮ  I በመታመን Adama Science & Technology University Evangelical Christian Students Fellowship Official  Telegram channel contact us: @ASTUECSF_inbox CBE:1000696321179 Bethelhem & Lidiya &or Aklilu Telebirr:0950267178

Mostrar más
2 818
Suscriptores
+224 horas
+307 días
+2730 días
Archivo de publicaciones
Google formኡን እየሞላችሁ ስለሆነ ጌታ ይባርካችሁ። 📌 ነገር ግን አሁንም ይሄን form ያልሞላ ብዙ ሰው ስላለ ያልሞላችሁ እባካችሁ በፍጥነት እንድትሞሉ ይሁን! 👉Google formኡ የተዘጋጀው 2018 አ.ም በግቢያችን የነበሩ ክርስቲያን ተማሪዎች በግቢ ውስጥ እንዲሁም በፌሎ ከነበራቸው ቆይታ አንፃር እንዲሞሉት ታስቦ የተዘጋጀ መጠይቅ ስለሆነ በዚህ አመት (2019 አ.ም) ግቢያችንን የምትቀላቀሉ ተማሪዎች መጠይቁን መሙላት አይጠበቅባችሁም።

🔶🔶🔶🔶🔶🔶🔶🔶🔶🔶🔶🔶🔶🔶🔶 ሰላም በጌታ የተወደዳችሁ የህብረታችን ተማሪዎች፣ እንደምን ቆያችሁ? 👉 ከታች የምታገኙት google form በ2019 አመት ለምናደርጋቸው ፕሮግራሞች የሚረዳንን  መረጃ ለማግኘት ታስቦ የተዘጋጀ የተለያዩ መጠይቆች ስለሆኑ ሁላችሁም የህብረታችን ተማሪዎች እንድትሞትሉት ይሁን።
‼️Attention ይህንን የGoogle form ስትሞሉ anonymous ስለሆነ የሚሞላው ሰው ማንነት አይገልጽም፤ ስለዚህ በነፃነት እንድትሞሉ ስንል በትህትና እንጠይቃለን።
 📌 ከህብረታችን ተማሪ ያልሞላ እንዳይኖር! ተባረኩ❤️ https://forms.gle/X5yu7ZLhoHTpErHaA

🌼እንኳን ለ2019 እግዚአብሔር በሰላም አደረሳችሁ ፣ አደረሰን🌼 ነፍሴ ሆይ፥ ወደ ዕረፍትሽ ተመለሺ፥ እግዚአብሔር መልካም አድርጎልሻልና፤ መዝ 116:7 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼�
🌼እንኳን ለ2019 እግዚአብሔር በሰላም አደረሳችሁ ፣ አደረሰን🌼
ነፍሴ ሆይ፥ ወደ ዕረፍትሽ ተመለሺ፥ እግዚአብሔር መልካም አድርጎልሻልና፤ መዝ 116:7
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 ይህ ዓመት እንደ ሕብረት እግዚአብሔር ለሃሳቡ በይበልጥ አኛን መጠቀሚያ የሚያደርግበት ፣ ወደ እርሱ በይበልጥ የምናድግበት እና እርሱን የምንመስልበት እንዲሁም እርሱን በይበልጥ የምንታመንበት እና የምንፈልግበት ይሁንልን! መልካም በዐል! በይበልጥ ተባረኩ😁 ✨ ASTUECSF 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 #2019 #astu_ecsf #digital_strategy OUR SOCIALS: INSTAGRAM | YOUTUBE | TIKTOK

ጷጉሜ 05 📣 ዛሬ ደግሞ ስለ ህብረታችን እንፀልያለን፤ አንዳንዶች ማድረጉን እንደተዉት መሰብሰባችንን አንተው፤ ይልቁንም ቀኑ እየተቃረበ መምጣቱን ስታዩ እርስ በርሳችን እንበረታታ። ዕብ 10:25 �
ጷጉሜ 05 📣 ዛሬ ደግሞ ስለ ህብረታችን እንፀልያለን፤
አንዳንዶች ማድረጉን እንደተዉት መሰብሰባችንን አንተው፤ ይልቁንም ቀኑ እየተቃረበ መምጣቱን ስታዩ እርስ በርሳችን እንበረታታ። ዕብ 10:25
🌼 የሕብረታችንን አንድነት አንድንጠብቅ ጌታ አንዲረዳን ወደ ክርስቶስም ፍፁም ሙላት ማደግ አንድንችል በመያያዝና በመደጋገፍ አንድናድግ በጌታ ፊት አንፀልይ::
ፍጹም ትሑታንና ገሮች ሁኑ፤ እርስ በርሳችሁም በፍቅር እየተቻቻላችሁ ትዕግሥተኞች ሁኑ። በሰላም ማሰሪያ የመንፈስን አንድነት ለመጠበቅ ትጉ። ኤፌ 4:2-3
🌼 መፅናናትን እግዚአብሔር በእኛ መካከል አንዲያበዛ : ፀንተንም የወንጌሉን ስራ በትጋት አንድንሰራ::
ስለዚህ በርግጥ አሁን እንደምታደርጉት ሁሉ እርስ በርሳችሁ ተጽናኑ፤ አንዱም ሌላውን ያንጽ። 1ኛ ተሰ 5:11
በህብረታችን ለጠፉ ልጆች አንፀልይ ደግሞ ጌታ አንድመልሳቸው ማስተዋልም ጌታ አንዲሰጣቸው አንማልድላቸው በጌታ ፊት :: 🌼 ለህብረታችን መሪዎች አንፀልይ ጌታ በማስተዋል እና በጥበብ ህብረቱን መምራት አንዲችሉ እና በመጪውም ዘመን የእግዚአብሔር ድምፅን በመስማት እና በመታዘዝ ጌታ አንዲረዳቸው አንፀልይላቸው:: 🌼 ሕብረታችንን ሊያፈርስ ያለ የክፉ ስራን አያፈረስን አንፀልይ ምክንያቱም ስንቃወመው ከኛ ይሸሻል ::
እንግዲህ ራሳችሁን ለእግዚአብሔር አስገዙ፤ ዲያብሎስን ተቃወሙት፤ ከእናንተም ይሸሻል። ያዕ 4:7
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 #pray_week #pagume_2018 #astu_ecsf #digital_strategy OUR SOCIALS: INSTAGRAM | YOUTUBE | TIKTOK

የአማራ ህዝብ ክፍል 💥እጅግ አብዛኛው የአማራ ሕዝብ ከ4ኛው ክፍለ ዘመን ዓ.ም ጀምሮ ከዕለታዊ ህይወቱ፣ ከማንነቱና ከማኅበራዊ እቅዱ ጋር በጥብቅ የተዋሐደውን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ክርስቲያ
የአማራ ህዝብ ክፍል 💥እጅግ አብዛኛው የአማራ ሕዝብ ከ4ኛው ክፍለ ዘመን ዓ.ም ጀምሮ ከዕለታዊ ህይወቱ፣ ከማንነቱና ከማኅበራዊ እቅዱ ጋር በጥብቅ የተዋሐደውን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ክርስቲያናዊ እምነት ይከተላል። እንዲሁም እንደ ወሎ ባሉ ምሥራቃዊ አካባቢዎች ጥቂት የማይባል የአማራ ሕዝብ የሱኒ እስልምና እምነት ተከተይ ሲሆን፣ እዚያም የእስልምና ትምህርትና የሱፊ መንገድ ከአጎራባች ኦርቶዶክሶች ጋር ለዘመናት ጎን ለጎን ቆይቷል። የጸሎት ርዕሶች 🙏 👉በእምነታቸው ምክንያት ከቤተሰብ፣ ከማኅበረሰብ ወይም ከተለያዩ አካላት ጫናና ስደት የሚደርስባቸው አማኞች በክርስቶስ ፍቅርና ጽናት እንዲቆሙ፣ ከጥቃትም እንዲጠበቁ እንጸልይ። 👉 ስለ አማራ ሕዝብ መዳን፣ ሰላምና መንፈሳዊ መነቃቃት ቀንና ሌሊት የሚጾሙና የሚጸልዩ የጸሎት ቡድኖች በየቦታው እንዲቋቋሙ፤ የእግዚአብሔርም ታላቅ ጉብኝት በምድሪቱ ላይ እንዲሆን እንጸልይ። 👉በአማራ ክልል የሚታየው ግጭትና አለመረጋጋት በሰላማዊ መንገድ እንዲፈታ፣ የእግዚአብሔር ሰላም በምድሪቱ ላይ እንዲነግስ እንጸልይ።

ቀን 4 📣 ክርስቶስን ላላመኑት እና አምነው ወደ ኋላ ለተመለሱት ወንድሞችና እህቶች እንጸልያለን::
"እውነተኛ አምላክ ብቻ የሆንህ አንተን የላክኸውንም ኢየሱስ ክርስቶስን ያውቁ ዘንድ ይህች የዘላለም ሕይወት ናት።" ዮሐ17:3
🌼 መንፈስ ቅዱስ ልባቸውን እንዲከፍት፣ እግዚአብሔር ሲጠራቸው እንዲሰሙ፣ የሰሙትንም አስተውለው እንዲረዱ እንጸልይ፤
"ከትያጥሮን ከተማም የመጣች ቀይ ሐር ሻጭ እግዚአብሔርን የምታመልክ ልድያ የሚሏት አንዲት ሴት ትሰማ ነበረች፤ ጳውሎስም የሚናገረውን ታዳምጥ ዘንድ ጌታ ልቧን ከፈተላት።" ሐዋ 16:14
🌼 የዘላለም ሕይወት የሆነውን ክርስቶስን ላላወቁት ምስኪን የዶርም ጓደኞቻችን እግዚአብሔር ወደ እርሱ እንዲያመጣቸው፣ ደግሞም እግዚአብሔር በእኛ እንዲጠቀም እንጸልይ፤
"የእግዚአብሔርም ልጅ እንደ መጣ፥ እውነተኛም የሆነውን እናውቅ ዘንድ ልቡናን እንደ ሰጠን እናውቃለን፤ እውነተኛም በሆነው በእርሱ አለን፥ እርሱም ልጁ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። እርሱ እውነተኛ አምላክና የዘላለም ሕይወት ነው።" 1ኛ የዮሐ 5:20
🌼 ክርስቶስን አምነው ወደ ኋላ ለተመለሱ ወንድሞችና እህቶች ልጅነታቸውን ማስታወስ እንዲችሉ፣ ወደ አባታቸው ቤት ለመመለስ መወሰን እንዲችሉ ጌታ እንዲረዳቸው እንጸልይ፤
"ወንድሞቼ ሆይ፥ ከእናንተ ማንም ከእውነት ቢስት አንዱም ቢመልሰው፥ ኃጢአተኛን ከተሳሳተበት መንገድ የሚመልሰው ነፍሱን ከሞት እንዲያድን፥ የኃጢአትንም ብዛት እንዲሸፍን ይወቅ።" ያዕ 5:19-20
🌼 ከወዴት እንደወደቁ አውቀው በንስሐ መመለስ እንዲችሉና ጌታ የቀድሞ ሕይወታቸውን እንዲያድስላቸው እንጸልይ፤
"አቤቱ፥ ንጹሕ ልብን ፍጠርልኝ፥ የቀናውንም መንፈስ በውስጤ አድስ። ከፊትህ አትጣለኝ፥ ቅዱስ መንፈስህንም ከእኔ ላይ አትውሰድብኝ። የማዳንህን ደስታ ስጠኝ፥ በእሽታ መንፈስም ደግፈኝ።" መዝ 51:10-12
🌼 በእነዚህ የፀሎት ርዕሶችና በቃሉ መሰረት በእግዚአብሔር ፊት በምልጃ እና በምስጋና እንቅረብ። 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 #pray_week #pagume_2018 #astu_ecsf #digital_strategy OUR SOCIALS: INSTAGRAM | YOUTUBE | TIKTOK

photo content

ቀን 3 📣 ራሳችንን ሙሉ በሙሉ ለክርስቶስ መስጠት
“ከዚያም ለሁሉም እንዲህ አላቸው፦ ‘በኋላዬ ሊመጣ የሚፈልግ ማንም ቢኖር ራሱን ይካድ፣ መስቀሉንም በየዕለቱ ተሸክሞ ይከተለኝ።’”ሉቃ 9፥23
🌼 ዛሬ ደግሞ ፈቃዳችንን፣ ወጣትነታችንን፣ ምኞታችንንና ሕይወታችንን ሙሉ በሙሉ ለጌታ እንድንሰጥ፣ በክርስቲያናዊ ጉዟችንም በንጽሕናና በቅድስና እንድንመላለስ እንጸልያለን። 🌼 የራሳችንን ፈቃድና ምኞት ከመከተል ይልቅ የጌታን ፈቃድ እንድንመርጥ፣ ያለንን ሁሉ ለእርሱ በመስጠት ለክርስቶስ ብቻ የተለየ ሕይወት እንድንኖር እንማልዳለን ፤ በጉዟችን እየተቀደስንና እየታነጽን እስከ መጨረሻ በንጽሕና እንድንጸና እንጸልያለን፤
“የሰላም አምላክ ራሱ ሁሉንተናችሁን ይቀድስ፣ መንፈሳችሁ፣ ነፍሳችሁና ሥጋችሁ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሚመጣበት ጊዜ ያለ ነቀፋ ይጠበቁ።” 1 ተሰ 5፥23
ጌታ ከሚያረክስ ነገር ሁሉ እንዲያነጻን፣ ልባችንንና ምኞታችንን እንዲቀድስ፣ በቅድስና እያደግን ክርስቶስን የሚያሳይ ሕይወት እንድንኖር እንጸልያለን። 🌼 የጌታን መምጣት በማሰብ በቅድስናና በእግዚአብሔር ፊት በሚገባ እንድንኖር እንጸልያለን፤
“የጌታ ቀን ግን እንደ ሌባ ይመጣል፣ በዚያች ቀን ሰማያት በታላቅ ድምፅ ያልፋሉ፣ ፍጥረትም በታላቅ ግለት ይጠፋል፣ ምድርና በርሷም ላይ ያለ ነገር ሁሉ ወና ይሆናል። እንግዲህ ሁሉም ነገር በዚህ ሁኔታ የሚጠፋ ከሆነ፣ እናንተ እንዴት ዐይነት ሰዎች ልትሆኑ ይገባችኋል? አዎን፣ በቅድስናና በእውነተኛ መንፈሳዊነት ልትኖሩ ይገባችኋል።” 2 ጴጥ 3፥10-11
የዚህ ዓለም ነገር ጊዜያዊ መሆኑን አውቀን፣ ልባችንን በዓለም ነገር ሳንይዝ ለጌታ በመለየት በቅድስና፣ በንጽሕናና እግዚአብሔርን በመፍራት እንድንኖር እንጸልያለን። 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 #pray_week #pagume_2018 #astu_ecsf #digital_strategy OUR SOCIALS: INSTAGRAM | YOUTUBE | TIKTOK

photo content

📣 OUT NOW❗️ https://youtu.be/5Aln-MhH9hM 📌 ትምህርቱን እንደገና ማጤን ብሎም በዙሪያችሁ ላሉ ማጋራት እንዳትረሱ😊 ተወዳጆች ናችሁ💛 #astu_ecsf #digital_str
📣 OUT NOW❗️ https://youtu.be/5Aln-MhH9hM 📌 ትምህርቱን እንደገና ማጤን ብሎም በዙሪያችሁ ላሉ ማጋራት እንዳትረሱ😊 ተወዳጆች ናችሁ💛 #astu_ecsf #digital_strategy

ጷጉሜ 02 📣 በንስሃ ፣ በመመለስ እግዚአብሔር እንፈልግ "እግዚአብሔር በሚገኝበት ጊዜ ፈልጉት፥ ቀርቦም ሳለ ጥሩት፤ክፉ ሰው መንገዱን በደለኛም አሳቡን ይተው፤ ወደ እግዚአብሔርም ይመለስ እርሱም ይ
ጷጉሜ 02 📣 በንስሃ ፣ በመመለስ እግዚአብሔር እንፈልግ
"እግዚአብሔር በሚገኝበት ጊዜ ፈልጉት፥ ቀርቦም ሳለ ጥሩት፤ክፉ ሰው መንገዱን በደለኛም አሳቡን ይተው፤ ወደ እግዚአብሔርም ይመለስ እርሱም ይምረዋል፥ ይቅርታውም ብዙ ነውና ወደ አምላካችን ይመለስ።" ኢሳ 55:6-7
🌼 በተለያዩ ድረግቶች ሀሳቦች እግዚአብሔር ባሳዘንበት ነገር ንሰሐ በመግባት እግዚአብሔር ይቅር እንድለን እንፀልይ፤
ኃጢአቴን ለአንተ አስታወቅሁ፥ በደሌንም አልሸፈንሁም፤ ለእግዚአብሔር መተላለፌን እነግራለሁ አልሁ፤ አንተም የልቤን ኃጢአት ተውህልኝ። መዝ 32:5
🌼 በስንፍናና በችላ ባይነት ስናደርግ ሰለቀረንባቸዉ ነገር ላይ (ለቃሉ እና ለፀሎት....) ፤ የ እግዚአብሔር ሀሳብ በልሰመንበት ነገር ላይ  እግዚአብሔር ይቅር እንድለን በፍቱ በመቅረብ እንፀልይ፤
እንግዲህ በጎ ለማድረግ አውቆ ለማይሠራው ኃጢአት ነው። ያዕ 4:17
🌼 በዝኛዉ አመት እንደ ህበረታች ጌታን በበደልንበት ነገር ላይ ጌታ ይቅር እንድለን ደግሞም የትጋር እንዲወድቅን አዉቀን መነሳት እንድንችል ጌታ እንድረዳን እንፀልይ፤
እንግዲህ ከወዴት እንደ ወደቅህ አስብ ንስሐም ግባ የቀደመውንም ሥራህን አድርግ፤ አለዚያ እመጣብሃለሁ ንስሐም ባትገባ መቅረዝህን ከስፍራው እወስዳለሁ። ራእ 2:5
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 #pray_week #pagume_2018 #astu_ecsf #digital_strategy OUR SOCIALS: INSTAGRAM | YOUTUBE | TIKTOK

👋 ስላም የተወደዳችሁ ወጣቶች አንዴት ቆያችሁ ፤ ከነገ ጀምሮ "መንፈስ ቅዱስ ማነው" የሚለውን ትምህርት በዩትዩብ ገፃችን ላይ ማግኘት ትችላላችሁ። https://youtu.be/5Aln-MhH9hM 📌
👋 ስላም የተወደዳችሁ ወጣቶች አንዴት ቆያችሁ ፤ ከነገ ጀምሮ "መንፈስ ቅዱስ ማነው" የሚለውን ትምህርት በዩትዩብ ገፃችን ላይ ማግኘት ትችላላችሁ። https://youtu.be/5Aln-MhH9hM 📌 ትምህርቱን እንደገና ማጤን ብሎም በዙሪያችሁ ላሉ ማጋራት እንዳትረሱ😊 ተወዳጆች ናችሁ💛 #astu_ecsf #digital_strategy

ጷጉሜ 01 📣 እግዚአብሔርን እያመሰገንን እንጸልያለን። “መልሶም፦ ለዘሩባቤል የተባለው የእግዚአብሔር ቃል ይህ ነው። በመንፈሴ እንጂ በኃይልና በብርታት አይደለም፥ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር።
ጷጉሜ 01 📣 እግዚአብሔርን እያመሰገንን እንጸልያለን።
“መልሶም፦ ለዘሩባቤል የተባለው የእግዚአብሔር ቃል ይህ ነው። በመንፈሴ እንጂ በኃይልና በብርታት አይደለም፥ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር።” ዘካ 4፥6
🌼 መዳናችንን እያሰብን፤
‎“አሁን ግን እናንተ በፊት ርቃችሁ የነበራችሁ በክርስቶስ ኢየሱስ ሆናችሁ በክርስቶስ ደም ቀርባችኋል።” ‎ኤፌ 2፥13
🌼 ዛሬም በክርስቶስ የመስቀል ስራ ወደ እግዚአብሔር አብ አባ አባት ብለን የምጠራበት የልጅነት መንፈስ ስለተሰጠን፤
“አባ አባት ብለን የምንጮኽበትን የልጅነት መንፈስ ተቀበላችሁ እንጂ እንደገና ለፍርሃት የባርነትን መንፈስ አልተቀበላችሁምና።” ሮሜ 8፥15
🌼 በግቢ በነበረን ቆይታ ሁሉ በድካምም ሆነ በብርታት በትምህርታችን፣ በመንፈሳዊ ህይወታችን፣ ምልልሳችን ሁሉ እግዚአብሔር ስለረዳን፣ ምህረትና ጸጋዉን ስላበዛልን እያመሰገንን እንጸልያለን፤
“መልሶም፦ ለዘሩባቤል የተባለው የእግዚአብሔር ቃል ይህ ነው። በመንፈሴ እንጂ በኃይልና በብርታት አይደለም፥ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር።” ዘካ 4፥6
🌼 እንደ ህብረት ደግሞ የአገልግሎት ዘርፎችን እግዚአብሔር ስለረዳቸው፣ በተካሄዱ በወንጌል ስርጭቶች፣ በአጠቃላይ ህብረታችን ጌታ በብዙ ስለረዳ፣ መሪዎችም ሚቆረስ ህይወት እንዲኖራችው ጸጋዉን ስላበዛላችው እግዚአብሔርን እያመሰገንን እንጸልያለን። 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 #pray_week #pagume_2018 #astu_ecsf #digital_strategy OUR SOCIALS: INSTAGRAM | YOUTUBE | TIKTOK

ስላም ሰላም የጌታ ውዶች እንደምን ቆያችሁ ፤ ይኸው በጌታ ትከሻ 2019 ሊያልቅ ነው እናም እኛ እንደ ሕብረት የረዳንን እግዚአብሔር በጋራ የምናመሰግንበት፣ምህረት እንደገና ምንጠይቅበት ብሎም ከፊታች
ስላም ሰላም የጌታ ውዶች እንደምን ቆያችሁ ፤ ይኸው በጌታ ትከሻ 2019 ሊያልቅ ነው እናም እኛ እንደ ሕብረት የረዳንን እግዚአብሔር በጋራ የምናመሰግንበት፣ምህረት እንደገና ምንጠይቅበት ብሎም ከፊታችን ላለው ዓመት የጌታን ፈቃድ የምንሰማበትና እርሱንም የምናደርግበት አቅምን የምንጠይቅበት የጾም እና ጸሎት ፕሮግራም አዘጋጅተናል። ይህም የሚሆነው ከጷጉሜ 1-5 ሲሆን በጋራ የምንቆይባቸውን የተመረጡ የየቀኑን ሃሳቦች በማህበራዊ ሚዲያዎቻችን የምናጋራ ይሆናል። 📌ሁላችንም በያለንበት በሚለቀቁት ርዕሶች ለይ እንድንፀልይ ይሁን። እንወዳችኋለን🤗 #pray_week #pagume #astu_ecsf #digital_strategy

ቁ.14 የክርስቶስ መስቀል አለም ለእኛ የተሰቀለበት ፣እኛም ለአለም የተሰቀልንበት ነው ። የስጋን ፈቃድ እና ምኞት በመስቀሉ ገድለናል( ገላ 2:20)። ቁ.15-17 የዳነ ሰው ምልክቱ የተለያዪ ሥረአቶችን መፈፀሙ ፣ ቤተክርስቲያን መመላለሡ ሣይሆን አዲስ ፍጥረት መሆኑ፣ ዳግም መወለዱ ነው። ቁ.18 የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ፀጋ ከሁላችን ጋር ይሁን።አሜን። 🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉 የክረምት የመፅሐፍ ቅዱስ ጥናታችንን አጠናቀናል፤የረዳን እግዚአብሔር ይመስገን፣አብራችሁንም ስታጠኑ የነበራችሁ በሙሉ ጌታ ይባርካችሁ፤በጣም በቅርቡ ደግሞ በአዲስ ነገር እንከሰታለን ተከታተሉ!😉 እንወዳችኋለን🤗 OUR SOCIALS: INSTAGRAM | YOUTUBE | TIKTOK #summer_bs #galatians #astu_ecsf #digital_strategy

ምዕራፍ 6 6:1-10 ለሰው ሁሉ በጎ ማድረግ ቁ.1-6 መንፈሣዊ የሆነ ሠው ሁሉ ማለትም በመንፈስ ቅዱስ የሚመራ ሁሉ ወንድሙ በደከመና በሳተ ጊዜ በቅንነት ወንድሙን ሊያቀና ይገባል። - አንዳችን ለአ
ምዕራፍ 6 6:1-10 ለሰው ሁሉ በጎ ማድረግ  ቁ.1-6  መንፈሣዊ የሆነ ሠው ሁሉ ማለትም  በመንፈስ ቅዱስ  የሚመራ ሁሉ  ወንድሙ በደከመና በሳተ ጊዜ  በቅንነት ወንድሙን ሊያቀና ይገባል። - አንዳችን ለአንዳችን ድጋፍ፣አንዳችን ለአንዳችን ረዳት በመሆን ሊወድቁ ላሉት  መበርቻ ልንሆን ይገባል ። - ነገር ግን ለራሱ የቆመ የሚመስለው ሁሉ እንዳይወድቅ ራሡን ይጠብቅ። /1 ቆሮ 10:12/ - ጳውሎስ እስካሁን ሰው የሙሴን ሕግ  ቢጠብቅም  እንደማይፀድቅ ገልፆ  ፣ በዚህ ክፍል ግን የክርስቶስን ሕግ  እንድንጠበቅ ይናገራል ።በዚህም የክርስቶስ ሕግ የተፃፈው የሙሴ ሕግ እንዳልሆነ እንረዳለን።የክርስቶስ ሕግ  ፍቅር ነው። የክርስቶስ ሕግ በወንድሞች መካከል የሚገለጥ ፍቅር ነው። የክርስቶስ ሕግ  ራሳችንን በምንወድበት መውደድ  ወንድማችንን መውደድ  ነው  /ዮሐ 13:34  ማቴ 19:19 /። ቁ.7-8 ሰው የስጋን ስራን ሰርቶ የመንፈስን ፍሬ ሊያፈራ አይችልም። ሰው የሚዘራውን ሁሉ ያንኑ ያጭዳል።የስጋን ፍሬ የሚያፈራ መበስበስን ያጭዳል፤የመንፈስን ፍሬ የሚያፈራ የዘላለምን ሕይወት ያገኛል። /ገላ5:21,6:8/ ቁ.9-10 ምንም እንኳን መልካም ስራ ድነትን የሚሰጠን ባይሆንም የዳነ ሰው መገለጫ ና እግዚአብሔር ለኛ ያሳየውን ፍቅር  ለሌሎች የምናሳይበት ነው። ለዚህም ነው ጳውሎስ የገላትያ ሰዎችን መልካምን ስራ እንዲሰሩ የሚያበረታታው ። 6:11-18  አዲስ ፍጥረት መሆን ቁ.11-13 የገላትያ ሠዎችን እንዲገረዙ የሚያስጨንቁት የሀሰት አስተማሪዎች ይህንን የሚያደርጉት አይሁድ መሆናቸው ታውቆ  ራሳቸውን  ከስደት እና ከመከራ ሊያድኑ በመፈለግ  ነው(በጊዜውም አይሁድ ከክርስቲያኖች ይልቅ ተቀባይነት ያላቸው እና በክርስቲያኖች ላይ ስደት ስለነበር )።

"ክርስቶስን መምሰል" ክርስቶስን መምሰል ስንል ምን ማለታችን ነው? እኛ የሰው ልጆች ገና ከጅምሩም ስንፈጠር በእግዚአብሔር መልክ እና አምሳል ነው ። እግዚአብሔርም አለ፡— 'ሰውን በመልካችን እንደ
+5
"ክርስቶስን መምሰል" ክርስቶስን መምሰል ስንል ምን ማለታችን ነው? እኛ የሰው ልጆች ገና ከጅምሩም ስንፈጠር በእግዚአብሔር መልክ እና አምሳል ነው ።
እግዚአብሔርም አለ፡— 'ሰውን በመልካችን እንደ ምሳሌአችን እንፍጠር፤ ዘፍ 1÷26
👉 ሙሉ ለማንበብ ጠቅ_ያድርጉ 📌ማንኛውም አይነት የማማከር አገልግሎት ለማግኘት ከታች ያለውን የቴሌግራም ቦት ይጠቀሙ፤ለመመለስ ሪፕላይ(REPLY) የሚለውን መጫን እንዳይረሱ! 👇👇 @counselling_CBot OUR SOCIALS: INSTAGRAM | YOUTUBE | TIKTOK #article_06 #counseling_team #Godliness #astu_ecsf #digital_strategy

የአፋር ህዝብ 💥የአፋር ሕዝብ በምሥራቅ አፍሪካ (በኢትዮጵያ፣ በኤርትራ እና በጅቡቲ) የሚኖር፣ ታሪካዊ አመጣጡንም ከኖህ ልጅ ከካም ዘሮች ጋር የሚያያይዝ ሕዝብ ነው። ጀግንነትን፣ ጥንካሬንና ወኔን
የአፋር ህዝብ 💥የአፋር ሕዝብ በምሥራቅ አፍሪካ (በኢትዮጵያ፣ በኤርትራ እና በጅቡቲ) የሚኖር፣ ታሪካዊ አመጣጡንም ከኖህ ልጅ ከካም ዘሮች ጋር የሚያያይዝ ሕዝብ ነው። ጀግንነትን፣ ጥንካሬንና ወኔን የሚያከብር ማኅበረሰብ ነው። የጸሎት ርዕሶች 🙏 👉ልዩነት ሳይገድባቸው፣ መላው የአፋር ሕዝብ ፍጹም የሆነ ፍቅርና አንድነት እንዲኖረው፤ የክርስቶስ ወንጌልም በመካከላቸው እውነተኛ ሰላምንና እኩልነትን እንዲያሰፍን እንጸልይ። 👉 የክርስቶስን የምስራች በጅቡቲ፣ በኢትዮጵያና በኤርትራ በድፍረት ለሌሎች የሚያደርሱ ጠንካራ የክርስቶስ ምስክሮች እንዲሆኑላቸው እንጸልይ። 👉በሦስቱም አገራት (በኢትዮጵያ፣ በኤርትራና በጅቡቲ) በስፋት ለሚገኙት አፋሮች፣ በተለይም በሩቅ በረሃማ አካባቢዎች ለሚኖሩና የወንጌል ድምፅ በቀላሉ ለማይደርሳቸው ወገኖች የሕይወት ውኃ የሆነው የኢየሱስ ፍቅር የሚደርስበት መንገድ እንዲከፈት፤ በገዛ ቋንቋቸው የእግዚአብሔርን ቃል የሚያሰሟቸው የሰለጠኑ አገልጋዮችና ሠራተኞች ወደ ስምሪት እንዲወጡ እንጸልይ።

ቁጥር 19-21.ጳውሎስ የኃጢኣተኛ ተፈጥሮ ተግባራትን ይዘረዝራር። የሥጋ ሥራ  ብሎ የገለጣቸው ወደ አሥራ ስምንት ባህርያት ሲሆኑ  ከተጠቀሱት ጥቂቶቹ ደግሞ በክርስትያኖች መካከል ስለሚኖሩ የሻከሩ ግንኙነቶች ምሳሌ ናቸው። ጳውሎስ እነዚህን ድርጊቶች ከዘረዘሩ በኋላ እነዚህን ኃጢኣቶች ሁል ጊዜ የሚያደርጉ ፥ ንሰሐም የማይገቡ ወደ እግዚአብሔር መንግስት እንደማይገቡ ይናገራል።  አዎን እያወቀ ኃጢኣትን የሚያደርግ ፤ ንስሐም የማይገባ የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርስም። ቁጥር 22-23. በአማኝ ሕይወት ውስጥ መንፈሳዊ ፍሬዎች ይፈራሉ። እነዚህን ፍሬዎች ጳውሎስ በዝርዝር አስቀምጧል ። እነዚህ የመልካም ባሕርያት ፍሬዎች በማንኛውም የክርስቲያን ግላዊም ሆነ የህብረት ሕይወት ውስጥ ሁል ጊዜ ሊታዩ ይገባቸዋል። ይሁን እንጂ እኚ የመንፈስ ቅዱስ ፍሬዎች ከመንፈስ ቅዱስ ስጦታዎች የተለዩ መሆናቸውን ልብ ማለት ያስፈልጋል። °ፍቅር- ለእግዚአብሔር እና ለሰው °ደስታ- የደህንነት ደስታ °ሰላም- ከእግዚአብሔር እንዲሁም ከአማኞች ጋር °ትዕግስት- በፈተና ጊዜ ያለ ጽናት °ደግነት- መማር፣ማለፍ °በጎነት-መልካም ማድረግ(መመኘት) °ታማኝነት-መታመን °ገርነት- ትህትና °ራስን መግዛት- የሥጋን ምኞት አለመፈፀም እነዚህ የመንፈስ ፍሬዎች የሚገኙት በሰው ድካምና ጥረት ሳይሆን በውስጣችን በሚኖረው በመንፈሱ አማካኝነት ነው ። እነዚህን ፍሬዎች ብናፈራ የእግዚአብሔርን ሕግ በሕይወታችን እንፈፅማለን። ምክንያቱም እነዚህን ሕጎች ክፉ ናቸው ብሎ የሚቃረን ሕግ የለምና። ቁጥር 24.  በኃጢኣት ተፈጥሮ ስር ያለው የቀድሞ ማንነት በመስቀል ላይ ሊሆን ይገባዋል። ይህም ሁል ጊዜ መሆን አለበት ። የክርስቶስ የመሆናችንም ማረጋገጫ ነው ። ቁጥር 25-26. የእግዚአብሔር ልጆች ከሆንን እንደ እግዚአብሔር ልጆች እንመላለስ ይልና ጳውሎስ በአማኞቹ መካከል መፈጠር ስለሌለባቸው ከመንፈስ ቅዱስ ስላልሆኑ ባህርያት ይጠቅሳል። OUR SOCIALS: INSTAGRAM | YOUTUBE | TIKTOK #summer_bs #galatians #astu_ecsf #digital_strategy

የሐዋርያው ጳውሎስ መልዕክት ወደ ገላትያ ሰዎች ምዕራፍ 5፥16-26 ቁጥር 16. አዳማዊ ማንነት ወይም ስጋ በመንፈስ ቅዱስ ቁጥጥር ስር መሆን አለበት ።ይህም የመሆኑ ጥቅሙ መንፈስ ቅዱስ ኃጢኣት እን
የሐዋርያው ጳውሎስ መልዕክት ወደ ገላትያ ሰዎች         ምዕራፍ 5፥16-26 ቁጥር 16. አዳማዊ ማንነት ወይም ስጋ በመንፈስ ቅዱስ ቁጥጥር ስር መሆን አለበት ።ይህም የመሆኑ ጥቅሙ  መንፈስ ቅዱስ ኃጢኣት እንዳናደርግ ስለሚጠብቀን ነው ። በሃጢኣት እንዳንወድቅ ሁሌ በመንፈስ ቅዱስ  መደገፍ አለብን። በዚህም ኃጢኣትን ወይም ስጋዊ ምኞትን ማሸነፍ ይቻላል  ይላል ጳውሎስ። ቁጥር 17. አማኞች ብንሆንም የድሮ ማንነታችንን በሞላ ከእኛ ስላላስወግድነው ኃጢኣትን በፈፀምን ጊዜ ስናምን የተቀበልነውን መንፈስ ቅዱስን ይቃወማል ። አዲሱ የመንፈስ ሕይወት መልካሙን ለማድረግ ቢቀናም አሮጌው አዳማዊ ማንነት ግን ይከለክለዋል። ነገር ግን በመንፈስ ቅዱስ ቁጥጥር ሥር ስንኖር ኃጢኣተኛ ተፈጥሮኣችን ይሰቀላል ፤ ምክንያቱም ኃጢኣተኛው ተፈጥሮ በውስጣችን ባለው መንፈስ ቅዱስ ላይ ኀይል ስለማይኖረው ነው ። ይህን ብንተው ግን የቀድሞው ኃጢኣተኛ ማንነት ነፍስ ይዘራል ፤ በርሱም ቁጥጥር ስር እንሆናለን። ቁጥር 18. ሮሜ 8፥2-14 እዚህ ቦታ የተጠቀሰው የአይሁድ ሕግ ነው ። (ሮሜ.8፥2 ላይም የኃጢኣትና የሞት ሕግ ተብሏል)። አይሁድ ሕግጋትን እና ትዕዛዛትን መፈፀም በኃጢኣት ከመውደቅ እንደሚያድን እምነት ነበራቸው። ይህን ማድረጋቸው ውጫዊ ወይም የሚታዩ ኃጢኣቶችን እንዳይፈፅሙ ቢያደርጋቸውም ውስጣዊ ከሆኑት ኃጢኣቶች ግን አያድናቸውም። ምክንያቱም እግዚአብሔር ቀድሞ የሚመለከተው ልብን ስለሆነ ነው ። ጳውሎስ በቀደሙት ክፍሎች ከሕግ በታች መሆን ከእርግማን (የኃጢኣት ኃይል ፣ የሞት ፍርድ) በታች መሆን እንደሆን ተናግሮ ነበር ። አሁን ደግሞ በመንፈስ ብንመራ ከሕግ በታች አንሆንም ይላል። ይህም ሕግጋትን በመጠበቅ እግዚአብሔርን ደስ ለማሰኘት ከመሞከር እስረኝነት መዳንን ያመለክታል።